Friday, May 18, 2012

የማቅ ሁለት ባላ!

ማኅበረ ቅዱሳን ከደጀ ሰላም፤አንድ አድርገንና ከሌሎቹ ውርንጭላ ብሎጎቹ ውጪ የዘመቻ አድማሱን በማስፋትበሀገሪቱ  ፖለቲካዊ ለውጥ እንዲመጣ ከሚታገሉ ሚዲያዎች ጋር ኅብረቱን በማሳየት ወደግልጽ እርምጃ ቀይሮታል። ማንም በፈለገው የፖለቲካ አቋም የመሄድና የመሰለፍ መብት እንዳለው ብናምንም ማኅበረ ቅዱሳን ግን ሃይማኖታዊ አቋሙን ከየትኛውም ፖለቲካ ገለልተኛ ሆኖ ለመስራት የተስማማበትን መተዳደሪያ ደንቡን ጥሶ በማኅበሩ አመራር አባል በኩልም ጭምር መግለጫ በመስጠት ለፖለቲካዊ ለውጥ ትግል መድረኮች የጽሁፍና የቃል አቤቱታውን በመስጠት መቀላቀሉን አሳይቷል። ድሮም «ማቅ» ፖለቲካውንና ሃይማኖቱን እያቀላቀለ የሚሄድ እንጂ ስለኦርቶዶክስ የሚገደው አይደለምና ይህንኑ አሳይቷል። ማቅ ሁለት ባላ መትከሉን አቁም!