Wednesday, May 2, 2012

ባለጭድ

በጮራ ቊጥር 3 ላይ የቀረበ 
from chorra blogger

ለፈገግታ


ገበሬው ባለው አንድ በሬ ከሌሎችም አቀናጅቶ ማረሱ ከፍተኛ ችግር ይፈጥርበትና ያንን ሸጦ ሁለት መለስተኛ በሬዎችን መግዛት ይፈልጋል፡፡ በሬው ለዐይን ሞላ ብሎ ጥሩ ዋጋ እንዲያወጣለት በማሰብ ጭድ በገፍ ሲያበላው ይሰነብትና ለገበያ ያቀርበዋል፡፡ 

በሬውን ሊገዛ የመጣ ነጋዴም የበሬው አቋም ከሩቅ ይስበውና ጠጋ ብሎ ተዟዙሮ በደንብ ይመለከተዋል፤ በመጨረሻም ከወደ ሆዱ ጐሸም እያደረገ፤ «ባለ ጭድ ዋጋውስ?» ይለዋል በሽሙጥ፡፡ 

ነገሩ የገባው ገበሬም «ለጠንቋይ አይሸጥም» በማለት አጸፋውን መለሰለት ይባላል፡፡