Tuesday, August 27, 2013

የማይቀረው ለውጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን መጎብኘቱ አይቀርም!




ባልተዘጋጀችበትና በማትፈልገው ለውጥ የሚደርስባት ጉዳት ከባድ ነው!
ክፍል ሁለት / ነሐሴ 21/ 2005/

በክፍል አንድ ጽሁፋችን ስለለውጥና የለውጥ አስተሳሰብ ጥቂት ለማለት ሞክረን ነበር። ጊዜውን ጠብቆ በመጣው ለውጥ ሳቢያ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ስላቋቋመችው የለውጥ ማስታገሻ መንገድና ስለኢየሱሳውያን/ JESUIT/ አመሰራረት መንስዔም በመጠኑ አስቃኝተናል። ስለጀስዊትስ ዓላማና ግብ በዝርዝር እዚህ ላይ እንዳንሄድ የተነሳንበት ርእስ መሠረተ ሃሳብ ይገድበናልና ትተነዋል። አንባቢዎቻችን ተጨማሪ መረጃ ያገኙ ዘንድ በዚህ ሊንክ እንዲገቡ እንጠቁማለን።/http://www.biblebelievers.org.au/jesuits.htm የጀስዊትስ መመሥረት የአዲስ አስተሳሰብና የለውጥ እንቅስቃሴን ባያቆምም የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያንን ከመፈራረስ በተወሰነ መልኩ አግዟታል። ወደማትፈልገውና ወዳላሳበችው የለውጥ መንገድ እንድትንሸራተት ያስገደዳት ሲሆን የነበራትን የሮማን ህግና ደንብ በየሀገራቱ ውስጥ ከመትከል ይልቅ የየሀገራቱን ባህልና ወግ ከካቶሊክ አመለካከት ጋር እያስማማች ለመጓዝ ረድቷታል። ለምሳሌ ኢትዮጵያ ውስጥ አብዛኛው ሕዝብ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታይ እንደመሆኑ መጠን የኢትዮጵያ ካቶሊክም ኢትዮጵያዊ ካቶሊክ እንዲመስል እንጂ ቫቲካናዊ ካቶሊክ እንዲመስል ስለማይጠበቅበት ማንኛውም የቤተ ክርስቲያን ሥርዓት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ግልባጭ ነው። ታንዛንያ ስንሄድ ደግሞ ታንዛንያዊ ቋንቋ፤ ባህልና ወግን ይከተላል። ሌላ ቋንቋ፤ ባህልና ሥርዓት አምጥቶ ከመጫን ይልቅ ሕዝቡ በሚኖርበት ቋንቋ፤ ባህልና ሥርዓት ሲያስተምሩት ውጤታማ መሆኑ አይጠረጠርም። ሐዋርያው ጳውሎስም ያደረገው እንዲሁ ነበር። ያልተገረዘ ወደ መገረዝ አይሂድ ማለቱ ወንጌል ማለት አይሁዳዊውን ሥርዓት በሌላ ሕዝብ ላይ በመጫን የሚፈጸም እንዳልሆነ መግለጡ ነበር። እንኳን ግእዝን አማርኛን በውል ለማይሰማ ለሸኮ መዠንገር ሕዝብ ሄደህ የያሬድ የቅዳሴ ዜማ ነው ብለህ ብትጮህለት ለምሥጋናህ እንዴት አሜን ሊል ይችላል? ክርስትና የሰዎችን ቁጥር የማብዛት ጉዳይ ባይሆንም ወንጌል ያልደረሳቸውን ለማዳረስ ትክክለኛው መንገድ እኛ የምንኖርበትን ሥርዓትና ሕግ በማያውቀው ሌላ ሕዝብ ላይ የመጫን ጉዳይ ሳይሆን ኢየሱስ ክርስቶስ የሕይወታችን መድኃኒት መሆኑን ከማስተማር ባለፈ አሳማ በመብላትና ባለመብላት የማትገኘውን የጽድቅ መንገድ በላተኛውን በመከልከል ሊሆን አይችልም።
በዚህ አንጻር የካቶሊክ ተገዳዳሪ ሆኖ ለመጣው አዲስ የፕሮቴስታንት ዓለም ያልተፈለገውን የለውጥ መንገድ ለመጀመር ምክንያት ሆኗል። በ 12ኛው ክ/ዘመን መገባደጃ ላይ ካቶሊክ የፈጠረችውን የመካነ ንሥሐ/ purgatory/ ጽንሰ ሃሳብ የግድ ህግ እንደሆነ ማስተማርን ለመተው ተገዳለች። ኃጥእ ሰው ንስሐ ሳይገባ ከሞተ፤ የንስሐ ቦታ በሰማይ አለው የሚለው ጸረ ወንጌል አስተሳሰብ በአዲስ ለውጥ እንቅስቃሴ ተቀባይነቱን አጥቷል። በእርግጥ ይህ አስተምህሮ ዛሬም ሳይጠፋ ተጠብቆ በሀገራችን ይገኛል።  መጽሐፈ ግንዘት «እምድኅረ ሞቱ ለሰብእ አልቦቱ ንስሐ» ሰው ከሞተ በኋላ የንስሐ ጊዜ የለውም» ቢልም ፍታትና ተስካር ንስሐ ሳይገባ የሞተውን ሰው ሥርየት ለማሰጠት የሚደረገው ሥርዓት አሁን ድረስ አለ። በካቶሊክ አስተምህሮ ላይ ከተነሳው የለውጥ ጥያቄ አንዱ ይህ ነበር።

Thursday, August 22, 2013

የማይቀረው ለውጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን መጎብኘቱ አይቀርም!

ባልተዘጋጀችበትና በማትፈልገው ለውጥ የሚደርስባት ጉዳት ከባድ ነው!

ክፍል አንድ፤

ለውጥና የለውጥ አስተሳሰብ
ለውጥ የሂደት ውጤት ነው። ስለወደድነው አይመጣም፤ ስለጠላነው አይቀርም። አንዳንዶች ለውጥን ለማስቀረት ይታገላሉ፤ ወይም በእነሱ ትግል የሚቀር ይመስላቸዋል። የለውጥ ህግጋት ግን አይቀሬ መሆኑን ስለሚያሳይ ይዘገይ እንደሆን እንጂ ያ የተፈራው ለውጥ እንደሚሆን አድርገው ለመቀበል ካልፈለጉት እንደማይሆን ሆኖ ይመጣል። በዚህ ምድር ላይ ባለበት ችክ ብሎ የኖረ ነገር የለም። ድንጋይ እንኳን ተፈረካክሶ አፈር ይሆናል። ፀሐይም በጭለማ ትጋረዳለች። በጋም በክረምት ይቀየራል። ብሉይም በሐዲስ ተሽሯል። ከእስራኤል ዘሥጋ ይልቅ እስራኤል ዘነፍስ የጸጋ ፍሰት ደርሶታል።በመወለድና በመሞት፤በመምጣትና በመሄድ፤ በመፈጠርና በማለፍ መካከልም የለውጥ ሕግጋት አለ። እግዚአብሔር ነገሮችን በጊዜ ዑደት ውስጥ እንዲያልፉ አድርጎ ፈጠረ እንጂ ባለበት ቆሞ እንዲቀር ያደረገው አንዳች ነገር የለም። ሌላው ቀርቶ ያለንባት ሰማይና ምድር እንኳን በአዲስ ሰማይና ምድር ትለወጣለች። መቼም የማይለወጠው እግዚአብሔር ብቻ ነው። ዘመን የማይቆጠርለትና የማይለወጥ እሱ ብቻ ስለሆነ ነብዩ ዳዊት እንዲህ አለ።
«አንተ ግን ያው አንተ ነህ፥ ዓመቶችህም ከቶ አያልቁም» መዝ 102፤27      
  የሀገራችን ገበሬ ክረምት ከመድረሱ አስቀድሞ የወራቶችን ለውጥ አስልቶ ቅድመ ዝግጅት አድርጎ መጻዒውን ጊዜ ይጠባበቃል። ዘመኑን ጠብቆ በሚመላለሰው ለውጥ ውስጥ ራሱን አስማምቶና ውጤታማ ሆኖ እንዲቀጥል ለማድረግ ቅድመ ዝግጅቱን በየተራ ካልፈጸመ በስተቀር የበጋው በክረምት መለወጥ በራሱ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖውን አሳርፎ ያልፋል።    በሰለጠነው  ዓለም ያሉ ምሁራን በማይቀረው የለውጥ ሂደት የተነሳ ስለለውጥ ያላቸው ግንዛቤ ትልቅ ስለሆነ ሥራቸውን ከለውጥ ጠቀሜታና ተግዳሮት አንጻር ቅድመ ምልከታ በማድረግ ለምላሹ አስቀድመው ይዘጋጃሉ።                                                                                                                                    
 

Thursday, August 15, 2013

ለአቡነ ገብርኤል ጥሪ የሀዋሳ ምእመናንና የሰ/ት/ቤት ወጣቶች ምላሽ ሰጡ!

«እስከ ጥቁር ዉሃ ሄዶ የተቀበለ  ሕዝብ እስከ ጥቁር ውሃ ተሰደደ» (ደጀ ብርሃን)

 /ምንጭ፦dejeselaam-dejeselaam.blogspot.com/
 በሀዋሳ በግፍ የተሰደዱት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ምዕመናንና የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች ብፁዕ አቡነ ገብርኤል "ኑ ልጆቼ ወደ ቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ ተመለሱ" ሲሉ ላደረጉት ጥሪ ምላሽ መስጠታቸውን ከስፍራው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ ምዕመናኑ ለአቡነ ገብርኤል በአድራሻ፣ ለ17 የቤተክርስቲያንና መንግሥታዊ ተቋማት ደግሞ በግልባጭ ያሠራጩትን ደብዳቤ በብሎጋችን ፖስት እንድናደርግላቸው ለዝግጅት ክፍላችን በኢሜይል ልከውልናል፡፡ የደብዳቤው ሙሉ ይዘት የሚከተለውን ይመስላል፡፡
ነሐሴ 7 ቀን 2005 ዓ.ም
ለብፁዕ አቡነ ገብርኤል
የሲዳማ፣ ጌዴኦ፣ አማሮና ቡርጂ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ሀገረስብከት ሊቀጳጳስ
ሀዋሳ፣
ጉዳዩ: ̶  "ወደ ቤተክርስቲያን እንድትመለሱ" በማለት ለተጻፈልን ደብዳቤ ምላሽ ስለመስጠት
በቀን 25/1/171/2005 (ቀኑን ከደብዳቤው ላይ ማየት እንደሚቻለው) በቁጥር 1459/171/2005 የተጻፈ ደብዳቤ ሐምሌ 25 ቀን 2005 ዓ.ም ከምሽቱ 1፡30 ሰዓት በሁለት ፖሊሶች እጅ ተልኮልን ወንጌል ከምንማርበት ሥፍራ ተጠርተን መተማመኛ ፈርመን በመቀበል በአንክሮ ተመልክተነዋል፡፡ ቀጥሎም ለምዕመናን ተነቦ ውይይት ከተደረገበት በኋላ የጋራ አቋም የተወሰደበት ሲሆን፣ ጥሪ ማድረግዎን በስምንቱም አጥቢያ ቤተክርስቲያናት ዐውደ ምሕረቶች እንዲነበብ እንዳደረጉት ሁሉ ይህንን የምላሽ ደብዳቤያችንንም  ለሰፊው ምዕመን በተመሳሳይ ሁኔታ እንዲያስነብቡልን አደራ እንላለን፡፡ የሰጠነውም ምላሽ የሚከተለው ነው፡፡ 
አንደኛ፣ ደብዳቤውን እንደ ወንጀል ክስ መጥሪያ በፖሊስ እጅ መላኩ እና ከመደበኛ የሥራ ሰዓት ውጪ ከምሽቱ 1፡30 ከሆነ በኋላ መምጣቱ፣ እንዲሁም መተማመኛ ፈርመን እንድንቀበል መደረጉ ከሕግ አንፃር ተገቢ ካለመሆኑም በላይ የጥሪው አካሄድ የፍቅር እንዳልሆነ ተገንዝበናል፡፡ በተጨማሪም ደብዳቤው ቅንነትና እውነት ያለበት ሳይሆን ማስመሰልና ውሸት የተሞላበት ከመሆኑም በላይ እርቅ፣ ሠላምና አንድነትን ከማምጣት ይልቅ ራስን ከሕዝብ (ከታሪክ) ፍርድ ለመከላከልና ለገጽታ ግንባታ (ፕሮፖጋንዳ ፍጆታ) ሲባል ብቻ የተዘጋጀ መሆኑን ተረድተናል፡፡
በደብዳቤው ውስጥ "የተወደዳችሁ ልጆቻችን ምዕመናንና ወጣቶች" የሚል ሐረግ ተደጋግሞ ይታያል፡፡ ልጆቻችሁ እንደሆንን ሲነግሩን ከእርስዎ ሳይሆን ከሌላ አካል የሰማነው ያህል መስሎ ነው የተሰማን፡፡ ምክንያቱም እኛ ልጆችዎ እንደሆንን ባንክድም ከእርስዎ ዘንድ ግን የአባትነት ወግ ፈጽሞ አይተን ስለማናውቅ ነው፡፡ ከዚህ አንፃር የደብዳቤውን ይዘት ስንመረምረው የተረዳነው ነገር ቢኖር ̶ አንዳንዴ በግልጽ፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ በስውር በሀገረ ስብከታችን የሚካሄዱትን ሕገወጥ ሥራዎች ለመሸፋፈንና "ለምን አሳደዳችኋቸው? ለምን አትመልሷቸውም"? ብሎ ለሚጠይቃችሁ አካል "ይኸው፣ በደብዳቤ ጠርተናቸውም እምቢ ብለውናል" በማለት በብልጣብልጥ አካሄድ ሪከርድ ለማስያዝ እና ወደፊት ለምታደርጉት የተለመደ እንቅስቃሴ ምክንያት ለማመቻቸት መሆኑን ለማወቅ ልዩ ጥበብ አያስፈልገውም፡፡
ጥሪዎ ቅንነት ቢኖረው ኖሮና እኛን "ልጆቻችን" እንዳሉን ሁሉ እርስዎም አባትነትዎን አምነውበት ቢሆን በአባትና በልጅ መካከል አለመግባባት ተፈጥሮ ልጅ ቤቱን ለቆ ቢኮበልልና አባትም በበኩሉ የኮበለለው ልጅ ወደ ቤቱ እንዲመለስ ቢፈልግ ደብዳቤ ጽፎ በፖሊስ በኩል መላክ ትክክለኛው መንገድ አለመሆኑን ለእርስዎ መንገር ለእናት ምጥ እንደማስተማር ይቆጠራል፡፡
በተጨማሪም፣ ከቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ ተባርረን ከወጣን ሁለት ዓመታት እስኪቆጠሩ ድረስ ከሀገረ ስብከቱ ውጪ ያሉ ካህናትና አገልጋዮች መጥተው ሲባርኩንና ሲያፅናኑን እርስዎና ከእርስዎ ሥር ያሉ አባቶች ግን የጠፉትን በጎች ፍለጋ ሳትወጡ ኖራችሁ፣ ዛሬ ከረፈደና ከመሸ፣ ጉዳዩም ከእጃችሁ ወጥቶ በጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤትና በቅዱስ ሲኖዶስ ከተያዘ በኋላ ድንገት ይህንን ኦፊሴላዊ ጥሪ ለማድረግ የተገደዳችሁበትን ሚስጥር ስናሸተው ጠረኑ የሚነግረን ሌላ ጉዳይ መሆኑን ነው፡፡ ደብዳቤው ሆን ተብሎ እውነታውን ለማዛባት የተደረጉ ጥረቶች እንዳሉበት ከማሳየቱም በላይ "እንዳያማህ ጥራው፤ እንዳይበላ ግፋው" እንደሚባለው ለይተበሀል ያህል ብቻ የተጻፈ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡
ሁለተኛ፣ በደብዳቤው የመጀመሪያ መሥመር ላይ፣ "ከቤተክርስቲያን ተባረናል በሚል . . .  እየተሰባሰባችሁ የምትገኙ ልጆቻችን ምዕመናንና ወጣቶች . . . " የሚል ሐረግ ሰፍሯል፡፡ ይህ የሚያሳየን እኛ ተባረናል እንላለን እንጂ እናንተ ማባረራችሁን አምናችሁ ለመቀበል እንደማትፈልጉና ዛሬም እንኳን ፀፀት እንዳልተሰማችሁ ያመለክታል፡፡  ታዲያ ከእናት ቤተክርስቲያናችን ውጪ ለመገኘታችን ምክንያቱ እርስዎ፣ የእርስዎ አስተዳደር እና እርስዎ ያደራጁት ማኅበር ካልሆነ፣ ቤተክርስቲያንና ቅጥሯ አስጠልቶን አካባቢ ለመለወጥና ለሽርሽር የሄድን መስሎዎት ይሆንን? ይሁን እንጂ እንዳባረራችሁን መላው የሀዋሳ ምዕመናን ምሥክር ናቸው፡፡

Tuesday, August 13, 2013

ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ አገልግሎቷን እንድታድስ የተቋቋመ ትምህርት ቤት

                          ቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ 
  ከተመሠረተበት እስከ አሁን
  (ክፍል አንድ) www.tehadeso.com
  ቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ በቀድሞ መጠሪያው “ከፍተኛ የትምህርት ማዕከል”፣ አሁን ወዳለበት ቦታ ከመዘዋወሩና ደረጃውም ወደ ኮሌጅነት ከፍ ከማለቱ በፊት ትምህርት ማስተማር የጀመረው በገነተ ልዑል ቤተ መንግሥት ውስጥ ነበር፡፡ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በጣልያን ወረራ ምክንያት ሕገ ወጥ የሆነውን ወረራ ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለማስረዳትና አቤቱታን ለማቅረብ ከሀገር ውጭ ተጉዘው ነበር፡፡  በውጪው ዓለም በስደት በቆዩበት ዓመታት እርሳቸውና አብረዋቸው የተሰደዱ ባለስልጣናት ከጎበኟቸው ልዩ ልዩ ተቋማት መካከል የእንግሊዝ ቤተ ክርስቲያን አንዷ በመሆኗ፣ የቤተ ክርስቲያኒቱ ጥንካሬ ምክንያት ደግሞ መንፈሳዊ የትምህርት ተቋማቶቿ አገልጋዮችን በብቃትና በጥራት እያስተማሩና እያዘጋጁ ለቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊ አገልግሎት በማሰማራቷ መሆኑን በመገንዘባቸው ይህንንም ከኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ሁኔታ ጋር አገናዝበው ቤተ ክርስቲያን ልትታደስ ይገባታል ብለው በማመናቸው ከስደት እንደተመለሡ ቤተ ክርስቲያን ለምእመናን የምትሰጠው መንፈሳዊ አገልግሎት መጽሐፍ ቅዱሳዊ እንዲሆንና ሰባክያንና መምህራን በትምህርተ ወንጌል ዘመኑንና ትውልዱን መዋጀት የሚችሉ እንዲሆኑ፣ እውቀት የበለጠ እንዲስፋፋ ትኩረት በመስጠታቸው፣ በተለይም ካህናት በሕዝቡ ዘንድ ተሰሚነት ስላላቸው እውቀታቸው ከተሻሻለ ለሕዝቡ የተሻለ አገልግሎት ይሰጣሉ ብለው በማሰብ፣ ትምህርት ቤት እስኪዘጋጅ ድረስ እንኳ ሳይጠብቁ ቤተ መንግሥታቸውን (አሁን አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ስድስት ኪሎ ካምፓስ) ትምህርት ቤት አድርገው ተማሪዎችን በመቀበል፣ በቶሎ ደርሰው ሀገርንና ቤተ ክርስቲያንን በበለጠ ያገለግላሉ ተብለው የተገመቱትን ሊቃውንት ሰብስበው መምህር መድበው የእንግሊዝኛ ቋንቋ እንዲማሩ አደረጉ፡፡ የዚህን ቋንቋ ትምህርት ቤት ጀምረው እስከ መጨረሻው ከተከታተሉት ሊቃውንት መካከል መምህር መልእክቱ (በኋላ ብፁዕ ወቅዱስ.አቡነ.ቴዎፍሎስ) ይጠቀሳሉ፡፡

       ከዚህ በኋላ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ በ1935 ዓ.ም. የቅድስት ሥላሴን መንፈሳዊ ትምህርት ቤት ሕንጻ የመሠረት ድንጋይ አስቀመጡ፤ በ1937 ዓ.ም. በይፋ ተመርቆ ተከፈተ፡፡ በዚያ ወቅት የአስተዳደር ኃላፊነት የተሰጣቸው የሚከተሉት ነበሩ፡-
1.     ሊቀ ሥልጣናት መልእክቱ (በኋላ ብፁዕ አቡነ ቴዎፍሎስ)- ሊቀ መንበር
2.    ሚስተር ሃፍዝ ዳውድ ግብጻዊ- ዳይሬክተር
3.    ብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ-  አባል
4.    አለቃ ሐረገ ወይን- አባል
5.    ባላንባራስ ወልደ ሰማዕት- አባል
6.    መ/ር ፌላታያስ ሰማዕት- አባል
7.    መጋቤ ሐዲስ ወ/ሚካኤል- አባል
የትምህርት ቤቱ መምህራንም፡- ሃፍዝ ዳውድ፣ መ/ር ፌላታዎስ፣ አለቃ መኩሪያ፣ አለቃ ወልደየስ፣ አባ ፍስሐ፣ አባ አሥራት ዘገየ፣ ሊቀ ጠበብት አክሊለ ብርሃን ወልደ ቂርቆስ ይባሉ ነበር፡፡ ለትህምርት ቤቱ በአመራር ደረጃ እና በመምህርነት የተመደቡ በወቅቱ ሀገሪቱ ላይ ዕውቅ ሊቃውንትና ባለ ሥልጣናት መሆናቸው ተቋሙ የታለመለትን ዓላማ ከግብ እንዲያደርስ ከልብ የታሰበበት እንደነበረ በግልጽ ያስረዳል፡፡

Sunday, August 4, 2013

የማኅበረ ቅዱሳን የተሸፈነ ማንነት በአሜሪካ ተገለጠ!



One of his loyal bishop
እንደስንዝሮ ታሪክ ሰኞ ቀን ዩኒቨርስቲ ተረከዝኩ፤ ማክሰኞ ብላቴ ላይ ተወለድኩ፤ ረቡዕ ዕለት በአቡነ ገብርኤል ማኅበረ ቅዱሳን በሚል የክርስትና ስም ተጠመኩ፤ ሐሙስ የቤተ ክርስቲያንን ጉዳይ ልሰብር የነገር እንጨት ለቀማ ሄድኩ የሚለው ይህ ማኅበር ብዙዎቹን ለማሰለፍ ቢችልም የስንዝሮ ታሪኩ እየተገለጠና እየተገፈፈ በመታወቅ ላይ ይገኛል። በተለይም የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህናት ይህንን ማኅበር በጭለማ መንፈስ የሚነዳ፤ የክፋት ኃይል አድርጎ በመመልከቱ ደረጃ ትልቅ ግንዛቤ እንዳለ ይታወቃል። ወጣቱ ትውልድም ቢሆን እየዋለ እያደረ የማኅበሩን እንቅስቃሴና እርምጃ ፤ የገንዘብ አቅሙን ማደርጀትና ወደንግዱ ዓለም ጎራ ማለቱን በማየት ከየት ተነስቶ ወደየት? ለመሄድ እንደፈለገ በተፈጠረበት ግርታ የተነሳ ባለበት ቆም ብሎ ለማስተዋል መገደዱን የምናገኛቸው ትዝብቶች ያስረዱናል። አንዳንዶቹም ርቀው ሲያዩት ወርቅ የመሰላቸው ይህ ማኅበር ቢቀርቡት የመዳሪያና የገንዘብ መሸቀጫ ስብስብ መሆኑን ተመልክተው አፍረውበት እርባና እንደሌለው ሲናገሩም ይደመጣል።  ይህ ማኅበር ከራሱ ከንግድ ተቋሙ ኃላፊዎችና የእንደጋሪ ፈረስ ከሚነዱለት ጥቂት ተከታዮቹ በስተቀር እንደመንፈሳዊና ጠቃሚ ማኅበር የመቆጠሩ ነገር እንደገለባ በመቅለል ላይ ይገኛል
በ1950 ዓ/ም የተቋቋመውና  ከሃይማኖት የለሹ የደርግ መንግሥት ጋር በመተባበር የጠቅላይ ቤተክህነት ሹማምንት በ1975 ዓ/ም እንዲፈርስ የኢሠፓአኮ ሠይፍ የመዘዙበት «ሃይማኖተ አበው» የተሰኘውን አንጋፋ ማኅበር ከደርግ ውድቀት በኋላ እንደገና ነፍስ ዘርቶ ሊቋቋም ሲንቀሳቀስ ከእኔ ሌላ ማንንም አልይ የሚለው የብላቴው የወታደሮች ማኅበር፤ ማኅበረ ቅዱሳንና ደጋፊዎቹ ሁለተኛ ጊዜ ሠይፍ አሳርፈውበት ከነአካቴው እንዳይኖር አድርገው አከርካሪውን እንደመቱት የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው። ማኅበረ ቅዱሳን ከክፋቶቹ ሁሉ የላቀው ክፋት ከእርሱ በስተቀር አንድም ማኅበር ኅልውና አግኝቶ እንዳያንሰራራ በተለጣፊ ጳጳሳቶቹና በአገልጋዮቹ በኩል ማስመታት መቻሉ ነው። እንኳን ማኅበራት ጳጳሳሶቹ እንኳን ከፓትርያርኩና ከፌዴራል ፖሊስ በላይ የሚፈሩት ይህንን ማኅበር መሆኑ የአደባባይ ምስጢር ነው። በሹክሹክታ የሚያወሩትን የሚሰማቸው እስኪመስላቸው ድረስ ይህንን ማኅበር እንደሚከተላቸው ጥላ ይከታተለናል ብለው ይንቀጠቀጡለታል። ገሚሶቹም ነውራሞች ሳይወዱ እየሳቁ በታማኝ ሎሌነት ያገለግሉታል።