Showing posts with label መረጃ. Show all posts
Showing posts with label መረጃ. Show all posts

Wednesday, March 9, 2022

የቤተ ክርስቲያኒቱ ጠላቶች በጉያዋ ናቸው!

ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በሦስት መንገድ ችግር ውስጥ ናቸው። 1ኛ/ ወደው ባልተወለዱበት ዘር ትግሬ በመሆናቸው በኦሮሙማው ኃይል የሚታዩት እንደጠላት ነው። 2ኛ/ የራሳቸው የአመራርና የሥልጣን አጠቃቀም ድክመት የተነሳ የመፈራትና የመከበር አቅማቸው አናሳ መሆኑ ሌላኛው ችግር ነው። 3ኛ/ ሊቃነ ጳጳሳቱ በራሳቸው የግል ኑሮ ምቾትና ምንግዴለሽነት የተነሳ ቤተ ክርስቲያኒቱን ስለረሷት ከፓትርያርኩ ጋር መቆም አልቻሉም። ወደፊትም ቢሆን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አሁን ባለችበት መንገድ ከተጓዘች በውስጥና በውጪ ጠላቶቿ እየተገዘገዘች የመውደቋ ነገር የጊዜ ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር መፍረሷ አይቀርም። የዚህ ፅሁፍ አቅራቢ ሦስት ምክር ያቀርባል። 1/የቀድሞው ፓትርያርክ ከዚህ ዓለም ስላረፉ አሁን ያሉት ፓትርያርክ ከእድሜ: ከህመምና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች የተነሳ በቂ ውሳኔ እየተሰጠ ባለመሆኑ ችግሮቹ ተደራራቢ እየሆኑ በመገኘታቸው ለቤተክርስቲያኒቱ ፈጣን አመራር መስጠት የሚችል ሰው በራሳቸው በፓትርያርኩ አቅራቢነት እንደራሴ ቢሾም: 2/ አጠቃላይ የሰበካ ጉባኤ ስብሰባ በዓመት ሁለት ጊዜ መሆኑ ከድግስና ከተጋነነ ሪፖርት ውጪ ችግር ፈቺ ስላልሆነ የየአህጉረ ስብከቶቹን ችግር የሚያጠናና ለእንደራሴው ቢሮ የሚያቀርብ ቡድን ተሰይሞ በየችግሮቹ ዘርፍ ፈጣን ውሳኔ ቢሰጥባቸው: 3/ ለቤተ ክርስቲያኒቱ የሚቆረቆሩ በሙያ: በልምድና በችሎታ ከልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የአማካሪ ቦርድ ቢቋቋም የተሻለ ይሆናል። ይህ አሰራር በግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያና ተግባራዊ ሆኖ ብዙ ችግር መቃለል ተችሏል። ከዚህ ውጪ አሁን ባሉት ጳጳሳት የሚፈታ የቤተ ክርስቲያን ችግር የለን። አይኖርምም። ራሳቸው የቤተ ክርስቲያኒቱ ችግሮች ናቸው። ፈሪሃ እግዚአብሔር የነበራቸውና በጥብዓት ይታገሉ የነበሩት ሁሉ በዐረፍተ ዘመን ሁሉን ትተው ሄደዋል። አሁን ካሉት ጳጳስ ተብዬ ወመኔዎች አንዱ የሆነው ቅዱስ ፓትርያርኩ ለመናገር ያሰቡትን ሃሳብ እንዳያስተላልፉ የዱርዬ ስራውን እንዴት ይሰራ እንደነበር ይህ ቪዲዮ ያሳያልና ተመልክታችሁ ፍረዱ! በፕሮቶኮል ደረጃ ከፓትርያርኩ ፊት መነጋገሪያ ማይክ አይነሳም። ማፊያው ጀነራል ሦስት መነጋገሪያ ፓትርያርኩ እንዳይነጋገሩ ሲያሸሽና ለአዳነች አቤቤ ሲሰጥ ተመልከቱ።

Friday, October 20, 2017

"ማኅበረ ቅዱሳን ኢትዮጵያዊው ሙስሊም ብራዘርሁድ"



ማኅበረ ቅዱሳንን ከግብፁ ሙስሊም ብራዘርሁድ ጋር የሚያመሳስለው ተግባራትና ሂደቶች!

ሙስሊም ብራዘር ሁድ ወይም የሙስሊም ወንድማማቾች ማኅበር የተባለው ድርጅት በ1928 ዓ/ም በግብጽ ተመሠረተ። ከሰማንያ ዐመታት በኋላ በጄኔራል አልሲሲ መንግሥት በአሸባሪነት ተፈርጆ ድምጥማጡ እስኪጠፋ ድረስ በ70 ሀገሮች ውስጥ ቅርንጫፎቹን ከፍቶ በዘመናዊና ሃይማኖታዊ ትምህርት ቤቶች፤ በገበያ ማዕከላት፤ በንግድ ሱቆች፤ በማከፋፈያ ድርጅቶች፤ በሚዲያ ተቋማት ወዘተ የሀብት ማግበስበሻ መንገዶች እየተሳተፈ ክንዱን በማፈርጠም ለእንቅስቃሴው የሚጠቅመውን የገንዘብ ምንጭ ሲፈጥር ቆይቷል። ይህ የግብጹ ሙስሊም ብራዘር ሁድ በዐረብ ሀገራት ውስጥ ተመሳሳይ የሙስሊም ወንድማማች ማኅበራትን በማደራጀትና በማሰልጠን መንግሥታቱን ሲያስጨንቅ የቆየ ሲሆን አሁንም እያስጨነቀ ይገኛል።

የሙስሊም ብራዘር ሁድ ለተባለው ሃይማኖታዊ-ፖለቲካዊ ድርጅት ዋነኛ ተቀባይነት ማግኘት ዋናው ምክንያት የሆነው በእስላሙ ሕብረተሰብ ውስጥ ቶሎ ሰርጾ እንዲገባ የሚያካሂደው ሃይማኖታዊ አስተምህሮቱና  ለዚህ እምነት መክፈል የሚገባውን ዋጋ ሁሉ በመክፈል ከአላህ ዘንድ የሚከፈለውን ምንዳ ለመቀበል ቶሎ መሽቀዳደም ተገቢ መሆኑን አበክሮ በመስበኩ የተነሳ ነው።

1/ የሙስሊም ብራዘር ሁድ መዋቅራዊ እንቅስቃሴ

 ሙስሊም ብራዘር ሁድ መዋቅሩ በሀገሪቱ የመንግሥት ሲቪላዊ መዋቅር ደረጃ የተዘረጋ ነው። ይህም ከማዕከላዊ ቢሮው ተነስቶ አባል በሆኑ በእያንዳንዱ ቤተሰብ ውስጥ በሰንሰለት የተያያዘ ነው። ቤተሰባዊውን የአባልነት ማኅበር «ኡስራ» ይሉታል። አንድ «ኡስራ» አምስት አባላት ሲኖሩት ከአምስት በላይ ከሆነ በሁለተኛ የኡስራ ስያሜ ደረጃ ይዋቀራል። በቤተሰቡ ያሉትን ኡስራዎች የሚመራ ደግሞ የቤተሰቡ አባል የሆነ በእስልምና ሃይማኖቱ የበሰለና የብራዘር ሁድ አስተምህሮት በደንብ የገባውን ሰው የቤተሰቡ ጉባዔ ይመርጠውና «ናቂብ» ተብሎ ይሰየማል። ይህ «ናቂብ» የተባለው ሰው የቤተሰቡ አባላት በእስልምናው ደንብ ዘወትር ስለመንቀሳቀሱ ይቆጣጠረዋል፤ ያስተምረዋል፤ ይነግረዋል። ያልተመለሰውን በማኅበረሰቡ ደረጃ ለተቀመጠውና ከፍ ላለው ሃይማኖታዊ መሪ ያቀርበዋል። ይህ ሁሉ ሲሆን ስለእስልምናው የሚደረግ እርምጃ በመሆኑ በደስታ ከሚቀበል በስተቀር ማንም በተቃውሞ አያንገራግርም፤ ሊያንገራግርም አይችልም። ምክንያቱም ጸረ እስልምና እንደሆኑ ራሳቸውን አስገዝተዋልና። በዚህ ዓይነት አደረጃጀት የሙስሊም ወንድማማቾች ማኅበር ከላይ ወደታችና ከታች ወደላይ የተሳሰረ መዋቅር አለው።

2/   የገንዘብ ምንጮቹን ማሳደግ

ገንዘብ የዚህ ዓለም እንቅስቃሴ የደም ሥር ነው። አባላት ለመመልመል፤ እንቅስቃሴውን ለማስፋፋት፤ የሽብር ተግባሩን ለመፈጸም፤ ለመደለል፤ ለመሰለል፤ ሃይማኖታዊ ዶክትሪኑን ለማስተማር  እጅግ ጠቃሚ ነገር መሆኑን ጠንቅቆ የተረዳው ብራዘር ሁድ የገንዘብ አቅሙን ለሀገር ውስጥና ድንበር ዘለል ተግባሩ ያውለው ዘንድ ተግቶ ይሰራል።

የእስላም ወንድማማቾች ማኅበር ሁለት ዓይነት የገንዘብ ምንጮች አሉት። አንዱ በውጪ ሀገራት ካሉ አባላቱ በመዋጮ የሚሰበሰብ እንዲሁም ብዙ ሃብት ካላቸው የድርጅቱ ደጋፊ ሚሊየነሮች  የሚደረግለት የገንዘብ ፈሰስና በእስላማዊ መንግሥታት ስር ከተሸሸጉ ባለስልጣናት የሚዋጣለት ገንዘብ ነው።  ሁለተኛው ደግሞ በተራድዖ ስም ከውጭ የሚያሰባስበውን ገንዘብ ወደልማት ካዝና በመቀየር በአካባቢ ልማት፤ በትምህርት ቤቶችና መድራሳ ማቋቋም፤ ሥራ አጥ ህብረተሰብን በማደራጀት፤ የራስ አገዝ እንቅስቃሴን በመመሥረት የሚሳተፍ ሲሆን ለዚህም ሀገር በቀል የእርዳታ ስልት በመቀየስ መዋጮውን ቅርጹን ለውጦ ያግበሰብሳል። ይህም፤

ሀ/ ከአባልነት መዋጮና
ለ/ ከንግድ ድርጅቶቹና ከሚዲያ ተቋማቱ የሚገኝ ገቢ ነው። በዚህ አካሄዱ ማኅበረ ቅዱሳን ትክክለኛ ገፅታው የሙስሊም ብራዘርሁድ ግልባጭ ነው። በሚሊየን ብሮችን ይሰበስባል፣ ያንቀሳቅሳል።

ይህንን ገንዘብ በተለያየ የገንዘብ ማስቀመጫ ስልቶችና በብዙ የሂሳብ አካውንቶች ቋት ውስጥ በተለያየ ስም በማስቀመጥ ለሚፈልገው ዓላማ በፈለገበት ሰዓት ማንም ሳያውቅበት ያውለው ነበር።

3/ በመንግስታዊ ተቋማት ውስጥ ሰርጎ መግባት

ብራዘር ሁድ አባላቱን ሲመለምል ነጻና ገለልተኛ የሆኑትን ብቻ አይደለም። ከሚኒስትሮች እስከፍርድ ቤቶች፤ ከመከላከያ እስከ ፖሊስ መምሪያዎች፤ ከድርጅት ሥራ አስኪያጆች እስከ አስተዳደር ኃላፊዎች ድረስ በአባልነት መልምሎ፤ አሰልጥኖና ሃይማኖታዊ ትጥቅ አስታጥቆ የሚንቀሳቀስ ድርጅት ነበር። እነዚህ የመንግሥታዊ አካላት ክፍሎች ድርጅታቸው ለሚነሳበት ተቃውሞና ኅልውናውን ፈታኝ ለሆኑ ችግሮች የግብዓት ምንጭ ሆነው ያገለግላሉ። አስፈላጊ በሆነ የመረጃ፤ የፋይናንስና የአፈና ሥራው በትጋት ይሰራሉ።
ይህ ድርጅት እንደሃይማኖታዊ ተቋም አራማጅነት ተነስቶ ወደፖለቲካዊ ሥልጣን መቆናጠጥ እርምጃው ለማደግ መሠረት አድርጎ የሚነሳው የእስልምና ሃይማኖትን ነው። ይህም ብራዘር ሁድን መቃወም እስልምናን እንደመቃወም እንዲቆጠር በሕብረተሰቡ ዘንድ የኅልውናውን ስዕል በማስቀመጥ እንዳይነካ ወይም እንዳይጠፋ ረድቶታል። የእስልምናውን አስተምህሮ መነሻ በማድረጉ የማይነቃነቅ ፖለቲካዊ ግብ ለማስረጽ ያገዘው ሲሆን የዚህም መገለጫው በአልሲሲ መንግሥት ላይ በአንድ ጊዜ እስከ 33 ሚሊዮን ተቃዋሚ ሰልፈኞችን በመላ ሀገሪቱ ማንቀሳቀስ የሚችል ድርጅት አድርጎታል።
 ይሁን እንጂ የጀነራል አልሲሲ መንግሥት እርምጃ ስልታዊ በመሆኑ በአንድ ቀን ብቻ ከሁለት ሺህ በላይ ከፍተኛና ዝቅተኛ አመራሩንና የሃይማኖታዊ ተፍሲር መምህራኖቹን ለቃቅሞ ወደማጎሪያ ካምፕ በመክተቱ ድርጅቱ በ85 ዓመት እድሜው አይቶት የማያውቀውን ውድቀት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እንዲያስተናግድ አድርጎታል። በአልሲሲ መንግሥት የተተገበረው «ወፎቹ እንዲበተኑ ቅርንጫፉን መቁረጥ» የሚለው አባባል ብቻ ሳይሆን ግንዱን መንቀል በመሆኑ የብራዘር ሁድ ዋና መሪ መሐመድ ሙርሲን ጨምሮ ከፍተኛውን የሹራ ካውንስል ሳይቀር ከስር ገርስሶታል። በሺዎች የሚቆጠሩ አባላቱም የሞትና የእስራት ፍርድ ተከናንበዋል። አልሲሲ በቲቪ ቀርበው "ብራዘር ሁድን ከስረ መሠረቱ ነቅለን ካላጠፋን ሰላም የለንም" በማለት ድራሹን አጥተውታል። ዛሬም ድረስ የተቃውሞ ሰልፎች ያሉ ቢሆንም በሃይማኖት ካባ ስር በተሸፈነው ድርጅት በኩል የአእምሮ አጠባ ተደርጎ የተታለለው ሕብረተሰብ እንጂ ብራዘር ሁድ እንደተቋም በግብጽ ታሪክ ግብዓተ መሬቱ ተፈጽሟል። ያ ማለት ግን ብራዘር ሁድን የሚደግፍ፤ የሚጠባበቅና እንዲያንሰራራ የሚፈልግ የለም ማለት አይደለም። ኢትዮጵያዊው ሙስሉም ብራዘርሁድ ማምጣት የሚፈልገው ለውጥ በራሱ ቅኝት የሚዘወር ቤተ ክህነትና በአባላቱ ተሳትፎና ስውር እጆቹ የሚቆም አዲስ ስርአተ መንግስት ነው። ያ ካልሆነ በኦርቶዶክስ መንፈሳዊ መዋቅር ውስጥ ሳይዋጥ የራሱን ልእልና እያስጠበቀ ተከልሎ ለመቆም ባልፈለገም ነበር።

4/ማኅበረ ቅዱሳን እንደክርስቲያን ብራዘር ሁድ ስንል ምን ማለታችን ነው?

1/ ተቋማዊ አደረጃጀቱ ከመንግሥትም፤ ከቤተ ክህነትም ቁጥጥር ነጻ መሆኑ
2/ የራሱን አባላት የሚመለምልና የሚያደራጅ መሆኑ
3/ የራሱ የሆነ የገቢ ምንጭ ያለውና የንግድ ተቋማትን የሚያንቀሳቅስ መሆኑ
4/ ከአባላቱ ልዩ ልዩ መዋጮዎችና የስጦታ ገቢዎችን በመሰብሰብ በልማት ውስጥ እየተንቀሳቀሰ እንዳለ የማሳየት ብልሃት ያለው መሆኑ
5/ በመንግሥት ተቋማትና መሥሪያ ቤቶች፤ ፍርድ ቤቶች፤ ፖሊስ መምሪያዎች፤ በኮሌጆችና ዩኒቨርሲቲዎች ስውር መዋቅር ያለው መሆኑ
6/ በቤተ ክርስቲያኒቱ ላዕላይ መዋቅርና እስከ አጥቢያ ድረስ በተዘረጋው አስተዳደር የራሱ አደረጃጀት የዘረጋ መሆኑ
7/ በቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ውስጥ የራሱን ጳጳሳት በመመልመል ማስሾም የቻለ መሆኑ፣




በመመልመል ማስሾም የቻለ መሆኑ
9/ ከሀገር ውጭ ዓለም አቀፍ ቢሮዎችን ከፍቶ የሚንቀሳቀስና አባላት ያሉት መሆኑ
10/ ከዓለም አቀፍ የገቢ ፈጠራው ውስጥ በልማት ሰበብ የሚያጋብስ መሆኑ
11/ የመረጃ፡ የስለላና የትንተና መዋቅር ያለው መሆኑ
12/ የቤተ ክርስቲያኒቱን አደረጃጀቶች ለራሱ ዓላማ የመጠቀም አቅም ያለው መሆኑ
( ሰንበት ት/ቤቶችን፤ የጥምቀት ተመላሽና የጽዋ ማኅበራትን)
14/ የግለሰቦችን ስም በማጥፋት ወይም ራሳቸውን በማጥፋት፡በማባረር፡በመደብደብ ወይም ግለታሪካቸውን ለራሱ ዓላማ ጠምዝዞ በማዋል እርምጃ መውሰድና ማስወሰድ የቻለ መሆኑ
15/ ስሙን ለማግነን፤ ክብሩን ለማስጠበቅ የሚያስችል በራሱ የሚመራ እንዲሁም በፖለቲካ የተቃውሞው ጎራ የተሰለፉ ደጋፊዎችና በስውር መረብ የሚንቀሳቀስ የሚዲያ ተቋም ያለው መሆኑ፤
ማኅበረ ቅዱሳንን ክርስቲያናዊ ብራዘር ሁድ እንድንለው ያስችለናል።

እስካሁንም ማንም ምላሽ ሊሰጥበት ያልቻለው ዋናው ነጥብ ማኅበረ ቅዱሳን ከመንግሥት እይታ ውጪ መሆን ባይችልም ከመንግሥት ቁጥጥር ውጪ የሆነ ክርስቲያናዊ ማኅበር መሆኑ ሲሆን እንደክርስቲያናዊ ተቋምነቱ  ደግሞ ቤተ ክርስቲያኒቱ በማኅበሩ ላይ ቁጥጥርና ክትትል የማድረግ ችሎታ አንዳችም አቅም የሌላት በመሆኑ ያሳዝናል:: በመንግሥትም፤ በቤተ ክህነቱም ማንም ጠያቂ የሌለው ሆኖ መቆየቱን ለማመን ያለመፈልግ ዝንባሌ መኖሩም ያስገርማል::  ማኅበሩ እንደምክንያት ሁልጊዜ የሚያቀርበው ሲኖዶስ በሰጠኝ ደንብ እመራለሁ ቢልም እውነታው ግን ብራዘር ሁድ በሆኑ ጳጳሳት አባላቱ በኩል የሚመቸውን ደንብ አስጸድቆ ያለጠያቂ በነጻነት ከሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ የገቢ አቅሙን እያሳደገ፤ የቤተ ክርስቲያኒቱን አባላት ለራሱ አባላት እየመለመለ፤በቤተ ክርስቲያኒቱ ቁመናና መልክ የራሱን አደረጃጀት፤ መዋቅርና እንቅስቃሴ እያከናወነ ያለ ማኅበር መሆኑ የማይካድ እውነታ ነው። ለምሳሌ የማኅበሩ ብራዘር ሁድ አባላት ጳጳሳቱ አባ ማቴዎስ፡አባ ቀውስጦስ፡ አባ ቄርሎስ፡ አባ ያሬድ፡አባ አብርሃም፡አባ ሳሙኤል፡ በአባ ማቴዎስ አደራዳሪነት የትግሬን መንግስት በጋራ መዋጋት በሚል ፈሊጥ ከማኅበሩ እግር ላይ ወድቀው የታረቁት አባ ፋኑኤል ተጠቃሾች ናቸው:: አባ ገብርኤል ግን ከአቶ ኢያሱነታቸው ጀምሮ የተጠጋቸው የውግዘት በሽታ  መቼም አይለቃቸውም::

5/ ለመሆኑ አሁን ያለው ማኅበረ ቅዱሳን አደረጃጀት፤  

የሰንበት ት/ቤት ስብስብ ነው? እርዳታ ድርጅት ነው? የልማት ተቋም ነው? የበጎ አድራጎት ማኅበር ነው? ራሱን ከሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ውጪ አስደርጓል። በዋና ሥራ አስኪያጅ ሥር የሚተዳደር ነገር ግን የቤተ ክህነቱ መምሪያ ያልሆነ መምሪያ ነው?
በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ ሥፍራው ከየት ነው? በምንስ እንመድበው? ማኅበሩ በምን ሂሳብ እንደተቋቋመና በምን አደረጃጀት ኅልውና እንዳገኘ አይታወቅም::

እስከሚገባን ድረስ እንቅስቃሴውንና ያለውን አደረጃጀት ተመልክተን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማኅበረ ቅዱሳናዊ ብራዘር ሁድ ብንለው ተግባሩ ያረጋግጣል።
በሌላ መልኩ መንግሥት በኢትዮጵያ የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ዘንድ እንዲህ ዓይነት ማኅበር ከእስልምና ምክር ቤቱ ውጪ እንዲቋቋም ይፈቅዳል ወይ ብለን እንጠይቃለን? መልስ የሚያሻው ጥያቄ ነው።

Wednesday, October 5, 2016

"የጎርፍ ዘመን ላይ ደርሰናል"


ቀን 08/27/2016

ይድረስ
       
ለክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ፣
ለኢትዮጵያ የመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት በሙሉ ።

   በቅድምያ እናንተ በዚህ በአገራችን በኢትዮጵያ የሥልጣን ወንበር ላይ ለበጎም ይሁን ለክፉ ያስቀመጣችሁ ቸሩ አምላክ እግዚአብሔር እርሱ ባወቀው መንገድ እንደሆነ ስለማምን ለዚህም ኃላፊነትና ሥልጣን የተሰጣችሁ ናችሁና በእየ መዓርጋችሁ የከበረ የአክብሮት ሰላምታዬን አቀርባለሁ።

  ከዚህ በመቀጠል ሌላው
 ፩ኛ ሳሙ ፲፭፥፳ "....ሳሙኤልም እግዚአብሔር የእስራኤልን መንግሥት ዛሬ ከአንተ ቀደዳት፥ ከአንተም ለሚሻል ጎረቤትህ አሳልፎ ሰጣት...."ይላል።

 ይህንን ካልኩ በኋላ በእውነቱ የኢትዮጵያ ሕዝብ የዛሬ ሃያ አምስት ዓመት የደርግን መንግሥት አስተዳደራዊ ሥርዓትን አስወግዳችሁ እናንተ በትረ መንግሥቱን በጨበጣችሁ ጊዜ ምናልባት ከደርግ የተሻለ ለአንድነት ለእኩልነትና ለነፃነት የሚያስብልን፣የብሔር ብሔረሰቦችና፣ሁሉን ያቀፈ፣በሕገ መንግሥቱ የሚተዳደር መንግሥት ይፈጠራል ብሎ ሲጠብቅ እናንተ ግን የሕገ መንግሥቱን ሥርዓት ባልጠበቀ መልኩ የኢትዮጵያን ሕዝብና የኤርትራን ሕዝብ ፍላጎት ባላካተተ፣ ባልጠበቀና፣ባላገናዘበ መልኩ የኹለቱን ሰላማዊ ሕዝብ አንድነት አጥፍታችሁ፣በአንድነቱ ፈንታ ኹለትነትን ፈጥራችሁ፣ ለያይታችሁ፣በኹለቱ ሕዝብ መካከል ጥቁር ነጥብ ጥላችሁ፣ ለኢትዮጵያ ሕዝብ አንድነት፣ነፃነትና እኩልነት ያልቆማችሁ ለመሆናችሁ የምልክት ማህተብ በአንገታችሁ ያጠለቃችሁባትን ቀን ሳስብ መቼ ይሆን ይህ ዘመን የሚያልፈው ብዬ አስብ ነበር። የሚመጣውም ዘመን ምን እንደ ሚመስልና እንደሚሆን ስገምት በጣም ያስፈራኛና ያስጨንቀኝ ነበር።ታዲያ ዘመናትም ተቆጥሮ ዕለታትም አልፎ ኢየዋለ ኢያደረ ልዩነቱ፣መከፋፈሉ፣መለያየቱ፣መናናቁ፣መተራረዱ፣መገዳደሉና፣መጠላላቱ...ወዘተ በዝቶ ተባዝቶ እነሆ ዛሬ ያለንበት የደም ጎርፍ ዘመን ላይ ደርሰናል።

  ቅዱስ መጽሐፍ በማቴ ፩፪፥፳፭ ላይ "....ኢየሱስ ግን አሳባቸውን አውቆ እንዲህ አላቸው።እርስ በእርሷ የምትለያይ መንግሥት ሁሉ ትጠፋለች፤እርስ በእርሱ የሚለያይም ከተማም ወይም ቤት አይቆምም....."ይላልና ይህንን በአንድነት ሊያኖረን የማይችለውን ነገር አስወግደን ለሕዝብ የፈለገውን የመጠየቅ፣የመኖር፣ፍትህ የማግኘት እድል ካልሰጠን የኛም ሕልውና አጠራጣሪ ነው የሚሆነው።ሕዝብን ሁሉ በመግደልና፣በማሰር የምንመራው ከሆነ የሚቀረው ማነው?ሁሉም ከሞተ? ሁሉ ከታሰረ? በመንግሥት ስር የሚተዳደረው ማነው?ሕዝብ አልገዛም፣ አልተዳደርም፣እምቢ ካለ? ካመፀ? ።
ስለዚህ መንግሥት ለሕዝቡ ተማርኮ እጁን ሰጥቶና በቃኝ ብሎ መውረድና ሥልጣኑንም ለሕዝቡ መልቀቅ ላለፈው ላጠፋው ጥፋትና፣ በደል ይቅርታ ጠይቆ መቀመጥ አለበት።
   ምክንያቱም እስከ ዛሬ ድረስ ለተፈጠረው ጥፋት ሁሉ በየሚድያችሁ የመንግሥት የመልካም አስተዳደር ብሉሽነት ነው ኢያላችሁ ትናገራላችሁ።ሕዝቡም ያላችሁ ይህንኑ ነው።ትርፍ ነገርም አልጨመረም።መልካም አስተዳደር ከሌለ ያለው በተቃራኒው ክፉ አስተዳደር ነው ማለት ነው።ክፉ አስተዳደር ደግሞ ለሃያ አምስት ዓመታት ከመምረር አልፎ ይጎመዝዛል።አሁን ዛሬ የናንተን የመንግሥት አስተዳደር ማብቃት የሚፈልግና የሚጠይቅ ሁሉ ዕድሜ ተርፎትና በሚመጣው አዲስ የመንግሥት አስተዳደር ውስጥ ገብቶ ተደስቶና ተንደላቆ ለመኖር ፈልጎ ሳይሆን ለቀሪውና ለተተኪው አዲስ ትውልድ መልካም አስተዳደር ይምጣለት ሲል ብቻ ነው እንጂ፤እርሱማ አስራ ሰባት ዓመታት በደርግ መንግሥት፣ሃያ አምስት ዓመታት በእናንተ/ኢህአዴግ/ በአጠቃላይ ከአርባ ዓመታት በላይ በጥይት ሲቆላና ሲታመስ፣አንጀቱ አሮና ከስሎ፣ተስፋው ተሟጦ፣የሞተው ሞቶ፣የቀረው ያለ ፍትህ በየእስር ቤቱ ታፍኖና፣ታስሮ፣ሌላውም በዘር፣በጎሳ፣ቋንቋና፣ክልል ተከፏፍሎና፣ተበትኖ፣በስደት የአውሬና የውቅያኖስ እራት ኢየሆነ ይገኛል።

      ስለዚህ እናንተ የኢትዮጵያ መንግስት ባለሥልጣን ሆይ፥እስቲ እናንተም አሁን ይብቃችሁና ይህንን ምስኪን ሕዝብ በተራው በቃህ በሉትና ዕረፍት ስጡት፤እናንተም ደግሞ ዕረፉ።ደክሞአችኋል፣ዝላችኋል።አሥራ ሰባት ዓመታት በጫካ ሃያ አምስት ዓመታት በሕዝብ ጫንቃ ላይ ሳትወርዱ ተንጠላጥላችሁ በጣም ብዙ ዓመታትና ዘመናት ነው ይከብዳል።ከዚህ በላይ ብዙ ብትደክሙ መልካም አስተዳደርን ለሕዝቡ ልታመጡ በፍፁም አትችሉም።ምክንያቱም ሃያ አምስት ዓመታትን በሙሉ ተደክሞበት ያልታየ መልካም አስተዳደር በአንድ ሌሊት ስብሰባና ግምገማ በተአምራት ልታመጡ አትችሉም፣አይሆንም።ጊዜያችሁና ዕድላችሁ ሻግቶ ተበላሽቶአል።ስለሆነም እናንተ በሰላማዊ መንገድ እውነተኛ ሰላምን ፈልጋችሁ መልካም አስተዳደራዊ መንግሥት ሊፈጠርበት የሚችለውን የሕዝብ የሆነ የሽግግር መንግሥት ይመሠረት ዘንድና ሥልጣናችሁንም ለአንድ የፖለቲካ ፓርቲ ወይም ድርጅት ሳይሆን ለኢትዮጵያ ሕዝብ አስረክባችሁ በሰላም ውረዱና የዘመኑን ታሪክ ሥሩ።ያን ጊዜ የታሪክ ባለቤቶች ትሆናላችሁ።
አለበለዚ ግን ነቢየ እግዚአብሔር ሳሙኤል ለእስራኤል ንጉሥ ለሳዖል እንደ ነገረው ሳዖል በእስራኤል ሕዝብ ላይ መልካም አስተዳደርን አላመጣምና "... እግዚአብሔር መንግሥትህን ዛሬ ከአንተ ላይ ቀደዳት፣ለጎረቤትህም ሰው ሰጣት.." እንዳለው የዚህ ምስኪንና ደግ ሕዝብ እንባ
ወደ አምላኩ ወደ እግዚአብሔር ወደ ፀባዖት ጌታ ደርሶ መንግሥታችሁን ከእናንተ ላይ በቀደደ ጊዜ ያን ሰዓት ወየውላችሁ፣ወዮታ አለባችሁ።ምክንያቱም ያን ወቅት እናንተ በሰፈራችሁበት መስፈሪያ፣በመዘናችሁበት ሚዛንና፣በፈረዳችሁበት ፍርድ መሰፈር፣መመዘንና መፈረድ አለና ነው።
ያን ጊዜ ጩኸት ይሆናል የማይጠቅም ጩኸት ነው፤ያን ጊዜ ልቅሶ ይሆናል የማይጠቅም ልቅሶ ነው።ይህ ሁሉ የብድራታችሁ ክፍያ ውጤት ነው።

    ጊዜያት ሁሉ የአምላክ ናቸው።ሰዎች የጊዜያት ባለቤቶች አይደሉም።ነገር ግን በተሰጣቸውና፣ በተወሰነላቸው ጊዜ ውስጥ ኖረው መልካምም ይሁን ክፉ ሠርተው ያልፋሉ።ያ የሠሩትም መልካምም ይሁን ክፉ ሥራቸው ለዘለዓለም ሲነገርና ሲዘከር ይኖራል።እናም ምናልባት እናንተም ሥልጣናችሁን ተመክታችሁ ያላችሁበትን ወቅትና ሰዓት ሁሉ የእኛ ብቻ ብላችሁ የምታስቡ ከሆነ ተሳስታችኋል።ትላንት ያልነበራችሁብትን፣ዛሬ ደግሞ ያላችሁበትንና ነገ ደግሞ በተራው የማትኖሩበትን ጊዜ እንዳለ ማስተዋል ያስፈልጋችኋል ነው የምለው።ነገር ግን
እናንተ የደነደነ ልባችሁን ሰብራችሁ በይቅርታ ከዚህ ንፁህ፣ቅዱስና፣ደግ ሕዝብ ጋር ባትደራደሩ ነገ የጊዜያት ባለቤት ቸሩ አምላክ በጊዜው ለዚህ የዋህ ሕዝብ እጁን አጥፎና፣አመሳቅሎ፣ኢየታሰረ፣ኢየተደበደ፣ኢየደማና፣ኢየሞተ፣ለነፃነቱ፣ለእኩልነቱ፣ለአንድነቱና፣ለፍትህ ለሚጮኸው እናንተ ጩኸቱን ባትሰሙትና፣ባትፈርዱለት የሰማይ አባታቸው ቸሩ አምላክ ግን እንኳን ወደ እርሱ ጮኸው ለምነውት ቀርቶ ያልለመኑትንና ያልጠየቁትን
ሳይለምኑትና ሳይጠይቁት ይሰማቸዋል፣
ይሰጣቸዋል፣ይፈርድላቸዋል።

ክቡር የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስቴር ኃይለ ማርያም፥
ክቡራን የኢትዮጵያ መንግሥት ከፍተኛ ባለ ሥልጣናትና ኃላፊዎች በሙሉ፥
እስከ ዛሬ ድረስ ለሃያ አምስት ዓመታት እኛ ብቻ ነን የምንናገረው፣እኛ ብቻ ነን የምናውቅላችሁ ብላችሁ ስትናገሩልንና፣ስታውቁልን እውቀታችሁንም፣ንግግራችሁንም ሰምተናል፣ተቀብለናል።ዛሬ ደግሞ የእኛ ተራ ነው።እናንተም ስሙን።ስለ እናንተ እናውቅላችኋለን አድምጡን።
እግዚአብሔርን በማመን የሚሠሩት ሥራ ይባረካል፣ ይቀደሳል።
እግዚአብሔር በማመን የሚጓዙት መንገድ ቀና ነው።
እግዚአብሔርን በማመን ለሚቀርቡት ይቀርባልና እመኑበት።
እግዚአብሔርን በማመን የሚመሩት ሕዝብ
ታዛዥ ይሆናል።
ስለዚህ እስቲ እናንተ ደግሞ ዛሬ ላለፈው ጊዜና ዘመን በሕዝብ ላይ ለሠራችሁት በደልና ግፍ ምህረቱ ይደረግላችሁ ዘንድ ከልባችሁ ቸሩ እግዚአብሔርን በነገሮች ሁሉ ጠይቁት።ንስሐ ጠማማውን ያቀናል፣ኃጥኡን ጻድቅ፣ክፉውን መልካም፣
 መልካም አስተዳደርን፣ቅን ፍርድንና ሰላማዊ ሕይወትን ለሕዝቡና ለአገሩ ያጎናፅፍላችኋል። ለዚህ ሁሉ ጥፋት ጉስቁልና የመሪዎች ከእግዚአብሔር ሕግና መግቦቱ መራቅና ከእርሱ ጋር ያይደለ ድካም ለብቻቸው በክፉ መንፈስ ኃይል ስለሚድክሙ ጭምር ነው።
ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት በመዝሙሩ
መዝ፦፻፳፮፥፩-፫
"እግዚአብሔር ቤትን ካልሠራ
ሠራተኞች በከንቱ ይደክማሉ፤
እግዚአብሔር ከተማን ካልጠበቀ
ጠባቂ በከንቱ ይተጋል፤
በማለዳ መግሥገሣችሁም ከንቱ ነው...."
ይላልና እናንተ መሪዎች ቸሩ አምላካችን በነገሮች ሁሉ ተጨምሮ ለአገሪቱና ለሕዝቡ ሥልጣናችሁን በማስረከብ መልካም አስተዳደርን የምታመጡበትን የንስሐ ዘመንን ይሰጣችሁ ዘንድ አምላኬን እለምነዋለሁ።ለዚህም ቅን ልቡናን፣ አስተዋይ አእምሮን፣እግዚአብሔርን የምትፈሩበትን፣ሰውንም የምታከብሩበት ሕሊናን ይስጣችሁ።አሜን።

ቅዱስ እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር.
ተፃፈ
በቀሲስ አሸናፊ ዱጋ ዋቄ።

Thursday, September 8, 2016

"ሳይቃጠል በቅጠል"




by ኢትዮ - አፖሎጂስት

አክራሪ እስልምና አፋጣኝ መፍትሄ ይሻል

ይህ ጊዜ ዓለማችን በከፍተኛ ሁኔታ እየተናጠችና እየታመሰች ያለችበት ጊዜ ነው፡፡ ሰላሟን እያናጉ የሚገኙ ዘርፈ ብዙ ችግሮች ቢኖሩም አብይ መንስኤው ግን ለሰው ልጆች ሰላምና ደህንነት እንደቆመ የሚሰብከው የእስልምና ሃይማኖት መሆኑ የሚያከራክር አይደለም፡፡ በሦርያ፣ በኢራቅ፣ በየመን፣ በሊብያ፣ በናይጄሪያ፣ በሶማሊያ፣ በፓኪስታን፣ በአፍጋኒስታንና በሌሎችም ብዙ የዓለም ሃገራት የሚታዩት ሁኔታዎች ይህንኑ የሚያረጋግጡ ናቸው፡፡ በሌላ ወገን ደግሞ እስልምና “የሰላም” ሃይማኖት መሆኑ በተደጋጋሚ ይነገረናል፡፡ እንዲህ ዓይነት ስብከቶች ከሙስሊሞች ዘንድ ብቻ ሳይሆን ሙስሊም ካልሆኑት እና እንዲያውም የሽብር ተግባራቱ ሰለባዎች ከሆኑት ግለሰቦችና ሃገራት ዘንድ መሰማታቸው ጉዳዩን አደናጋሪ ያደርገዋል፡፡ እስልምና የሰላም ሃይማኖት ከሆነ እምነቱን አክርረው የያዙ ሙስሊሞች ስለምን እጅግ ሰላማውያን ከመሆን ይልቅ እጅግ ነውጠኞች ሆኑ? እንዲህ ዓይነት ተግባራትስ ስለምን የእምነቱ መታወቂያዎች ሆኑ? በማለት ተገቢ የሆነውን ጥያቄ የሚሰነዝሩ ወገኖች “እስላሞፎብያ” የሚል “የአዕምሮ ህመም” ስም ይለጠፍላቸዋል፡፡ እስልምና የሰላም ሃይማኖት እንዳልሆነ በድፍረት የሚናገሩ ሰዎች ሕይወታቸውን ለአደጋ ያጋልጣሉ፡፡ ታዋቂ ግለሰቦች እስልምና የሰላም ሃይማኖት አለመሆኑን ሲናገሩ ከተደመጡ ፅንፈኛ ሙስሊሞች አደባባይ በመውጣት ንብረት ያወድማሉ፣ የንፁኀንን ደም ያፈስሳሉ፣ በእምነት ተቋማት ላይ ቦምብ ይጥላሉ፣ የሰላም ሃይማኖት መሆኑን ለማሳመን ሰላምን ያደፈርሳሉ፡፡ የሙስሊሞች ተግባርና ስለ እምነቱ የሚሰበከው ስብከት አራምባና ቆቦ ሆኖብን ግራ ተጋብተን ሳናበቃ እስልምና የሰላም ሃይማኖት አለመሆኑንና “ካፊሮችን” ማሸበር እስላማዊ መሆኑን የሚናገሩ ሙስሊም ሊቃውንት ይገጥሙናል፡፡ በአንድ ወቅት የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ጆርጅ ደብሊዩ ቡሽ “እስላም ሰላም ነው” በማለት መናገራቸውን ተከትሎ አቡ ቀታዳ የተሰኘ በጂሃድ የሚያምን ሙስሊም አስተማሪ የሚከተለውን ብሎ ነበር፡- “ፕሬዚዳንት ቡሽ በእስልምና ስም የሚደረገውን የጂሃድ ሽብር የሚደግፍ ምንም ዓይነት ነገር በቁርአን ውስጥ አለመኖሩን መናገሩ በእጅጉ አስገርሞኛል፡፡ ለመሆኑ እርሱ የሆነ ዓይነት የእስልምና ሊቅ ነውን? እንደው በእድሜ ዘመኑ ቁርአንን አንብቦ ያውቃልን?”[1]
ሙስሊሞች በሚበዙባቸው ሃገራት ውስጥ የሚገኙት ብዙ ሙስሊም ሊቃውንት እስልምና የሰላም ሃይማኖት አለመሆኑን ይናገራሉ፡፡ በምዕራብ ሃገራት እና ሃገራችንን በመሳሰሉ የሙስሊሞች ቁጥር ከአጠቃላዩ የሕዝብ ቁጥር በሚያንስባቸው ሃገራት ውስጥ የሚገኙት ደግሞ እስልምና የሰላም ሃይማኖት መሆኑን ይሰብካሉ፡፡ የፖለቲካ መሪዎቻችንና የሃይማኖት አባቶቻችንም ከእነርሱ ጋር ይስማማሉ፡፡ እውነቱ የቱ ነው? ማንን እንስማ? የቱን እንቀበል? ከዚህ ግራ መጋባት ለመውጣት እስላማዊ የሃይማኖት መጻሕፍትን ማጥናት አማራጭ የሌለው መፍትሄ ነው፡፡
ከፊት ለፊታችን ከባድ አደጋ የተጋረጠ ቢሆንም ብዙዎቻችን የአደጋውን ግዝፈት ማየት አለመቻላችን ወይም ለማየት አለመፈለጋችን የሚያሳዝን ነው፡፡ በአክራሪ ሙስሊሞች በዚህች ሃገር ውስጥ ለደረሱት ጉዳቶች የኛ ቸልተኝነትና ዝምታ አስተዋፅዖ ማበርከቱን መካድ አንችልም፡፡ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ውስጥ ነገሮች ከልክ አልፈው ሃገሪቱ ከገደሉ አፋፍ ደርሳ ከመውደቋ በፊት እግዚአብሔር መንግሥትን ባያነቃ ኖሮ መፃዒ እጣ ፋንታችን ምን ሊሆን እንደሚችል ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡ አሁንም ቢሆን የማስታገሻ እርምጃ እንደተወሰደ እንጂ ትክክለኛ መፍትሄ እንደተሰጠ በልበ ሙሉነት መናገር አይቻልም፡፡ ምክንያቱም የህመሙ ምልክት እንጂ መንስኤው አልታከመምና፤ መንስኤው እስካልታከመ ድረስ ደግሞ ጊዜ ጠብቆ መልሶ ማገርሸቱ የማይቀር ሃቅ ነው፡፡ የአክራሪነት ሥረ መሰረት በቁርአን፣ በሐዲሳትና በሌሎችም እስላማዊ ምንጮች ውስጥ ሰፍረው የሚገኙት ትምህርቶች መሆናቸውን መካድ አያዋጣንም፡፡ ሽብርተኝነት የዛፉ ፍሬ በመሆኑ ሥራ መሰራት ያለበት ከፍሬው ይልቅ በግንዱ ላይ ነው፡፡ ይህንን የተረዱት የግብፁ ፕሬዚዳንት አብዱል ፈታህ ኧል-ሲሲ የዓለም ግምባር ቀደም እስላማዊ ዩኒቨርሲቲ እንደሆነ በሚነገርለት በአል-አዝሃር ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ሊቃውንት ፊት ያደረጉት ዓለምን ያስደመመ ንግግር ጥሩ ምሳሌ ይሆነናል፡፡ ፕሬዚዳንቱ ያለ ምንም መሸፋፈን ችግሩ የሚገኘው እድሜ ጠገብ በሆኑት እስላማዊ ቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ መሆኑን በማስገንዘብ በዓለም ላይ ለሚገኘው የሽብርተኝነት ችግር መፍትሄ እንዲመጣ ከተፈለገ እነዚህ ቅዱሳት መጻሕፍት መስተካከል እንዳለባቸው ጥብቅ ማሳሰብያ ሲሰጡ ተደምጠዋል፡፡ ሙስሊሞች በዓለም ላይ የሚገኙትን ሕዝቦች ሁሉ በማጥፋት እራሳቸው ብቻ ለመኖር መፈለጋቸው የሚያስከትለውን አደጋ በመጠቆም የማስጠንቀቂያ መልእክት አስተላልፈዋል፡፡ የሚከተለው ከንግግራቸው ተቀንጭቦ የተወሰደ ነው፡-
“… እዚህ ጋ እየተናገርኩ ያለሁት የእምነት አባቶችን ነው፡፡ እየተጋፈጥን ስላለነው ነገር በአንክሮ ማሰብ ያስፈልገናል – በእርግጥ ይህንን ጉዳይ ከዚህ ቀደም አንድ ሁለት ጊዜ አንስቻለሁ፡፡ በጣም ክቡርና ቅዱስ አድርገን የያዝነው አስተሳሰብ አጠቃላይ ኡማውን [እስላማዊውን ማሕበረሰብ] ለዓለም ማሕበረሰብ የጭንቀት፣ የአደጋ፣ የግድያ እና የጥፋት ምንጭ እንዲሆን ማድረጉ የማይታመን ነው፡፡ ይህ ሊሆን አይችልም!
ያ አስተሳሰብ – “ሃይማኖት” እያልኩ አይደለም ነገር ግን “አስተሳሰቡ” – ከእርሱ ማፈንገጥ የማይቻልበት ደረጃ ላይ እስክንደርስ ድረስ ለክፍለ ዘመናት አክብረን የያዝነው የመጻሕፍትና የአስተሳሰብ ስብስብ መላውን ዓለም እየተፃረረ ይገኛል፡፡ ዓለምን በሞላ እየተፃረረ ነው!
እነዚህን ቃላት እዚህ በአል-አዝሃር ዩኒቨርሲቲ፣ በዚህ የሊቃውንትና የኡላማ ጉባኤ ፊት እየተናገርኩ ነው – አሁን እየተናገርኩ ያለሁትን ነገር በተመለከተ ሁሉን ቻይ የሆነው አላህ በፍርዱ ቀን ስለ እውነተኛነታችሁ ምስክር ይሁንባችሁ፡፡
እየነገርኳችሁ ያለሁትን ይህንን ሁሉ ነገር በዚህ አስተሳሰብ ውስጥ ተጠምዳችሁ የምትኖሩ ከሆነ ልትረዱት አትችሉም፡፡ በትክክል መገምገም እንድትችሉና የበለጠ አብርሆት ካለው ፅንፍ ማየት ትችሉ ዘንድ ከራሳችሁ ሁኔታ መውጣት ያስፈልጋችኋል፡፡
ደግሜ ደጋግሜ እላለሁ ሃይማኖታዊ አብዮት ያስፈልገናል፡፡ እናንተ ኢማሞች በአላህ ፊት ተጠያቂዎች ናችሁ፡፡ መላው ዓለም፣ እደግመዋለሁ መላው ዓለም የእናንተን ቀጣይ እርምጃ እየተጠባበቀ ይገኛል… ምክንያቱም ይህ ኡማ እየፈረሰ ነው፣ እየወደመ ነው፣ እየጠፋ ነው – እየጠፋ ያለው ደግሞ በገዛ እጃችን ነው፡፡[2]
በዚህ ንግግር ውስጥ ፕሬዚዳንት ኧል-ሲሲ በእስላማዊ ቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የተሰገሰገው የነውጠኝነት አስተሳሰብ የዓለም ስጋት ምንጭ መሆኑን በግልፅ አስረድተዋል፡፡ በዚህ ገፅ ላይ በተከታታይ ስናወጣ እንደቆየነው የሽብርተኝነት ሥረ መሰረት እስላማዊ መጻሕፍት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡ (አይ ኤስ የተሰኘው የሽብር ቡድን እየፈፀማቸው የሚገኙት የሽብር ተግባራት በእስላማዊ ምንጮች የተደገፉ መሆናቸውን ማስረጃዎችን በመጥቀስ ያሳየንበትን ጽሑፍ ለአብነት ያህል ማየት ይቻላል፡፡) ካለማወቅም ይሁን ከፖለቲካዊ ትክክለኝነት (Political Correctness) በመነጨ አስተሳሰብ እስላማዊ መጻሕፍት ሰላምን እደሚያስተምሩ በመስበክ ለእስልምና ጥብቅና ሲቆሙ የነበሩ ወገኖች ይህንን ማድረጋቸው ምንም አልፈየደም፡፡ አንድን ከሥነ ምግባር የወጣ ሰው ሥነ ምግባሩ ጥሩ እንደሆነ ደጋግሞ በመንገር ፀባዩን እንዲያርም ማድረግ እንደማይቻል ሁሉ ሽብርን የሚሰብክ ሃይማኖት ሰላምን እንደሚሰብክ በመናገር ሰላማዊ ማድረግ አይቻልም፡፡ ይልቁኑ ስህተቱን ነቅሶ በማውጣት እንዲያስተካከል መንገር እንጂ መፍረግረግና መለማመጥ አጥፊው የልብ ልብ እንዲሰማው ማድረግ ነው፡፡ እውነትን ሸሽጎ ውሸትን በመናገር ችግሩን ማፈርጠም መፍትሄ አይሆንም፡፡ የፖለቲካዊ ትክክለኝነት ንግግሮች ዘላቂ መፍትሄ ሊያመጡ ይቅርና ጊዜያዊ መፍትሄ እንኳ ሊሆኑ አልቻሉም፡፡ የሃይማኖት አባቶችና የፖለቲካ መሪዎች የእስልምናን ሰላማዊነት አጥብቀው ቢሰብኩንም ነገር ግን ችግሮች እየተባባሱ ሄዱ እንጂ ሲቀንሱ አልታዩም፡፡ እውነትን በመናገር ሊፈጠር የሚችለውን ጊዜያዊ ችግር በመፍራት ዝንተ ዓለም በሽብር እየተናጡ ከመኖር እውነቱን አፍረጥርጦ በመናገር ዘላቂ መፍትሄ መፈለግ ይበጃል፡፡ “ጅቡ እግሬን እየበላው ነውና እንዳይሰማን ዝም በል” እንዳለው ሞኝ ሰው መሆን ይበቃናል፡፡
ማሕበረሰባችንን ከዚህ አስከፊ የጥፋት ማዕበል ለመታደግ የመጀመርያው እርምጃ መሆን የሚገባው የችግሩን ምንጭ ለመረዳት ጥረት ማድረግ ነው፡፡ በአንድ ወቅት የምንጊዜም ምርጥ ሳይንቲስት የሆነው አንስታይን ዓለምን ከጥፋት ለመታደግ አንድ ሰዓት ብቻ ቢሰጠው የተሰጠውን ጊዜ እንዴት እንደሚጠቀም ተጠይቆ ሲመልስ 55 ደቂቃዎችን ችግሩን ለመረዳትና 5 ደቂቃዎችን ብቻ መፍትሄ ለማፈላለግ እንደሚጠቀም ተናግሮ እንደነበር ይነገራል፡፡ የብዙ ችግሮቻችን መፍትሄ ያለማግኘት ምክንያቱ ችግሮቹን ራሳቸውን በትክክል አለማወቃችን መሆኑ እሙን ነው፡፡ ሽብርተኝነት በህዝባችን ላይ አደጋን የደቀነ የዘመናችን ችግር መሆኑን እናውቃለን፡፡ ነገር ግን የሽብርተኝነት ምንጭ ምን እንደሆነ ስለማናውቅ የችግሩ አሳሳቢነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ይገኛል፡፡ ዛሬ ኢትዮጵያ ሃገራችን በዙርያዋ ከሚገኙት ጎረቤቶችዋ ጋር ሊነፃፀር በማይችልበት ሁኔታ ከሽብር አደጋዎች ተጠብቃ ትገኛለች፡፡ ነገር ግን የሽብርተኝነት ምንጭ የሆነውን የእስልምናን ትምህርት በትክክል ተረድተን መፍትሄ ካላፈላለግን በስተቀር ይህ አንፃራዊ ሰላም በዚህ ሁኔታ ለመቀጠሉ ምንም ዋስትና አይኖረንም፡፡ ስለዚህ ዜጎችም ሆንን መሪዎች እስልምና ሽብርተኝነትን በተመለከተ ምን እንደሚያስተምር፣ ምን እንደሚያቅድ፣ የአፈፃፀም ስልቶቹ እንዴት እንደሆኑ፣ ወዘተ. ማጥናት ያስፈልገናል፡፡ እውቀቱ ካላቸው፣ በተለይም ደግሞ በእስልምና ትምህርቶች ከሰለጠኑና እስልምናን ለቀው ከወጡ ሰዎች መማር እጅግ ጠቃሚ ነው፡፡
አክራሪ እስልምና ለዓለምም ሆነ ለሃገራችን አዲስ አይደለም፡፡ ቤተ ክርስቲያን በየዘመናቱ የአክራሪ እስልምናን ተግዳሮቶች ስትጋፈጥ ኖራለች፡፡ አንዳንዶች አክራሪ እስልምና ፖለቲካዊ ችግር በመሆኑ መፍትሄው ፖለቲካዊ ነው ስለዚህ ችግሩ ለመንግሥት ብቻ መተው አለበት ይላሉ፡፡ ነገር ግን፡-
መንግሥት ሥልጣንና ጉልበት ቢኖረውም የትምህርቱን ውጤት እንጂ ትምህርቱን መጋፈጥ አይቻለውም፡፡ የመንግሥት አካላት ብዙ ጊዜ በሃይማኖት ካባ ተሸፍኖ ለክፍለ ዘመናት የኖረውን አይ የእስልምናን ፖለቲካ ለመረዳት ሲቸገሩ ይስተዋላሉ፡፡ ስለዚህ ትክክለኛ መፍትሄ ለመስጠት ይቸገራሉ፡፡
የመንግሥት አካላት የነገሩን ውስጠ ሚስጥር ቢረዱትም እንኳን መንግሥት ሁሉን አቀፍ በመሆኑ ገለልተኛነትን ይመርጣሉ፡፡ ስለዚህ የችግሩ መንስኤ የሆነውን የእስልምናን መሰረት መንካት አይፈልጉም፡፡
አክራሪ እስልምና አይዲዎሎጂ በመሆኑ በጉልበት አይቀለበስም፡፡ ስለዚህ መንግሥት አክራሪ እስልምና የጦር መሳርያ ይዞ አደባባይ ሲወጣ በጦር መሳርያ ማስታገስ ቢችልም ነገር ግን ትምህርቱን የሚጋፈጥበት ሥነ መለኮታዊ መሳርያ የለውም፡፡
ባለፉት ጥቂት ዓመታት እንደታዘብነው አንዳንድ የፖለቲካ ፓርቲዎች ይባስ ብለው ከአክራሪ እስልምና ጋር በመተባበር አጀንዳውን ሲያራግቡና ጥብቅና ሲቆሙለት ታይተዋል፡፡ ይህ የሚያመለክተው አንዳንድ ፖለቲከኞች የዛሬ ጥቅማቸውን እንጂ የነገውን አደጋ ማየት አለመፈለጋቸውን ነው፡፡ እንዲህ ዓይነት ሰዎች ሥልጣን ቢይዙ ችግሩን ከማባባስ ውጪ መፍትሄ መስጠት አይችሉም፡፡
የመገናኛ ብዙኃንን ስንመለከት እንኳንስ መፍትሄ ሊሰጡ ይቅርና ጥያቄውን እንኳ በትክክል የተረዱት አይመስልም፡፡ በትክክል ቢረዱትም እንኳን ፖለቲካዊ ትክክለኝነት ስለሚጫናቸው የችግሩን ስረ መሰረት በመንካት መፍትሄ ማፈላለግ አይችሉም፡፡
ምሑራን ጥያቄውን የተወሰነ ያህል ይረዱታል ነገር ግን የችግሩን ስረ መሰረት በመጥቀስ የመፍትሄ ሐሳቦችን እንዳይሰነዝሩ በፍርሃትና በፖለቲካዊ ትክክለኝነት ተሸብበዋል፡፡
አንዳንድ ለዘብተኛ አመለካከት ያላቸው ምዕራባውያን የሚከተሉትን “መፍትሄዎች” ያስቀምጣሉ፡-
ለአክራሪ ሙስሊሞች ምንም ትኩረት አለመስጠትና ችላ ማለት፡፡ ነገር ግን ችላ የሚባሉት እምን ድረስ ነው? ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል፡፡ ሰይፍ አንገታችን ላይ ተቀምጦ ትኩረት አንሰጠውም ማለት የሞኝ መፍትሄ ነው፡፡
ባሉበት እንዲሆኑ ማገድ (ወደ ክልላችን እንዳይገቡ ማድረግ፡፡) o አሁን ካለው የሕዝቦች እንቅስቃሴና የመረጃ ቴክኖሎጂ ደረጃ አኳያ አያስኬድም፡፡ የውጪዎቹ እንዳይገቡ ማገድ ይቻል ይሆናል፣ ውስጥ የሚገኙትንስ? መግደል? ማሰር? ከሃገር ማባረር? አያዋጣም፡፡
እስልምናን ከፖለቲካዊ ይዘቱ በማፋታት ምዕራባዊ መልክ ያለውን እስልምና መፍጠር [ለምሳሌ ኪልያም (Quilliam) ፕሮጀት]፡፡[3]

Monday, August 22, 2016

ወሀቢዝም በኢትዮጵያ ውስጥ!


by ኢትዮ - አፖሎጂስት

ከ1983 ዓ.ም. የመንግሥት ለውጥ ወዲህ በኢትዮጵያ ውስጥ የሃይማኖት ነፃነት ከቀደሙት ዘመናት ጋር ሊነፃፀር በማይችልበት ሁኔታ መከበሩ የማይካድ ሃቅ ነው፡፡ ነገር ግን ይህንን ነፃነት የለአግባብ የተጠቀሙና የጥፋት መርዛቸውን በትውልዱ መካከል ለማሰራጨት የተጉ፣ ከዚህም የተነሳ ብዙ ጥፋቶችን ያስከተሉ ቡድኖች መኖራቸው አልቀረም፡፡ በዚህ ረገድ በተለይ የወሃቢዝም (ሰለፊ) ፍልስፍናን የሚከተሉ ወገኖች ይጠቀሳሉ፡፡ ዛሬ በሃገሪቱ ውስጥ በብዛት ተሰራጭቶ በሕዝቦች መካከል ያለውን የመቻቻልና አብሮ የመኖር ባሕል እያደፈረሰ የሚገኘው ወሃቢዝም ይህንን ነፃነት ተጠቅሞ የተስፋፋ ይሁን እንጂ እግሩን  በሃገሪቱ ውስጥ ካሳረፈ ብዙ አስርተ አመታት አልፈዋል፡፡

ፋሺስት ኢጣልያ  በኢትዮጵያ ላይ የነበረውን እኩይ አጀንዳ ለማስፈፀም ሙስሊሞችን መንከባከብ የሚል መርሃ ግብር ስለነበረው ሙስሊሞች የሐጅ ጉዞ እንዲያደርጉ ያበረታታ ነበር፡፡ በገንዘብም በመደጎም ይልክ ነበር፡፡ በ1933 ለሐጅ ወደ መካ የተጓዙት ኢትዮጵያውያን ቁጥር 11 ብቻ ሲሆን ከ1934-1935 የሄዱት 29፣ ከ1935-1936 ደግሞ 7 ሰዎች ብቻ ነበሩ፡፡ ነገር ግን በ1937 ይህ ቁጥር ወደ 1,700 አድጓል፡፡ ሁሉም ደግሞ በኢጣሊያ መንግሥት ድጎማ የሄዱ ነበሩ፡፡[1] ሳዑዲ አረብያ ለሐጅ የሚሄዱትን ኢትዮጵያውያን በወሃቢዝም ፍልስፍና አጥምቃ ወደ ሃገር ውስጥ በማስገባት ፍልስፍናውን የማስፋፋት ሥራዋን የጀመረችው ኢጣሊያ ኢትዮጵያን ከመውረሯ በፊት ነበር፡፡ በተለይም ደግሞ ሼኽ ዩሱፍ አብደል ረህማን እና ሐጂ ኢብራሂም ሀሰን የተሰኙ ሁለት ሰዎች ለዚህ በዋናነት ይጠቀሳሉ፡፡ ሁለቱም ወደ ሳዑዲ የተጓዙት በ1930ዎቹ መጀመርያ አካባቢ ነበር፡፡ ሼኽ ዩሱፍ በ1939 ወደ ኢትዮጵያ በመመለስ በሐረር ከተማ የወሃቢዝም ትምህርታቸውን ማስተማር የጀመሩ ሲሆን የሐረርን ከተማ የቀድሞ ነፃነት ለመመለስ የከተማይቱን ሙስሊም ሊቃውንት አደራጅተው ፊርማ በማሰባሰብ በወቅቱ የብሪቲሽ የአካባቢው አማካሪ ለነበሩት ለኮሎኔል ዳላስ ጥያቄ አቅርበው ነበር፡፡ ነገር ግን ኮሎኔሉ ጥያቄያቸውን ውድቅ አድርገዋል፡፡ ከዚህ በኋላ ነበር ሼኽ ዩሱፍ ለረጅም ጊዜ ትግል መሰረት ለመጣል የወሰኑት፡፡ ከዚያም ብሔራዊ እስላማዊ ማሕበር (አል-ጀማኢያ አል-ወኒያ አል-ኢስላሚያ) ወይም አል-ዋታኒ የተሰኘ ማሕበር በማቋቋም መንቀሳቀስ ጀመሩ፡፡ የማሕበሩ አባላት በሙሉ ሐረርን “ከኢትዮጵያ ቅኝ ነፃ በማውጣት” አሕመድ ግራኝባስቀመጠው ምሳሌነት መሰረት እስላማዊ መንግሥት እንደገና ለማቋቋም ቃል ኪዳን ገቡ፡፡ የሐረርን ሕዝብ በሚገባ ሳያስተምሩ መንግሥትን መጋፈጥ እንደማይቻል ስለተገነዘቡም ዋታኒ እስላማዊ ማሕበር ቀደም ሲል የተሰራውን ትምህርት ቤት በመጠቀም እስላማዊውን ትምህርት በማስተማር ላይ እንዲያተኩር ተወሰነ፡፡ ትምህርት ቤቱም ዘመናዊ መልክ ኖሮት አረብኛና በሐጂ ኢብራሂም ሀሰን አማካይነት ደግሞ የወሃቢዝም ትምህርት እንዲሰጥ ተባለ፡፡ ሐጂ ኢብራሂምም በከፍተኛ ትጋት በየምሽቱ በቤታቸውም ጭምር ይህንን ፍልስፍና ማስተማር ተያያዙ፡፡ የግራኝ ታሪክና ወታደራዊ አካሄድ እንደ አንድ ዋና ትምህርት ይሰጥ ነበር፡፡ ዋታኒ እስላማዊ ማሕበር በሚያዘጋጃቸው ክብረ በዓላት ላይ በአሕመድ ግራኝ ዙርያ የሚያጠነጥኑ ግጥሞችና የውዳሴ መዝሙሮችም ተዘጋጅተው በተማሪዎች ይዘመሩ ነበር፡፡ ሼኽ አብደል ረህማን ደግሞ በአዲስ አበባ ውስጥ በነበራቸው የመጻሕፍት መደብር አማካይነት በአረብኛ የተዘጋጁ የወሃቢያ መጻሕፍትን እያስመጡ ያከፋፍሉ ነበር፡፡ ነገር ግን ኋላ ላይ የትምህርት ሚኒስቴር ሆነው የተሾሙት ከበደ ሚካኤል ትምህርት ቤቱን በጎበኙበት ወቅት ለግራኝ የሚዜሙትን መዝሙሮች ትርጉም ከሰሙ በኋላ እንዳይዘመሩ ያገዱ ሲሆን አማርኛም የመማርያ ቋንቋ እንዲሆን አዘዋል፡፡[2]

ነገር ግን ከመንግሥት ይልቅ የዋሃቢዝም ዋና ጠላት የነበሩት ሼኽ አብደላህ ኢብን ሙሐመድ ኢብን ዩሱፍ (አብደላህ አል-ሐረሪ) የተሰኙ ሙስሊም ሊቅ ነበሩ፡፡ እኚህ ሰው የሃገራችን አብዛኛው ሙስሊም የሚከተለው በአንፃራዊነት ሰላማዊ ሊባል የሚችለው የሱፊ እስልምና ተከታይ ሲሆኑ ከፀረ ሰላም ትምህርቱ በተጨማሪ አሁን በዝርዝር የማናያቸውን የወሃቢዝም አስተምህሮዎች ይቃወሙ ነበር፡፡ ሼክ አብደላህ ከሐረር ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ውሏቸውን በመርካቶ አካባቢ በማድረግ ሙስሊሙን ህብረተሰብ በማስተማር ዝነኛ ሆነው ነበር፡፡ ኋላም ወደ ሊባኖስ በማቅናት በመካከለኛው ምስራቅ ትምህርታቸውን በማስፋፋት በዓለም ላይ ዋነኛ ፀረ ወሃቢዝም ለሆነው ዓለም አቀፍ እስላማዊ ማሕበር ሊቀ መንበር ሆነዋል፡፡[3] የኚህን

ኢትዮጵያዊ ትምህርት አረቦች “አሕባሽ” በማለት ይጠሩታል፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ሐጂ አብደላህ ከሐበሻ ምድር የመጡ መሆናቸው ነው፡፡ ትምህርቱ ግን በኢትዮጵያ ውስጥ ለዘመናት የኖረውና አብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝበ ሙስሊም የሚከተለው የሱፊ እስልምና እንጂ ሌላ አይደለም፡፡ ትምህርቱን የተቀበሉና ከኢትዮጵያዊው የተማሩ ሊቃውንት ስልጠናዎችን ለመስጠት ከሊባኖስ በመጡበት ወቅት ወሃቢዮች “መንግሥት አሕባሽ የሚባል አዲስ ሃይማኖት አመጣብን” በማለት ሁከት መፍጠር ጀመሩ፡፡ እነርሱ ባለ ሃገር ሆነው የሃገሪቱን የሱፊ ሊቃውንት ማሳደድና መግደል ተያያዙ፡፡ መንግሥትም የኢትዮጵያ ሕዝብ ቅሬታ እስኪገባው ድረስ ታገሳቸው፡፡ አሁንም አቅማቸው ቢሟስስም በየስርቻው መሽሎክሎካቸውንና “ድምፃችን ይሰማ” እያሉ በሰላላ ድምፆቻቸው መጮኻቸውን አልተውም፡፡

ሼኽ አብደላህ በአንድ ወቅት በሐረር ውስጥ በነበረው የወሃቢዮች ትምህርት ቤት ላይ ባስነሱት ተቃውሞ ምክንያት ለእስር ተዳርገው ነበር፡፡ አዲስ አበባ በነበሩበት ጊዜ ሐጂ ኢብራሂም ለአንድ የአረብኛ ጋዜጣ በፃፉት መጣጥፍ ክርስቲያናዊት ኢትዮጵያንና ንጉሡን ማጣጣላቸውን ለመንግሥት መረጃ እንደሰጡም ይነገራል፡፡ በዚህም ምክንያት ሐጂ ኢብራሂምና የትምህርት ቤቱ የወሃቢያ መምህራን ታስረው ለፍርድ የቀረቡ ሲሆን ሐጂ ኢብራሂም ከሐረር ከተማ ወደ ሌላ የኢትዮጵያ ክፍል ሄደው እንዲኖሩ ተፈርዶባቸዋል፡፡ እኚህ ሰው አሁን በሕይወት የሉም፡፡ ከዚያም ሼኽ አብደላህ የሐረር ከተማ ሙፍቲ ሆነው በመሾማቸው ምክንያት ወሃቢዮች ድምፃቸውን አጥፍተው ለመኖር የተገደዱበት ሁኔታ ነበር፡፡ የሐረር ወሃብዮች ኋላ ላይ በ1948 የሶማሌ ወጣቶች ክበብ ተብሎ በመንግሥት ፈቃድ በተቋቋመው ቡድን ውስጥ እጃቸውን አስገብተው የነበረ ሲሆን የአሕመድ ግራኝ መንፈስ እንደገና በመምጣት ከተማይቱ ላይ አንዣቦ ነበር፡፡ ነገር ግን ጥር 1948 ጉዳዩ ይፋ በመሆን 200 የሚሆኑ የክበቡ አባላት በቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡ ወጣቶቹ ይቅርታ በመጠየቅ የተፈቱ ሲሆን ሰማንያ አንድ የሚሆኑ የወሃቢያን እንቅስቃሴ የሚመሩ የዋታኒ ማሕበር አባላት ከተማይቱን በመልቀቅ እንዲበተኑ ተደርጓል፡፡ በዚሁ ዓመት ኢትዮጵያ የኦጋዴን ግዛቷን በማግኘቷ ምክንያት በሐረርጌ ላይ ያላት ሙሉ ቁጥጥር እውን ስለሆነ በ1936 በሐረር ከተማ የተጀመረውም በወሃቢዝም የተመራው የእስላማዊ ፖለቲካ መነቃቃት ሊከሽፍ ችሏል፡፡[4]ኢትዮጵያዊ ትምህርት አረቦች “አሕባሽ” በማለት ይጠሩታል፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ሐጂ አብደላህ ከሐበሻ ምድር የመጡ መሆናቸው ነው፡፡ ትምህርቱ ግን በኢትዮጵያ ውስጥ ለዘመናት የኖረውና አብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝበ ሙስሊም የሚከተለው የሱፊ እስልምና እንጂ ሌላ አይደለም፡፡ ትምህርቱን የተቀበሉና ከኢትዮጵያዊው የተማሩ ሊቃውንት ስልጠናዎችን ለመስጠት ከሊባኖስ በመጡበት ወቅት ወሃቢዮች “መንግሥት አሕባሽ የሚባል አዲስ ሃይማኖት አመጣብን” በማለት ሁከት መፍጠር ጀመሩ፡፡ እነርሱ ባለ ሃገር ሆነው የሃገሪቱን የሱፊ ሊቃውንት ማሳደድና መግደል ተያያዙ፡፡ መንግሥትም የኢትዮጵያ ሕዝብ ቅሬታ እስኪገባው ድረስ ታገሳቸው፡፡ አሁንም አቅማቸው ቢሟስስም በየስርቻው መሽሎክሎካቸውንና “ድምፃችን ይሰማ” እያሉ በሰላላ ድምፆቻቸው መጮኻቸውን አልተውም፡፡

የደርግ መንግሥት ባጠቃላይ ሃይማኖትን በተመለከተ ከሚከተለው ፖሊሲ የተነሳ ያን ያህል የጎላ የወሃቢዝም እንቅስቃሴ አልነበረም፡፡ ነገር ግን ውስጥ ለውስጥ የተሰሩ ሥራዎች እንደነበሩ እሙን ነው፡፡ በ1958 ከየመን በመጣ ስደተኛ የተመሰረተው የአል-አወልያ ትምህርት ቤት በዘመነ ደርግ ጥብቅ በሆነ የመንግሥት ቁጥጥር ስር ነበር፡፡[5] ደርግ ወደ መውደቂያው አካባቢ “የሰርገኛ መጣ…” ዓይነት የፖሊሲ ለውጦችን በማድረጉ ምክንያት ለሳዑዲ እንቅስቃሴዎችም በር ከፍቶ ነበር፡፡ በዚህም መሰረት የዓለም የሙስሊሞች ሊግ ከእርዳታ ማስተባበርያና ማቋቋሚያ ኮሚሽን (እማማኮ) ጋር በመተባበር ትምህርት ቤቶችን፣ እጓለ ሙታንን እና ክሊኒኮችን ለማቋቋም ስምምነት አደረገ፡፡ መንግሥትና ሊጉ ያላቸው ግንኙነት መጥበቁን ከሚያመለክቱ ተግባራት መካከል አንዱ ሊጉ የሃይማኖትና የአረብኛ ቋንቋ ሥልጠናዎችን እንዲሰጥ መፈቀዱ ነበር፡፡ በ1991 ወደ ኢትዮጵያ ለጉብኝት የመጣው የሊጉ ልዑካን ቡድን በወሎ፣ በሐረር፣ በአዲስ አበባና በደብረ ዘይት ትምህርት ቤቶችን በመገንባት ሥራ ላይ መሆኑን መግለፁ ኢትዮጵያን የማስለም እንቅስቃሴው በአዲስ መልክ መጀመሩን አመላካች ነበር፡፡[6]

ከ1991 ወዲህ የተደረገውን የመንግሥት ለውጥ ተከትሎ በሃገራችን ውስጥ የተገኘውን የእምነት ነፃነት ሽፋን በማድረግ ብዙ ጥፋቶች ተፈፅመዋል፡፡ በተለይ የወሃቢዝም ፍልስፍና ተከታዮች ነፃነቱ የሰጣቸውን ክፍተት በመጠቀም አክራሪ የሆኑ ትምህርቶችን በማስተማር  ግርምቢጠኛ ባህርያቸውም ከልክ አልፎ በሚያሰራጯቸው ጽሑፎችና የድምፅ እንዲሁም የምስል መልዕክቶች ሌሎች ሃይማኖቶችን በነገር በመጎሽመጥ ሃገሪቱን ሲያምሱ ቆይተዋል፡፡ የተሰጣቸውንም የመንግሥት ሥልጣን ለእምነታቸው ማስፋፍያ በመጠቀም ብዙ በደሎችን ፈፅመዋል፡፡ በአንድ ወቅት ከውጪ ሃገራት በገፍ በመግባት ሃገሪቱን ያጥለቀለቁት የጂሃድ ፊልሞችና አክራሪነትን የሚሰብኩ የህትመት ሥራዎች ያስከተሉትን ውጤት ሁላችንም በግልፅ ያየነው ነው፡፡ በተለይ ከሳዑዲ አረብያ በሚመጣው ፔትሮ ዶላር የተገነቡት መስጊዶችና እስላማዊ ማዕከላት  ሃገሪቱን እንደሙጃ ውጠዋታል፡፡ በበጎ አድራጎት ሥም ወደ ሃገር ውስጥ የገቡ በርካታ እስላማዊ ድርጅቶችም ውስጥ ለውስጥ ጂሃዳውያንን እያሰለጠኑና የገንዘብ ድጋፍ እያደረጉ ሃገሪቱን ቁልቁል ወደ ጥፋት አዘቅት ነድተዋታል፡፡ እቅዳቸው ተሳክቶ ቢሆን ኖሮ ሊከተል የሚችለውን አደጋ ማሰብ በእጅጉ ይከብዳል፡፡ አደጋውን ከማስቀረት አንፃር መንግስት ይበል የሚያሰኙ እርምጃዎችን ወስዷል፡፡ በተለይም የወሃቢዝም ዋነኛ የርቢ ማዕከል የሆነው አል-አወልያ እስላማዊ ትምህርት ቤት ከወሃቢዮች እጅ ወጥቶ ለተገቢው አካል መሰጠቱ ትክክለኛ እርምጃ ነበር፡፡ ይህ ከአንደኛ ደረጃ ተነስቶ በኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ ሳይሆን በምስራቅ አፍሪቃም ጭምር ግምባር ቀደም እስላማዊ ትምህርት ቤት ለመሆን የበቃው የፅንፈኞች ማዕከል በሃገሪቱ ላይ ያሳደረው ተፅዕኖ ቀላል አልነበረም፡፡ የተወሰደው እርምጃ ከረፈደ በኋላ ቢሆንም ነገር ግን ከመሸ በኋላ አለመሆኑ ተስፋ ሰጪ ነው፡፡ አሁንም ቢሆን በመርዛማ ትምህርቱ ተበክለው የወጡ ወጣቶች ክትትል ሊደረግላቸውና በፅንፈኝነት ቅልበሳ መርሃ ግብር (De-radicalisation Program) ሊታቀፉ ይገባል፡፡

በኢትዮጵያ ክርስቲያኖች ላይ የደረሱ እስላማዊ ጥቃቶች የቅርብ ዘመን ትዝታዎች

ቀን ቦታ የሞተ የቆሰለ የክስተቱ ዝርዝር
6/2/97 አርሲ – ቆሬ 10 3 2237 ክርስቲያኖች ተፈናቀሉ፡፡ 1 ቤተ ክርስቲያንና 194 የክርስቲያን ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተቃጠሉ፡፡ 24 የክርስቲያን ቤቶች በከፊል ተቃጠሉ፡፡ 304 ከብቶች ተዘረፉ፡፡
16/1/99 ጀምሮ ጂማ – በሻሻ 18 38 488 በግድ ሰልመዋል፡፡ ከ2000 በላይ ተፈናቅለዋል፡፡ ከ850 በላይ የክርስቲያን ቤቶች ተቃጥለዋል፡፡ 3 አብያተ ክርስቲያናት ተቃጥለዋል፡፡ 4 ተዘርፈዋል፡፡
ከላይ የተቀመጡት መረጃዎች የተወሰዱት “በኢትዮጵያ የሃይማኖት መቻቻል አለን” በሚል ርዕስ በአባ ሳሙኤል ከተዘጋጀው መጽሐፍ ገፅ 28-31 እና “አክራሪ እስልምና በኢትዮጵያ” በሚል ርዕስ በኤፍሬም እሸቴ ከተዘጋጀው መጽሐፍ ገፅ 172-175 ነው፡፡ ዓመታቱ እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር ናቸው፡፡

ቀን ቦታ የሞተ የቆሰለ የክስተቱ ዝርዝር
3/8/11 ጅማ – አሰንዳቦ 2 – በቁጣ የተሞሉ ሙስሊሞች አብያተ ክርስቲያናትን የማቃጠል ዘመቻ አድርገዋል፡፡
3/1/11 ባሌ – ሆማ ቀበሌ – 17 ወንጌልን ለማስተማር በወጡ የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ክርስቲያን ተማሪዎች ላይ ድብደባ ተፈፅሟል፡፡
9/13/10 አፋር – ዱፍቲ – 1 ከእስልምና የወጣን አንድ ክርስቲያን ወጣት ሙስሊሞች በስለት ወግተዋል፡፡
8/21/10 አዲስ አበባ – 1 ታዋቂ ክርስቲያን መሪ በበትር ተደብድቧል፡፡
7/16/2010 አዲስ አበባ – 1 ከእስልምና የመጣ ክርስቲያን በቁጣ በተሞሉ ሙስሊሞች ተደብድቧል፡፡
9/11/09 ሸዋ – ሰንበቴ – 3 የሙስሊሞች ቡድን ወደ ቤተ ክርስቲያን ግር ብሎ በመግባት በፀሎት ላይ የነበሩትን ክርስቲያኖች ክፉኛ አቁስለዋል፡፡
7/3/09 ደሴ 2 – በቤተ ክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ በሥራ ላይ የነበሩ 2 ክርስቲያኖች ተኩስ ተከፍቶባቸው ተገድለዋል፡፡
9/20/08 አዲስ አበባ – 1 አንድ ዕድሜው 35 ዓመት የሚሆን ክርስቲያን መሪ ለሞት እስኪቀርብ ድረስ በሙስሊሞች ተደብድቧል፡፡
7/19/08 ጂጂጋ – 2 ሁለት ከእስልምና የመጡ ክርስቲያኖች በድንጋይ ተደብድበዋል፡፡
4/30/07 ጂጂጋ 2 3 ሙስሊሞች በድንኳን ውስጥ በተሰበሰቡ ክርስቲያኖች ላይ ቦምብ በመጣል 2 ክርስቲያኖችን ሲገድሉ 3 አቁስለዋል፡፡
1/5/07 ኮፈሌ 1 – ሙስሊሞች አንድ ክርስቲያን በብረት ቀጥቅጠው ገድለዋል፡፡
10/1/06 ጂማ 10 12 ሁለት አብያተ ክርስቲያናት ተቃጥለዋል፡፡
4/16/06 ጂጂጋ 3 23 በሁለት ምግብ ቤቶችና በአንድ ቤተ ክርስቲያን ላይ በሙስሊሞች በተፈፀመ የቦምብ ጥቃት የደረሰ አደጋ
3/22/06 አርሲ ነጌሌ 1 – ሙስሊሞች በአንድ የፕሮቴስታን ቤተ ክርስቲያን በር ፊትለፊት ከእስልምና የመጣን አንድ ክርስቲያን በጥይት ገድለዋል፡፡ ሟች የ 7 ልጆች አባት ነበሩ፡፡
7/19/05 ጂጂጋ 1 – የታጠቁ ሙስሊሞች አውቶብስ በማስቆም በውስጥ የነበሩትን ክርስቲያኖች ሸሃዳ አስብለዋል፤ ወደ መካም በመዞር እንዲሰግዱ አስገድደዋል፡፡ ይህንን ለማድረግ ፍቃደኛ ያልሆነ አንድ ወጣት ተገድሏል፡፡
መረጃዎቹ የተወሰዱት በክርስቲያኖች ላይ የሚደርሱትን እስላማዊ ጥቃቶች በመዘገብ ከሚታወቅ ክርስቲያናዊ ድህረ ገፅ ላይ ነው፡፡ ዓመታቱ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ናቸው፡፡

http://www.thereligionofpeace.com/pages/christianattacks.htm

ከላይ የተጠቀሱት ጥቃቶች ከብዙዎቹ ጥቂቶቹ ሲሆኑ ፍትህን በማዛባት፣ አድማ በማድረግ፣ የክርስቲያን ልጆችን አፍኖ በመውሰድ፣ አስገድዶ በመድፈር፣ አስፈራርቶ አካባቢን በማስለቀቅ፣ የክርስቲያን ይዞታዎችን በልዩ ልዩ ዘዴዎች በመንጠቅ፣ ወዘተ. የተፈፀሙ የግፍ ሥራዎችን ዘርዝሮ መጨረስ አይቻልም፡፡

[1] Haggai Erlich, Saudi Arabia & Ethiopia, 2007, p. 73

[2] Ibd, 80-83

[3] Ibd, 84

[4] Ibd, 85-92

[5] Ibd, 189-190

[6] ኤፍሬም እሸቴ፣ አክራሪ እስልምና በኢትዮጵያ፣ 2000፣ ገፅ 142-143


Thursday, August 18, 2016

ከመንጋ አድር ባይ ጳጳስ፣ ፓስተር፣ ቄስና ሼክ ተብዬ አንድ ሳበኬ ወንጌል ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ያቀረበው ማሳሰቢያ ይሻላል!


ለኢትዮጲያ የኢፌድሪ መንግስት ጠቅላይ ሚንስተር ለአቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ እና አመራሩ።

ከፀጋአብ በቀለ(የወንጌል ሰባኪ)

          የየትኛውም የፖለቲካ ርዕዮተ ዓለም አራማጅ አይደለሁም፡፡ ጥሪዬ ስላልሆነ፡፡ ለፖለቲከኞች ግን አክብሮቴ ትልቅ ነው፡፡ በግሌ በዚህ መንግሥት ከቀበሌ እስከ ፌደራል ስላሉት መሪዎች እግዚአብሔርን አመሰግናለሁ፡፡ ቃሉ፡-"ነፍስ ሁሉ በበላይ ላሉት ባለ ሥልጣኖች ይገዛ። ከእግዚአብሔር ካልተገኘ በቀር ሥልጣን የለምና፤ ያሉትም ባለ ሥልጣኖች በእግዚአብሔር የተሾሙ ናቸው"(ሮሜ.13፡1) የሚለውን ቃል ስለማምን፡፡ እንዲሁም በእግዚአብሔር መንፈስ የተመራው ሐዋርያ "ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ በፊት እመክራለሁ"(1ጢሞ.2፡1) ስለሚል ሁለም እግዚአብሔር ማስተዋልና ጥበቡን እንድሰጣችሁ እፀልያለሁ፡፡ እግዚአብሔር መንግሥትን ያፈልሳል ደግሞም ሌላ ያስነሣል፡፡ እግዚአብሔር፡- "ጊዜያትንና ዘመናትን ይለውጣል ነገሥታትን ያፈልሳል፣ ነገሥታትንም ያስነሣል ጥበብን ለጠቢባን እውቀትንም ለአስተዋዮች ይሰጣል"(ዳን.2፡21)፡፡
ለመንግሥት ያለኝ አድናቆት

      በዚህ ሥርዓት እውነተኛና ሚዛናዊ ሕሊና ያለው ዜጋ ቀርቶ ዓለም ሁሉ ያደነቀው በትምህርት፣ በጤና፣ በኢኮኖሚ፣ በመሠረተ ልማት ግንባታ፣ የብሔርሰቦች እኩልነት፣ በኢንቪስትመንት፣ በሃይማኖት ነፃነት፣ ...ረገድ የተገኘው ድል ትልቅ በመሆኑ ለዚህ ሁሉ አቅምና ኃይል የሆነን እግዚአብሔርን በማመስገን ለኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት ያለኝ ግላዊ አድናቆቴን ከልቤ መግለጥ እፈልጋለሁ፡፡ እግዚአብሔር የአገሬን ሕዝብና መንግሥት ይባርክ!

ለመንግሥታችን በትህትና የቀረበ ግልጽ መልዕክት                                                                                                                      
    በተቃራኒው ኃላፊነትና ሸክም እንደምሰማው እንደ አንድ የዚህች አገር ዜጋና የወንጌል አገልጋይ ስለዚህች አገር መጻኢ ሕይወት ሳስብና ስጸልይ ብሩህ ገጽታና ያን ለማጥፋት የሚታገል አሉታዊ ሁለት ገጽታዎች ይታዩኛል፡፡ በዚህም ይች አገር በመስቀለኛ መንገድ ላይ መሆኗ ተገነዘብኩ፡፡ እነዚህ ተግዳሮቶች በትክክል ከተጠቀምንባቸው የሚበልጥ ዕድገትና ለውጥ ይዞ የመጣ ሲሆን ካልተጠንቀቅን በዚህች አገር ትልቅ ጥፋትም ሊያመጣ የሚችል አቅም እንዳለሁ ስገነዘብ ባልተለመደ መንገድ ያልተለመደ ድምፅ ግልጽ አሰተያየት በትልቅ ትህትናና አክብሮት በማኅበራዊ ሚዲያ ለማቅረብ ወሰንኩ፡፡

1. የብሔር ብሔረሰቦች እኩልነት በሕግ መደንገጉ፤ ራስን በራስ ማስተዳደሩ፣ የራስን ቋንቋ፣ ባሕልና እሴቶች ማሳደጉ መልካም ሆኖ ሳለ ባለፉት ሁለት አሥርት ዓመታት ስለ ልዩነታችን፣ ስለመንደራችን፣ ስለብሔራችን፣ ስለጎጣችን እንድናስብ የተደረገውን ያህል ስለ አንድነታችንና ስለአገራችን እንድናስብና እንድንነጋገር አልተደረግንም የሚሉ ብዙዎች ናቸው፡፡
 ዓመታዊ የብሔር ብሔረሰቦችን ቀን ለአንድ ሳምንት ከማክበር ያለፈ፡፡ ዛሬ ከደቡብ ወደ ሰሜን፣ ከሰሜን ወደ ምዕራብ፣ ከምዕራብ ወደ ምስራቅ ሄዶ በነፃነት ከመሥራት ኢትዮጵያውያን ወደ ተለያዩ አገራት መሰደድን ይመርጣሉ፡፡ ለመገናኛ ብዙሀን ዜና ግብአት አንድነታችንን የሚያሳዩ ሰሞነኛ ዜናዎችና ትእይንቶች እንጂ ለእርስ በርሳችን ያለን እይታና ልብ እጅግ መጥበቡ የአደባባይ ምስጢር ነው፡፡
 ለምሳሌ፡- በቅርቡ በተነሳው ግጭት አንዳንድ አካባቢዎች ሌላውን ብሔር ለይቶ የማጥቃትና ከአካባቢያችን ውጡ የሚሉ ግልጽ መልዕክቶች ሲተላለፉ አይተናል፡፡ ሌላው ከኦሮምያ ዩንቨርሲቲ የጨረሱ ወጣት ተማሪዎች ወደ ሌሎች ክልሎች ሄደው ሥራ መሥራት እየቻሉ አይደለም፡፡ ምክንያቱም የአገሪቷን ብሔራዊ ቋንቋ አማርኛን ስለማይችሉ፡፡ በአብዛኛው የተማረ ኃይል ተምሮ እየተመለሰ ያለው ወደ መንደሩ ሲሆን ወደ ሌላ ስፍራ ሲሄዱ ተቀባይነት የላቸውም፡፡ ከዚህም የተነሣ በብዙ ወረዳዎች ዩንቪርሲቲ የጨረሱ ወጣቶች ሥራ ፈተው ይቀመጣሉ፡፡ ሥራ የፈታ አዕምሮ ደግሞ አደገኛነቱ የታወቀ ነው፡፡
 ያ ሚዛናዊ ሥራ እንደሚገባው ባለ መሠራቱ አሁን የገባንበት አንዳንድ ተግዳሮቶች ተጨባጭ ማስረጃዎችና ገሃዳዊና ጊዜ የማይሰጣቸው የለውጥ ጥሪ ናቸው፡፡ ለዚህ ትክክለኛ ጥሪ መንግሥት የተቃዋሚዎች ድምፅ አድርጎ ከመደምደም ይልቅ ትክከለኛ ምላሽ ቢሰጥ የሚል የብዙዎች ጩኼት ነው፡፡
 መንግሥታችን ያለፈውን ድልና ስኬት ብቻ ሳይሆን በብዙዎች ልብ በቅሎ ምድሪቷ ወዳልተፈለገው አቅጣጫ ሊወስዳት እየታገለ ያለውን በብሔርና በቋንቋ ላይ ያውጠነጠነ አደገኛ ጽንፈኝነት ላይ በጥንቃቄ መሥራት አለበት፡፡ ተሐድሶ የግድ ነው፡፡ ይህ ዓይነቱ ጠባብነት ታላቅቷን ሶቪየት ኅብረት፣ ዩጎዝላቪያ ...የሕዝብን ጭፍጨፋ፣ መፈናቅሎችና የአገር መፋራረስና የሩዋንዳውያን መተላለቅ ምክንያት መሆኑን ምሁራን ይጠቅሳሉ፡፡ በብዙ አስቸጋሪ መንገድ ውስጥ ሄዶ ለዚህ የበቃውና ሕዳሴን መለያው ያደረገ መንግሥት ይህን ማድረግ ቀላል ባይሆንም አይችልም የሚል ልብ ግን የለኝም፡፡ ይህን እውን ለማድረግ መንግሥት ብቻውን አይደለም፡፡ ዜጎች ሁላችንም እጅ ለእጅ ተያይዘን መሥራት አለብን፡፡ መንግሥት በዚህ ላይ ለመሥራት ካልፈቀደ ግን መጪው መልካም እንዳልሆነ የማገለግለው የሕያው አምላክ መንፈስ አመልክቶኛል፡፡

ቤንጃሚን ፍራንከሊን የተባሉ ሊቅ ሲናገሩ፡- "የፖሊሲ ማሻሻያ ማድረግ እንደ ሞት ሽረት የሚቆጥሩ መንግሥታት በተፈጠሩበት ቆዳ ተጠቅልለው የሚሞቱ ናቸው፡፡ አንድ አገር ወይም ሕዝብ የሚመራበት ፖሊሲ፣ ስትራቴጂዎችና ርዕዮተ ዓለማዊ ፍልስፍናዎች እንደ ተጨባጭ ዓለማዊ ሁኔታ ወይም ሕዝቡ ከደረሰበት የግንዛቤና የውጤት ደረጃ አንፃር መቃኘት አለባቸው፡፡ ይህን ማድረግ አለመቻል ነው ጉዞን የሚያደናቅፈው፡፡"

2. መንግሥት የደጋፊዎችን ድምፅ ብቻ ሳይሆን የተቃዋሚዎችንም ድምፅ ከዚህ በበለጠ ቢሰማ መልካም ነው፡፡ (በስሜት የሚደገፍ የደጋፊዎች ድምፅ አንዳንዴም መንግስት እውነቱን ሊጋርደው ይችላል) የሚሰራው ፖለቲካ እንጂ የሃይማኖት ህግ አይደለም። ዴዝመንድ ቱቱ እንዳሉት፡" ሰላም ከፈለክ ከወዳጅ ጋር ሳይሆን ከጠላት ጋር መንጋገር ጀምር" እንዳሉት የተለያየ ርዕዮተ ዓለም መከተል ጠላትነት ባይሆንም እኛ ከሚንለው የተለየ ፍልስፍና ላላቸው ሰዎች ትክክለኛ ቦታ ልኖረን ይገባል፡፡ ሁለታችንም ለአንድ አገር ጥቅም እስከቆምን ድረስ፡፡ ይህን የሚንለው ብዙውን ጊዜ የፖለቲካው ምህዳር ከቀን ወደ ቀን እየጠበበ እንደመጣና አሳታፍ አይደለም በማለት አንዳንዶች በተስፋ ቁረጥ ስናገሩ ይሰማልና፡፡ ይህ ደግሞ ለዲሞክራሲያዊ ግንባታ አይበጅም፡፡

3. መንግሥት ቀርቶ መላዕክትም ይሳሳታሉ፤ ስለዚህ መንግሥት አንዳንዴ ገሃዳዊ ስህተት ሲፈጽም ይቅርታን ይጠይቅ፡፡  (እንደሚሳሳት አምኖ ለፈፀመው ስህተት ይቅርታ አለመጠየቅ ግብዝነት ነው)

መደምደሚያ
    መንግሥት ጠባብነት፣ ሙስናና የመልካም አስተዳደር ችግሮች እንዳሉ አምኖ ደጋግሞ በመገናኛ ብዙሃን ስናገር ይሰማል፡፡ ይህም ትልቅ ነገር ነው፡፡ ብርቱ አቋም፣ ጠንካራ እርምጃ ከእያንዳንዱ ዜጋ ይጠበቃል፡፡ ከላይ የተዘረዘሩ ሀሳቦች አዲስ ባይሆኑም አዲስ ትኩረት ከመቼውም ጊዜ ይልቅ ይፈልጋሉ የሚል እምነት አለኝ፡፡ የትላንቱ ታሪክ ታሪክ ነው፡፡ መጥፎም ይሁን ጥሩ፡፡ የእኛ ታሪክ ነው፡፡ ያለፈው ታሪክ አይለወጥም፤ አይከሰስም፡፡ ዛሬ የተሻለ ነገር ከሠራን ግን መልካም ታሪክ ሆኖ ነገ ይጻፋል፡፡ መልካም ታሪክ በሠራን መጠን የትላንቱ አሉታዊና የማንፈልገው ታሪካዊ ገጽታዎች እየተዋጡ ይመጣሉ፡፡ የትላንቱን አሉታዊ የታሪክ ክስተት ለበቀልና ለህቡዕ የጥፋት አጀንዳ እየመዘዝን ከተጠቀምንበት ግን የጥፋት ሠራተኞች እንሆናለን፤ ምድራችንን የደም መሬት እናደረጋታለን፡፡ ከመጥፎ ታሪክ ጋር ሁልጊዜ ስማችን እየተጠራ ይኖራል፡፡ ስለዚህ መልካም ታሪክ ለመሥራት መልካም አመለካከት ይኑረን፡፡

 ትልቁ ችግራችን ችግሮቻችንን ያየንበት ዓይን እንጂ ያለፉም ሆኑ አሁን ያለንበት ችግሮቻችን በራሳቸው ከአሉታዊ አመለካከቶቻችን በላይ አደገኞች አይደሉም፡፡ ችግሮቻችን ከእኛ በላይ ትልቅ አይደሉም፡፡ ችግሮቻችን አደገኛ መሆን የሚጀምሩት እኛ ፈጥረናቸው መፍትሔ በመስጠት ማስወገድ ሲገባን እኛን መፍጠር ወይም መምራት ሲጀምሩ ብቻ ነው፡፡

 
ሰላም፣ ብልጽግና፣ ዕድገት፣ ለውጥ፣ አንድነት፣ ፍቅር በአገራችን ለሚገኙት ብሔር ብሔረሰቦችና መንግሥት ይሁን፡፡


እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ!
ፀጋአብ በቀለ/ሐዋሳ/ ነሐሴ 4/12/2008 ዓ.ም

ይህን ፅሁፍ ከጠቅላይ ሚንስተሩ እጅ ይደርስ ዘንድ ሼር በማድረግ የበኩሎን ይወጡ።

Wednesday, June 15, 2016

በማኅበረ ቅዱሳንና በደጋፊዎቹ ጳጳሳት ግብዓተ መሬትዎ ሊፈጸም የቀረው ጥቂት ነው!!


የቁልቁለት መንገድ ተጀምሯል!

ይህ ጽሑፍ በመጋቢት ወር 2004 በመካነ ጦማራችን ላይ የወጣ ነው። ደግመን ማውጣት ያስፈለገን፤ ሞት የሁሉም ሰው ጽዋ ቢሆንም ማኅበረ ቅዱሳን ፓትርያርክ ጳውሎስን በደጋፊ ጳጳሳቱ በኩል እስከሞት እያዋከበ መቆሚያና መቀመጫ እንዳያሳያቸው እነሆ ፓትርያርክ ማትያስን በተራቸው እስከሞት እየተዋጋ ለመቆየት መቁረጡ በዳበረ ልምዱ ሲሰራበት መቆየቱን ለማሳየት ነው። እንዲህ ብለናቸው ነበር። አንዳች ነገር ሳያደርጉ ሞት ወሰዳቸው፤ ማኅበሩም ሰፋለት። (አመኑንም አላመኑም ፓትርያርክ ጳውሎስ፤ አንድ ነገር አስረግጠን እንነግርዎታለን። በማኅበረ ቅዱሳንና በደጋፊዎቹ ጳጳሳት ግብዓተ መሬትዎ ሊፈጸም የቀረው ጥቂት ነው) ዛሬም ፓትርያርክ ማትያስን ለተመሳሳይ ጽዋ  በወከባና በአድማ እያንደረደረ ይገኛል። ማኅበሩ የሚተዳደርበት አዲስ ሕግ ሳይጸድቅ፤ በዐቃቤ መንበርና በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የሥልጣን ነጠቃውን ጀምሯል። ወደፊትስ?

በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ማኅበረ ቅዱሳን ከተራ ማኅበርነት ወደ ሀገረ ስብከትነት  አደገ። በዚህም የተነሳ ሲኖዶሱ ሙሉ በሙሉ በማኅበረ ቅዱሳን እጁን ተጠምዝዞ እንደሚሰራ አስመሰከረ። የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ተጠሪነቱ ለቅዱስ ሲኖዶስ ሆኖ  የየሀገረ ስብከቶቹ  ጠቅላይ ጽ/ቤት ሆኖ ያገለግላል። ይህ ጽ/ቤት ደግሞ የሚመራው ቅዱስ ሲኖዶስ በየ3 ዓመቱ በሚያደርገው ምርጫ በሚመድበው ሊቀጳጳስ ነው። እንግዲህ ማኅበረ ቅዱሳን ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ዋና አሥኪያጅ ሆነ ማለት ራሱን የቻለ ሀ/ስብከት  ሆነ ማለት ነው። የጠቅላይ ቤተክህነቱ መምሪያዎች ሊያዙት አይችሉም። ከዚያም በላይ ቅዱስ ፓትርያርኩ ሊያዙት፤ ሊናገሩትና ሊቆጡት አይችሉም ማለት ነው። በቀጥታ በቅዱስ ሲኖዶስ በሚመደበው ሊቀጳጳስ በኩል ግንኙነቱ ከቅዱስ ሲኖዶሱ ጋር ብቻ ይሆናል ማለት ነው። እንዲህ ነው እንጂ ሹመት፤ መሾም ካልቀረ!! አንድ ማኅበር ባንድ ጊዜ እመር ብሎ አናት ላይ ፊጢጥ ብሎ ከመቀመጥ ወዲያ ሹመት ከወደየት ይገኛል? ከእንግዲህ  ከተቀመጠበት ደረጃ አንጻር ማኅበር መባሉ ዝቅ የሚያደርገው ስም ስለሆነ የቅዱሳን መምሪያ ወይም የወጣቶች ሀ/ስብከት እንዲባል ሲኖዶሱ በነካካው እጁ ስሙንም ማሻሻል ይገባዋል። ከዚያም አያይዞ ለዚሁ አዲስ ሀ/ስብከት አንድ ሊቀጳጳስ እንዲመድቡለትም ጥቆማውን እናቀርባለን። አንድ ነገር ታዘብን። ቤተክርስቲያኒቱ ሲኖዶስ የሚባል አካል እንደሌላት ተረዳን። በአንድ ተራ ማኅበር እየተመሩ የእሱን ጉዳይ ብቻ ሲያነሱና ሲጥሉ ሦስትና አራት ቀናት ስብሰባ መወዘፍን ምን ይሉታል? ስንት ስራ መስራት እየቻሉ ቁጭ ብለው የሰቀሉትን ማውረድ እስኪያቅታቸው ድረስ ስለ ማኅበረ ቅዱሳን አጀንዳ ይዞ መከራከርን እውነት ሰዎቹ በመንፈስ ቅዱስ ነው የሚመሩት እንድንል ያደርገናል። ይህ ማኅበር ባይኖር ኖሮ ስለምን ጉዳይ ሊሰበሰቡ ነበር፤፤
ይህ ማኅበር እስካሁን እየታዘዘ እንዳልቆየ የተጻፉለት ደብዳቤዎች አረጋጋጮች ናቸው። እሱ ራሱ አልቀበልም ብሎ በደብዳቤ አረጋግጧል። አንዴ ከኢህአዴግ፤ አንዴ ደግሞ ከተቃዋሚ ነኝ እያለ፤ ሌላ ጊዜ ከሀገር ቤቱ ሲኖዶስ፤ ሌላ ጊዜ ደግሞ ገለልተኛ እየመሰለ የተጓዘበትን ሁላችንም እናውቃለን። የወንድሞች ከሳሽና አሳዳጅ ስለመሆኑም ግፉን የቀመሱ ሁሉ ይመሰክራሉ። የተጓዘባቸውን ስልቶች ሁሉ ያጠናው መንግሥት ከሽብር አቀንቃኝ  ከሰለፊያ ጋር በአንድ ረድፍ አንዳስቀመጠው ነግሮናል። ስለሆነም አቡነ ጳውሎስ ይህንን የአድማና በጥቅም የተሳሰረ ውሳኔ አልፈርምም በማለት ውድቅ ሊያደርጉት ይገባል። ማኅበሩ አስቀድሞ ከሰለፊያ ተግባር ነጻ ስለመሆኑ ማረጋገጫ ማምጣት ይጠበቅበታል። ደጋፊዎቹ ጳጳሳትን በማስረጃና በሰው ምስክር ተጠንተው ብቁ ሆነው ያልተገኙ ካሉ ከማዕርጋቸው መሰናበት አለባቸው።  ቄስ የነበሩ፤ ልጆች የወለዱ፤ ቅምጥ ያላቸው እንዳሉ ይወራል፤ የአንዳንዶቹም ይታወቃል።  እየተሸፋፈነ መቀመጡ ለቤተክርስቲያን ጠንቅ የሆነ ውሳኔ ለማስወሰን ያልተመለሱ ሰዎች ስብስብ መሆኑ ከታየ ውሎ አድሯል።  ነውራቸውን ለመሸፈን እንኳን ከድመት አንሰዋል።
በአንድ ወቅት አባ ገብርኤል፤ አቶ ኢያሱ ተብለው ከማዕርጋቸው ተገፈው እንደነበረው፤ ማንነታቸው እንደገና ተመርምሮ  አስቸጋሪ በሆኑት ላይ ዛሬም ተመሳሳይ ውሳኔ ሊሰጥባቸው ይገባል። ጨከን ያለ የሥርዓት ማስከበር አካሄድ መውሰድ ካልተቻለ ሲኖዶሱን በነሱ በኩል እያወከ ነገ ፓትርያርክነቱን አስቀድሞ ከዚያም ቤተመንግሥቱን እንደሚረከብ የሚጠራጠር ካለ የማኅበሩን አካሄድ የማያውቅ ብቻ ነው። አመኑንም አላመኑም ፓትርያርክ ጳውሎስ፤ አንድ ነገር አስረግጠን እንነግርዎታለን። በማኅበረ ቅዱሳንና በደጋፊዎቹ ጳጳሳት ግብዓተ መሬትዎ ሊፈጸም የቀረው ጥቂት ነው። ከሆነለት ፓትርያርክነቱን ለሚታዘዝ  ሰው  ሰጥቶ ወደ ቤተመንግሥት ሰተት ብሎ ለመግባት ከጽዋ ማኅበርነት ወደ መምሪያ ተገዳዳሪነት፤ አሁን ደግሞ ወደ ሀገረ ስብከትነት ማደጉ ከምንም በላይ ማሳያ ነው።  ታዲያ ከእንግዲህ የቀረው ምንድነው? ይህ ሁሉ ለጽድቅ ነው እንዳይትሉንና እንዳንስቅ ጥቂት እዘኑልን። ነጋዴና  ሸቃጭ የሆነ  ቅዱስ ማኅበር  አራት ኪሎ የለም ። እያየነው በትንሽ በትንሹ የወጣው ይህ ሐረግ ቤተ ክህነቱን አንቆ ወዳሰበበት በመጓዝ ላይ ነው። እግዚአብሔር ለዚህ ክፉ ማኅበር አሳልፎ ከሰጠ በእውነትም ቤተክርስቲያኒቱ ለፈተናና ለውድቀት ተመርጣለች ማለት ነው። ተወደደም፤ ተጠላ ሲኖዶስ በየዓመቱ ያለህውከት ማለፍ አይችልም።
ሰውዬው «ሁሉን ለማየት መቆየት»እንዳለው የሚሆነውን ለማየት ከዕድሜው አይንፈገን!

Monday, June 13, 2016

"ፓ" ይላል ምዕመኑ!!!



«በዘውድአለም ታደሰ»
ነብይ ነኝ ባዩ የቤተክርስቲያን ደላላ!

ይሄ ሰውዬ "ጎሳ" ይባላል። በተለያየ ጊዜ የተለያዩ ቸርቾች ሲሰብክ አይቼዋለሁ። (ጎፋ መድሃኒአለም ፣ ዘፀአት ፣ FBI ፣ ወዘተ... ) የሚደክም አይነት ሰው አይደለም። ውሃ ሳይጎነጭ በተከታታይ ለሶስት ሰአታት የማውራት አቅም አለው! የምእመኑን ሳይኮ በልቶታል። ህዝቤን ምን እንደሚያስጮሀት ስለሚያውቅ አዳራሹን በጩኸት መናጥ ለነብይ ጎሣ ቀላል ነው!
ብዙ ግዜ ቸርቾች ይህን ሰውዬ ሚጋብዙት ገንዘብ ክፉኛ ሲያስፈልጋቸው ነው። ወይ መሬት ሊገዙ ሲያስቡ ... አሊያም የተሻለ አዳራሽ ሊከራዩ ሲፈልጉ ... ብቻ የሆነ የፈንድ ሬይዚንግ ጉዳይ ሲኖር ጎስሻን ይጠሩትና በዚያች ጮሌ ምላሱ የራሱንም ሆነ የሌሎች ሰዎችን ታሪክ እያጋነነ በመስበክ የዚህን ምስኪን ምእመን ኪስ ያራቁትላቸዋል!
«ነኝ ያልኩ ኮንትራክተር ነበርኩ፣ ነፍፍ መኪኖችና ብዙ ሰራተኞች ነበሩኝ፣ ጌታ ሲገባኝ ግን ንብረቶቼን ሸጬ ለቸርች ሰጠሁ» ብሎ ይጀምራል ተረት ተረቱን።
«ፓ» ይላል ምእመኑ!
«ከዛ ክፉኛ ተቸገርኩና፣ ምልስ ምቀምሰውን አጣሁ፣» ብሎ ለፅድቅ ሲል የከፈለውን መከራ እያጋነነ ያወራል!
«በከተማዋ ስሜ የተጠራ ኮንትራክተር እንዳልነበርኩ ምልስ ምቀምሰውን አጥቼ ተቸገርኩ» ሲል ረሃብን የሚያውቀው የዚህ ህዝብ አንጀት በሀዘኔታ ይላወሳል።
የሰዉን አቴንሽን ማግኘቱን ሲያረጋግጥ ታዲያ ... እንዴት ተአምራዊ በሆነ ሁኔታ እግዜር ሀብታም እንዳደረገው፣ እንዴት እንዳበለፀገው ትረካ በሚመስል ሁኔታ ያወራ ያወራና የህዝቡን አእምሮና ስሜት በሚገባ እንደተቆጣጠረ ሲረዳ እንዲህ ይላል ..
«ጌታ እንዲህ ሲል ተናግሮኛል» ብሎ ይጀምራል ነብይ ጎሳ። (ማን ነብይ እንዳረገው እንጃለቱ)
«ጌታ ዛሬ በዚህ አዳራሽ ውስጥ ያላችሁትን ሁላችሁን እባርካለሁ ብሎኛል» ሲል እቺ በረከቷን ከአርያም ሳይሆን መድረክ ላይ ከቆመው አረም የምትጠብቅ ምእመን አዳራሹን በጩኸት ታቀልጠዋለች! በጭብጨባው የሚሟሟቀው ጎሲሻም «አንዳንዶቻችሁ ከዚህ አዳራሽ ስትወጡ ከበረከታችሁ ጋር ትገናኛላችሁ» ሲል አዳራሹ በአንድ ድምፅ «አሜን» ይላል።
«አንዳንዶቻችሁ ደግሞ ቤታችሁ ስትገቡ በረከታችሁ ቁጭ ብሎ ይጠብቃችኋል»
«አሜን»
«አንዳንዶቻችሁ ስራ ቦታችሁ ላይ»
«አሜን»
«አንዳንዶቻችሁ የዛሬ ሳምንት»
«አሜን»
«አንዳንዶቻችሁ የዛሬ ወር»
«አሜን»
«እግዜር በተራራው ላይ ሙሴን ሲያገኘው በእጅህ ላይ ምን አለ? ብሎ ነው የጠየቀው ወገኖቼ። እግዜር እጃችን ላይ ባለ ነገር ነው ሚሰራው። ዛሬ በእጃችሁ ላይ ምን አለ?» ይላል ብልጣብልጡ ጎሳ!
ይሄ የዋህ ሁን ሲባል ሞኝ የሆነ ህዝብም እውነት መስሎት እጅና ኪሱን ያያል! ከዛማ በቃ አዋራው ይጨሳል .... ፒፕሉ በረከቱን በስጦታው ለመግዛት ይጋፋል! አዳሜ ወርቋን ከአንገቷ ላይ እየበጠሰች፣ ገንዘቧን ከቦርሳዋ እያራቆተች፣ ምንም የሌላት ደግሞ የእጅ ስልኳን ሳይቀር መባ እቃ ውስጥ እየጨመረች የማይፈፀም ትንቢት ታቅፋ እርቃኗን ከአዳራሹ ትወጣለች ... ልትባረክ ነዋ ሃሃሃሃ
ከላይ እንዳልኩት ነብይ ጎሳ ነብይነቱን ከየት እንዳገኘው ማንም አያውቅም። የሚያወራው ታሪክም እውነት ስለመሆኑ ምንም ማረጋገጫ የለም። ይህን ሰውዬ የሚጋብዙት ስግብግብ የቤተክርስቲያን አገልጋዮችም የሰውየው ምስክርነት እውነት የተፈፀመ ይሁን አይሁን ለማረጋገጥ ምንም አይነት ጥረት አያደርጉም! እነሱ ሚፈልጉት በሱ ጅንጀና የሚዘንበውን የገንዘብ ዶፍ ነው። የስብከቱ መለኪያ በሱ ስብከት አማካኝነት የገባው የገንዘብ መጠን ነው እንጂ የእግዚአብሔር ቃል አይደለም!
አሁን ቤተክርስቲያን በጎሳና ጎሳን በሚመስሉ መንፈሳዊ ደላሎች እየታመሰች የምትገኝበት ሰአት ላይ ትገኛለች። መፅሀፉ ጎሳንና መሰል አገልጋዮችን «ለመንጋው የማይራሩ» ይላቸዋል!
እንዲጠብቁት የተሰጣቸውን ምእመንና እረኛ የሆኑለትን መንጋ ስጋ እየበሉ ሰብተው ቆዳውን ገፍፈው ይለብሳሉ! በአስራትና በበኩራት፣ በመባና በፍቅር ስጦታ ስም፣ ገንዘቡ ወደካዝናቸው ይጋዝ እንጂ የገንዘቡ አመጣጥ እነሱን አያስጨንቃቸውም። በምእመኑ ፍራንክ ትልልቅ እቅዶች ያቅዳሉ፣ የህዝቡን መሶብ አራቁተው ሰማይ ጠቀስ ፎቆችን ይገነባሉ፣ በሊትር ሶስት ኪሎሜትር የሚሄዱ ላግዥሪ መኪኖችን ይነዳሉ። ይሄ ተስፈኛ ምእመን ግን ከሰማይ መና እየጠበቀ በደረቅ ምድረ በዳ ደረቅ ትንቢታቸው ታቅፎ ከቃዴስ ቃዴስ ሲንከራተት ይኖራል።
በአብዛኞቹ የወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያኖች ዘንድ ምድር ምድር የሚሸት ስብከት በዝቷል። ሰባኪው ሁሉ የ prosperity Gospel (የብልፅግና ወንጌል) አቀንቃኝ ሆኗል፣ ምእመኑም በረከቱን የሚለካው በምድራዊና ቁሳዊ ሀብት ብቻ ነው! «ሀገሬ በሰማይ ነው» አይነት ንግግሮች ከምእመኑ አንደበት መደመጥ አቁመዋል። ኢየሱስ የሞተው ለቼቭሮሌት መኪናና ለግራውንድ ፕላስ ስሪ ፎቅ ይመስል ወሬው ሁሉ ቤት ስለመስራትና ቤት ስለማፍረስ ሆኗል ... እንደ ዊነርስ ቻፕል አይነት ቸርቾችማ ወሬው ሁሉ ሱሪ ስለመቀየርና መኪና ስለመንዳት ከሆነ ቆየ። «በመንፈስ መኪና የመንዳት» ፕሮግራም ሁሉ ያካሂዳሉ አሉ! ሃሃሃ
ነብያቶች በዝተዋል። ነብይነት ግን ከሞተ ቆየ! ሰባኪዎችም አሸን ናቸው። ስብከት ግን ስልሳዎቹ ላይ ቆሟል! በየመድረኩ ተኳኩለው እንጣጥ እንጣጥ የሚሉ (ባለብዙ ሚስት ዘማሪዎች እልፍ ናቸው) መንፈሳዊ ማንነትን የሚያንፅ መዝሙር ግን ከመድረኩ ነጥፏል!
በፅድቅና በቅድስና የሚያገለግሉ አንዳንድ አገልጋዮች እንዳሉ አይጠፋኝም። ግን እነዚህ አገልጋዮች ከጎሳውያኑ ጋር ሲተያዩ በገምቦ ውስጥ እንዳሉ ጥቂት ጠብታዎች ናቸው! ስለዚህ ባህር ውስጥ እንዳሉ አይቆጠሩም። እኔ ማወራው ባህሩን ስለሞሉት የተበከሉ አሳዎች ነው!
 ቸርቾች በየመቶ ሜትሩ ከተማ ውስጥ ፈልተዋል። ደቀመዝሙር ማፍራት የማይችሉ ውሀ አልባ ምንጮች ናቸው እንጂ! ክርስቲያን ያልሆኑ የክርስቶስ ሰባኪዎችና ክርስቶስን የማያውቁ አገልጋዮች ይሄን ምስኪን ምእመን እንደአሻንጉሊት እየተጫወቱበት ነው! አገልግሎታቸው ያከበራቸውን ህዝብ በመናቅና በማስፈራራት ላይ የተመሰረተ ነው! «ለምን?» ብሎ ጥያቄ የሚያነሳ ሲመጣ «ጌታ በቀባው ላይ እጅህን አታንሳ» በማለት በጥቅስ ያስፈራሩታል። በፅድቅ ለማገልገል ከላይ እታች እያሉ የጅብ ድግሳቸው ላይ የማይሳተፉትን ንፁሀን ደግሞ የተለያየ ስም ጀርባቸው ላይ በመለጠፍ ከአገልግሎት ያግዷቸውና የሚከተላቸውን ምእመን ኑሮ እየቀሙ ይኖራሉ! ሳቁን መንትፈው ይስቃሉ! ደስታውን አራቁተው ይደሰታሉ! እውነትም ለመንጋው የማይራሩ ሆዳሞች!
ዘመኑ የባቢሎናውያኑን ዘመን ይመስላል። ትርምስ እንጂ መረጋጋት የለም! ጩኸት እንጂ መግባባት ጠፍቷል። ግራ የተጋቡ ባለራእዮችና ያልተማሩ አስተማሪዎች መሬት ባልረገጠ የትምህርት ወጀብ ህዝቡን እየናጡት ነው። በተቀየጠ ዶክትሪንና በስህተት አስተምህሮ ምእመኑን ከወንጌል አርቀው አይኑን በማሰር ወደቁልቁለት እየነዱት ነው! ነብያት ነን ባዮቹ ወንዝ በማያሻግር ትንቢት ሲወራጩ መድረኮቻችን ላይ ውለው ያድራሉ። ዝናብ የሌላቸው ደመናዎች በተራ ፉከራና ሽለላ የተሞሉ ፍሬ አልባ ደረቅ መሬቶች ናቸው!
በተለያዩ ቤተክርስቲያኖች እየተጋበዘ ህዝቡን የሚያራቁተው ደላላው ነብይ .... «ነብይ ጎሳም» ከላይ ለጠቀስኳቸው ሆዳም አገልጋዮች እውነተኛ ምልክት ሊሆን ይችላል ባይ ነኝ!

እቀጥላለሁ!‎

Saturday, June 4, 2016

ማኅበረ ቅዱሳን አሁን የቤተ ክርስቲያን፤ ቆይቶ የመንግሥት መጥበሻ ምድጃ ነው!


በታሪክ አጋጣሚ የደርግን መውደቅና ግርግርን ተተግኖ የተፈጠረው ማኅበረ ቅዱሳን የመጥበሻ ምድጃ ከሆነ እነሆ 23 ዓመታት አለፉት። ብዙዎችን በትኗን፤ አሳዷል። ዳግም እንዳይመለሱ በማድረግ እንደተዋጊ በሬ እየበጠበጠ ከበረት አስወጥቷል። በማወቅም ይሁን ባለማወቅ አፋፍተው ያሳደጉትን አቡነ ጳውሎስን ሳይቀር በአድማ የመጥበሻ እሳት እየለበለበ እስከመቃብር ሸኝቷል። የአሁኑን ፓትርያርክ የአቡነ ማትያስን ወንበር በተሾሙ ሰሞን ለመረከብ ተፍ ተፍ ብሎ ሳይሳካለት ቢቀር በተለመደ የመጥበሻ ምድጃው ላይ አስቀምጦ ላለፉት 3 ዓመታት  በአድማው ግሪል / GRILL/ እየጠበሰ ይገኛል።

ፓትርያርክ ማትያስ ብቻቸውን ሆነው ይህንን መጥበሻ ምድጃ ሊያስወግዱ ብዙ ታግለዋል። ነውራም ጳጳሳቱ እዳ በደላቸው በዚህ ማኅበር የኃጢአት መዝገብ ላይ ስለሰፈረ ከፓትርያርኩ በተጻራሪ ቆመው ውግንናቸው ለማኅበሩ ሆኖ ታይቷል። የማኅበሩ ሥፍራ በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ የት ነው? በሚለው ነጥብ ላይ ጥያቄ ያላቸው ፓትርያርክ ማትያስ ድርሻውን፤ አቅሙንና ተጠሪነቱን የሚወስን አዲስ መተዳደሪያ ደንብ እንዲወጣለት ያደረጉት ተጋድሎ ላይ ውሃ በመቸለስ የሲኖዶስ ጉባዔ በመጣ ቁጥር የሚያጨቃጭቅ አጀንዳ እያስገባ ሲሾልክ ቆይቷል። ዘንድሮም ይህን የቤት ሥራ ሰጥቶ በአንድ አጀንዳ ላይ ለ4 ቀናት ካጨቃጨቀ በኋላ የሲኖዶስ አባል የሆነው የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስትር መፍትሄ አስምጦ ሊገላግላቸው ችሏል። ይህ ሁሉ የሆነው በማኅበሩና በጉዳይ ፈጻሚ ጳጳሳቱ የተነሳ ነው።

የእንደራሴ መኖር አለመኖር ለማኅበረ ቅዱሳን አሳሳቢው አይደለም። ነገር ግን በዘንድሮው ጉባዔ ላይ ማንሳት ያስፈለገው የራሱ ስሌት ስላለው እንጂ ለቤተ ክርስቲያኒቱ ድክመት ከሱ መኖር በላይ አስቸጋሪ ፍጡር ስለመጣ አይደለም። በዚህም የተነሳ በአቅም ማነስ ሰበብ ፓትርያርኩን አሸመድምዶ በማስቀመጥ ለ3 ዓመታት ያህል እሳት ካነደዱበት ሥጋት ነጻ ለመውጣት የተያዘ መላ ከመሆን አይዘልም። ከዚህም በፊት እንዳልነው ጳጳሳቱ በሀገረ ስብከታቸው መሥራት ያልቻሉትን የመንፈሳዊና ሥጋዊ የልማት ሥራዎች  እንደራሴው እየዞረ የሚሰራላቸው አለመሆኑንም በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል። ማኅበረ ቅዱሳን እስካለ ድረስ ታዛዥ ያልሆነ የትኛውም የቤተ ክርስቲያኒቱ ባለሥልጣን  ማኅበሩ ባዘጋጀው መጥበሻ ላይ ይጣዳል። ምርጫቸው ከማኅበሩ ጋር መቆም አለያም በተጻራሪ ሆነው ለመጥበሻው ራሳቸውን ከማዘጋጀት የግድ ነው። አባ ሳዊሮስ ከአዲስ አበባ ማኅበረ ካህናት ጋር ቆመው ማኅበሩን ሲያጋልጡ ምድጃውን አዘጋጅቶ መጥበስ ሲጀምር እጃቸውን አንስተው ለማኅበሩ ለማስረከብ መገደዳቸውን አይተናል። አባ ፋኑኤል ማኅበሩ የሌለበት ቦታ የት ሄጄ ልሥራ? እንዳላሉ ሁሉ ምርኮኝነታቸውን ካረጋገጡ በኋላ ግን ከማኅበሩ መጥበሻ ግሪል ላይ ወርደው እረፍት ሊያገኙ ችለዋል። ሌሎቹ ግን የሚደርስባቸውን እሳት አስቀድመው ስለሚያውቁ ቃላቸውን አክብረው የጫናቸውን በማራገፍ ግንቦትና ጥቅምት በመጣ ቁጥር በማኅበሩ አጀንዳ አስፈጻሚነታቸው ቀጥለዋል።

 ማኅበረ ቅዱሳን በስመ ተሐድሶና ሙሰኛ ነጠላ ዜማው የፈጃቸውና ያቃጠላቸው ካህናት ቁጥራቸው ብዙ ነው። ስለቅድስናና መንፈሳዊ ንጽህና በዋለበት ያልዋለ የዋልጌዎች ስብስብ ይህ ማኅበር ስም እያጠፋ ያሳደዳቸው፤ ስለኃጢአታቸው ንስሐ የሚገቡበትን በር እየዘጋ ተስፋ በማስቆረጥ ያስወጣቸው የትየለሌ ናቸው። የሚገርመው ግን ነውራም ጳጳሳቱን በቅድስና ካባ ሸፍኖ ለአገልግሎቱ የሚጠቀምባቸው የከባቴ አበሳ ተፈጥሮ ስላለው ሳይሆን እስካለገለገሉት ድረስ ብቻ ነው። እያንዳንዱ የማኅበሩ አባል በተለይም አመራሩ እነአቡነ እገሌ እስከምን ድረስ የጉስቁልና ባሕር ውስጥ እንደሰጠሙ እያወቀ በስምምነት አብሮ ይሰራል። ነገር ግን ከማኅበሩ አቋም ካፈነገጡ ከዚህ በፊት እንዳደረገው የእዳ ደብዳቤአቸውን ከማንበብ አይመለስም። ይህ በተግባር የተረጋገጠ እውነት ነው።

አንዳንዶች ማኅበሩን የቤተ ክርስቲያኒቱ ችግር ብቻ አድርገው ያያሉ። ነገር ግን ማኅበሩ  እንደግብጹ የሙስሊም ወንድማማቾች ማኅበር በፖለቲካው መድረክም የረቀቀ ተልእኮ ያለው ማኅበር ነው። በአባልነት ያቀፋቸው ሚኒስትሮች፤ ከፍተኛ ባለሥልጣኖች፤ ሥራ አስኪያጆች፤ ፖሊሶች፤ ዳኞች፤ የሕዝብ አገልግሎት ሠራተኞች፤ መምህራንና ተማሪዎች፤ የሙያ ማኅበራት፤ በ44 አኅጉረ ስብከት ውስጥ ያሉ ሚሊዮኖች የሰንበት ት/ቤት አባላት፤ የጥምቀት ተመላሽ ተጠባባቂ ጦር የመሳሰሉትን በአባልነት እየመለመለ በቤተ ክርስቲያኒቱ ስም የራሱን ዶክትሪን በመጋት ማኅበረ ቅዱሳን፤ ማኅበረ ቅዱሳን ካሰኛቸው ውሎ አድሯል። ዛሬ ከሲኖዶስ ወይም ከፓትርያርኩ በላይ ለቤተ ክርስቲያኒቱ ተቆርቋሪና ጠባቂ ከማኅበሩ በላይ የለም የሚለው አስተሳሰብ በእያንዳንዱ ሰው አእምሮ ውስጥ እንዲሰርጽ በሰፊው ተሰርቷል። ዘመናዊ የክርስቲያን ብራዘር ሁድ ማለት ማኅበረ ቅዱሳን ነው።

ሌላው የማኅበሩ ተንኮል አሁን ካሉት ታማኝና ታዛዥ ጳጳሳት በተጨማሪ ከእንግዲህ የሚሾሙ ኤጲስ ቆጶሳት በራሱ መስፈርት የተመለመሉና ወደፊት ችግር እንደማይፈጥሩ የተረጋገጠላቸው ብቻ እንዲሆኑ ይፈልጋል። እነዚህ የማኅበሩ እጩ ኤጲስቆጶሳት ያለፈ ታሪካቸው የቱንም ቢመስል አሳሳቢ አይደለም። ተቀባይነታቸው አርአያነት ባለው ሁኔታ ቢሆንም፤ ባይሆንም ለማኅበሩ አስጊ እስካልሆኑ ድረስ እንዲመረጡ አጥብቆ ይሰራል። ነገር ግን በተቃራኒ ማኅበሩን የሚፋለሙ ከሆነ እንደአባ ሠረቀብርሃን ወ/ሳሙኤልን የመሳሰሉት በልዩ ልዩ ስምና ወንጀል በሕይወት ዘመናቸው ሁሉ እጃቸውን ካልሰጡ በስተቀር ለእጩነት ሊቀርቡ አይችሉም።

በአጠቃላይ ማኅበሩ በታሪክ አጋጣሚ በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ የተገኘ መጥበሻ ምድጃ ነው። በዚህ ምድጃ ዲያቆናት፤ ቀሳውስት፤ መነኮሳት ተጠብሰዋል። ሰባኪያነ ወንጌልና አስተዳዳሪዎች ተጠብሰዋል። ጳጳሳትና ፓትርያርኮች ተጠብሰዋል። እውነቱን እያወቁ ከመናገር ብዙዎች የተቆጠቡት ማኅበሩ መጥበሻው ላይ ከጣዳቸው የሚያወርዳቸው ስለሌለ ነው። ልክ እንደ መንግሥታዊ የስለላ መዋቅር የማኅበሩን ስም በተቃውሞ በአውቶቡስ፤ በታክሲ፤ በሬስቶራንት፤ በየካፌውና በሕዝብ መሰብሰበቢያ ቦታዎች መጥራት ከማይቻልበት ደረጃ ላይ ተደርሷል። መንግሥት ላይ ምን ዓይነት የአንኮበር መድኃኒት እንደተረጨበት ባናውቅም እሱም በፍርሃት ይሁን በድንዛዜ ፈዞ ቀርቷል።  እውነታው ግን ማኅበሩ ለየትኛውም ወገን መጥበሻ ምድጃ መሆኑ በተግባር የተረጋገጠ ነው።

Wednesday, June 1, 2016

«ምላጭ ቢያብጥ በምን ይበጡት፤ ውሃ ቢያንቅ በምን ይውጡት?




አበው ዘይቤያዊ ምሳሌ ሲሰጡ፤ ፍሬ ነገሩን  ሊገልጥ የሚችል ጥሩ ኃይለ ቃል ይጠቀማሉ። በአንድ ዐረፍተ ነገር ብዙ ሐተታ ሊወጣው በሚችል መልኩ የጉዳዩን ብስለትና ጠጣርነት በደንብ ያሳዩበታል። ለዚህም ነው «ምላጭ ቢያብጥ በምን ይበጡት፤ ውሃ ቢያንቅ በምን ይውጡት?» በማለት መሆን የማይገባው ነገር ሆኖ ቢገኝ መፍትሄው ግራ የሚያጋባ እንደሆነ ለማስረዳት ይፈለጉት። አዎ፤ በዘመነ አበው ምላጭ፤  እባጭ እንዲፈነዳ፤ የተቋጠረው መግል እንዲፈርጥ ይበጡበት ነበር። በገጠሪቱ ኢትዮጵያ ዛሬም አልፎ፤ አልፎ ይሰራበታል።  ነገር ግን ምላጭ ራሱ ቢያብጥ በምን ይቆረጣል? ውሃስ ቢያንቅ በምን ማወራረድ ይቻላል? ግራ የሚያገባ ነገር ነው። መሆን የሌለበት ሆኖ ሲገኝ ያስገርማል፤ ያስደነግጣል፤ መፍትሄውም ሩቅ ይሆናል።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከቅርብ ዓመታት ወዲህ እየታየ ያለው ድርጊት የዚሁ ምሳሌ ተመሳሳይ ነገር ነው። በቤተ ክርስቲያኒቱ ታሪክ የቅዱስ ሲኖዶስ መንበር ከተመሠረተ ከ50 ዓመታት እጅግም ያልዘለለ ጊዜን ያስቆጠረ ቢሆንም በዚህ አጭር እድሜው 50 ጉድ አሳልፏል። ፓትርያርኳን አሳልፋ በመስጠት ለደርግ ጭዳ ማቅረቧም በማስረጃ የተረጋገጠ እውነት ነው። ፓትርያርክ አውርዳ ፓትርያርክ ሾማለች። ለሁለት የተከፈለ ሲኖዶስም የያዘችው በዚሁ አጭር እድሜዋ ነው። የሐዋርያትን መንበር ተረክቤአለሁ የምትለዋ ቤተ ክርስቲያን ሐዋርያት እንዳደረጉትና የራሱን ሥፍራ በለቀቀው በይሁዳ ምትክ እንደሾመችው ሐዋርያ በመንፈስ ቅዱስ ምርጫ እጣ ማጣጣል ሲገባት እንደፖለቲካ የካድሬ ምርጫ በሰውኛ አሳብና እንደተሰጣቸው ተልእኮ በሚመለመሉ ሰዎች ምርጫ መሾሟም የዚሁ የአጭር ዘመን ታሪኳ አንዱ ክፍል ነው። 

ነውርና ነቀፋ የሌለበት፤ ራሱንና ቤተሰቡን በአግባቡ ስለመምራቱ በምእመናንና ምእመናት የተመሰከረለት አገልጋይ ሰው ኤጲስ ቆጶስ እንዲሾም ቃለ ወንጌሉ ቢናገርም ከንባብና ከአንድምታው በዘለለ ተግባር ዳገቷ ቤተ ክርስቲያን ሆና ለሰሚ የሚቀፍ፤ ለሚያውቁት የሚያሳፍር ሹመት እየፈጸመች በመገኘቷ እነሆ ጥቅምትና ግንቦት በመጣ ቁጥር የዘራችውን እያጨደች ትገኛለች።
   «መልካም ዘር መልካም ፍሬ ያፈራል» እንዲል ወንጌል የዚህ ተቃራኒ በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ ስለመዘራቱ ደግሞ ፍሬውን ሲኖዶስ በመጣ ቁጥር ጭቅጭቅ፤ ንትርክ፤ ሁከትና አድማ ሲያስተናግድ ማየት የተለመደ ሆኗል። ከላይ ለመግለጽ እንደተሞከረው ለትውልድ የፈውስና የምሕረት መልእክተኛ መሆን የሚገባው አካል ለራሱ ከፈውስም ሆነ ከምሕረት ስለራቀ መሆን በማይገባው ሁኔታ ውስጥ ይገኛል። 

«ምላጭ ቢያብጥ በምን ይበጡታል፤ ውሃስ ቢያንቅ በምን ይውጡታል?» ማለት ይኼ ነው። ሰው በልቡ መታደስ ካልተለወጠና የማይሞተውን የሞት አሸናፊ ካልለበሰ አዲስ ፍጥረት እንደማይሆን ሐዋርያው በመልእክቱ ነግሮናል።  ካልተለወጠና የቀድሞ ግብሩን ካልተወ አሮጌነት ደግሞ አብሮት ያለው ማንነት በክፋትና በተንኮል ተግባር እየተገለጠ በዘመኑ ሁሉ ይቀጥላል። ዛሬም በሲኖዶስ ጉባዔ ላይ የሚታየው ችግር ሁሉ የውስጥ ማንነቱ ማሳያ መስታወት ነው። ሰው የሌለውን ውበት ከየትም ሊበደር አይችልም።
ሰሞኑን እየተካሄደ ባለው ሲኖዶስ (ቅዱስ ለማለት ይከብደኛል) ምክንያቱም ካልተወሻሸንና ሞራል እንጠብቅ ካልተባለ በስተቀር መንፈስ ቅዱስ የሁከትና የንትርክ አምላክ ስላይደለ ቅዱስ ለማለት ይከብዳል። በስብሰባው ላይ እየታየ ያለው ኢ-መንፈሳዊና ኢ-ሥነምግባራዊ ድርጊት ከስምና ከማዕርግ እድገት በስተቀር ያልተለወጠ ማንነት የተንጸባረቀበት እጅግ አሳፋሪና አሳዛኝ ክስተት የታየበት ስለሆነ ነው። 

 «ከእናንተ አንዱ ከባልንጀራው ጋር ሙግት ቢኖረው በቅዱሳን ፊት በመፋረድ ፋንታ በዓመፀኞች ፊት ሊፋረድ ይደፍራልን? ቅዱሳን በዓለም ላይ እንዲፈርዱ አታውቁምን? በዓለምስ ላይ ብትፈርዱ ከሁሉ ይልቅ ትንሽ ስለሚሆን ነገር ልትፈርዱ አትበቁምን?» 1ኛ ቆሮ 6፤1-2

በቅዱስ ስም ተሰብስቦ፤ በዓለማውያን ምናልባትም እግዚአብሔርን በማያውቁ ዐመጸኞች ፊት የጉባዔ ዳኝነት ከመጠየቅ ወዲያ ለሲኖዶስ ምን ሞት አለ? አሁን እውነት ሕይወት ያለው ሲኖዶስ የሚባል አካል አለ ማለት ነው? ይህ ሁሉ የሆነውና እየሆነ ያለው በሞተ አካል ውስጥ ያለው የሙት መንፈስ ፍሬውን እያፈራ በመገኘቱ የተነሳ ነው።  ለዚህም ነው ሐዋርያው ጳውሎስ፤

 «በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ። ከሄድሁ በኋላ ለመንጋው የማይራሩ ጨካኞች ተኩላዎች እንዲገቡባችሁ፥ ደቀ መዛሙርትንም ወደ ኋላቸው ይስቡ ዘንድ ጠማማ ነገርን የሚናገሩ ሰዎች በመካከላችሁ እንዲነሡ እኔ አውቃለሁ» በማለት የተናገረው። የሐዋ 20፤28-30

መንጋው ተበትኗል፤ ለሚጠፋው በግ የሚራራ እረኛ የለም፤ ቤተመቅደሱ በርግብ ሻጮችና በለዋጮች ተሞልቷል፤ እርስ በእርሳቸው የሚነካከሱና የሚበላሉ ሆነዋል፤ ነገር ግን በሕይወት አለን ይላሉ። ለሥልጣን ሽሚያ፤ ለመፈንቅል፤ ለቡድን አሸናፊነት፤ ለማኅበር የበላይነት ይጋደላሉ።
 በየተመደቡበት ሀገረ ስብከት እንደነገሥታት የሚሰጣቸው ስግደት ሳይጎድል፤ እንደሰማያዊ ሹም ሆነው መታየታቸው ሳይጠፋ ምንም የሰሩትና ያለሙት በሌለበት ሁኔታ ዓይናቸው ሁል ጊዜ የሚያየው እዚያ ጣሪያ ላይ ነው። ጣሪያው ደካማ ይሁን ሰነፍ የሚያስቀምጠው አንድ ሰው ነው። ጣሪያው ላይ ሰው ሲቀመጥ ያልታገሉ ፈራህያን ዛሬ የሚያደቡት ምን ለማግኘት ነው? ለቤተ ክርስቲያኒቱ አስበው? ተጨንቀው? በጭራሽ አይደለም።
 ጳጳሳቱ ሰው ከመቅጠርና ከማባረር ባለፈ ሚሊዮን ተከታዮቻቸውን አሰልፈው ትምህርት ቤት፤ ጤና ጣቢያ፤ የንጹህ መጠጥ ውሃ፤ የብሎኬት ማምረቻ፤ የእንጨት መሰንጠቂያ፤ የመስኖ ልማት፤ የልብስ ስፌት፤ የጧፍና ሻማ ማምረቻ፤ የአልባሳትና ቅርሳ ቅርስ ተቋም፤ የዶሮና የከብት እርባታ፤ የዳቦ መጋገሪያ፤ የካህናት ማሰልጠኛ፤ ኮሌጆች፤ ዩኒቨርሲቲዎች፤ የህጻናት ማሳደጊያ፤ የአረጋውያን መጦሪያ ለምን አያቋቁሙም? ለምን አይሰሩም? ማን ከለከላቸው?
ከ15 ሚሊዮን ያልበለጠ ተከታዮች ያሏት የግብጽ ቤተ ክርስቲያን ገዳማትና አድባራት በረሃውን ገነት ያደረጉት፤ ምርትና ሃብታቸው የተትረፈረፈው እንደእኛ ጳጳሳት በፎጣ በመሸፋፈን ሳይሆን በአጭር ታጥቀው ከእስላም ሰይፈኞች ጋር በመታገልና ተግተው በመስራታቸውና በማሰራታቸው ነው። ከላይ ከተዘረዘሩት ውስጥ የግብጽ ቤተ ክርስቲያን ያልሰራችው የልማት ስራ የለም።  በጀት ተመድቦላቸው፤ ባለሙያ ተቀጥሮላቸው ሳይሆን መነኮሳቱን፤ ካህናቱን፤ ምእመናኑን በማስተማርና በማሰልጠን በራስ አገዝ የልማት ተሳትፎ የተመሰረተ ነው።
 የኛዎቹ ለግንቦቱ ጉባዔ ከጥቅምት ጀምሮ ከመዶለትና ለጥቅምቱ ጉባዔ ደግሞ ከግንቦት ጀምሮ ሴራ ከመጎንጎን በስተቀር በሀገረ ስብከታቸው የልማት ርእይ፤ እቅድና ግብ በጭራሽ የላቸውም። ከሐውልት ምርቃት፤ ከቀብር ክፍያ፤ ከክርስትና፤ ከጋብቻ፤ ከፍትሃት፤ ከጸበል፤ ከሰበካ ጉባዔ አባልነት ወዘተ የሚሰበስቡትን ሚሊዮኖች ብር ለደመወዝና ለስራ ማስኬጂያ ከማዋል ባለፈ ተመልሶ ለሕዝቡ ልማት የዋለው ምን ያህሉ ነው? በደቡብ ክልል አካባቢ ያሉ የኦርቶዶክስ ምእመናን «እናንተ አምጡ እንጂ እንደሌሎቹ እንኩ አታውቁም» ማለታቸውን ስንሰማ የኛዎቹ መስጠትን ሳይማሩ አምጡን ከየት ለመዱት ያሰኛል።

    በአጠቃላይ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ውድቀትና ማሽቆልቆል ተጠያቂዎቹ ጳጳሳቱ ናቸው። ለመንጋው መበተን፤ ለስርቆትና ሥነ ምግባር ጉድለት ኃላፊነቱን መውሰድ አለባቸው። የታጣው መሪ እንጂ  ለመመራት ፈቃደኛ፤ ለመስጠት እጁን የማይዘረጋ  ምእመን የለም። ደግሞስ እንደኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ምእመን እጁን የሚዘረጋ አለ እንዴ?
 በሀገረ ስብከታቸው ልማት ሳያሳዩ ወደላይ መንጠራራት ስንፍናቸውን እንጂ አዋቂነታቸውን አያመለክትም። ጳጳሳቱ ለድክመታቸው ምክንያት ፓትርያርኩ ላይ አመልካች ጣታቸውን ከመቀሰራቸው በፊት እኔ በሀገረ ስብከቴ ምን ሰራሁ? ብለው ራሳቸውን ይጠይቁ። ብዙዎቹን ጳጳሳት ከምንኩስና ጀምሮ ስለምናውቃቸው ስለማንነታቸው ነጋሪ አያሻንም። ከታች ጀምሮ ያልተገነባ ስብእናና ችሎታ ደረጃቸው ስላደገ ባንዴ አብሮ አይመነደግም። ቁም ነገሩ እንደእኛው ችሎታ የሚያጥራቸው ሰዎች መሆናቸው ሲሆን አሁን አለቃቸውን ማስቸገር ቀደም ሲል በአለቅነታቸው ካዳበሩት ችግር የተማሩት ብቸኛ እውቀት ይመስለኛል።  ከዚያ ባሻገር በልማታቸው ለሕዝቡ የመኖር ተስፋ ወይም በጸሎታቸው ለሀገር የሚተርፉ ሆነው 15 ሚሊዮን ሕዝባችንን ከድርቅ ሲታደጉ አላየንም። ከመንጋ ጳጳስ እንዴት አንድ ኤልያስ ይጥፋ? ተግባር እንጂ ስም አላልኩም።

በግንቦቱ ሲኖዶስ ተሰብስበው በፓትርያርክ ማትያስ የችሎታ ማነስ ላይ ከመሳለቅ አስቀድመው በራሳቸው የአቅም ማነስ ላይ ቢወያዩ የተሻለ ነበር። ምሳሌ እንስጥ፤  ከ1985 ዓ/ም ጀምሮ 23 ዓመት በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ጳጳስ ሆነው የቆዩት የአሁኑ አባ ጎርጎርዮስ፤ ሟቹ አቡነ ጎርጎርዮስ ከመሰረቱት የዝዋይ ካህናት ማሰልጠኛና የአትክልት ልማት ወዲህ ስንት ማሰልጠኛ አቋቋሙ? ስንት የልማት አውታር ተከሉ? እውነታው ምንም ነው። አባ ቄርሎስስ በሰሜን ወሎ ሀ/ስብከት ስንት የካህናት ማሰልጠኛ፤ ስንትስ የእደ ጥበብ ተቋም ተከሉ? ስንት የከብት ማድለቢና የዶሮ እርባታ አቋቋሙ? ማን እንዳያደርጉ ከለከላቸው? ሟቹ አባ ጳውሎስ ወይስ ሕያው አባ ማትያስ?

 በምሥራቅ ጎጃምና በምዕራብ ጎጃምስ ምን ተሰራ፤ በሰሜንና ደቡብ ጎንደር ሀ/ስብከትስ ምን ልማት ተቋቋመ? በአጭር ጊዜና በረጅም ጊዜ እቅዳችሁ ምን አሳካችሁ?  በደን ልማት ላይ ሕዝቡን በማስተባበር በዚህ ዓመት ስንት ሚሊዮን ችግኝ ለመትከል ተዘጋጅታችኋል?
እርግጥ ነው ጳጳሳቱ በሌላ የሥራ መስክ ላይ አልቦዘኑም። የግል ቤታቸውን ገንብተዋል፤ ዘመናዊ መኪና አስገዝተዋል። በባንክ ገንዘባቸውን አጭቀዋል። ዘመድ አዝማዳቸውን በየቤተ ክርስቲያናቱ ቀጥረዋል።  
በአንድ ወቅት መንግሥቱ ኃ/ማርያም ሚኒስትሮቹን ሰብስቦ « የምትነዱትን የመኪና ዓይነትና ብዛት፤ ያላችሁን ቤት፤ የምትውሉበትን፤ የምታድሩበትን ቦታና ጭምር ይኽ ሕዝብ ብታምኑም ፤ ባታምኑም አሳምሮ ያውቃል» ብሏቸው ነበር።  ሕዝብ ምን የማያውቀው አለ? ተከድኖ ይብሰል ብለነው እንጂ የኛዎቹን ስንቱን ጉድ እናውቃለን።
 አሁን እነሱ ምን ስለሆኑ ነው፤ እንደራሴ ይሾም የሚሉት?  እንደራሴ ምን ያድርግላቸው? መፈንቅለ ፓትርያርክ መሆኑ ነው ወይስ እንደራሴው በየሀገረ ስብከታቸው እየሄደ ት/ቤት ሊሰራላቸው ነው? ጉዳዩ ፓትርያርኩን ወደጎን አስቀምጦ ለጳጳሳቱና ለማኅበረ ቅዱሳን ያደረ ሰው ለማስቀመጥ እንደሆነ ሳይታለም የተፈታ ነው። እቅዱም የኃጢአታቸው ዐቃቤ ኃጢአት ከሆነው ከማኅበረ ቅዱሳን ሴራነት የዘለለ አይደለም።  የሚያሳዝነውና የሚያስገርመው ነገር የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስትር እንደራሴ ለመሾም ይችሉ ዘንድ እንዲያግዛቸው መለመናቸው ነው።
 የፖለቲካ ሰው ምን ማድረግ እንዳለባችሁ ቅዱስ በሚባለው ጉባዔያችሁ ተቀምጦ ሲነገራችሁ ከመስማት ሞት ይሻላችሁ ነበር። ዳሩ ግን የሞታችሁት ቀድሞ ነውና ይኼ ለቤተ ክርስቲያኒቱ ውርደት ለእናንተ ግን ክብር ነው። ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር በጠሩት ጉባዔ ላይ አንድ የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ተወካይ የተናገረውን ጠቅሼ ልቋጭ። «ፖለቲከኛው እጣን፤ እጣን ሲሸት፤ የሃይማኖት አባት ፖለቲካ፤ ፖለቲካ ሲሸት አስቸጋሪ ነው» ማለቱን አስታውሳለሁ።
አዎ፤«ምላጭ ቢያብጥ በምን ይበጡት፤ ውሃ ቢያንቅ በምን ይውጡት?» እንዲሉ።




Saturday, March 26, 2016

ቀሲስ የ“ክብረት ልጅ”፥ ምነው በስድብ ቃል በጣም ጮኸ?!


ምንጭ፦ የአቤኔዘር ተክሉ ገጽ http://abenezerteklu.blogspot.com/
የክብረት ልጅ እይታዎቹን በሚያቀርብበት ብሎጉ፥ “ፓትርያርኩ፦ ለኢትዮጲያ የደኅንነት ፣ ለምእመናን የድኅነት ሥጋት” በሚል አንድ ጽሁፍ፥ ዛሬ አስነብቦ ድንገት ያየ ሰው ጠቆመኝና ወደጡመራው መድረኩ ገብቼ አነበብኩት፡፡ ዳንኤል በዚህ ጽሁፉ “100% ማኅበረ ቅዱሳን ሊያዘጋጀው ከጫፍ የደረሰውን ዐውደ ርእይ የከለከሉት ፤ ያስከለከሉት ፓትርያርኩ ናቸው”፥ ብሎ ደምድሞ አስቀምጦታል፡፡ የዐውደ ርእዩ ባለቤት ማኅበረ ቅዱሳን ደግሞ፥ በዋናው ጸሐፊው አቶ ተስፋዬ ቢኾነኝ በኩል ትላንት ማምሻውን ለጋዜጠኞች በሰጠው ጋዜጣዊ “መግለጫ”፥ “ለመታገዱ ፓትርያርኩ እንደሌሉበትና በመንግሥት አካላት መመሪያ መታገዱን”ይፋዊ መግለጫ ሰጥቷል፡፡

ዳንኤል ፓትርያርኩን ከሰይጣን እኩል ነበር የሳላቸው ፤ “... ፓትርያርክ ማለት በግሪክ “ታላቅ አባት” ማለት ነው፡፡ የታላቅ አባት ተግባር የልጆቹን ሥራ ማፍረስ አይደለም ፤ ለዚህማ አባት አያስፈልግም ሰይጣን እንጂ፤ ...” በማለት፡፡ እንደከዚህ ቀደም ልማዱ ዳንኤል ሌሎች ማስጮኺያዎችንም በዚህ ጽሁፍ ለማካተት ጥሯል፡፡ አዳዲስ ስድቦችንም ለፓትርያርኩ እንደእጅ መንሻ አቅርቦላቸዋል፡፡

ቅዱስ ቃሉ ግን እንዲህ ይላል፥ “ፈራጆችን አትስደብ፥ የሕዝብህንም አለቃ አትርገመው።” (ዘጸ.22፥28) የሕዝብ አለቃ ወይም መሪ የሆነ ገዥ በምድር ላይ የእግዚአብሔር ተወካይ ፤ እንደራሴም ነው፡፡ ስለዚህ ልናከብረው ፤ በመውደድም ከሁሉ በፊት ልንጸልይለት ይገባል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ሳያስበው ይህን ቃል በመተላለፉ ምክንያት ወዲያው ተጸጽቶ ተመለሰ ፤ አለማስተዋሉንም ተናገረ፡፡ (ሐዋ.23፥4-5) ፍትሐ ነገሥቱም “በእነርሱ ላይ የተሾመውን ጳጳስ ... እንደትልቅ ወንድም ያክብሩት መሪና አስተዳዳሪ እንደመሆኑ መጠን ሊታዘዙለት ይገባል” ይላል፡፡ (አን.4 ቁ.53) ዳኒ! ይህ የሕግ ቃል አንተን አይመለከትም ይሆን?!

የቤተ ክርስቲያን የቀኖና መጽሐፍ ፍትሐ ነገሥት በአንቀጽ.6 ስለቀሳውስት ድርሻ ባሰፈረበትና ቀሳውስት ከማዕረገ ክህነታቸው ስለሚሻሩበት ሁኔታ ሲዘረዝር “... ሕግን አውቆ የማይሠራባት ... ቄስ ይሻር፡፡” በማለት በግልጥ ያስቀምጣል፡፡ ዳኒ! እንኳን መንፈሳዊውን ሥጋዊውን የዚህን አለም ምድራዊ ሕግ መጣስህን አውቀኸዋል? ማኅበሩ ፓትርያርኩ አልከለከሉኝም እያለ፥ አንተ ግን ለፓትርያርኩ የስም ማጥፋት ዘመቻ ከፍተሃል፡፡ እንደቤተ ክርስቲያን ቀኖና ከቅስናህ ትሻር ይሆን? እውነታው ግን አይመስልም፡፡

ፓትርያርኩ ቢያጠፉ እንኳ የቤተ ክርስቲያን ቀኖና ምን ነበር የሚለው? ጅል ፣ ሰይጣን ፣ የክፋት አነሳሽ ... እያሉ በአደባባይ ፓትርያርክን መዘርጠጥ አለበት የሚል “ቀኖና” አለን?! ለመሆኑ ስድብ ከማን ነው? የሕዝብን አለቃ አለማክበርስ? ያንን ሁሉ መጽሐፍ የጻፈው “ደራሲና ተመራማሪ” ምነው ምራቅ እንዳልዋጠ “ፍንዳታ”(የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስቴራችን ቃል ናት) ደርሶ ቱግ አለ?! እንዴ ይህ ነበር እንዴ በውስጡ የነበረው?!

ውድ ወንድሜ ቀሲስ ዳንኤል፦ ቤተ ክርስቲያን ቀኖና አላት ፤ በየትኛውም የቤተ ክርስቲያናችን ቀኖና ሽቅብ ፓትርያርክን እንዲህ መዘርጠጥ አይደለም ምእመንን መናገር አጸያፊ ነው፡፡ ተግሳጽ ነው ብትለኝ፥ ለመሆኑ ተግሳጽ መቼ ነው የሚመጣው? ደርሰህ ከመገሰጽህ በፊት ስንቴ ይሆን የመከርካቸው? ስንቴ ይሆን የወቀስካቸው? ስንቴ ይሆን ካሉበት ነቀፌታ እንዲርቁ በሚራራ ልብ አዝነህላቸው እንደእግዚአብሔር ቃል በጸሎት ቃል ወደጌታ የማለድክላቸው? ... ደጋፊ ስላገኙ ብቻ ብዙ ማለት፥ ከማያዳላ ኅሊና ጋር ያፋጥጣል፡፡ ወንድምን ሰባት ጊዜ ሰባ ይቅር ማለትና መቀበል እኮ ከአባት ባሻገር ወንድም ለሚሆነን ፓትርያርክንም ያካትታል ፤ ለመሆኑ ይህን ታውቀዋለህን?!

ፓትርያርኩ ቢያጠፉ ቤተ ክርስቲያን ቀኖና አላት፡፡ “...የአገሩ ሁሉ ኤጲስ ቆጶሳት ስለእርሱ የሚገባውን ይመረምሩ ዘንድ እርሱንም ለማየት በየዓመቱ ሁለት ጊዜ ከጳጳሳቸው (ፓትርያርካቸው) ዘንድ ይሰብሰቡ፡፡ ስለተሰጣቸው ሥልጣን በምታስፈራዪቱ ቀን መልሳቸው የጸናች ትሆን ዘንድ፡፡” (አን.4 ቁ.55) የሚል፡፡ የሚያዩት ፊቱን ብቻ አይደለም ፤ ሥራውን በማየት ያመሰግኑታል ፤ ነቀፌታም ካለ ይነቅፉታል፡፡ ዳኒ! ይህችን አላነበብካት ይሆን?! ፓትርያርኩን መውቀስና መምከር ፤ መገሰጽም ካለብህ መንገዱን አልሳትከው ይሆን? ይህን ያህል ግን ለምን ይሆን የጠላሃቸው? ዳኒ! ወንድምን ስለመጥላት ቃሉ በትክክል ይወቅስሃል፡፡

በእርግጥ ዳንኤልና ማኅበሩ መንገድ ሲተላለፉ ይህ የመጀመርያው አይደለም፡፡ ግን እውነት ለመናገር ባልተጣራ ወሬ ፤ በተራ አሉባልታ ያውም ስንት ሽልማት ያግበሰበሰው ሰው ይቺን ትንሿን ነገር ከማጣራት ቸኩሎ “በሚቆረቆርላት” ቤተ ክርስቲያን መሪ ላይ የስድብ ናዳ ያወርዳል ብሎ ማን ይጠብቃል?! ከዚህ ስህተቱ ይማር ይሆን ዳንኤል? ወይስ ወደፊትም ሌላ የስድብና የመዘርጠጥ ጽሁፍ ያስነብበን ይሆን? ወይስ እንደጳውሎስ በግልጥ የይቅርታ ልብ ይዞ “የሕዝብን አለቃ” ስለተሳደበበት ስድቡ ንስሐ ይገባ ይሆን? የምናየው ይሆናል፡፡ ፈጥነህ ንስሐ ብትገባ ግን ማሰናከያን ታስወግዳለህና እስኪ ቀድመህ ወደራስህ እይ!!!

ጌታ ማስተዋሉን ያብዛልን፡፡ አሜን፡፡

Sunday, February 14, 2016

የቫላንታይን ዴይ ከክርስትና አንፃር!


ስንቶቻችን ይሆን የቫለንታይን ቀን (የፍቅረኞች ቀን ብለን የምናከብረው) የሚከበርበት ምክንያትና መነሻው የምናውቀው? ወይስ ሰው ስለ አከበረውና የስልጣኔ መገለጫ መስሎን ነው የምናከብረው? ክርስቶስ ከመወለዱ ከብዙ ክፍለ ዘመናት በፊት አረማዊ ሮማውያን የካቲት 14 ማታና የካቲት 15 "የተኩላ አዳኙ" ለሚሉት ሉፐርኩስ (Lupercus) ክብር በማለት በጣኦት አምልኮ ያከብሩት ነበር። ሮማውያን ይህ በዓል ሉፐርካልያ (Lupercalia) ይሉታል።
ንጉሥ ቆንጠንጢኖስ ክርስትና የሮማውያን ይፋዊ ሃይማኖት መሆኑ በማወጁ ማንኛውም የጣኦት አምልኮ እንዲቀር ቢያስጠነቅቅም የተወስኑ ሮማውያን ሰዎች ግን በዓሉን ማክበር አልተዉም።
ይህንን አረማዊ በዓል ማለትም ሉፐርካልያ የሮማው ጳጳስ ገላስዮስ ክርስትያናዊ በዓል ሆኖ እንዲከበር አደረጉ። ጳጳስ ገላስዮስ ለካቲት 15 ሲከበር የነበረው በዓል የቅዱስ ቫለንታይን ቀን በሚል አዲስ ስያሜ የካቲት 14 እንዲከበር አደረጉ።
እንዴት ይህ አረማዊ በዓል የቅዱስ ቫለንታይን ቀን የሚል ስያሜ ተሰጠው?
ቫለንታይን የሚል ስም በሮማውያን ዘንድ የተለመደ ስያሜ ነው። ቫላንታይን ጥንታዊው ታዋቂው ሉፐርኩስ ነው። ሉፐርኩስ በግሪካውያን ፓን (pan) ተብሎ ይጠራል። በጥንታውያን አይሁድ ደግሞ ይህ ፓን በአል (Baal) በሚል ስያሜ ይታወቃል። በአል በመጽሓፍ ቅዱስ ዘፍጥረት 10-9 ላይ ታላቁ አዳኝ ተብሎ ለተገለጸው ኒምሮድ ሌላኛው መጠርያው ነው። ኒምሮድ የሮማውያን የተኩላ አዳኙ ሉፐርኩስ ነበር። በዚህ መሠረትም የቅዱስ ቫለንታይን ቀን የአረማውያን ለኒምሮድ ክብር የሚያከብሩት የጣኦት አምልኮ ነው።
ቫለንታይን የሚል ቃል ቫለንቲኑስ (valentinus) ቫለንስ ከሚል የላቲን ቃል የመጣ ነው። ቀጥተኛ ትርጉሙ ጠንካራ፣ሃይለኛ ታላቅ ማለት ነው። ዘፍጥረት10-9 ላይ እንደምናነበው " እርሱም በእግዚአብሔር ፊት አዳኝ ነበረ። ስለዚህም በእግዚአብሔር ፊት ሃያል አዳኝ እንደ ኒምሮድ ተባለ።  ኒምሮድ የሮማውያን ጀግና ሃይለኛ ሰው ቫለንታይን ነበር።
ሌላኛው የኒምሮድ ስም ሳንክቱስ (Sanctus) ወይ ሳንታ (santa) ነው። ሳይንት (saint) የሚል የእግሊዝኛ ትርጉም አለው ማለትም ቅዱስ። የሮማውያን ሉፐርካልያ በመጨረሻ ቅዱስ ቫለንታይን የሚል ስያሜ ያዘ ማለት ነው።
ጥንታውያን ሮማውያን ከባቢሎናውያን በቀዱት አረማዊ የልብ (heart) ምልክት ይጠቀማሉ። በባቢሎናውያን በአል (baal) ልብ የሚል ፍቺ ነው ያለው። በአሁኑ ጊዜ ይህ አረማዊ የልብ ምልክት ለቫለንታይን ቀን (የፍቅረኛሞች ቀን የምንለው) መገለጫ እንጠቀምበታለን። በአል የባቢሎናውያን የጣኦት ጌታ ነበር። በሌላ መንገድም ኒምሮድ ወይም ቅዱስ ቫለንታይን ሳተርን ተብሎ ይጠራል። ሳተርን የሮማ-ባቢሎን ከአባራሪዎቹ ለመሸሽ በምስጥራዊ ቦታ የሚደበቅ ጣኦት ነው። ሳተርን የሚል የላቲን ቃል ሴሜቲክ (አይሁድ) ቋንቋ ከሚናገሩ ባቢሎናውያን የተገኝ ነው። መደበቅ፣ ራስን መደበቅ የሚል ፍቺ አለው።
በጥንታዊ እምነትም ኒምሮድ (ሳተርን) ከአባራሪዎቹ በመሸሽ ወደ ጣልያን እንደተጓዘ ይነገራል። የአፐኒን ተራራ ስያሜው ወደ ኔምብሮድ ወይም ኒምሮድ ተቀየረ።ይህ ተራራ ኒምሮድ በጣልያን የተሸሸገበት ቦታ ነበር። ሮማም በዚህ ተራራ ላይ እንደ ተመሰረተች ይታወቃል። ሮም ፈርሳ እንደገና ከመሰራትዋ 753 ዓ/ዓ በፊት ሳቹርንያ (ሳተርን፡ኒምሮድ የተደበቀባት ቦታ) የሚል ስያሜ ነበራት። ኒምሮድ በዚህ ቦታ ተይዞ በፈጸመው ወንጀል ተገደለ። በንጉሥ ቆስንጠንጢኖስ ጊዜም ክርስቲያናዊ ሰማዕት የሚል የውሸት ክብር ተሰጥቶት በሮም ካቶሊክ ቤተ ክርስትያን መዘከር ጀመረ። ኒምሮድ፣ ባል፣ ቫለንታይን፣ ታላቁ አዳኝ፣ ፋውኑስና ሉፐርክስ 31ኛ፣ 32ኛና 33ኛና ደረጃ (ዲግሪ) ላይ ያሉ ፍሪማሶኖሪዎች ከሚያመልኩት ባፎሜት (የሜንደዝ ፍየል) አምልኮ አጋንንት ጋር የሚስተካከል ነው።
እንግዲህ በሰላቢ እጆች (ኢሉሚናቲ) ሴራ ዘመናዊነት ተላብሶ ድብቅ ጣኦት የሚመለክበት የቅዱስ ቫለንታይን ቀን እኛ ደግሞ የፍቅረኛሞች ቀን በማለት እያከበርን ማለትም እያመለክን ነው። አንድ በአል የሚከበርበትን ምክንያትና አስፈላጊነት ሊኖረው ግድ ነው። ሆኖም የምናከብረውን በአል የምናከብርበትን ምክንያትና አስፈላጊነት ሳናውቅ ከሴረኞች ድብቅ አላማ ማስፈጸሚያ ከመሆን መቆጠብ ይበጀናል፡፡ እግዚአብሔር ፍቅር ነዉ!

Saturday, January 30, 2016

ፓትርያርክ ማትያስ ስለማኅበረ ቅዱሳን የጻፉት ደብዳቤ ከመዘግየቱ በስተቀር ሀቅነቱ ጥያቄ የሚያስነሳ አይደለም!

ማኅበረ ቅዱሳን ማለት ለተረት፤ ለእንቆቅልሽ፤ ለልማድና ለባህል እምነት ጥብቅና የሚቆም፤ የወንጌል ቃል ጆሮውን የሚያሳክከው፤ በኢየሱስ ክርስቶስ የእውነት መንገድ ላይ ቆሞ እንዳይገለጥ መጋረጃ የሚጋርድ የጠላት መልእክተኛ ማለት ነው። ማኅበረ ቅዱሳን በሀገሪቱ ላይ የብርሃን ወንጌል እንዳይበራ የጭለማ ሥራ የሚሰራ፤ ሰዎች በእጃቸው ያለውን እውነት እንዳያዩ ወደገደል የሚመራ እውር መሪ ማለት ነው።
ማኅበረ ቅዱሳን ማለት በአንድ ወቅት የእግዚአብሔር ሕዝብ የተባለው እስራኤል በእግዚአብሔር ላይ ያለውን እምነት ትቶ የራሱን የልብ መሻትና ምኞት በተከተለበት ወቅት እንደሆነው ዓይነት በተመሳሳይ መልኩ በሀገራችን በኢትዮጵያም ከፊት ሆኖ በሀሰት እየመራ በእውነት የሚፈርድ እንዲታጣ ያደረገ፤ በሀሰትም የሚያስተምር እንዲበዛ የፈለፈለ፤ ልቡን ያደነደነ ትውልድ እንዲበረከት ሚና የተጫወተ ማኅበር ነው።
ያንን የእስራኤል ዐመጽ ነቢዩ ኤርምያስ እንዲህ ሲል ተናግሮት ነበር።

«እናንተ ሰነፎች ልበ ቢሶች፥ ዓይን እያላችሁ የማታዩ፥ ጆሮም እያላችሁ የማትሰሙ ሕዝብ ሆይ፥ ይህን ስሙ። በውኑ እኔን አትፈሩምን? ከፊቴስ አትደነግጡምን? ይላል እግዚአብሔር፤ እንዳያልፍ አሸዋን በዘላለም ትእዛዝ ለባሕር ዳርቻ አድርጌአለሁ፤ ሞገዱም ቢናወጥ አያሸንፍም፥ ቢጮኽም አያልፍበትም። ለዚህ ሕዝብ ግን የሸፈተና ያመፀ ልብ አላቸው፤ ዐምፀዋል ሄደውማል። በልባቸውም፦ የፊተኛውንና የኋለኛውን ዝናብ በጊዜው የሚሰጠውን፥ ለመከርም የተመደቡትን ወራት የሚጠብቅልንን አምላካችንን እግዚአብሔርን እንፍራ አላሉም። በደላችሁ እነዚህን አስቀርታለች፥ ኃጢአታችሁም መልካምን ነገር ከለከለቻችሁ። በሕዝቤ መካከል ክፉዎች ሰዎች ተገኝተዋል፤ እንደ አጥማጆችም ያደባሉ፥ ወጥመድንም ይዘረጋሉ ሰዎችንም ያጠምዳሉ»           ኤር 521-26

ማኅበረ ቅዱሳን በዘመናት ብዛት ማን እንደጻፋቸውና ማን እንዳስገባቸው የማይታወቁ የተረትና የእንቆቅልሽ መጻሕፍት እንዳይነኩ ዘብ የቆመ የጠላት ወታደር ነው። ብዙዎች እውነት በመናገራቸውም ያወገዘና ያስወገዘ ማኅበር ነው። ለምሳሌ አንድ አስረጂ እናንሳ!

መስተብቍእ ዘመስቀል በተባለው የቤተክርስቲያን የጸሎት ክፍል ውስጥ እንዲህ የሚል ክህደት ተሰንቅሮ ይገኛል። 
«ለእሉ ክልዔቱ ፍጡራን/ለማርያም ወለመስቀል/ ስብሐተ ፈጣሪ ይደልዎሙ፤ እስመ ተዐረዮሙ በክብሮሙ»
ለነዚህ ሁለቱ ፍጡራን  (ለማርያምና ለመስቀል) ለፈጣሪ የሚሰጠው  ምስጋና ይገባቸዋል። በክብር ፈጣሪያቸውን ተካክለዋልና!

 እግዚአብሔር ቢከብር ክብር የባህርይው እንጂ አክባሪ የሚጨምርለትና የሚቀንስለት ነገር የለም። ማንም የቱንም ያህል ቢከበር ከእግአብሔር ፈቃድ አንጻር እንጂ በራሱ ብቃት በሚያመጣው ችሎታ አይደለም። ደግሞም በክብር እግዚአብሔርን የሚስል፤ የሚያክልና አቻ የሚሆን ፍጥረት ፈጽሞ የለም። «በልዑል እመሰላለሁ» ካለው ከሰይጣን በስተቀር ከፍጥረታት ውስጥ በክብር እግዚአብሔርን የሚተካከል የለም።
«ከዳመናዎች ከፍታ በላይ ዐርጋለሁ፥ በልዑልም እመሰላለሁ አልህ» ኢሳ 1414

ነገር ግን እግዚአብሔርን የሚመስለው ማንም የለም? በማንም ልንመስለውና ከማንም ጋር ልናስተካክለው አይገባም። ራሱ እግዚአብሔር በነቢዩ አንደበት እንደዚህ ሲል ተናግሮናልና።

«እንግዲህ እተካከለው ዘንድ በማን መሰላችሁኝ? ይላል ቅዱሱ። ኢሳ 4025»
  
ማኅበረ ቅዱሳን ማለት እንደነዚህ ዓይነት ተረቶችና ክህደቶች እንዳይነኩ ለእውነት ሁሉ ጠላት ለሆነው ለሰይጣን ጥብቅና ቆሞ የሚከራከር ማኅበር ነው። መንፈሳዊ ኮሌጆችና ዩኒቨርሲቲዎች የእውቀትና የማስተዋል ተቋማት እንደመሆናቸው መጠን ጥያቄ የሚጠይቁና ከእግዚአብሔር ቃል የተገናዘበ አሳማኝ ምላሽ እንዲሰጣቸው የሚተጉትን በክህደትና በምንፍቅና እየወነጀለ መቆሚያና መቀመጫ የሚያሳጣ፤ ወይ ከእውቀቱ ወይ ከእውነቱ አንዱንም ያልያዘ ድርጅት በመሆኑ ነው።
ስለዚህ ፓትርያርክ ማትያስ ለመንፈሳዊ ኮሌጆች ጥያቄ ምላሽ የሚሰጥ ደብዳቤ ለመጻፍ የተገደዱት ከኮሌጆቹ ተማሪዎች ጥያቄ አንጻር ብቻ ሳይሆን ፓትርያርኩ ለሚያደርጉት ትግል የሊቃነ ጳጳሳቱ ድጋፍ አናሳ ሆኖ በመገኘቱ ቢያንስ የትግላቸው አጋር የተማረውን ክፍል ለመያዝ ከመፈለግ የተነሳ ይመስላል።
በዚህ አጋጣሚ የመንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪዎችና የቤተ ክርስቲያኒቱ ጉዳይ ግድ የሚለው ሁሉ ከፓትርያርኩ ጋር በመቆም የያዙትን ትግል ከግብ ለማድረስ በጸሎትና በሃሳብ እንዲያግዝ ለማሳሰብ እንወዳለን።
ደብዳቤዎቹን ለማንበብ ሊንኩን ከከፈቱ በኋላ ለማስፋትና በደንብ ለማንበብ ጽሁፉን ይጫኑት!
እዚህ ይጫኑ 1

እዚህ ይጫኑ 2

እዚህ ይጫኑ 3

እዚህ ይጫኑ 4