Thursday, March 29, 2012

«ክብሩን እንመልስ፤ እጃችንንም እንታጠብ!»

«ክብሬን ለሌላ አልሰጥም»
(by dejebirhan)        to read in PDF   (Click here)

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ድርሻ አላት። በቀደሙት ዘመናት ውስጥ ሃይማኖታዊ መንግሥት የሀገሪቱ አስተዳደር ሥርዓት ስለነበረ ቦታዋና ወሳኝነቷ አሌ ሊባል የማይችል እውነት ነው። ቤተክርስቲያኒቱ ያልፈቀደችው ሰው ዙፋን ላይ ሊወጣ አይታሰብም ነበር። በጉልበትም ይሁን በዘዴ አንዱ አንዱን አጥፍቶ ሥልጣን ላይ ቢወጣ እንኳን የቤተክርስቲያኒቱን እውቅና ለመጠየቅ መገደዱ አይቀርም። የንጉሠ ነገሥትነቱ ክብር እሷ ካላጸደቀችው የጸና ስለማይሆን ይህንኑ ለመስጠትና ለመፍቀድ ድርሻዋ ትልቅ ነው። በእርግጥም «እምነ መንግሥት የዐቢ ክህነት» እንደሚለው ቃሉ ቢያንሳት እንጂ ይህ ድርሻዋ የሚበዛባት አይደለም። ከተወሰነኑ ወቅቶች ማለትም ከወለተ ጌዴዎን ዮዲት 40 ዘመንና ከኢብን ኢብራሂም አልጋዚ (ግራኝ) 15 ዓመታት ወረራ ጊዜያት በስተቀር የቤተክርስቲያኒቱ ሥፍራ ላለፉት 1600 ዓመታት ከቤተመንግሥቱ የራቀ አልነበረም። በዚህም የተነሳ ቤተክህነቱ ከቤተመንግሥቱ አልራቀም ወይም ቤተመንግሥቱ ከቤተክህነቱ አልወጣም ማለት ይቻላል።
በነዚህ ዘመናት ሀገርን በማስከበር፣ በተለይም ዛሬ ኢትዮጵያ የምንላትን ሀገር ከመገንባትና ከመጠበቅ አንጻር፣ ፊደላትንና ስነ ጽሁፋትን በማስፋት፣ ቅርስን እንዲሁም ትውልዱን ከታሪክ፣ ታሪኩን ከሀገር ጋር በማስተሳሰር ረገድም ሚናዋ የጎላ ነው። ብዙ ብዙ ሊባልላት እንደሚቻል የሚታወቅ እውነታ ነው።
ከዚሁ ጋር በተነጻጻሪ ነገሥታቱ በዘመናቸው በሰሯቸው መልካምም ይሁን መጥፎ ስራቸው ድርሻዋ አብሮ የሚታይ መሆኑንም መካድ አይገባንም። ለምሳሌ አፄ ዘርዓ ያዕቆብ ደቂቀ እስጢፋኖስ የተባሉ ክፍሎችን አንድ በአንድ እየለቀሙ ጆሮ እየቆረጡና አፍንጫ እየፎነኑ ሲያሰቃይዋቸው መናፍቃንንና ጸረ ማርያሞችን ማስወገድ ነው በማለት ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ትብብሯን አሳይታለች። እነዚህን መናፍቃን አሰቃይቶ መግደል ተገቢ እንደነበር በማመንና በማሳመን በየተአምራት መጻሕፍቱና በየታሪክ ድርሳናቱ ጽፋ አቆይታለች። ዛሬም በነዚሁ ታሪክ የጸሎት ቡራኬ ይደርስባቸዋል።
ጉዳዩን አስቸጋሪ የሚያደርገው መናፍቃንንና ጸረ ማርያም የተባሉትን (ለዚያውም ሆነው ከተገኙ) እየለቀማችሁ አጥፏቸው የሚል አስተምህሮ አለ ወይ ብለን ብንጠይቅ የእውነቱን ጽዋ ለመጠጣት ካላስቸገረን በስተቀር በወንጌል አለሁ የሚል ማንም ቢኖር ይህንን በፍጹም ሊቀበል የሚችለው አይደለም።
«እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በሰማያት ላለ አባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ ጠላቶቻችሁን ውደዱ፥ የሚረግሙአችሁንም መርቁ፥ ለሚጠሉአችሁም መልካም አድርጉ፥ ስለሚያሳድዱአችሁም ጸልዩ፤ እርሱ በክፎዎችና በበጎዎች ላይ ፀሐይን ያወጣልና፥ በጻድቃንና በኃጢአተኞችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና» ማቴ 544
ብላ የምታስተምር ቤተክርስቲያን የነገሥታቱን የግድያ ተግባር ደግፋ ብቻ ሳይሆን አሞካሽታ ስታበቃ ግድያቸውን የጽድቅ ተግባር አድርጋ መጻፏ ወንጌል አልተሰበከም ወይም ሃይማኖቱ የቆመው ሠይፍ በታጠቀው ንጉሠ ነገሥት ብርታት ነው ለማለት እንደፍራለን።
መቼም እንደዚህ ዓይነት ጠጠር ያለ ግን እውነተኛ ጽሁፍ በአክራሪዎች የሚታየው ቤተክርስቲያንን ለማጥፋት እንደሚነገር እንጂ በሰራነው መልካም ነገር መሞገስን እንደምንሻው ሁሉ ባጠፋው ነገር ደግሞ ልናዝን እንደሚገባን ለማሰብ በማይችሉ ሰዎች ዘንድ ይሆናል። «በሽታችንን ደብቀን መድኃኒት እናገኛለን ማለት ዘበት ነው»
ምንም ይሁን ምንም ነገሥታቱ በፈጸሙት ግድያና ትውልድን ለቅሞ የማጥፋት ዘመቻ አብራ በተሰለፈችው ቤተክርስቲያናችን ላይ አመልከዋለሁ የምትለው ኢየሱስ ክርስቶስ «እሰይ አበጀሽ፣ ለእኔ ስትይ ልቅምቅም አድርገሽ ስለፈጀሻቸው ደስ ብሎኛል» የሚል የምስራች ይነገራታል የሚል ቢኖር እሱ ክርስቶስን የማያውቅ ሰው መሆን አለበት ብለን እውነቱን አስረግጠን እንናገራለን።
ምክንያቱም ለሰቀሉት ይቅርታ የጠየቀ፣ ለሚገድሉ ክብርንና ጸጋን ይሰጣል ተብሎ አይጠበቅምና ነው።
«ኢየሱስም፦ አባት ሆይ፥ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው አለ። ልብሱንም ተካፍለው ዕጣ ተጣጣሉበት» ሉቃ 2334
ስለዚህ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በመልካምነትዋና በጥሩ ስራዋ በሀገራችን ታሪክ ከፍ አድርገን እንደምናያት ሁሉ በመጥፎ ነገሯና ይህንን መጥፎ ነገሯንም እንደጀብድ የምትቆርበትን የሚያሳዝን ተአምራዊ ድርሰቷን አንብበን ልናፍርብ ይገባል። ወደድንም ጠላንም የእነዚያን የእግዚአብሔር ፍጡራን ደም ከሰማይ ይጮሃል! እግዚአብሔርም ደማቸውን ከእጃችን ይፈልጋል።
እስኪ ከእነ አባ እስጢፋኖስ ፍጅት በኋላ የሆንነው እንይ!

Wednesday, March 28, 2012

ፍጹም ከቅጣቱ!


ማን ይገኝ ነበረ?


(By dejebirhan)     to read in PDF (click here)
በከንቱ አትጥራኝ፤ ስሜን ባንተ ይክበር
ኢታምልክን ጠብቅ፣ ምልክት አታስቀር
ባልንጀራን ውደድ፤በሀሰት አትመስክር
እድሜህ እንዲረዝም፤ ወላጅህን አክብር
ገላህንም ቀድስ፣ክልክል ነው ማመንዘር
አድርግና ጠብቅ፣ የቆመውን አጥር
ያልሰማ ማን አለ? ኦሪት ስትናገር?
በከንቱ የጠራው በደለኛ ይሆናል፤ (ዘጸ ፳፣፯)
ከአምላኩ መጽሐፍ፤ ከርስቱ ይፋቃል፤ (ዘጸ ፴፪፣፴፫)
ቢሰግድና ቢወድቅ ለቀረጸው ምስል
ቢያሸው፤ ቢዳብሰው ሥሩ ቢንከባለል
የአምላኩ መልክ ሆኖ ከፊቱ ቢተከል፣
ኢታምልክን ሽሯል ትለዋለች ኦሪት
ሕጓን ትጠቅስና፣ ታወርዳለች ቅጣት
...................ከቶ ያየኝ የለም፤
አይቶኝም የሚቆም፣ (ዘጸ ፴፫፣፳)
ምስሌ ምንድነው፣ ከማን ጋር ልተያይ? (ኢሳ ፵፮፣፭)
ከቶ ማን አይቶኛል? ከደመናት በላይ፣ (ዘዳ ፴፫፣፳፮)
በምድር የተካኝ ፣እኔነቴን ወካይ፣
ከወዴት ተገኘ፣ሴትና ወንድ መሳይ? (ዘዳ ፬፣፲፮)

Monday, March 26, 2012

«ማኅበረ ቅዱሳን» ከፍተኛ የፖለቲካ ኪሳራ ደረሰበት

 ይህ ድንቅ ጽሁፍ በደጀብርሃን ሲገለጽ ለበጎች ነጻነት የተቆጣው እንስሳን  ያስታውሰናል ።
(የጽሁፍ ምንጭ፤http://dejeselaam-dejeselaam.blogspot.com)
እውን "ማኅበረ ቅዱሳን" ከመንበረ ፓትርያርክ፣ ከቅዱስ ሲኖዶስና ከጠቅላይ ቤተክህነት በላይ የሃይማኖት ጠባቂ እና ተቆርቋሪ ነውን?
ግርግር ለሌባ ይመቻል፤ "ማኅበረ ቅዱሳን" የዝቋላን እሳት ለማጥፋት ለአንድ ጀሪካን ውኃ 40 ብር ለሁለቱ ደግሞ 80 ብር ያስፈልገኛል ብሏል
በዋልድባ፣ በአሰቦትና በዝቋላ ገዳማት ጉዳይ የ"ማኅበረ ቅዱሳን" ዌብሳይቶችና ብሎጎች ለምን ተንጫጩ? ሌሎቹ ለምን እርጋታ ታየባቸው?
መንግሥት፣ ሃይማኖትና ቀጣዩ ልማታችን
"ማኅበረ ቅዱሳን" በቅርቡ ከገዳማት ሕይወት ጋር ተያይዞ በተነሳው ውዝግብ ከምንጊዜውም በላይ የፖለቲካ ኪሣራ የደረሰበት መሆኑን ልዩ ልዩ ምንጮች አረጋገጡ፡፡ ምንም እንኳን ሃይማኖታዊ ተፈጥሮ ባይኖረውም "ማኅበረ ቅዱሳን" የሃይማኖት ተቋም መስሎ በመንቀሳቀስ ብዙዎችን ቢያሳስትም፣ ዛሬ በፈጠረው የፖለቲካ ግጭት ከመንግሥትና ከሕግ ጋር ተፋጦ በመገኘቱ እውነተኛ ማንነቱ መጋለጡን የወቅቱ ሁኔታው ያስረዳል፡፡
ከአፈጣጠሩ ጀምሮ ከፖለቲካ አካሄድ ተላቆ የማያውቀው "ማቅ" ውስጥ ውስጡን ሲያተራምስ ከርሞ ዛሬ ሙሉ በሙሉ ራሱን በመግለጥ ፀረ ቤተክርስቲያንና ፀረ መንግሥት መሆኑን አሳይቷል፡፡ ይህ የሃይማኖት "ማኅበር" ነኝ ባይ ተቃዋሚ ድርጅት ቤተክርስቲያንን በእርስ በርስ ሁከት ሲያተራምስ ቆይቶ በአሁኑ ወቅት ቀይ መስመሩን አልፎ ከሕዝብና ከመንግሥት ጋር የሚያጋጨውን ድርጊት በመፈጸም ላይ ይገኛል ተብሏል፡፡
"ማኅበሩ" ከ40 ሺህ እስከ 80 ሺህ የሚሆኑ አባላት አሉኝ የሚል ሲሆን በመንግሥትም ሆነ በቤተክርስቲያን የአባላቱ ዝርዝር አይታወቅም፡፡ ይህ ኅቡዕ አደረጃጀቱም እጅግ አደገኛ፣ ለውንብድናም ለምለም ሁኔታን እንደሚፈጥር ልብ ይሏል፡፡ ስውር ኃይል እንደሚመራውም የማኅበሩ አመራር የሆነው ዳንኤል ክብረት እንዳጋለጠም የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው፡፡ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር የሚደረጉት የገንዘብ ዝውውሮቹ ቁጥጥር አይደረግባቸውም፡፡ ከዚህ የተነሳም አደገኛነቱን ማስተዋል ይቻላል፡፡
ቤተክርስቲያን ላወጣችው መመሪያ አይገዛም፡፡ በዚህም ምክንያት ተከታታይ መመሪያዎች ሲወጡበት ይታያል፡፡ በቤተክርስቲያን ስም የንግድ ፈቃድ ይወስዳል፡፡ ነገር ግን ለቤተክርስቲያንም ሆነ ለመንግሥት ተገቢውን ገቢ አያስገባም፡፡ ገቢዎቹንና ወጪዎቹን ቤተክርስቲያን በምታሳትማቸው ደረሰኞች እንዲመዘግብ ቢነገረውም ፈቃደኛ አልሆነም፡፡ ሀብትና ንብረቱን በነፃና ገለልተኛ ኦዲተር እንዲያስመረምር ቢታዘዝም በእምቢተኝነቱ ጸንቷል፡፡ በአጠቃላይ ሲገመገም፣ የ"ማኅበሩ" አደገኛነት ሊለካ የማይችል እጅግ አስጊ ነው፡፡ ጉዳዩ ፈር እንዲይዝ ከተለያዩ አካላት ለመንግሥትና ለጠቅላይ ቤተክህነት ጥቆማ ቢቀርብም በተለያዩ ምክንያቶች ችግሩ ከመባባስ በስተቀር መፍትሔ አልተበጀለትም፡፡ "ማኅበሩ"ም ባላሰለሰ ጥፋት ውስጥ ቀጠለበት እንጂ የመታረም ዕድል አላገኘበትም፡፡
ምንም እንኳን "ማቅ" መቶ በመቶ ለጥፋቱ ተጠያቂ ነው ባንልም፣ ዛሬ ቤተክርስቲያናችን ለገባችበት ቀውስና አስተዳደራዊ መዋቅሯ ወደ ሁለትና ስምንት ቦታ መከፋፈሏ የ"ማኅበሩ" የሃያ ዓመታት እንቅስቃሴ ውጤት ግንባር ቀደም ተጠቃሽ መሆኑ አሌ አይባልም፡፡ "ማኅበሩ" ካህናትንና ምዕመናንን በተሃድሶነትና በመናፍቅነት በመክሰስ እና በራሱ ሥልጣን ዱላ ሁሉ በማንሳት ብዙዎችን ከየአጥቢያው በማባረር የግፉአንንና የስደተኞችን ቁጥር አበራክቷል፡፡

እግዚአብሔር ለምን ሰው ኾኖ መገለጥ አስፈለገው?


ለአዳም ካሣ በመክፈልና የእግዚአብሔርን ትክክለኛ ፍትሕ በመጠበቅ ሞትን ለመሻር የተደረገ መገለጥ

       * * *
የተወለደ ከአዳም፣
መሬት ያልገዛ የለም፡፡
ግብሩን መገበር አቅቷቸው፣
ገና ብዙ ዕዳ አለባቸው፡፡[1]
 * * *
ለክርስቶስ በስብዕና መገለፅ ዋና ምክንያት ተደርጎ የሚወሰደው በአዳም መሳሳት የተነሳ በሰው ልጆች ላይ ያረፈውን የሞት ፍርድ በመሻር ለማስቀረት ሲኾን በሞት መሻርም የእግዚአበውሔር ትክክልኛ ፍርድ ሳይዛባ እንዲፈፀም ለማድረግ ነው፡፡ ምክንያቱም አዳምና ሔዋን በገነት በነበሩ ጊዜ እግዚአብሔር እንዳይበሉ ያስጠነቀቃቸውን ዕፀ በለስ በመብላት ትዕዛዙን በመሻራቸው ሞት የሚባል ዕዳ በሰው ልጆች ኹሉ እንደመጣባቸው በመጽሐፍ ቅዱስ የኦሪት ዘፍጥረት ታሪክ ተገልፆ ይገኛል፡፡ ምናልባት እዚህ ላይ ‹የተሳሳቱት አዳምና ሔዋን ለምን ልጆቻቸው የሞት ቅጣት ተቋዳሽ ይሆናሉ?› የሚል ጥያቄ ሊነሳ ይችላል፡፡
በመጽሐፍ ቅዱስ ገለፃ ከኾነ ግን አዳምና ሔዋን የተሳሳቱ የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ናቸው፤ኹሉም በዓለም ላይ በመዋለድ የተራባው የሰው ዘር ደግሞ ከእነሱ የመጣ ነው፡፡ ይህም የኾነው ስህተት ፈፅመው የሞት ፍርድ ከተላለፈባቸው በኋላ ስለኾነ ማንም ከእነሱ የተወለደ ዘር ኹሉ የእነሱን ሀብትና ማንነት ይወርሳል፡፡ ከእነሱ የተገኘው ሀብትም በስህተት ላይ የተመሠረተ የስብዕና ማንነት ሲኾን የእሱም መቋጫም ሞት ነው፡፡ ስለዚህ ልጆቻቸው ወይም ዘሮቻቸው በሙሉ በስህተት የመጣ የሞት ፍርድ ተካፋይ ናቸው፡፡ ያለበለዚያ በእነሱ ላይ የተፈረደውን የሞት ፍርድ ልጆቻቸው መውረስ የለባቸውም ከተባለ  የእነሱን የስብዕና ማንነትም ልጆቻቸው መውረስ የለባቸውም፡፡ እንዲሁም በአዳምና ሔዋን የተወከለው የሰው ዘር በሙሉ ነው እንጂ የሁለት ሰዎች የመሳሳት ጉዳይ አይደለም፡፡ ምክንያቱም አዳምና ሔዋን ልጆቻቸውን በአብራካቸው ውስጥ በመያዝ ወክለው ትዕዛዙንና ፍረዱን ተቀብለዋል፤ ፍርዱም የተላለፈው ለሰው ልጅ ኹሉ ነው፡፡ ልጆቻቸው የእነሱ ዝርዝር ማንነቶች ናቸው፡፡ ስለዚህ የሞት ፍርድ የተላለፈው በአዳምና በሔዋን ከእነ ልጅ ልጆቻቸው ነው፡፡

Sunday, March 25, 2012

አቡነ ሳሙኤል በቅ/ሥላሴ መንፈሳዊ ኰሌጅ ...

አቡነ ሳሙኤል ቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ውስጥ ሽምቅ ውጊያ መጀመራቸው ተሰማ


በጠቅላይ ቤተክህነት ግቢ ለጳጳሳት ማረፊያ በተሰራው ህንጻ ውስጥ ሳይሆን፣ ተምረው ባላለፉበት በቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ቅጥር ግቢ የሚኖሩት የልማት ኮሚሽን የበላይ ጠባቂ አቡነ ሳሙኤል ከማህበረ ቅዱሳን የተሀድሶ መናፍቃንን ዘመቻ ለመከላከል በሚል ከሰበሰበው ገንዘብ ላይ እንደተለቀቀላቸው በሚታመነው ገንዘብ አንዳንድ የኮሌጁን ተማሪዎች በማባበልና ከብጹእ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ጋር መልካም ግንኙነት አላቸው የሚባሉ ተማሪዎችን በመዋጋት በውስጣቸው ተዳፍኖ አልወጣላቸው ያለውን መፈንቅለ ፓትርያርክ እንደገና ለመሞከር ሽምቅ ውጊያ መጀመራቸው ተሰማ፡፡
አቡነ ሳሙኤል ከማህበሩ ጋር በመቀናጀት ለጀመሩት ሽምቅ ውጊያ አንዱ የቤት ስራቸው በኮሌጁ ውስጥ ከዚህ ቀደም በደጀሰላም ድረገጽ ላይ ወጥቶ የነበረውና ማህበረ ቅዱሳን ‹‹ተሀድሶ ናቸው ይባረሩልኝ›› ብሎ ያለባለቤትና አድራሻ የላከውንና በኮሌጁ አስተዳደር ውድቅ የተደረገውን ክስ እንደአዲስ ማንቀሳቀስና የተባሉትን ደቀመዛሙርት ከኮሌጁ ማስወጣት ነው፡፡ ከሰሞኑም ያው ስም አጥፊ ደብዳቤ እንደ ተለመደው ያለባለቤትና አድራሻ ተልኮ ለኮሌጁ አስተዳደር ከደረሰ በኋላ ፍሬከርስኪ ሆኖ በመገኘቱ ውድቅ ተደርጓል፡፡ ምክንያቱም ባለቤት የለውም አድራሻም የለውም፡፡

Thursday, March 22, 2012

አንድ ጥያቄ አለኝ!

 ሰላም ለእናንተ ይሁን
በብሉይ ዘመንና በአዲስ ኪዳን ዘመን ስላሉት ነብያት ልዩነት ላኩልኝ በአዲስ ኪዳን ያሉት ነብያት በበለጠ አገልግሎታቸው እንዴት መሆኑን እንዳለበት ላኩልኝ ተባረኩ! (ስሙን ያልገለጸ ጠያቂ)
ከደጀብርሃን መልስ፣
 በአዲስ ኪዳን ውስጥ ነቢይነት ጨርሶ የሚረሳና የማይሰራ ጸጋ ነው እንዴ?
ስለ ነብይ ምንነት፣ማንነትና አገልግሎት በዚህ በአዲስ ኪዳን ዘመን ብዙ እያከራከረ ይገኛል። አንዳንዶች አብያተ ክርስቲያናት እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ያሉት በአዲስ ኪዳን ስላለ ነብይነት ምንም ሲናገሩ አይሰማም። አዲስ ኪዳን ግን ብዙ ቦታ ላይ ከጸጋ ስጦታዎች አንዱ የነብይነት አገልግሎት እንደሆነ ጽፎ ይገኛል። ስለየትኛውና ስለምን ነብይነት አዲስ ኪዳን እየተናገረ እንደሆነ አንድም ሰው ትንፍሽ ሲል አይሰማም። ለምን?  የተጻፈውን መተንተን ወይም መካድ ወይም መናገር እየተገባ ዝምታ ለምን? ኢየሱስ ነብይ ነው ከሚል ጥቅል ሃሳብ ውጪ ስለጸጋ ስጦታው ምንነት ግን ምንም አለመባሉ ያሳዝናል። ሌሎች ደግሞ እኛ ለነብይነት የተላኩና የተመረጡ ሰዎች ያሉባቸው አብያተክርስቲያናት ነን ይላሉ። እንዴትና ለምን? ብለን እነዚህኞቹንም ብንጠይቅ አጥጋቢ መልስ ከሚሰጡን ይልቅ ለራሳቸው እንደሚመቻቸው አድርገው ይተነትናሉ። ስለአዲስ ኪዳኑ ነብይነት ጨርሶ የረሱና እንደራሳቸው ምርጫ የሚጠቀሙበት ክፍሎች ቢኖሩም ስለብሉይ ኪዳን ዘመን ነብይነት ግን ሁሉም ብዙ አይከራከሩም። አለመከራከራቸውም የሚገለጸው ሁሉንም የብሉይ ኪዳን ነብያት በጋራ ይቀበሏቸዋልና ነው። በሁሉም ዘንድ ማለት በሚቻልበት ደረጃ ሃሳቡና ትርጉሙ የጋራ ተቀባይነት አለው። ከሥነ መለኰት ምሁራንና ሚዛናዊ አስተምህሮ ካላቸው ሊቃውንት ያገኘነውን ትምህርትና መረጃ መሠረት አድርገን ስለነብይነትና የነቢያት እንዴትነት ጥቂት ለማለት እንፈልጋለን።
  ነቢይ ማለት ምን ማለት ነው?
የግሪኩ «ፕሮፌሚ» ቃል ሲሆን ትርጉሙም «አስቀድሞ መናገር» ማለት ነው። ይህም ትንቢቱ ከመፈጸሙ በፊት ትንቢቱ ለተነገረለት ሕዝብ የትንቢቱን ምንነትና የፍጻሜ ሂደት አስቀድሞ ማሳወቅ ወይም ማስተላለፍ ነው።


ብሉይ ኪዳን፣
 

ነብይነት ለምን አስፈለገ?
የነብይነት አገልግሎት የተፈለገው የመጀመሪያው ሰው አዳም ከእግዚአብሔር ጋር ያለው ግንኙነት ከተቋረጠ በኋላ ነው። እስከ ክርስቶስ መምጣት ድረስ ሰው ከእግዚአብሔር ጋር ያለው ግንኙነት የተቋረጠ ስለነበር እግዚአብሔር መልእክቱን «አስቀድሞ መናገር» ፕሮፌማ ሰው ስለፈለገ ለዚህ አገልግሎት ከሰው መካከል በመምረጥ ነው ነብይነት የተፈገለው።
መልእክቱ የሚተላለፍበት መንገድ፣
በራእይ፣ በህልም፤ በድምጽና በምልክት ሊሆን ይችላል።
«እርሱም፦ ቃሌን ስሙ በመካከላችሁ ነቢይ ቢኖር፥ እኔ እግዚአብሔር በራእይ እገለጥለታለሁ፥ ወይም በሕልም እናገረዋለሁ» ዘኁ 12፤6
«እግዚአብሔር ሳሙኤልን ጠራው እርሱም፦ እነሆኝ አለ»1ኛ ሳሙ3፣4
«እርሱም፦ በአንተ ዘንድ ሞገስ ካገኘሁ፥ የምትናገረኝም አንተ እንደ ሆንህ ምልክት አሳየኝ»መሳ 6፣17
ኢሳይያስ ራእይ አይቶ፣ ኤርምያስ ቃል ሰምቶ፣ሕዝቅኤልም ዳንኤልም ራእይ አይተው ነብይነታቸውን ፈጽመዋል። ሌሎቹም እንዲሁ!
እንግዲህ የብሉይ ኪዳን ነብያት ከእግዚአብሔር የተሰጣቸውን ሸክም ወደሕዝቡ በማድረስና የሕዝቡንም ጩኸት ወደእግዚአብሔር በማድረስ የነብይነት አገልግሎታቸውን መካከለኛ ሆነው ፈጽመዋል።
አዲስ ኪዳን፣

የተሰደዱ የሐዋሳ ምእመናን የደብረ ዘይትን በዓል...

(ደጀብርሃን ብሎግ ለሐዋሳ ምእመናን አድናቆቱንና አክብሮቱን ይገልጻል)
ከወንጌል፣ ከሠላምና ከልማት ውጪ የተለየ አጀንዳ እንደሌላቸው በድጋሚ አረጋገጡ

አቡነ ገብርኤል የተከፈለም ሆነ የተሰደደ ሕዝብ የለም ያሉት የሀዋሳ ምዕመናን የደብረ ዘይትን በዓል አስመልክቶ ታላቅ መንፈሳዊ ጉባዔ ማዘጋጀታቸውን የደረሰን መረጃ ያረጋግጣል፡፡ ይኸው ለሁለተኛ ጊዜ የተዘጋጀው ታላቅና ደማቅ መንፈሳዊ ጉባዔ በየዕለቱ በሺዎች የሚቆጠር ሕዝብ እንደተከታተለው ታውቋል፡፡

እንደወትሮው ሁሉ ገቢው የነጠፈባቸው አሥር የማይሞሉ ኪራይ ሰብሳቢ ነጋዴዎችና የማኅበረ ቅዱሳን አባላት ስድስቱን አጥቢያ ቤተክርስቲያናት በማሰተባበር ጉባዔውን ለማደናቀፍ እና ሕዝቡን ለመበተን አውደ ምሕረት ላይ የሐሰት ፕሮፓጋንዳ በመንዛት፣ ሲመቻቸው ደግሞ ዱርዬዎችን በመላክ፣ በሉ ሲላቸው ደግሞ ሕጋዊ በመምሰል በየፍትሕ እና ፀጥታ መሥሪያ ቤቱ በመዞር አስቁሙልን እያሉ ሲውተረተሩ ከርመዋል ተብሏል፡፡ ይሁን እንጂ ግፉአኑ እምነታቸውን በነፃነት የማራመድ ካላቸው ሕገ መንግሥታዊ መብት አንፃር መንግሥት ተረድቶላቸው ጉባዔውን ሊያኪያሂዱ መቻላቸው ታውቋል፡፡
 ከመጋቢት 7 እስከ መጋቢት 9/ 2004 ዓ.ም ለሦስት ቀናት በተካሄደው በዚህ ጉባዔ ተጋባዥ ሰባክያነ ወንጌል እና መዘምራን ተገኝተው ያገለገሉ ሲሆን፣ በጠላት ዲያብሎስ ሤራ ተዳክሞ የነበረው የወንጌል አገልግሎት እንደገና ትንሣኤ ያገኘበት ታላቅ የሐሴት ጉባዔ እንደሆነ ተገልጿል፡፡

Wednesday, March 21, 2012

አንድ ጥያቄ አለኝ!

 ትክክለኛ እድሜ የትኛው ነው?
[መንገሥ በጀመረ ጊዜ አካዝያስ የሀያ ሁለት ዓመት ጕልማሳ ነበረ በኢየሩሳሌምም አንድ ዓመት ነገሠ። እናቱም ጎቶልያ የተባለች የእስራኤል ንጉሥ የዘንበሪ ልጅ ነበረች] 2ኛ ነገ 8፡26

[አካዝያስም መንገሥ በጀመረ ጊዜ ዕድሜው አርባ ሁለት ዓመት ነበረ፥ በኢየሩሳሌምም አንድ ዓመት ነገሠ እናቱም ጎቶሊያ የተባለች የዘንበሪ ልጅ ነበረች] 2ኛ ዜና 22፣2 (በደጀብርሃን፣ የተጠየቀ)

በደጀብርሃን የተመለሰ፣
ይህ ጥያቄ ብዙ ጊዜ ሲቀርብ አይቻለሁ። ምናልባትም እናንተም አጋጥሟችሁ ይሆን ይሆናል። ከዚህም የተነሳ እዚህ ላይ ፖስት በማድረግ እኔ ከማውቀው የተለየ ምላሽ ካለ ለማየት ጠብቄ ነበር። እስካሁን ምላሽ የሚሰጥ ስላላገኘሁ እኔ ያገኘሁትን መረጃ በምላሽነት ላስቀምጥ ወደድሁ። ወደፊት የተሻለ ምላሽ የሚሰጥ ካለ እጠብቃለሁ።
በእብራይስጥ አኀዝ የሚጻፈው በፊደል (alphabet) ነው። በዚሁ መሠረት የአካዝያስ እድሜ በቀደሙት የሱርስትና የዐረቢያ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በሁሉም ቦታ 22 እድሜ እንደነበረው ተጽፎ ይገኛል። የሰባ ሊቃናት ትርጉም በተባሉት መጻሕፍትም ውስጥ 22 ዓመት ስለመሆኑ በዜና መዋእል ውስጥ ሳይቀር ተጽፎ ተገኝቷል። በአንዳንዶች ውስጥ ደግሞ 42 ዓመት እንደሆነ ተቀምጦ ይገኛል። ይህ የሚያሳየው ተርጓሚዎች ከአንዱ ቋንቋ ወደ ሌላ ቋንቋ ሲገለበጡ ያመጡት ክስተት መሆኑን ነው። ከላይ እንደተገለጸው የእብራይስጥ ቁጥር አኀዝ ሳይሆን ፊደል ስለሆነ 20 ለማለት כ የሚጻፍ ሲሆን 40 ለማለት ደግሞ מ ይጻፋል።
እነዚህ ፊደላትን አስማምቶ በቁጥር ካለማስቀመጥ የመጣ ሊሆን እንደሚችልና አካዝያስም ሲነግስ እድሜው ከአባቱ ከኢዮራም ኖሮ ከሞተበት እድሜ በሁለት ዓመት ሊበልጥ ስለማይችል (ኢዮራምም መንገሥ በጀመረ ጊዜ የሠላሳ ሁለት ዓመት ጕልማሳ ነበረ፥ በኢየሩሳሌምም ስምንት ዓመት ነገሠ 2ኛ ነገ 8፣17) በማለቱ የትርጉሙን ስህተት ማየት ይቻላል። የእብራይስጡን ב +כ =22 በማለት እንደማስቀመጥ 42=ב מ+ በማለት ስህተቱን መገንዘብ ይቻላል። ለተጨማሪ መረጃ ፤(ይህንን ይጫኑ)

አንድ ጥያቄ አለኝ!

በ2ኛ ሳሙ.11፤1 እንዲህም ሆነ በአመቱ መለወጫ-

-በ2ኛ ሳሙ.11፤1 እንድህም ሆነ በአመቱ መለወጫ ነገሥታት ወደ ሰልፍ በሚውጡበት ጊዘ ...ዳዊት ግን በእየሩሳሌም ቀርቶ ነበር።
ጥያቀ 1ኛ .የእሰራኤላዉያን የአመት መለወጫ የትኛው ወር ነው?ከ4ቱ ወቅቶች በየትኛው ውስጥ ይመደባል?እንደ እትዮጵያውያንሰ?
2ኛ.ነገሥታት ለሰልፍ የአመት መለወጫን ለምን መረጡ?
3ኛ.የእስራኤላውያን ግብርና ሁኔታስ ለስልፍ በሚውጡበት ጊዘ በምን ሁኔታ ላይ ይገኝ ነበር? ለግንዛቤ(4ቱ ወቅቶች winter,spring,summer,autumn)

አስተያዬት፦
ጥያቄ ካበዘሁባችሁ አስተዬታችሁን እፈልጋለሁ። እስካሁን እየጠየቅሁችሁ ላለው ጥያቄ አጥጋቢ መልስ እያገኘሁበት ሰላለ እ/ር አብዝቶ ይባርካችሁ።ቃሉን የሚገልጥ መንፈስ አብዝቶ ይጨምርላችሁ። Yonni Tibesso


(የደጀብርሃን መልስ)
የእብራውያን አዲስ አመት እንደኢትዮጵያውያን ወር አቆጣጠር በመስከረም ወር ላይ ነው። ወሩ በአብዛኛው በወሩ በ1ኛው ወይም በ2ኛው ቀን ላይ ይውላል።
በእብራይስጥም ሮሽ ሃሸና ראש השנהይባላል። «ሮሽ ሀሸና» ማለት የወሮች ሁሉ ራስ ማለት ነው። የኛው መስከረም ደግሞ «ትሽሪ» תִּשְׁרֵיይባላል። ከወቅቶች አቆጣጠር ደግሞ autumn ወይም በልግ የሚባለውን ይይዛል። ወርሃ ክረምት ከመግባቱ በፊት የሚመጣ ወር ነው።
እብራውያን አዲስ ዓመት አድርገው መስከረምን ያክብሩ እንጂ መስከረም የዓመቱ የመጀመሪያ ወር አይደለም። የዓመቱ የመጀመሪያ ወር ሚያዚያ ነው። ሚያዚያ የመጀመሪያ ወር ሊሆን የቻለው እስራኤላውያን ከግብጽ ባርነት ነጻ የወጡበት በዚህ ወር ስለሆነ ነው።
«ይህ ወር የወሮች መጀመሪያ ይሁናችሁ የዓመቱም መጀመሪያ ወር ይሁናችሁ» ዘጸ 12፣2
«በመጀመሪያው ወር በአሥራ አራተኛው ቀን ሲመሽ የእግዚአብሔር ፋሲካ ነው» ዘሌ 23፣5
እሱም ኒሳን נִיסָן ይባላል።
ኒሳን የመጀመሪያው ወር ስለመሆኑ መጽሐፍ ቅዱስ ራሱ ያረጋግጥልናል።

« አስቴር 3፥7
በንጉሡም በአርጤክስስ በአሥራ ሁለተኛው ዓመት ከመጀመሪያው ወር ከኒሳን ጀምሮ በየዕለቱና በየወሩ እስከ አሥራ ሁለተኛው ወር እስከ አዳር ድረስ በሐማ ፊት ፉር የተባለውን ዕጣ ይጥሉ ነበር»
ወደጥያቄህ ስንገባ ነገሥታቱ በሚያዚያ ወር መጀመሪያ ላይ ከጠላቶቻቸው ጋር ይዋጉ የነበረው፤ የነገረ መለኰት ምሁራን ይህንን ያስቀምጣሉ።
1/ ከግብጽ ባርነት ነጻ የወጡበት ወር በመሆኑ፣ በዚህ ወር ድል ሁሉ የእነሱ እንደሆነ ያምናሉ።
2/ የሀገራቸው ክረምት የሚያልቅበት ጊዜ በመሆኑ፣ከጭለማና ከአረንቋ ይልቅ ብርሃኑ ሲገልጥ ውጤታማ እንደሚሆኑ ስለሚያምኑ፤
3/ ጠላቶቻቸውም ይህንን ሰማይና ምድሩ የሚገፍበትን ጊዜ ጠብቀው ስለሚያጠቋቸው አስቀድሞ መምታት እንደሚገባቸው በማመን፣
ጥንት ጠላቶቻቸው ሲመክሩ እንዲህ ሲሉ ይጠጠቡባቸው ነበርና እስራኤላውያንም ሲጠበቡባቸው ይህንን ወር ይመርጡት ይሆናል።
«እንዳይበዙ፥ ሰልፍም በተነሳብን ጊዜ ጠላቶቻችንን አግዘው እንዳይወጉን ከምድሪቱም እንዳይወጡ፥ ኑ እንጠበብባቸው አለ» ዘጸ 1፣10
ስለዚህ እስራኤላውያንም በመጠበብ ይህንን ወቅት ይመርጡታል።

Tuesday, March 20, 2012

አንድ ጥያቄ አለኝ!

እ/ር ለሳኦል ያልመለሰበት ምክንያቱ ምንድነው?ማነው ትክክል?-
-1ኛ ሳሙ. 14፤ 37 በሚገኘው ክፍል እ/ር ለሳኦል ያልመለሰበት ዮናታን ከወለላው ስለ በላ ነው?የሳኦልስ ዉሳኔ ትክክል ነበር?1ኛ ሳሙ. 14፤24 ሳኦል ጾምን አወጀ ቁጥር 27 ላይ ዮናታን ስላልሰማ ከወለላው በላ አይኑም በራ ቁ.30 ህዝቡም ሁሉ ቢበሉ ይበረቱ ነበር ነገርግን ለሳኦል መልስ ማጣት ምክንያት ሆኖ የተገኘው ዮናታን ሆነ እጣ ስለወደቀበት ግን በህዝቡ ድምጽ ዮናታን ከመሞት ዳነ.
ትክክል ያደረገው ሳኦል ነው ወይስ ዮናታን ወይስ ህዝቡ? የተጠቀሱትን ጥቅስ በማስታረቅ ብታብራራው። እ/ር ይባርክህ።
yoni Tibesso

መልስ በደጀብርሃን


ይህ ጥያቄ ሰፊ ነገሮችን ወደመዳሰስ ይወስደናል። ስለሆነም ወደጥያቄህ ጭብጥ ከማምራታችን በፊት እስኪ ሕዝቡን፣ ሳኦልንና ዮናታንን ለየብቻቸው እንመልከታቸው።

ሕዝቡ፣

1/ ሕዝቡ ለእግዚአብሔር አልገዛም በማለቱ ታቦተ ጽዮን ተማርካ ነበር። በኋላም ተመልሳ አቢዳራ ቤት ተቀምጣ ሳለ ሕዝቡ ከጣዖት አምልኮ እንዲወጣ ሳሙኤል አስጠንቅቋቸዋል።

«ሳሙኤልም የእስራኤልን ቤት ሁሉ። በሙሉ ልባችሁ ወደ እግዚአብሔር ከተመለሳችሁ እንግዶችን አማልክትና አስታሮትን ከመካከላችሁ አርቁ፥ ልባችሁንም ወደ እግዚአብሔር አቅኑ፥ እርሱንም ብቻ አምልኩ ከፍልስጥኤማውያንም እጅ ያድናችኋል ብሎ ተናገራቸው» 1ኛ ሳሙ 7፣3
ሕዝቡም ያለ ንጉሥ በሳሙኤል ነብይነትና ፈራጅነት ይተዳደሩ ነበር።


2/ የእስራኤል ሕዝብ ነብይና ፈራጅ ሆኖ ሳሙኤል ለብዙ ዓመታት ቆይቷል። ሳሙኤል እርጅና እየተጫጫነው በመሄዱ በእርሱ ምትክ ልጆቹን ኢዮኤልና አብያን ሾሞላቸዋል። ይሁን እንጂ የነብዩ ሳሙኤል ልጆች ጉቦ እየተቀበሉ ፍርድን እያጣመሙ ሕዝቡን አስመረሩ እንጂ በአባታቸው መንገድ አልሄዱም።(1ኛ ሳሙ8፣2-3)
በዚህም የተነሳ ሕዝቡ ሳሙኤልን ንጉሥ በላያቸው ላይ እንዲሾምላቸው ግድ ብለው ያዙት።
«እነሆ፥ አንተ ሸምግለሃል፥ ልጆችህም በመንገድህ አይሄዱም አሁንም እንደ አሕዛብ ሁሉ የሚፈርድልን ንጉሥ አድርግልን አሉት» (ቁ፣5)

3/ እግዚአብሔርም ለሳሙኤል ተናገረው። እኔን አላከበሩኝም እንጂ የአንተን ነብይነት ስላልዘነጉ እንደጥያቄያቸው ሹምላቸው አለው።

«እግዚአብሔርም ሳሙኤልን አለው። በእነርሱ ላይ እንዳልነግሥ እኔን እንጂ አንተን አልናቁምና በሚሉህ ነገር ሁሉ የሕዝቡን ቃል ስማ» 1ኛ ሳሙ 8፣7
እንደሕዝቡ ጥያቄ ሳኦል በነሱ ላይ በሳሙኤል ተቀብቶ ነገሰ።

«ሳሙኤልም የዘይቱን ብርሌ ወስዶ በራሱ ላይ አፈሰሰው፥ ሳመውም፥ እንዲህም አለው፦ በርስቱ ላይ አለቃ ትሆን ዘንድ እግዚአብሔር ቀብቶሃል የእግዚአብሔርንም ሕዝብ ትገዛለህ፥ በዙሪያውም ካሉ ጠላቶቻቸው እጅ ታድናቸዋለህ» 1ኛ ሳሙ 10፣1

አንድ ጥያቄ አለኝ!

ስሙ ያልገለጸ ጠያቂ፣
እንደ ሮም፣ምዕራፍ 8 ሃሳብ ልጅነት ምንድን ነው?ስንት አይነት ልጅነትስ አለ?

የደጀብርሃን መልስ፣

 
ሰው ሁለት ልደት እንዳለው መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል። መጀመሪያ ከእናትና ከአባት የምንወለድበት ሥጋዊ ልደትና ቀጥሎም ከእግዚአብሔር የምንወለድበት መንፈሳዊ የእግዚአብሔር ልጅነት ናቸው።

«ከሥጋ የተወለደ ሥጋ ነው፥ ከመንፈስም የተወለደ መንፈስ ነው» ዮሐ 3፣6

ሥጋዊውን ልጅነት አይሁዳዊው ይሁን አረማዊው፤ ግሪካዊ ይሁን ሲሮፊኒቃዊ ሁሉም ይህን የሥጋ ልደት ያለ ልዩነት ያገኙታል። መንፈሳዊውን ልጅነት ግን በእምነት ብቻ የሚያገኙት ስጦታ ነው።
ሥጋዊው ልደት ምድራዊ ሲሆን መንፈሳዊው ልደት ሰማያዊ ነው። ሥጋዊውን ልደት የእግዚአብሔርን ሕልውና ቢያውቅም ባያውቅም፣ ቢያምንም ቢያምንም ሊያገኝ ይችላል። መንፈሳዊውን ልደት ግን በአንድያ ልጁ ያላመነ ማንም ቢሆን ሊያገኘው የሚችለው ልጅነት አይደለም።

«ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም አለው» ዮሐ 3፣3
ሰው ይህንን መንፈሳዊ ልጅነት እንዴት ሊያገኝ ይችላል?
እስራኤላውያን ከምድረ ግብጽ ከወጡ በኋላ የሖር ተራራን አልፈው ወደ ከነዓን ምድር ሲደርሱ እንዲህ ሲሉ በእግዚአብሔር ላይ አጉረመረሙ።

«ሕዝቡም በእግዚአብሔርና በሙሴ ላይ። በምድረ በዳ እንሞት ዘንድ ከግብፅ ለምን አወጣችሁን? እንጀራ የለም፥ ውኃ የለም ሰውነታችንም ይህን ቀላል እንጀራ ተጸየፈ ብለው ተናገሩ» ዘኁ 21፣5

ይህን ቀላል እንጀራ ሰውነታችን ተጸየፈ አሉ። ሳያቦኩና ሳይጋግሩ የሚበሉትን የሰማይ እንጀራ የሆነውን መና ተጸየፉት። ከሰማይ የወረደውን መና የጠሉ ሁሉ መጨረሻቸው ሞት ነውና በእነዚህ ሰዎች ላይ የሞት መርዝ ያለው ጠላት እባብ ገባባቸው።

Sunday, March 18, 2012

ፖፕ ሺኖዳ ሣልሳዊ


 (የደጀብርሃን ልዩ ዘገባ) ፖፕ ሺኖዳ ሳልሳዊ አረፉ! ፎቷቸው ላይ ሀገሬ በሰማይ ነው የሚሉ ይመስላሉ!

የግብጽ ኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ፓትርያርክ ሆነው ከ1971(እ ኤ አ) ጀምሮ በማገልገል ላይ የነበሩት ፖፕ ሺኖዳ ሳልሳዊ በፕሮስቴት ካንሰር፣ በጉበትና ሳንባ በሽታ ለዓመታት ሲሰቃዩ ቆይተው በተወለዱ በ88 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
ፖፕ ሲኖዳ በኮፕት ክርስቲያን ልጆቻቸው ዘንድ እጅግ በጣም ተወዳጅና ተፈቃሪ የነበሩ ሲሆን በበሽታ እየተሰቃዩ ከወንጌል አስተምህሮ ሳይለዩ፣ ቅዳሴ ሳያቋርጡ፣ በሐዋርያው ጉብኝቶቻቸው፣ አድባራትና ገዳማቶቻቸውን በማጽናናት ሌሊትና ቀን ደክመው አገልግሎታቸውን ለግብጽ ቤተክርስቲያን በትጋት ፈጽመው ያለፉ ታላቅ አባት ነበሩ። «ባባ ሹኑዳ» እያሉ የሚጠሯቸው ልጆቻቸው አስተምህሮአቸውን ለመስማት ሲሽቀዳደሙ፣እግሮቻቸውን፣ እጆቻቸውን ለመሳለም ሲሰለፉ ማየት እንግዳ ነገር አይደለም። ይህ ሁሉ ለክርስቶስ ቤተክርስቲያን የተሰለፉበትን አባታዊ ተልእኰ በመፈጸም እድሜአቸውን ሙሉ ባበረከቱት ትጋት የተነሳ የተሰጣቸው ትልቅ ክብር እንጂ ለውዳሴ ከንቱ እንዳልሆነ ሁላችንም የምንመሰክረው ሐቅ ነው። በአንድ ወቅት በቅዱስ ማርቆስ ቤተክርስቲያን ሥርዓተ ቅዳሴ ላይ ትምህርተ ወንጌል አስተምረው የተናገሩትና እሳቸው አልቅሰው ምእመናኑን ሁሉ ያስለቀሱት መቼም አይረሳም።
እንዲህ አሉ! «ልጆቼ ካስተማርኳችሁ ሁሉ ያልነገርኳችሁ ብዙ ነገር በልቤ ውስጥ አለ፣ እሱን ለእናንተ አልነግርም ፣ የልቤን ለሚያውቅ ለኢየሱስ ለክርስቶስ ትቼዋለሁ» ሲሉ ቁጭ ባሉበት ስቅስቅ ብለው አለቀሱ።ቤተክርስቲያኑን የሞላው ሕዝብ ተከትሎ አለቀሰ። ቅዳሴውን በቀጥታ ስርጭት ይከታተል የነበረው ሁሉ በየቤቱ አነባ። አዎ ፓትርያርኩ ብዙ ምስጢራቸውን፣ችግራቸውንና ስለቤተክርስቲያን ያላቸውን ጭንቀት የመፍትሄ ባለቤት ለሆነው ለክርስቶስ ይነግሩ ነበር። በዓለም አቀፍ ደረጃ ከሚያቀርቧቸው ሃሳቦቻቸው መካከል «ክርስቶስ የሰጠን አንዲቱን ቤተክርስቲያን ሆኖ ሳለ እኛ ተለያይተን እንዴት ክርስቶስን በእውነት እናመልካለን፣ ክርስቶስን ይህን እያየ ዝም የሚለው እስከመቼ ነው?» እያለ እለት እለት የሚያሳስባቸውን የቤተክርስቲያን ጉዳይ የሚያነሱ ባለትልቅ ራእይ አባት ነበሩ።

Saturday, March 17, 2012

ያኔ ሲኦልም ቢሆን የመረጡ ዛሬ ደግሞ ጳውሎስ ነን ይላሉ!

 
(ከደጀብርሃን) ዘመድኩን ከሐዋርያው ጳውሎስና ከሲላስ ጋር አይመሳሰልም!
«ለራስ ሲቆርሱ፣ አያሳንሱ» ማንም ወዳጁን ወይም ራሱን ሲክብና ሲያሞካሽ ይህ ቃል ይነገራል። ደጀ ሰላም የተባለው መካነ ጦማር ግን እሱ የጠላውን ሲያክፋፋና ስሙን ጥላሸት ሲቀባው ወዳጆቹን ደግሞ በማሞካሸት ጳውሎሳዊና ሲላሳዊ ዓይነት የወንጌል ተጋዳይ አድርጎ ሲያቀርብ እንኳን እንደሃይማኖት ሠራተኛነት፣ እንደሥጋውያን ሰዎች ይህንን ለማለት የሚያስችለውን አሳማኝ ማስረጃ ማቅረብ አለመቻሉ አስገራሚ ይሆንብናል።
ደጀ ሰላም እንዲህ ሲል ስለነዘመድኩን ጽፎልናል።
«ቅዱስ ጳውሎስና ሲላስ ከግንድ ተጠርቀው በታሰሩበት ወኅኒ ቤት የወኅኒውን መሠረት ያናወጠውን፣ ምድርን ያንቀጠቀጠውን፣ ወህኒ አዛዡንና ቤተ ሰዎቹን ካለማመን ወደ ማመን የመለሰውን መዝሙራቸውንና ትምህርታቸውን፤ ቅዱስ ጳውሎስ በእስራቱ ዓመታት የከተባቸውን መልእክታት፤ ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ በግዞቱ ሓላፊያትን፣ ማእከላውያንን፣ መፃዕያትን ያየበትን ራእዩን ያስታውሷል»
እንግዲህ ዘመድኩንን ከሲላስና ከጳውሎስ ጋር ለማመሳሰል የሚያስችለው መነሻ ምንድነው? ብለን ለመጠየቅ የምንገደድ ሲሆን ደጀ ሰላም የወደደውን እንኳን ጳውሎስና ሲላስ ከፈለገም ከሰማይ የወረደ መልአክ ከማድረግና የጠላውን ደግሞ ቤተክርስቲያን እንደተገኘች ውሻ እንደሚያሳድድ ስለምናውቅ እኛው ራሳችን አባባሉን «ለራስ ሰው ሲቆርሱ አያሳንሱ» ብለን ሀሰተኛነቱን ለማሳየት እንሞክራለን።

Thursday, March 15, 2012

ወሲብን መፈለግና ውጤቱን መጥላት አይቻልም!

ዝሙትና ማመንዘር፣ዘርን መዝጋትና ወሲብ እፈልጋለሁ! በስጋም ሆነ በነፍስ የሚታጨደውን ዋጋ ግን አልፈልግም?
«እንጀራ እበላለሁ፣ ውሃን  መጠጣት ግን  አልፈልግም»እንደማለት ነው።
ይሄ ነገር ይቻል ይሆን? እስካሁን እኔ አልሰማሁም፣ አላነበብኩምም። የቻለ ካለ ወይም  ወይም በዓለም አስደናቂ ታሪኮች መዝገብ ላይ ሰፍሮ አይቻለሁ የሚል ጽፎልን ሊያስደንቀን ይችላል። በእርግጥ ቢጽፍልንም አናምነውም። ምክንያቱም የሰው ሰውነት 66% የተገነባው በደም ነው። ደም ደግሞ ያለውሃ ደም ሳይሆን እንጨት ነው። ይደርቃል ማለት ነው። ስለዚህ «እንጀራ እበላለሁ፣ ውሃ ግን መጠጣት  አልፈልግም» የሚል ቢኖር ጤንነቱን ልንጠራጠር የግድ ይሆናል። እናንተስ ምን ትሉት ይሆን? ለመንደርደሪያ ተጠቀምኩኝ እንጂ  ስለእንጀራ መብላትና ውሃን ለመጠጣት አለመፈለግ ጉዳይ ሳይንሳዊ ትንተናን ለመስጠት የጽሁፌ ዓላማ አይደለም። ግን እንደዚያ ከማለት ተለይቶ የማይታይ  ሃሳብን በአንጻራዊነት ለመቃኘት በመፈለግ ነው። ልክ «እንጀራ እበላለሁ፣ ውሃ ግን መጠጣት አልፈልግም» እንደማለት ዓይነት የሚነገር የሰው ሃሳብ!! ይህን ሃሳብ ብዙ መንፈሳውያን ሰዎች ሲያስተምሩት አይሰማም። ምናልባትም በእነሱም ዘንድ አለመነሳቱ እነሱም ይህንኑ ሃሳብ በሕይወታቸው ውስጥ እየተለማመዱት ይሆናል። ታዲያ ምን እንበል? እግዚአብሔር እንድንበላ ፈቅዶ ውሃ መጠጣትን የሚከለክል እቅድ የለውም፣ አልነበረውም። በሰዎች ዘንድ እየሆነ ያለው መንፈሳዊ ጥፋት ይህንን የሚናገር ነው። እስኪ ወደጉዳዩ እንግባ።
1/ ዝሙትና ማመንዘር(Fornication & Adultery)
ማመንዘር  ሰው ከጋብቻ በፊት የሚፈጽሙት ተራክቦ  ነው። ይህ ደግሞ በእግዚአብሔር ዘንድ የተጠላ ሥራ ነው።ዝሙት ደግሞ በጋብቻው ውስጥ እያለ ከሌላ ሰው ጋር የሚፈጽመው ተግባር ነው።
ሮሜ 618
«ከዝሙት ሽሹ። ሰው የሚያደርገው ኃጢአት ሁሉ ከሥጋ ውጭ ነው፤ ዝሙትን የሚሠራ ግን በገዛ ሥጋው ላይ ኃጢአትን ይሠራል»