Showing posts with label ማብራሪያ. Show all posts
Showing posts with label ማብራሪያ. Show all posts

Saturday, April 20, 2024

ጸጋ ምንድነው? (What is grace?)

ጸጋ ምንድነው? (What is grace?) ክፍል ዐራት በባለፉት ክፍሎች የተመለከትነው በኢየሱስ አምነን ለዳንን ሰዎች ሁሉ የጸጋ ኃይል የሚያስፈልገን ለምንድነው? ለሚለው ጥያቄ ሦስት የኃጢአት በሮችን ለመዝጋት ነው በሚለው ሃሳብ ዙሪያ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማብራሪያ ስንሰጥ መቆየታችን ይታወሳል። በዚሁ መሠረት ከሦስቱ የኃጢአት በሮች መካከል 1/ሥጋ 2/ ዓለም እንዴት ሊፈትኑን እንደሚችሉና ከሁለቱም የሚመጡ ፈተናዎች እንዴት መዋጋት እንደሚገባን ተመልክተናል። ሥጋ ማለት የተሸከምነውና የራሱ መሻት ያለው በነፍስ ሕያውነት የሚንቀሳቀስ አካላችን ሲሆን ይህም የሚኖረው በዚህች ምድር ላይ እንደመሆኑ መጠን ዓለም ሥጋን በባርነት እንዳትገዛ በሚዛን ለመኖር የሚያስችለን ጸጋ የሚባል ጉልበት እንደሚያስፈልገን አይተናል። ዛሬ ደግሞ ሦስተኛው ክፍል የሆነውንና የክፋት ሁሉ የኃጢአት ሹም ስለሆነው ስለወደቀው መልአክ እንመለከታለን። ይህ ፍጥረት በትዕቢት፣ በተንኮልና በክፋት የተካነ ነው። ረጅም እድሜና ብዙ ልምድ ያለው የሰው ልጆች ሁሉ ጠላት ነው። የዚህ ዓለም ገዢ የተባለውም ዓለሙን ሁሉ በዐመፃና በኃጢአት ስለያዘው ነው። “ከእግዚአብሔር እንደ ሆንን ዓለምም በሞላው በክፉው እንደ ተያዘ እናውቃለን።”1ኛ ዮሐ 5፥19 ይህ ጥንተ ጠላታችን ወደጥልቁ ወርዶ ለዘለዓለም እስኪታሰር ድረስ ለሰው ልጆች ምንም ዓይነት ርኅራኄ የለውም። ራእይ 20:10 የወደቀው መልአክ እብሪትና ትዕቢትን ሞሪስ የተባለ የነገረ መጻሕፍት ተርጓሚ “ከዳመናዎች ከፍታ በላይ ዐርጋለሁ፥ በልዑልም እመሰላለሁ አልህ።” ኢሳ 14፥14 ያለውን ቃል ሲተረጉም የወደቀው መልአክ ምኞቱ የመላእክት ሁሉ አለቃ መሆን ብቻ ሳይሆን አምላካዊ ሥፍራንም መፈለጉን ያሳያል ሲል ይፈታዋል። የትኛውም ምኞትና አደገኛ የአምልኮ መሻት ሁሉ ምንጩ የዚህ የወደቀው መልአክ ውጤት ነው። የናቡከደነጾር የዱራ ሜዳ ሐውልት (ዳን3:1) የምናሴ የማመለኪያ አፀድ (2ኛ መዋዕል 33)፣ ዳጎን (መሣ16:23)፣ ቤል (ኤር 50:2) ወዘተ ሁሉም የወደቀው መልአክ ሥራዎች ናቸው። ይህንንም መዝሙረኛው እንዲህ ይላል። “የአሕዛብ አማልክት ሁሉ አጋንንት ናቸውና፤ እግዚአብሔር ግን ሰማያትን ሠራ።” መዝ 96፥5 ይህ የወደቀው መልአክ ለራሱ ብቻውን ወድቆ አልቀረም፣ የመጀመሪያዎቹንም የሰው ልጆች ጣለ እንጂ። የሚገርመው ነገር ሰዎቹ ሳይጠይቁት ራሱ ሰላማዊ ጠያቂ ሆኖ ነው የቀረበው። ከጠያቂነቱ ባሻገር እንዳይበሉ የተከለከሉት ተክል ስለመኖሩ እያወቀ፣ እንደማያውቅ ፍጥረት ሆኖ ነበር የቀረባቸው። "...ሴቲቱንም፦ በውኑ እግዚአብሔር ከገነት ዛፍ ሁሉ እንዳትበሉ አዝዞአልን? አላት።”ዘፍ 3፥1 ስለመከልከላቸው እውቀቱ ከሌለው ከገነት ዛፍ ሁሉ እንዳትበሉ አዝዞአልን? ብሎ ባልጠየቀም ነበር። በሚመልሱት መልስ ለማጥመድ ነው። ይህንን በቃል የማጥመድ ተንኮል በኢየሱስ ላይም ሞክሮት ነበር። “በሕዝቡም ፊት በቃሉ ሊያጠምዱት አልቻሉም በመልሱም እየተደነቁ ዝም አሉ።”ሉቃ 20፥26 ሔዋን እንዳትበሉ አዝዞአልን? ብሎ ለጠየቃት የማጥመጃ ቃል የሰጠችው መልስ እንዲህ የሚል ነበር። (ዘፍጥረት 3:2—3) ሴቲቱም ለእባቡ አለችው፦ በገነት ካለው ከዛፍ ፍሬ እንበላለን፤ ነገር ግን በገነት መካከል ካለው ከዛፉ ፍሬ፥ እግዚአብሔር አለ፦ እንዳትሞቱ ከእርሱ አትብሉ አትንኩትም። ሔዋን ሞትን ሞታ ስለማታውቅ ይሄ ጠላት በገዛ ቃሏ ምን እንደሚመስል ሊያሳያት ነው። (ዘፍጥረት 3፣3—4) እባብም ለሴቲቱ አላት፦ ሞትን አትሞቱም፤ ከእርስዋ በበላችሁ ቀን ዓይኖቻችሁ እንዲከፈቱ እንደ እግዚአብሔርም መልካምንና ክፉን የምታውቁ እንድትሆኑ እግዚአብሔር ስለሚያውቅ ነው እንጂ። ይህ ጠላት ከእግዚአብሔር ትእዛዝ ይልቅ የሱ ድምፅ የተሻለ ፍቺና ምስጢር እንዳለው እየተናገረ ሰዎቹን ወደቤተ ሙከራ እየወሰዳቸው እንዳለ እናያለን። በሚያምረውና በሚያስጎመጀው የጠላት ቤተ ሙከራ የገቡት እንግዶች አብሯቸው የነበረው ፍሬ የተለየ ውበት እንዳለው ያንጊዜ እንደአዲስ የተገለፀላቸው ይመስል ነበር። “ሴቲቱም ዛፉ ለመብላት ያማረ እንደ ሆነ፥ ለዓይንም እንደሚያስጎመጅ፥ ለጥበብም መልካም እንደ ሆነ አየች፤ ከፍሬውም ወሰደችና በላች፤ ለባልዋም ደግሞ ሰጠችው እርሱም ከእርስዋ ጋር በላ።” ዘፍ 3፥6 የወደቀው ጠላት አዲሶቹንም ፍጥረቶች ይዞ ወደምድር ተፈጠፈጠ። ይሄንን ሀተታ እዚህ ላይ ማንሳት ያስፈለገው ለመጽሐፍ ቅዱስ አንባቢያን ያልተነበበ ታሪክ ለመንገር ሳይሆን ይሄ ረጅም እድሜ፣ ልምድና ሁሉንም ክፋት የያዘ ፍጡር ዛሬም እየሰራ ያለ መሆኑን ለማስገንዘብ ነው። ዛሬም ያማልላል፣ ያስጎመጃል፣ ያስመኛል፣ ያስፈፅማል፣ ያጋድላል፣ ያፋጃል፣ ሁሉንም ክፋት በሰው ልጆች መሀል ያስፈፅማል። ስለዚህ ይሄንን ባለብዙ ልምድ ጠላት ለመዋጋት "ጸጋ" የተባለ መመከቻ የእምነት ጋሻ የግድ ልንታጠቅ ይገባል። ያለበለዚያ የመጫወቻው ሜዳ ከመሆን ልታመልጥ አትችልም። ይህ ጸጋ እንዴት እንደሚሰራ የጳውሎስ ተማሪ የነበረው ቲቶ በመልእክቱ እንዲህ እያለ ይነግረናል። “ይህም ጸጋ፥ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ እየጠበቅን፥ ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን እንድንኖር ያስተምረናል፤” ቲቶ 2፥12-13 ጸጋ በክርስቶስ ኢየሱስ አምነው የዳኑ ሰዎች የክርስቶስን መገለጥ እየጠበቁ፣ ራሳቸውን እየገዙ፣ በጽድቅና በቅድስና እየኖሩ ዘመኑን የሚሻገሩበት ሰማያዊ መሣሪያ ነው። ሐዋርያው ጳውሎስ በጻፋቸው መልእክታት በሙሉ የመዝጊያ ቃል አድርጎ ከሚጠቅሳቸው የጸሎት መደምዲያው ክፍል "ጸጋ" ከእናንተ ጋር ይሁን እያለ ይለምን የነበረው አለምክንያት አልነበረም። ሦስቱን የኃጢአት በሮች መዝጋት የሚቻለው ከእግዚአብሔር በሚሰጠን ጸጋ ብቻ ነው። ይህ ጸጋ እንዴት እንደሚገለጥና እንደሚሰራ እግዚአብሔር ቢፈቅድና ብንኖር በቀጣይ ፅሑፋችን ለማየት እንሞክራለን።

Tuesday, March 12, 2024

እግዚአብሔር ሰው በሠራው ቤተ መቅደስ አይኖርም!

ይህ አባባል እግዚአብሔር ሰው በሠራው መቅደስ ዛሬ ይኖራል ብለው ለሚያምኑ ሰዎች ጆሮን ጭው የሚያደርግ ቃል ነው። ነገር ግን እውነቱ እግዚአብሔር ዛሬ ሰው በሠራው መቅደስ አለመኖሩ ነው። ምክንያቱም እግዚአብሔር አዝዞት፣ ወርድና ቁመቱን ነግሮት የተሠራ ምድራዊ ቤተመቅደስ ዛሬ የለምና ነው። የቀደመችቱን የእስራኤል ቤተ መቅደስ ወርዱንና ቁመቱን፣ ስፋትና ርዝመቱን፣ ጽላቱንና ታቦቱን፣ ኤፉዱንና አልባሳተ ካህናቱን፣  መጋረጃዎቹንና ቀለማቱን፣ በአጠቃላይ የቤተ መቅደሱን ንዋያተ ቅድሳት የመረጠው እግዚአብሔር ራሱ ነበር እንጂ ምድራውያን ሰዎች አልነበሩም። ያቺ እግዚአብሔር ይገለጽባት የነበረችው ቤተ መቅደስ ዛሬ የለችም። በሙሴ የነበረው የመገናኛው ድንኳን እግዚአብሔር ራሱ ባዘዘው መሠረት የተሠራ ነው። (ዘጸ36:1) በሰሎሞን ዘመን ወደሕንጻ ቤተ መቅደስ ሲቀየር ለዳዊት ከወገቡ የሚወጣው ልጁ እንደሚሰራለት እግዚአብሔር ራሱ ተናግሮ ስለነበር እንጂ ሰሎሞን ከልቡ አንቅቶ የሰራው አልነበረም። (2ኛ ዜና 6:9) ይህ ሰሎሞን ያሠራው ቤተ መቅደስ የፈረሰበትን ታሪክ መጽሐፍ ቅዱሳችን ሲነግረን ሕዝቡ እንደአሳቡ፣ እንደፈቃዱና እንደትእዛዙ ባለመሄዱ የተነሳ የደረሰባቸውን መከራ እንዲህ ይተርክልናል።  “ሴዴቅያስም በነገሠ በዘጠኝኛው ዓመት በአሥረኛው ወር ከወሩም በአሥረኛው ቀን የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆርና ሠራዊቱ ሁሉ ወደ ኢየሩሳሌም መጥተው ከበቡአት፤ በዙሪያዋም ዕርድ ሠሩባት።  (2ኛ ነገሥት ምዕራፍ 25ን  ያንብቡ) ቤተ መቅደሱ በናቡከደነጾር ፈርሶ፣ ንዋያተ ቅድሳቱ ተዘርፎ፣ ሕዝቦ ለባርነት ተግዞ ከተወሰደ በኋላ ኢየሩሳሌም ዳዋ ወርሷት ነበር። “እናንተንም ከአሕዛብ መካከል እበትናችኋለሁ፥ ሰይፍንም አስመዝዝባችኋለሁ፤ ምድራችሁም የተፈታች ትሆናለች፥ ከተሞቻችሁም ባድማ ይሆናሉ።”   ዘሌ 26፥33 ያለው ቃል ተፈጽሟል። ሁለተኛው ቤተ መቅደስ ተመልሶ የተሠራው በታላቁ ሄሮድስ ሲሆን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለሞቱ በተናገረበት አንቀጽ የ2ኛውንም ቤተ መቅደስ መፍረስ ሲተነብይ እንዲህ ብሎ ነበር። “ኢየሱስም መልሶ፦ ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት፥ በሦስት ቀንም አነሣዋለሁ አላቸው።” ዮሐ 2፥19 አይሁዶችም ሲመልሱለት፣ "ወይቤልዎ ፡ አይሁድ ፡ በአርብዓ ፡ ወስድስቱ ፡ ዓመት ፡ ተሐንጸ ፡ ዝንቱ ፡ ቤተ ፡ መቅደስ ፡ ወአንተሰ ፡ በሠሉስ ፡ መዋዕል ፡ ታነሥኦ?" ይህ ቤተ መቅደስ ለማነጽ 46 ዓመት ፈጀ፣ አንተ በሦስት ቀን መልሰህ ትሰራዋለህን? ብለው ጠይቀውታል። ዋናው መልእክቱ ለሰውነቱ ቤተ መቅደስ ቢሆንም ከሕንጻው ቤተ መቅደስም መፍረስ ትንቢት ነበር። ይህ በሄሮድስ የታነጸው ሁለተኛው ቤተ መቅደስ 46 ዓመት የፈጀ ሲሆን ሰሎሞን ካሰራው ቤተ መቅደስ የተለየ ነበር። ምክንያቱም እግዚአብሔር ያዘዘው ቃል ሥርዓት የሚፈጸምበትና የሚከናወንበት ቤተ መቅደስ አልነበረም። ታቦቱ የለም። ታቦቱና ጽላቱ በሌለበት የእግዚአብሔር ክብር አይታይም ማለት ነው። የቤተመቅደሱ ሥርዓት የሌለበት፣ ታቦቱና ጽላቱ የማይገኝበት፣ እግዚአብሔርም በሁለቱ ኪሩብ መካከል በሚታየው የክብር ደመና መካከል  ተገልጾ በአሮን የክህነት ማዕረግ ተሹመዋል የተባሉትንና በወቅቱ ሊቀካህናት የነበሩት ሐናንና ቀያፋን የሚያናግርበት ቤተ መቅደስ አልነበረም። የእግዚአብሔር ድምጽ የሚሰሙበት ቤተ መቅደስ ሆኖ ቢሆን ኖሮ ስለኢየሱስ ድምጽ ይመጣላቸው ነበር። ከዚያ ይልቅ በዚህ በሄሮድስ ቤተ መቅደስ አደባባይ የሕዝቡ የኃጢአት ሥርየትና የደኅንነት መስዋዕት ሳይሆን ይቀርብ የነበረው የገንዘብ ለዋጮችና የርግብ ሻጮች ገበታ ነበር። ገንዘብ ለዋጮቹ ለበዓል ከተለያዩ ሀገራት የሚመጡትን ሰዎች ገንዘብ የሚመነዝሩ /money exchangers/ ሲሆኑ ርግብ ሻጮቹ ደግሞ ለበደል ሥርየት የሚሆኑ ርግቦችን ለሚመጡ ለእንግዶች የሚሸጡ የነጋዴዎች አደባባይ ሆኖ ነበር። ይህ ተግባር እግዚአብሔር አዝዞ በተሠራው በሰሎሞን ቤተ መቅደስ አደባባይ ተደርጎ ቢሆን ኖሮ ከሕዝቡ ተለይቶ ይጥፋ የሚለውን ቅጣት ያስከትል ነበር። ኢየሱስም፣ በዚህ ድርጊታቸው በተበሳጭቶ “ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች ተብሎ ተጽፎአል፥ እናንተ ግን የወንበዶች ዋሻ አደረጋችኋት አላቸው።” (ማቴ 21፥13) ይህ ቤተ መቅደስ እግዚአብሔር የማይከብርበት፣ ሥርዓተ መቅደሱ የማይፈጸምበት ስለነበረ መፍረስ ነበረበት። ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ቤተ መቅደሱ እንደሚፈርስ በተናገረው ቃል መሠረት ባረገ በዐርባኛው ዓመት፣ የሮማው ንጉሥ ጥጦስ በ70 ዓ/ ምህረት ገደማ ካፈረሰው በኋላ ላለፉት 2000 ዓመታት ቤተ መቅደስ የሚባል ታሪክ የለም። ከዚያ በኋላም  እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ስሩልኝ ያለው የተለየ ሕዝብና ሀገርም የለም። የቤተመቅደሱን ስፋትና ቁመት፣ የንዋያተ ቅድሳቱን ዝርዝርና ዓይነት የነገረው አንድም ሕዝብ ስለሌለ እግዚአብሔርን ለመገናኘት የምንሄድበት ቤተ መቅደስ በዓለም ላይ የትም ሀገር የለም። ልባቸው ያፈለቀውን፣ ኅሊናቸው ያሰበውን፣ ያላቸው የገንዘብ አቅም የፈቀደላቸውንና በሕንጻ አሠሪ ኮሚቴ በተፈቀደ ዲዛይን በተሠራ ሕንጻ ውስጥ እግዚአብሔርን ይገባበት ዘንድ በወይራና በቅብዐ ሜሮን ግንቡን ረጭተው እግዚአብሔር ሆይ ቀድሰነዋልና ና ግባበት እያሉ ሲጣሩ ውለው ቢያድሩ በዚያ በሰዎች ሃሳብ ሕንጻ ውስጥ እግዚአብሔር የለም። እግዚአብሔር እንደዚያ አድርገው እንዲሰሩለት ያዘዘው ሕዝብና ሀገር ስለሌለ፣ ሰዎች በልባቸው መሻት በሰሩት ቤተ መቅደስ ውስጥ በተሽሞነሞነ ጥሪና ልመና  የሚገባ አምላክ አለ ብለው የሚያስቡ ከሆነ ተሳስተዋል። የሚገባ ካለም ሌላ መንፈስ ይሆን ይሆናል እንጂ የሰማይ አምላክ አይደለም። ሐዋርያት 17፣ 24—25 "ዓለሙንና በእርሱ ያለውን ሁሉ የፈጠረ አምላክ እርሱ የሰማይና የምድር ጌታ ነውና እጅ በሠራው መቅደስ አይኖርም፤ እርሱም ሕይወትንና እስትንፋስን ሁሉንም ለሁሉ ይሰጣልና አንዳች እንደሚጎድለው በሰው እጅ አይገለገልም"። አሁን ቤተ መቅደሱ አንተ ነህ። ይሄን አንተ ቤተ መቅደስ የሆነው ሰውነትህን አቆሽሸህ ስታበቃ ሕንጻውን ቀድሼዋለሁ ብትል ስህተትም፣ ክህደትም ነው። ለዚህም ነው፣ የቆሸሹ፣ ከኃጢአት ያልተመለሱ፣ ለመመለስም ፍላጎት የሌላቸው ዐመጸኞች ቤተ መቅደስ በሚሉት ሕንጻ ውስጥ ተሰግስገው መደበኛ ኑሮአቸውን የሚኖሩት። እግዚአብሔር እኔ ውስጥ የለም፣ እዚያ እኔ በሠራሁት ሕንጻ ውስጥ አምላኬ ስላለ ጥዋትና ማታ እየሄድኩ ኃጢአቴን ይቅር እንዲለኝ እነግረዋለሁ ብትል ሕንጻ ውስጥ ቁጭ ብሎ የአንተን ኃጢአት የሚሰማ የሰማይ አምላክ ስለሌለ መጀመሪያ ራስህን ቀድስ። ኢየሱስ ከኦሪቱ ቤተ መቅደስ አገልግሎት ይልቅ ወደበለጠው የአዲስ ኪዳን አገልግሎት የመጣው አንተን አማኙን ለመቀደስ እንጂ በድንጋይ የተሠራ ቤት ለመቀደስ አይደለም። “ኢየሱስም መለሰ አለውም፦ የሚወደኝ ቢኖር ቃሌን ይጠብቃል፤ አባቴም ይወደዋል ወደ እርሱም እንመጣለን በእርሱም ዘንድ መኖሪያ እናደርጋለን።”   — ዮሐንስ 14፥23 እኔ ቅዱስ ነኝና እናንተም ቅዱሳን ሁኑ ስለተባለ ቤተ መቅደሱ አንተ ራስህ ነህ። ቃሉን ጠብቅ፣ አብ ይወድሃል። ወልድም ይወድሃል። አንተም መኖሪያው ትሆናለህ። አንተ መኖሪያው ካልሆንክ የእግዚአብሔር መኖሪያ የሆነ ሌላ ሕንጻ የለም። ሕንጻው አንተ ነህ። ይሄንን ሕንጻ የሠራው ኢየሱስ ነው። (በቀጣይ ፅሑፋችን "ሰው የእግዚአብሔር መኖሪያ ሕንጻ መሆን እንዴት ይችላል?") የሚለውን እንመለከታለን።

Wednesday, March 9, 2022

የቤተ ክርስቲያኒቱ ጠላቶች በጉያዋ ናቸው!

ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በሦስት መንገድ ችግር ውስጥ ናቸው። 1ኛ/ ወደው ባልተወለዱበት ዘር ትግሬ በመሆናቸው በኦሮሙማው ኃይል የሚታዩት እንደጠላት ነው። 2ኛ/ የራሳቸው የአመራርና የሥልጣን አጠቃቀም ድክመት የተነሳ የመፈራትና የመከበር አቅማቸው አናሳ መሆኑ ሌላኛው ችግር ነው። 3ኛ/ ሊቃነ ጳጳሳቱ በራሳቸው የግል ኑሮ ምቾትና ምንግዴለሽነት የተነሳ ቤተ ክርስቲያኒቱን ስለረሷት ከፓትርያርኩ ጋር መቆም አልቻሉም። ወደፊትም ቢሆን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አሁን ባለችበት መንገድ ከተጓዘች በውስጥና በውጪ ጠላቶቿ እየተገዘገዘች የመውደቋ ነገር የጊዜ ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር መፍረሷ አይቀርም። የዚህ ፅሁፍ አቅራቢ ሦስት ምክር ያቀርባል። 1/የቀድሞው ፓትርያርክ ከዚህ ዓለም ስላረፉ አሁን ያሉት ፓትርያርክ ከእድሜ: ከህመምና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች የተነሳ በቂ ውሳኔ እየተሰጠ ባለመሆኑ ችግሮቹ ተደራራቢ እየሆኑ በመገኘታቸው ለቤተክርስቲያኒቱ ፈጣን አመራር መስጠት የሚችል ሰው በራሳቸው በፓትርያርኩ አቅራቢነት እንደራሴ ቢሾም: 2/ አጠቃላይ የሰበካ ጉባኤ ስብሰባ በዓመት ሁለት ጊዜ መሆኑ ከድግስና ከተጋነነ ሪፖርት ውጪ ችግር ፈቺ ስላልሆነ የየአህጉረ ስብከቶቹን ችግር የሚያጠናና ለእንደራሴው ቢሮ የሚያቀርብ ቡድን ተሰይሞ በየችግሮቹ ዘርፍ ፈጣን ውሳኔ ቢሰጥባቸው: 3/ ለቤተ ክርስቲያኒቱ የሚቆረቆሩ በሙያ: በልምድና በችሎታ ከልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የአማካሪ ቦርድ ቢቋቋም የተሻለ ይሆናል። ይህ አሰራር በግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያና ተግባራዊ ሆኖ ብዙ ችግር መቃለል ተችሏል። ከዚህ ውጪ አሁን ባሉት ጳጳሳት የሚፈታ የቤተ ክርስቲያን ችግር የለን። አይኖርምም። ራሳቸው የቤተ ክርስቲያኒቱ ችግሮች ናቸው። ፈሪሃ እግዚአብሔር የነበራቸውና በጥብዓት ይታገሉ የነበሩት ሁሉ በዐረፍተ ዘመን ሁሉን ትተው ሄደዋል። አሁን ካሉት ጳጳስ ተብዬ ወመኔዎች አንዱ የሆነው ቅዱስ ፓትርያርኩ ለመናገር ያሰቡትን ሃሳብ እንዳያስተላልፉ የዱርዬ ስራውን እንዴት ይሰራ እንደነበር ይህ ቪዲዮ ያሳያልና ተመልክታችሁ ፍረዱ! በፕሮቶኮል ደረጃ ከፓትርያርኩ ፊት መነጋገሪያ ማይክ አይነሳም። ማፊያው ጀነራል ሦስት መነጋገሪያ ፓትርያርኩ እንዳይነጋገሩ ሲያሸሽና ለአዳነች አቤቤ ሲሰጥ ተመልከቱ።

Saturday, September 30, 2017

ማኅበረ ቅዱሳን ለቤተ ክርስቲያን ምንድነው?



ከማኅበረ ቅዱሳን መሥራቾች አንዱ እንደሆነ የሚናገረው የሜሪላንዱ ኤፍሬም እሸቴ  ስለማቅ ጥንስስ እንደተረከው ብላቴ ጦር ካምፕ ውስጥ ተቀፍቅፈን፤ ዝዋይ ላይ በመፈልፈልና አዲስ አበባ ላይ ኅልውና አግኝተን ሕይወት ዘራን ሲል ይተርክልናል። የኅልውናቸውን መስራቾችና ፈልፋዮች ማንነት ኤፍሬም ዘለግ አድርጎ ሲገልፅ በኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ በመንደር ምሥረታ ታሪክ ውስጥ ትልቅ ድርሻ የነበራቸው ሰዎች ሲሆኑ እነሱ ባሉበት የዳቦ ስም ወጥቶላቸው «ማኅበረ ቅዱሳን» እንደተባሉ «አደባባይ» በተሰኘው መካነ ጦማሩ በአንድ ፅሁፉ አውግቶናል። ለጠቅ አድርጎ: «ተማሪው በጋምቤላ፣ በመተከል፣ በወለጋ … ጎጆ ቤት ሲሠራ፣ ተፈናቃዩን ሲያቋቁም ቆይቶ ተመለሰ። በደህና ወጥቶ ለመመለስ ያልቀናውም ነበር። እነዚያ መንደር ሊመሠርቱ የወጡት ታላላቅ ወንድሞቻችን በየዛፉ ሥር፣ በየመንገዳቸው ጸሎተ ማርያም ማድረሳቸውን፣ ሲችሉም ተገናኝተው ቃለ እግዚአብሔር መስማታቸውን እንዳላስታጎሉ ሲናገሩ ሰምቻለሁ። እኛን ቃለ እግዚአብሔር ያስተማሩን የዚያ “መንደር መሥራች ትውልድ” አካላት የሆኑ ወንድሞች ናቸው። ወደ ዝዋይም የላኩን እነርሱ ናቸው። እኛ እና እነርሱ በአንድ ላይ ስንሆን ጊዜ በጋራ “ማቅ” ተባልን» ይለናል።
  በእርግጥ የዚያን ዘመን መንደር መሥራችና ትላልቅ ወንድሞች የተባሉት እነማን መሆናቸውን ባናውቅም ረጅም ህልም የነበራቸው: በእውቀትና በሥልጣን ትላልቅ ሰዎች እንደነበሩ መገመት ይቻላል። ለኤፍሬም ሆነ ለማቅ አባላት ትላልቅ ወንድሞች የተባሉት የማኅበሩ ፈጣሪዎችን ረጅም ዓላማ በግልጽ ያውቁት እንዳልነበር እርግጥ ቢሆንም አብዛኛው የማኅበሩን አባላት ያሰባሰባቸው ግን እምነታቸው ስለመሆኑ ከጥርጣሬ ላይ የሚወድቅ አይደለም። ብዙዎቹን የማኅበሩ ተከታይ ያደረጋቸው የቤተ ክርስቲያናቸው ቅናት ብቻ ነበር። ሲመሰረትም የወንድሞች ማኅበር «ማኅበረ ቅዱሳን» ከዚያ ከትንሹ ጅምር ተነስቶ ይህንን ያህል በመግዘፍ ሀገራዊ ማኅበርና የሲኖዶስ ጉባዔ የየዓመቱ የመነጋገሪያ አጀንዳ ይሆናል ብሎ የገመተ አይኖርም። ምናልባት ትላልቅ ወንድሞች የተባሉት እግር በእግር እየተከታተሉና እየኮተኮቱ ያሳደጉበትን  ኅቡእ አጀንዳ ራሳቸው ያውቁ እንደሆን እንጂ ዛሬም ድረስ ከጥቂቶች በስተቀር አብዛኛው የማኅበሩ አባላት እያገለገሉ ያሉት ቤተ ክርስቲያናቸውን እንደሆነ ያስባሉ።
 ነገር ግን ከአባላቱ መካከል በተለየ ተልእኮ ተመልምለው ረጅም አላማና ግቡን እንዲጨብጡ የተደረጉ አመራሮች በሂደት አልተፈጠሩም ማለት የማይቻልበት ምክንያት አንድ ተራ የፅዋ ማኅበር ከብላቴና ከዝዋይ ተነስቶና ግዝፈቱ እውን እየሆነ ሄዶ የጳጳሳቱን ጉባዔ ሲኖዶሱን ማነቃነቅና ለህልውናው ዘላቂነት እንዲቆሙ የማድረግ አቅም መጨበጥ መቻሉ ከበቂ በላይ አስረጂ ነው። ከዚህ ደረጃ ላይ  መድረሱ  እንዲደርስ የተፈለገበት ረጅም ህልምና ራእይ የለውም ማለት ጅልነት ነው። ኅልውናውን የሚያስጠብቅበትን የሕግ ማዕቀፍ በመጎናጸፍ፤ ማኅበሩን ለማሳደግ የሰው ኃይል በማደራጀት፤ የገንዘብ አቅሙን በማጎልበት፤ በአሰራር ውስጥ ጠልቆ በመግባት ራሱን የሚያስጠብቅበት ቅርጽና መዋቅር ቤተክርስቲያኒቱን መስሎና አኅሎ እየያዘ እንደመጣ እርምጃዎቹ ዋቢዎቻችን ናቸው። ዓላማና ግብ ሳይኖረው ኅልውናውን ማስጠበቅ እንደማያስፈልገው ይታወቃል።  እዚህ ይደርሳል ብለው ያልገመቱ ቢገኙም ሂደት ራሱ በሚፈጥረው ስኬት ከተነሳበት ሃሳብ ወጣ ባለ መልኩ ወደሚፈልግበት አዲስ ግብ ለመድረስ  ስትራቴጂ የለውም ማለት ሞኝነት ነው።  ታዲያ የት ሊደርስ ነው? ማኅበረ ቅዱሳን ተሰኝቶ እየደረጀ የሚሄደው?

የታላላቅ ወንድሞች ህልም ማኅበሩን ቅርፅና መልክ እየሰጡ ከትንሹ ትንሳዔው አንስቶ ያሳደጉት ስኬትን እያጎናፀፉ መድረስ ከሚፈልጉት ስውር ግብ ለማድረስ እንጂ በጽዋ ማኅበር ስር ታጥሮ እንዲቀር እንዳልነበር አሁን የደረሰበት ስኬት ያረጋግጥልናል። ዛሬ ከሲኖዶሱ ይልቅ ማኅበሩ ኃይል አለው። ከወዳጆቹ ጳጳሳት ተጠግቶ የበላቸውን እያከከ:ባልመሰላቸው ነገር ደግሞ እያስፈራራ ወይም በተአቅቦ አፋቸውን አስለጉሞ ማንም የማይደፍረውና የቤተ ክርስቲያኒቱ ያልታጠቀ ልዩ ኃይል መሆን ችሏል።
ማኅበረ ቅዱሳን በጥቂቶች አስተሳሰብ በእቅድ የተመሠረተ፤ በተራው አባል ግን በአጋጣሚ እግዚአብሔር ፈቅዶ የተቋቋመ ያህል የሚታሰብ ድርጅት መሆኑን ቢታሰብም እውነታው ግን ቤተ ክርስቲያንን ራሱ መውረስ ነው። መንግሥታዊ መንበሩንም አይመኝም ማለት የዋህነት ነው። አንዳንድ ነጥቦችን እያነሳን ማኅበሩን እንገምግም!

1/ማኅበረ ካኅናቱ ማቅን እንዴት ያየዋል?

ማኅበረ ቅዱሳን በማኅበረ ካህናቱ ዘንድ የሚታየው በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ ሽብልቅ የገባ ዘመን አመጣሽ የጭዋ ማኅበር: ሰላይ: ነጋዴ: ስም አጥፊና የኃጢአት ጸሐፊ ዐቃቤ መልአክ ተደርጎ ነው። ይህ የአደባባይ ምስጢር ነው።  ማኅበሩ በቀጥታ ከማኅበረ ካህናቱ ጋር መጋጨት የማይፈልገው ምእመናኑ በአጠቃላይ የተያዙት በካህናቱ አባትነት ስለሆነ. ከስልታዊ አዋጭነቱ አንፃር ጉዳት የሚያስከትልበት መሆኑን በመገምገም ሲሆን በሂደት ግን ጉልበት ለማግኘትና ማኅበረ ካህናቱን ለመናድ በህግ ማሻሻያ ሰበብ በደንብና በመመሪያ. ሽፋን በአባ እስጢፋኖስ የአዲስ አበባ ሀ/ ስብከት ዘመነ ጵጵስና ሞክሮ ሳይሳካለት ቀርቷል። ጊዜ ለመግዛት ካልሆነ በስተቀር ነገ ያንኑ  በሲኖዶስ አስፀድቆ ካህናቱን ለመበታተን ዳግመኛ አይመለስም ማለት የዋህነት ይሆናል። በጥቅሉ ማኅበረ ቅዱሳንና ካህናቱ ዓይንና ናጫ ናቸው።

2/ ማኅበረ ቅዱሳንና የሰንበት ት/ ቤት ወጣቶች:

ወጣቶች ከእድሜአቸው አንፃር ነገሮችን የሚመለከቱበት መነፅር በአንድ አቅጣጫ የተወሰነ ነው። በተለይ ደግሞ ከእምነት አንፃር በሚገባቸው  ስስ ስሜት በኩል በወጣት ቋንቋ የሚነግራቸውን ቶሎ ይቀበሉታል። አሁን ባለው ሁኔታ ነጠላን በመስቀልኛ አጣፍቶ የራሱን ስብከት ለነገራቸው ማቅ ያላቸው ፍቅር ልዩ ነው።  የማኅበሩ ያልታጠቀ ኃይል የሰንበት ት/ቤት ወጣት ነው። ይህንን ኃይል መያዝ ማለት በየአጥቢያው ለማኅበሩ ህልውናና ስርፀት አስፈላጊ በር ለማስከፈት ጠቃሚ መሆኑን አሳምሮ ያውቃል። በዚያ ላይ ለማኅበሩ ህልውና አደጋ የሚፈጥር የአጥቢያ አስተዳዳሪ ወይም ማኅበረ ካህናት የማስወገጂያ ጦር ሆኖ ያገለግላል። በተለይ ደግሞ ሙሰኛና ነውር የተገኘበት ከሆነ ግፋ በለው የሚል አዋጅ የሚታወጀው በሰንበት ት/ ቤት ወጣት በኩል ነው። ስለሆነም የወጣቶቹን የሰንበት ት/ቤት ኃይል መቆጣጠር ማለት አጥቢያውን መቆጣጠር ማለት ነው። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ደግሞ ለጥምቀት በዓል አስፋልት በመጥረግ: ቄጠማ በመጎዝጎዝና ምንጣፍ በማንጠፍ መንፈሳዊ ቅናት መሰል ቅንቅን የወረሳቸውን የበጎ ፈቃድ ወጣቶችን ማኅበሩ "የጥምቀት ተመላሾች ማኅበር" በሚል ስም አዋቅሯቸው በራሱ መረብ ስር አስገብቷቸዋል። ነገር መፈለጊያ ጥቅስ በማልበስ "አንዲት ሃይማኖት: አንዲት ጥምቀት" የሚል ቲሸርት አስለብሶም በአደባባይ ጠብ ያለሽ በዳቦ ሲያሰኝም ነበር።  በሌላ በኩልም በአባልነት የያዛቸው የየአጥቢያውን ሰንበት ተማሪዎች ብቻ ሳይሆን የዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን "ግቢ ጉባዔ" በሚል ሽፋን ለራሱ ዓላማ ስርፀት ከሚደክምባቸው ኃይሎች መካከል ተጠቃሾች ናቸው። ነገ በሚሰማሩበት የሥራና የሥልጣን ወንበር የማኅበሩ ወኪል የሚሆኑበትን መደላድል ዩኒቨርሲቲ ድረስ ገብቶ ይፈጥራል። ሌላው መረሳት የሌለበት ነገር ማኅበሩ የፖለቲካ ድርጅት የሆነ ያህል አሁን በሥልጣን ላይ ያለውን መንግሥት በሚጠሉ ፖለቲከኞች ሁሉ እንደ አንድ አስፈላጊ አካል ሆኖ የመቆጠሩ ጉዳይ
መዘንጋት የለበትም። ለምን? ብሎ መጠየም ተገቢ ጉዳይ ነው።
እነዚህ አብሮነት ያገናኛቸው የእምነት ስምምነት ውል መኖሩ ሳይሆን የሚያቀራርባቸው ፖለቲካዊ ስልት መሆኑን ለማወቅ ብዙም ምርምር አይጠይቅም።

ማኅበሩ ከላይ ከፍተኛው የሥልጣን አካል የሆነውን ሲኖዶሱን ይዟል። ከታች አብዛኛውን የገንዘብ ምንጭና የጉልበት ኃይል የሆነውን ወጣቱን አቅፏል። በመካከል ያለው የካህናቱ ኃይል የሚደመጥበትና ማኅበሩን የሚቋቋምበት አቅም ስለሌለው አንገቱን ደፍቶ ቀርቷል።

3// ማኅበረ ቅዱሳን ለቤተ ክርስቲያኒቱ ምዕመናን ያበረከተው ምንድነው?

ከላይ ለመጥቀስ እንደተሞከረው ማኅበረ ቅዱሳን በቤተ መቅደሱ የክህነት አገልግሎት ላይ የተሰማራ ባለመሆኑ ለምዕመናኑ ከካህናቱ በተሻለ የሚሰጠው አገልግሎት ይኖራል ተብሎ አይታሰብም። ቤተ ክርስቲያኒቱ ሳትሰጥ የቀረችውና ማኅበሩ ሊያሟላው የሚችለው አንዳችም ነገር የለም።
 በየአድባራቱ ወይም በየገዳማቱ ከምዕመናን አባላቱና ከሰንበት ትምህርት ቤቶች ወጣቶች ጋር ያለውን ቅርርብ በመጠቀም ዓላማና ግቡን ለማስረጽ በሚያደርገው ትግል ውስጥ ከካህናቱ በኩል ያለውን  ተቃውሞ ለመከላከል ሲል ለቤተ ክርስቲያን የሚቆረቆር በመምሰል ስም በማጥፋት፤ በአድማና በህውከት ከቦታቸው እንዲነሱ፤ እንዲጠሉ በማስደረግ ወይም ዝም ጭጭ ብለው፤ አንገታቸውን ደፍተው እንዲኖሩ በሚያደርገው ተግባሩ ያተረፈው ነገር ቢኖር የቤተ ክርስቲያኒቱ አባላት ወደሌሎች ቤተ እምነቶች መኮብለል ብቻ ነው። በሐረር፤ በድሬዳዋ፤ በደቡብ፤ በምዕራብና በምሥራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎች ያሉ የቤተ ክርስቲያኒቱ አባላት እንደጎርፍ ቤተ ክርስቲያኒቱን ትተው የኮበሉለት ማኅበረ ቅዱሳን በየቦታው በፈጠው ሁከትና ብጥብጥ የተነሳ ነው።

   በእርግጥ አንዳንዶች ማኅበረ ቅዱሳን ለቤተ ክርስቲያኒቱ አባላት ባሉበት መርጋት ትልቅ ሚና ተጫውቷል ቢሉም ተረትና እንቆቅልሽ ለማስተማር ካልሆነ በስተቀር ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንን የመተካት አንዳችም አቅም የሌለው ድርጅት መሆኑ ይታወቃል።
መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ከ1960 ዓ/ም በፊት ከ1% በታች የነበሩት የፕሮቴስታንት ቤተ እምነቶች እስከ 1984 ዓ/ም ድረስ 5.5% የደረሱ ሲሆን እስከ 1994 ዓ/ም ድረስ በዐሥር ዓመት ውስጥ ብቻ 10.2% ለመድረስ በቅተዋል። አሁን ባለው ስታስትስቲክ የፕሮቴስታንቱ ቁጥር ከሀገሪቱ ሕዝብ ውስጥ 18.6% ሲደርስ በተቃራኒው ደግሞ ከሀገሪቱ ሕዝብ 60% ገደማ የኦርቶዶክስ ቤተ እምነት ተከታይ የነበረው ቁጥር በአስደንጋጭ መጠን ወደ 43.5% ያሽቆለቆለው ባለፉት ዐሥርተ አመታት ውስጥ መሆኑ የሚያሳየን ነገር የማኅበረ ቅዱሳንን የስብከትና እንቅስቃሴ ምዕመናኑን ከመበተን ይልቅ በቤታቸው የማቆየት አቅም እንዳልነበረው አረጋጋጭ ነው። ውግዘትና ሁከት እንደውጤት ከተቆጠረ ማቅ በተገቢው ሰርቷል።   አንዳንዶች እንደሚያስወሩት ሰዎች ከነባር ቤተ እምነታቸው የኮበለሉት በስንዴና በአቡጀዲ ተገዝተው ሳይሆን መሬት ያለው እውነታ የሚነግረን ጊዜውን የሚመጥን አስተዳደርና ዘመኑን የሚዋጅ የወንጌል ቃል ትምህርት ስለሌለ ብቻ ነው። ለመሆኑ "ድንጋይ ዳቦ ነበረ" ከሚል ስብከት ያልተላቀቀው ማቅ ሁከትና ብጥብጥ ጨምሮበት ማን ባለበት ቆሞ ሕይወቱን በከንቱ ይገብራል?
ወደፕሮቴስታንቱ ጎራ ከኮበለለው 17% ገደማ የሚሆነው ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የወጣ እንጂ በዳንጎቴ ፋብሪካ የተመረተ የሰው ሲሚንቶ አይደለም። ማቅ እንኳን ከሌላ ቤተ እምነት ሰብኮና አሳምኖ ሊያመጣ ይቅርና ያሉት ተረጋግተው እንዳይኖሩ ሲሰራ የቆየ መሆኑ አይታበልም። የማኅበረ ቅዱሳን የተረትና እንቆቅልሽ አስተምህሮ ማንንም ሰብኮ መመለስ አይችልም።  ለጠያቂ ትውልድ የሚመጥን መልስ ሳይኖር ስመ ተሐድሶን መለጠፍና የስንዴ ሃይማኖት በማለት ማጣጣል ኩብለላውን ማስቆም አይቻልም። "አንድ ሳር ቢመዘዝ"  በሚል የሞኝ ተረት እያቅራሩ መኮፈስ የትም አያደርስም። ኢየሱስ ክርስቶስ ሥግው ቃል የሆነበት ምስጢር አንድ ሰው ፍለጋ ነው። ማቅና ደጋፊ ጳጳሳቱ ከአፋቸው የማይጠፋው ነገር በሰው ቁጥር መመካታቸው ቢሆንም ሳሩ ተመዞ ተመዞ እያለቀ መሆኑን አላቆመም።  ማኅበረ ቅዱሳን ኖሮ ቤተ ክርስቲያን ከተጠቀመችው ይልቅ ማኅበሩ በየቦታው በሚፈጥረው ሁከትና ግርግር የተጎዳችበት ይልቃል።
4// ማኅበረ ቅዱሳን ለቤተ ክርስቲያኒቱ ያበረከተው አገልግሎት እውነት እንደሚወራው ነው?

ሲጀመር ጀምሮ ማኅበረ ቅዱሳን የካዝና ቋቱንና ኪሱን ለቤተ ክርስቲያኒቱ አያሳይም። በሞዴላ ሞዴል ተጠቀም! ሂሳብህን አስመርምር! በምትሰራው ነገር ሁሉ የቤተ ክርስቲያኒቱን ፈቃድ ጠይቅ! መባሉ በቤተ ክርስቲያኒቱ ሥር የመሆኑ ማረጋገጫ  ካልሆነ በስተቀር ሀብትና ንብረቱን ስለመውረስ የሚያውጅ ድርጊት አልነበረም።  ቀደም ሲል ከእነአባ ሠረቀ ብርሃን ጋር ያጋጫቸው ይኸው ዘራፍ ባይነቱና ዘራፊነቱ ነበር።  ማኅበሩ የትኛውንም የቤተ ክርስቲያኒቱን ቁጥጥር መቀበል አይፈልግም። ለምን?

   ማኅበሩ ፈቃደኛ አለመሆኑ የሚያመለክተው ቢኖር አንድም ራሱ ብቻ አዋቂ ስለሆነ የቤተ ክርስቲያኒቱን አሠራር ይንቃል፤ አለያም ምን እየሰራ እንዳለ እንዲታወቅበት አይፈልግም። ስለዚህ ማኅበረ ቅዱሳን ለቤተ ክርስቲያን  አበረከትኩት የሚለው አገልግሎት የስም፤ የዝናና ራሱን በማሳደግ የሚጠቅምበት ስልታዊ እንቅስቃሴ ከመሆን የዘለለ አልነበረም ማለት ነው።
ለምሳሌ ጣሊያን ኢትዮጵያን ከወረረች በኋላ በመንገድ ሥራ፤ በውሃ ቧንቧ ግንባታ፤ በመብራት ዝርጋታ ላይ ተሰማርታ ነበር። ኢጣሊያ ያንን ማድረጓ ወረራዋን ፍትሃዊ ሊያሰኘው እንደማይችለው ሁሉ ማኅበረ ቅዱሳን ፈጸምኳቸው የሚላቸው አንዳንድ እንቅስቃሴዎች  የማኅበሩን ኢፍትሃዊ እርምጃዎችን ፍትሃዊ ሊያሰኙት በጭራሽ አይችሉም። ስለዚህ ማኅበረ ቅዱሳን ተመስርቶ ከተከናወኑት ሥራዎች ይልቅ ቤተ ክርስቲያኒቱ በማኅበሩ የደረሰባት ወከባና ሁከት ዐሥር እጅ ይልቃል። ደግሞስ በ25 ዓመት ዓመት እድሜው «ጧፍና ሻማ ረዳሁ» ከሚል በስተቀር የጧፍና ሻማ ማምረቻ ገነባሁ ሲል አልሰማንም። እንዲያውም ይህንን መንግሥት ለማጃጃል ካለው ገንዘብ ቀንሶ ቦንድ ገዛበት ሲባል ነበር።  በተዘዋዋሪ መንገድ ትመረመራለህ ከምትለው ቤተ ክርስቲያን ያለውን ገንዘብ የመደበቅ ባንዳነት ነው ። ለአብነት ት/ቤቶችና ለመምህራን ሠራሁ የሚለውም ቢሆን በአካፋ ከዛቀው በማንኪያ እያካፈለ ላለመሆኑ ቤተ ክርስቲያኒቱ ባደረገችው ምርመራ አልመሰከረችለትም።   በአጠቃላይ ማቅ በመኖሩ ቤተ ክርስቲያን ከኪሳራ በቀር ያተረፈችው ነገር የለም።

5/ከማኅበረ ቅዱሳን ጥፋት ዋነኛ ተጠያቂዎቹ ደጋፊ ጳጳሳቱ ናቸው!

በማኅበሩ ሁሉን አቀፍ ጥፋት ዋነኛ ባለእዳዎች ደጋፊ ጳጳሳቱ ናቸው። ይልቁንም የአማራ ጳጳሳት: በይበልጥም ሸዌ ጳጳሳት ግንባር ቀደሞቹ ናቸው። በቅርቡ ባየሁት አንድ የፌስቡክ ገጽ ላይ አባ ቀውስጦስ የአዞ እንባ ሲያፈሱ ነበር።  ማኅበሩ ከሌለ እኛ የለንም የሚሉና ቤተክርስቲያኒቱን መንፈስ ቅዱስ ሳይሆን ማኅበሩ የሚጠብቃት አድርገው የደመደሙ አስመሳይ ጳጳስ ናቸው። ብዙዎቹ ጳጳሳት በዐውደ ምሕረት ስለቅድስና ይስበኩ እንጂ ቀርቦ ገመናቸውን ለመረመረ የሚሰቀጥጥ ነገር ይሰማል። ይህንን ገመና ለመሸፈን ለማኅበሩ "ተናገር በከንፈሬ ተቀመጥ በወንበሬ" ብለው እሱ እነሱን አስቀምጦ ሀገረ ስብከታቸውን ያስተዳድርላቸዋል። ከዚያም በላይ ወደ ቅዱስ ሲኖዶስ አጀንዳ አስቀርጾ ለሚያስገባ ማኅበር ጥብቅና የሚቆሙ: የራሳቸው ኅልውና ለማኅበሩ አሳልፈው የሰጡ ጳጳሳት ለቤተ ክርስቲያን መዳከም ተጠያቂዎች ናቸው። ፓትርያርኩን በህገ ቤተ ክርስቲያን ተጣሰ ሽፋን እጅ ከወርች አስረው አላሰራ እያሉ ያሉት ሞቴን ከማኅበሩ በፊት ያድርገው የሚሉ የክርስቶስን ሞት በማኅበሩ ጉልበት የተኩ
ጳጳሳት ናቸው። እነዚህ ሥጋውያንእንጂ መንፈሳውያን አይደሉም። ቤተ ክርስቲያን በማኅበረ ቅዱሳን ነው ተጠብቃ ያለችው ከማለት ሌላ ሞት አለ?
ከዚያም ባሻገር ጵጵስና ማዕርግ እንጂ ከኃጢአት የመንጻት የመጨረሻ ማረጋገጫ አይደለም።  በሚሊዮኖች ብር የሚገመት ቪላ የሚገነቡ፤  ከደሃይቱ ቤተ ክርስቲያን በሚወጣ ገንዘብ እንደውሃ በሚፈስ መኪና የሚሄዱት: ገንዘባቸው ባንክን ማጨናነቁ በሚነገርበት ሁኔታ ዓለም በቃኝ ብለዋል ብሎ ስለብቃት በመናገር ማንንም ማታለል አይቻልም። እንኳን በፈጣሪ ፊት በካህናቱ ዓይን ብዙው ገመና እየታወቀ በብፅእና ማዕርግ ተቀብሎ መኖሩ  የራስ ገመና ለማን ይነገራል? ተብሎ እንጂ የተከደነ: ያልተገለጠ: የተሰወረ : ያልታወቀ ኖሮ አይደለም። የዘር ቆጠራውና የወንዜ ልጅ ዜማው የሚገነው በነዚሁ በጳጳሳቱ ላይ ነው። ዘመድ ከመቅጠርና የዓይኑ ቀለም ያላማራቸውን ሰው ከማባረር ባሻገር ለህዝባቸው አገልግሎት የሚውል  ጤና ጣቢያ: የውሃ ቧንቧና ለልጆቻቸው ት/ቤት ሰርተዋል ተብሎ ዜና በማይነገርበት የልማት ዘመን ለከንቱ ማኅበር መቆም ለኦርቶዶክስ የቆሙ ያህል ከማሰብ የበለጠ ከንቱነት ሊኖር አይችልም።
ስለዚህ ማኅበረ ቅዱሳንን በማወቅም ይሁን ባለማወቅ በማሳደግ፤ በማግነን አሁን ላለበት ደረጃ በማድረስ በኩል ጳጳሳቱ ኃላፊነት አለባቸው። የትውልድም፤ የታሪክም ተጠያቂነት እንዲሁም በሆነውና በሚሆነው ነገር ሁሉ በእግአብሔር ፊት ባለእዳዎች ናቸው።
ጳጳሳቱ በተቀመጡበት የቤተ ክርስቲያን አመራር ወንበር ላይ መንፈሳዊ ይሁን ቁሳዊ ልማት የማምጣት፤ ሕዝቡን ወደ እድገትና ራስን ወደመቻል የሥራ አቅም የማሳደግ ኃላፊነት የተጣለባቸው ቢሆንም ይህንን ሲያደርጉ አይታዩም። ከዚህ ይልቅ በማኅበረ ቅዱሳን ባላ እየተደገፉ ስሙን ጳጳሳቱ ተሸክመው ሥራውን ለማኅበሩ በመስጠት ቤተ ክርስቲያኒቱ ከነበረችበት ፈቀቅ እንዳትል አድርገዋታል። ቤተ ክርስቲያኒቱ ካሏት ሁለት ኮሌጆች በስተቀር በሀገረ ስብከት ደረጃ አንድም ጳጳስ ኮሌጅ ወይም ሴሚናሪ ት/ቤት ከፍቶ ማኅበረ ካህናቱን በሙያ: በክህሎት: በትምህርትና ዘመኑ ከደረሰበት የእውቀት መር አስተዳደር እያደረሱ እንዳልሆነ እናውቃለን።
 ቤተ ክርስቲያኒቱ ለሁለት የተከፈለችውም ይሁን ክፍፍሉ ባለበት ቦታ ሁሉ ውስጧ የሚታወከው በጳጳሳቱ በራሳቸው መሆኑን ያየናቸው ተሞክሮዎች ያስረዱናል። መንፈሳዊነታቸውን ያሸነፈ ሥጋዊ ጳጳስነት ባያይል ኖሮ ቤተ ክርስቲያን ለሁለት አትከፈልም ነበር። ተከፍላም አትቀርም ነበር።

6/ ማኅበረ ቅዱሳንና የቤተ ክርስቲያኒቱ አስተምህሮ አይገናኙም!

ቤተክርስቲያን በመዋቅር የሊቃውንት ጉባዔ እንዳላት ይታወቃል። ይሁን እንጂ ይህ የሊቃውንት ጉባዔ የቤተ ክርስቲያኒቱን በዘመኑ ያሉ አስተምህሮዎች እየመረመረ ስህተቶችን እየለየ፤ በሐዋርያት መሠረት ላይ ያሉትን እያጸና እውነታኛውንና የቀደምት አበውን ትምህርት ሕዝቡን መመገብ ሲገባው እስከመኖሩ በማይታወቅበት ደረጃ ላይ መገኘቱ ያሳዝናል። ዛሬ ላይ የሊቃውንት ጉባዔውን ጉባዔ በአጅ አዙር በመረከብ በመመርመር ለስደትና ለውግዘት ተሰልፎ የሚገኘው ይህ ማኅበረ ቅዱሳን የተባለው ያልተማረው ሊቃውንት ጉባዔ ነው። በዚህ ማኅበር የተነሳ እውነት ተደፍቆ ተቀብሯል። ሊቃውንት ተሰደዋል። እነ "ሆድ አምላኩና እነልጆቼን ላሳድግበት" ብቻ ወንበር ይዘው ቀርተዋል። ይሁን እንጂ ይህ ድርጊት መቀጠሉ መልስ ያልተገኘላቸውን ጥያቄዎች ማስቀረት አይችልም። የተለመደው ባህላዊ እምነት ሳይነካ ባለበት ተሸፍኖ እንዲቀመጥ ማድረጉ ኩብለላውን አያቆምም። ትውልዱ የሚነገረውን ብቻ እየሰማ የሚነዳ ሳይሆን የሚጠይቅም በመሆኑ ከፊት እየሄደ የሚመራ ሊቃውንት ጉባዔ ያስፈልግ ነበር። እንዳለመታደል ሆኖ ይህ አልሆነም። አሁን በሚታየው ሁኔታም መቼም ይሆናል ተብሎ አይጠበቅም። በዚህ ላይ የተረት አባትና የአፄው ዘውግ አንጋች ማኅበረ ቅዱሳንና ጳጳሳቱ እያሉ የወንጌል እውነት ተገልጦ፤ የአበው አስተምህሮ አደባባይ ላይ ይነገራል ማለት ዘበት ነው። ተረትና እንቆቅልሽ፤ ባህልና ወግ እንደእምነት ተቀላቅሎ መኖራቸው ያበቃል ተብሎ አይታሰብም። ተኀድሶ የባህሪው የሆነው እግዚአብሔር ነገሮችን በሆነ መንገድ ይለውጥ እንደሆነ ወደሰማይ ማንጋገጥ የወቅቱ አማራጭ ሆኗል። በአጠቃላይ ሲታይ ማኅበረ ቅዱሳን ሳይፈለግ የተገኘ፤ ሳይወደድ የቆየ፤ እየተጠላ ለመኖር የሚታገል በጥቂት አንጃ ጳጳሳት የሚደገፍና ለቤተ ክርስቲያኒቱ ሸክም የሆነ ድርጅት ነው።

"እርሱም። አሞጽ ሆይ፥ የምታየው ምንድር ነው? አለኝ። እኔም። የቃርሚያ ፍሬ የሞላበት ዕንቅብ ነው አልሁት። እግዚአብሔርም አለኝ። ፍጻሜ በሕዝቤ በእስራኤል ላይ መጥቶአል፤ ከእንግዲህ ወዲህ ደግሞ አላልፋቸውም። "
(ትንቢተ አሞጽ 8: 2)



Monday, May 15, 2017

የውግዘት ፖለቲካና የቤተ ክርስቲያናችን እጣ ፋንታ


( ክፍል አንድ ) # በቀሲስ መላኩ
መግቢያ
ባለፉት ሃያዎቹ ዓመታት፥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ
ቤተ ክርስቲያን በታሪኳ አይታ የማታውቃቸው ሦስት አበይት
ክስተቶች ታይተውባታል። የመጀመሪያው አንደኛው፥ ከፍተኛ
የሆነ የሕዝብ ፍልሰት ነው። በአዲስ አበባ ያሉት አባቶች
በግልጥ ያስቀመጡት ይፋዊ አኀዙ ሰባት ሚሊየን ይባል
እንጂ፥ ከአስር እስከ አስራ አምስት ሚሊየን የሚሆኑ የቤተ
ክርስቲያኒቱ አባላት ቤተ ክርስቲያኒቱን ትተው ወደ ሌሎች
ቤተ እምነቶችና ተቋሞች ሄደዋል። ሁለተኛው ዓቢይ
ክስተት ቤተ ክርስቲያኒቱ ለሦስት መከፈሏ ነው።
የመንግሥት ለውጥን ተከትሎ አራተኛው ፓትርያክ ብፁዕ
ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ከመንበራቸው ከተሰደዱበት
ጊዜ ጀምሮ ቤተ ክርስቲያኒቱ በስደት ያለው ቅዱስ
ሲኖዶስ፥ በአገር ቤት ያለው ቅዱስ ሲኖዶስ እና ገለለተኛ
በሚል ተከፍላለች። ሦስተኛው እና ቤተ ክርስቲያኒቱ
በታሪኳ አይታው በማታውቀው መንገድ የተከሰቱ ነገሮች
ቢኖሩ በተለይ አዲስ አበባ ባሉት አባቶች ዘንድ፥ «
ውግዘት» እንደ ታላቅ መሣሪያ መያዙ ነው።
በዚህ በያዝነው በ፳፩ኛው ክፍለ ዘመን ሰዎች ተቀራርበው
አሳባቸውን በሚካፈሉበት ዘመን፥ አብያተ ክርስቲያናት
ያለፈ ውግዘታቸውን በይቅርታና በመግባባት አስተካከለው፥
አንድ በሚያደርጋቸው ነገር ላይ ለመነጋገር እየጣሩ ነው።
በቅርቡ የሮም ፖፕና የእስክንድርያው ፓትርያርክ አንዳቸው
የአንዳቸውን ምእመን ዳግም እንዳያጠምቁ
መፈራረማቸው ይታወቃል። ሆኖም ግን ባለፉት 25
ዓመታት ውስጥ በአዲስ አበባ ባሉት አባቶች አማካይነት፥
የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በሺዎች የሚቆጠሩ
ምዕመናኖቿን እና አገልጋዮቿን አውግዛለች። ከአንድ
ቢሊየን አባላት በላይ ያላት የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን
ባለፉት አንድ መቶ አመታት ያወገዘቻቸውና በአዲስ አበባ
ያሉት አባቶች ያወገዙትን ስንመለከት በቍጥር የእኛው
በልጦ እናገኛለን። በአንድ በኩል የምዕመናኑ በሚሊየኖች
ወደ ሌሎች የእምነት ተቋማት መሄድ በሌላ በኵል ደግሞ
ጳጳሳትን ሳይቀር ምእመናንን ጨምሮ በመቶ ሺዎች
የሚቆጠሩ ምእመናንን ማውገዝ ከየት መጣ ለምንድነው
ይህ ክስተት በእኛ ዘመን የተደጋገመው? ከዚህ ውግዘት
በስተጀርባ ያሉት እነማን ናቸው? ተጠቃሚዎቹስ እነማን
ናቸው የሚለውን ለመመለስ በመጀመሪያ ስለውግዘት
በሚገባ ማወቅ ይኖርብናል።
ሀ. ውግዘት ምንድነው?
ውግዘት ቃሉ፥ ወገዘ ከሚለው ግሥ እንደሚገኝ እና
ፍቺውም መገዘት መለየት መካድ መርገም ማለት እንደሆነ
የሊቁ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ
ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ ይናገራል። ከዚህ ከቃሉ አንጻር
በምንመለከትበት ጊዜ፥ ቃሉ የሚያመለክተን ከዚህ በፊት
ከአንድ አካል ጋር አንድነት (communion) የነበረውን
እንዲለይ (excommuncate) ማድረግ ነው። ይህን
ግልጥ ለማድረግ ቃሉ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በእንዴት
ያለ መንገድ እንደተቀመጠ በማየት ትርጉሙን
እንመለከታለን።
1.ውግዘት እርግማን ነው።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለገላትያ ሰዎች ሲጽፍላቸው
«ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ፥
ከሰበክንላችሁ ወንጌል የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ፥
የተረገመ ይሁን። አስቀድመን እንዳልን እንዲሁ አሁን
ሁለተኛ እላለሁ፥ ከተቀበላችሁት የተለየውን ማንም
ቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን።» ይላቸዋል። ( ገላ ፩፥፰-
፱) ግእዙም « አትሙሰ መልአክ እምሰማይ ለእመ
መሀረክሙ ካልአ እምዘ መሀርናክሙ ውጉዘ ለይኩን።
በከመ እቤ ቀዳሚ ወይእዜኒ ካዕበ እብል ለእመቦ
ዘመሀረክሙ እምዘመሀርናክሙ ውጉዘ ለይኩን።»
አስተውሉ አማርኛው « የተረገመ ይሁን የሚለውን ግእዙ
የተወገዘ ይሁን ይለዋል። ይህ ውግዘት ወይም እርግማን
ምን ማለት እንደሆነ እንመልከት፥ አዲስ ኪዳን
ለመጀመሪያ ጊዜ የተጻፈበትን የግሪኩን ቃል
በምንመለከትበት ጊዜ፥ የተወገዘ ይሁን አናቴማ ኤስቶ
(ἀνάθεμα ἔστω ) ይለዋል። አናቴማ ቃሉ በብሉይ
ኪዳን « እርም»፥ «ለእሳት የተሰጠ» ማለት ነው። ለምሳሌ
ኢያሱ በኢያሪኮ የተገኘው ሁሉ እርም እንዲሆን ሲያዝ
አካን የተባለው ሰው « እርም ከሆነው ነገር ወሰደ»
ይለናል። ኢያሱ7፥1። እንዲህ ዓይነት ብዙ ጥቅሶች
በብሉይ ኪዳን እናገኛለን። በአዲስ ኪዳንም ይህንኑ ቃል
ሳይስት፥ አናቴማ ( ውግዘት እርግማን) ማለት
በእግዚአብሔር ፍርድ ውስጥ መውደቅ ማለት ነው።
ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ በገላያ መልእክቱ ላይ በሐዋርያት
ከተሰበከው የጸጋ ወንጌል የተለየ ወንጌልን የሚሰብክ
በዚህ የእግዚአብሔር ፍርድ ውስጥ እንደሚወድቅ ሲናገር
እናያለን።
2. ውግዘት ለሰይጣን አልፎ መሰጠት ነው።
አሁንም ወደ ቅዱስ ጳውሎስ መልእክት ስንመጣ
በ1ቆሮ5፥5 ላይ «መንፈሱ በጌታ በኢየሱስ ቀን ትድን
ዘንድ እንደዚህ ያለው ለሥጋው ጥፋት ለሰይጣን
እንዲሰጥ ፍርዴ ነው።» ሲል እናገኛለን። ቅዱስ ጳውሎስ
በዚህ ስፍራ ሐዋርያዊ ውግዘቱን ያሳረፈበት ሰው፥ በሥነ
ምግባር ውድቀት ውስጥ የተገኘ ማለትም የአባቱን ሚስት
ያገባ ሰው ነው። ሐዋርያው ለቆሮንቶስ ክርስቲያኖች
ሲናገር «ይህን ሥራ የሠራው ከመካከላችሁ ይወገድ። እኔ
ምንም እንኳ በሥጋ ከእናንተ ጋር ባልሆን፥ በመንፈስ
ከእናንተ ጋር ነኝ፥ ከእናንተም ጋር እንዳለሁ ሆኜ ይህን
እንደዚህ በሠራው ላይ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም
አሁን ፈርጄበታለሁ፤ እናንተና መንፈሴም ከጌታችን
ከኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል ጋር ተሰብስበን፥ መንፈሱ በጌታ
በኢየሱስ ቀን ትድን ዘንድ እንደዚህ ያለው ለሥጋው ጥፋት
ለሰይጣን እንዲሰጥ ፍርዴ ነው።» ይላል።
ይህ የቅዱስ ጳውሎስ ቃል ስለ ውግዘት ሦስት ዋና ዋና
ነገሮችን ያሳየናል። አንደኛ፥ ይህ ነገር በጉባኤ በጥንቃቄ
የሚታይ ነው። ጉባኤው የክርስቶስ ጌትነት የከበረበት
ጉባኤ መሆን አለበት። የሐዋርያው ሥልጣን የከበረበት
መሆን አለበት። « እናንተና መንፈሴም ከጌታችን ከኢየሱስ
ክርስቶስ ኃይል ጋር ተሰብስበን» በዚህ ዘመን ያለውን
በውግዘት ዙሪያ የሚከናወነው፥ ተመሳሳይነቱ ከፖለቲካ
አደባባዮች ጋር ነው። አንደኛ ከብሮ የሚታየው ክርስቶስ
ሳይሆን የሰዎች የተንኮለኛነት ችሎታ ነው። ለምሳሌ
ባለፉት ሃያ አምስት አመታት በኢትዮጵያ ያሉት አባቶች
በአመት ሁለት ጊዜ ሲሰበሰቡ፥ ከስብሰባቸው በፊት፥
የተቃውሞ ሰልፍ፥ የክስ ደብዳቤዎች፥ ዘመቻዎች፥
ይካሄድባቸዋል። ወደስብሰባው የሚሄዱ አባቶች
ስብሰባው ከመጀመሩ በፊት ተወጋዡ ማን
እንደሚሆን፥ውሳኔው ምን መሆን እንዳለበት ተነግሮአቸውና
ተጽእኖ ተደርጎባቸው ነው የሚገቡት። ነገሮችን ከምንም
ነገር ነጻ በሆነ መንገድ ለማየት የሚሞክሩ አባቶች፥
በስድብ በስም ማጥፋት ጥላሸት ይቀባባቸዋል። በዚህ
ምክንያት አንዳንዶች ዝምታን ሲመርጡ አንዳንዶች
ለተጽእኖው ያጎበድዳሉ። ቅዱስ ጳውሎስ « ከኢየሱስ
ክርስቶስ ኃይል ጋር ተሰብስበን» ሲል « ብርታታችንና
ጉልበታችን የሚሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ይሆናል» ማለቱ
ነው። እውነት የምትነግሠውና ሐሰት ሥፍራን የምታጣው፥
በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ኃይልና በመንፈስ ቅዱስ
መሪነት ስንጓዝ ነውና።
ቅዱስ ጳውሎስ ሌላ ታላቅ ነገር ያነሣል። ይኸውም
ውግዘት ምን ያህል አስፈሪ ነገር እንደሆነ የሚያመለክት
ነው። አንድ ሰው ከእድር ቢለይ፥ ሌላ እድር ውስጥ
ይገባል። ወይም በዘመናዊው ዓለም ሌላ ዘዴ ሊጠቀም
ይችላል። ( ላይፍ ኢንሹራንስ ሊገባ ይችላል።)ፋንታ
( ክፍል አንድ ) # በቀሲስ መላኩ
መግቢያ
ባለፉት ሃያዎቹ ዓመታት፥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ
ቤተ ክርስቲያን በታሪኳ አይታ የማታውቃቸው ሦስት አበይት
ክስተቶች ታይተውባታል። የመጀመሪያው አንደኛው፥ ከፍተኛ
የሆነ የሕዝብ ፍልሰት ነው። በአዲስ አበባ ያሉት አባቶች
በግልጥ ያስቀመጡት ይፋዊ አኀዙ ሰባት ሚሊየን ይባል
እንጂ፥ ከአስር እስከ አስራ አምስት ሚሊየን የሚሆኑ የቤተ
ክርስቲያኒቱ አባላት ቤተ ክርስቲያኒቱን ትተው ወደ ሌሎች
ቤተ እምነቶችና ተቋሞች ሄደዋል። ሁለተኛው ዓቢይ
ክስተት ቤተ ክርስቲያኒቱ ለሦስት መከፈሏ ነው።
የመንግሥት ለውጥን ተከትሎ አራተኛው ፓትርያክ ብፁዕ
ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ከመንበራቸው ከተሰደዱበት
ጊዜ ጀምሮ ቤተ ክርስቲያኒቱ በስደት ያለው ቅዱስ
ሲኖዶስ፥ በአገር ቤት ያለው ቅዱስ ሲኖዶስ እና ገለለተኛ
በሚል ተከፍላለች። ሦስተኛው እና ቤተ ክርስቲያኒቱ
በታሪኳ አይታው በማታውቀው መንገድ የተከሰቱ ነገሮች
ቢኖሩ በተለይ አዲስ አበባ ባሉት አባቶች ዘንድ፥ «
ውግዘት» እንደ ታላቅ መሣሪያ መያዙ ነው።
በዚህ በያዝነው በ፳፩ኛው ክፍለ ዘመን ሰዎች ተቀራርበው
አሳባቸውን በሚካፈሉበት ዘመን፥ አብያተ ክርስቲያናት
ያለፈ ውግዘታቸውን በይቅርታና በመግባባት አስተካከለው፥
አንድ በሚያደርጋቸው ነገር ላይ ለመነጋገር እየጣሩ ነው።
በቅርቡ የሮም ፖፕና የእስክንድርያው ፓትርያርክ አንዳቸው
የአንዳቸውን ምእመን ዳግም እንዳያጠምቁ
መፈራረማቸው ይታወቃል። ሆኖም ግን ባለፉት 25
ዓመታት ውስጥ በአዲስ አበባ ባሉት አባቶች አማካይነት፥
የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በሺዎች የሚቆጠሩ
ምዕመናኖቿን እና አገልጋዮቿን አውግዛለች። ከአንድ
ቢሊየን አባላት በላይ ያላት የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን
ባለፉት አንድ መቶ አመታት ያወገዘቻቸውና በአዲስ አበባ
ያሉት አባቶች ያወገዙትን ስንመለከት በቍጥር የእኛው
በልጦ እናገኛለን። በአንድ በኩል የምዕመናኑ በሚሊየኖች
ወደ ሌሎች የእምነት ተቋማት መሄድ በሌላ በኵል ደግሞ
ጳጳሳትን ሳይቀር ምእመናንን ጨምሮ በመቶ ሺዎች
የሚቆጠሩ ምእመናንን ማውገዝ ከየት መጣ ለምንድነው
ይህ ክስተት በእኛ ዘመን የተደጋገመው? ከዚህ ውግዘት
በስተጀርባ ያሉት እነማን ናቸው? ተጠቃሚዎቹስ እነማን
ናቸው የሚለውን ለመመለስ በመጀመሪያ ስለውግዘት
በሚገባ ማወቅ ይኖርብናል።
ሀ. ውግዘት ምንድነው?
ውግዘት ቃሉ፥ ወገዘ ከሚለው ግሥ እንደሚገኝ እና
ፍቺውም መገዘት መለየት መካድ መርገም ማለት እንደሆነ
የሊቁ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ
ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ ይናገራል። ከዚህ ከቃሉ አንጻር
በምንመለከትበት ጊዜ፥ ቃሉ የሚያመለክተን ከዚህ በፊት
ከአንድ አካል ጋር አንድነት (communion) የነበረውን
እንዲለይ (excommuncate) ማድረግ ነው። ይህን
ግልጥ ለማድረግ ቃሉ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በእንዴት
ያለ መንገድ እንደተቀመጠ በማየት ትርጉሙን
እንመለከታለን።
1.ውግዘት እርግማን ነው።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለገላትያ ሰዎች ሲጽፍላቸው
«ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ፥
ከሰበክንላችሁ ወንጌል የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ፥
የተረገመ ይሁን። አስቀድመን እንዳልን እንዲሁ አሁን
ሁለተኛ እላለሁ፥ ከተቀበላችሁት የተለየውን ማንም
ቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን።» ይላቸዋል። ( ገላ ፩፥፰-
፱) ግእዙም « አትሙሰ መልአክ እምሰማይ ለእመ
መሀረክሙ ካልአ እምዘ መሀርናክሙ ውጉዘ ለይኩን።
በከመ እቤ ቀዳሚ ወይእዜኒ ካዕበ እብል ለእመቦ
ዘመሀረክሙ እምዘመሀርናክሙ ውጉዘ ለይኩን።»
አስተውሉ አማርኛው « የተረገመ ይሁን የሚለውን ግእዙ
የተወገዘ ይሁን ይለዋል። ይህ ውግዘት ወይም እርግማን
ምን ማለት እንደሆነ እንመልከት፥ አዲስ ኪዳን
ለመጀመሪያ ጊዜ የተጻፈበትን የግሪኩን ቃል
በምንመለከትበት ጊዜ፥ የተወገዘ ይሁን አናቴማ ኤስቶ
(ἀνάθεμα ἔστω ) ይለዋል። አናቴማ ቃሉ በብሉይ
ኪዳን « እርም»፥ «ለእሳት የተሰጠ» ማለት ነው። ለምሳሌ
ኢያሱ በኢያሪኮ የተገኘው ሁሉ እርም እንዲሆን ሲያዝ
አካን የተባለው ሰው « እርም ከሆነው ነገር ወሰደ»
ይለናል። ኢያሱ7፥1። እንዲህ ዓይነት ብዙ ጥቅሶች
በብሉይ ኪዳን እናገኛለን። በአዲስ ኪዳንም ይህንኑ ቃል
ሳይስት፥ አናቴማ ( ውግዘት እርግማን) ማለት
በእግዚአብሔር ፍርድ ውስጥ መውደቅ ማለት ነው።
ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ በገላያ መልእክቱ ላይ በሐዋርያት
ከተሰበከው የጸጋ ወንጌል የተለየ ወንጌልን የሚሰብክ
በዚህ የእግዚአብሔር ፍርድ ውስጥ እንደሚወድቅ ሲናገር
እናያለን።
2. ውግዘት ለሰይጣን አልፎ መሰጠት ነው።
አሁንም ወደ ቅዱስ ጳውሎስ መልእክት ስንመጣ
በ1ቆሮ5፥5 ላይ «መንፈሱ በጌታ በኢየሱስ ቀን ትድን
ዘንድ እንደዚህ ያለው ለሥጋው ጥፋት ለሰይጣን
እንዲሰጥ ፍርዴ ነው።» ሲል እናገኛለን። ቅዱስ ጳውሎስ
በዚህ ስፍራ ሐዋርያዊ ውግዘቱን ያሳረፈበት ሰው፥ በሥነ
ምግባር ውድቀት ውስጥ የተገኘ ማለትም የአባቱን ሚስት
ያገባ ሰው ነው። ሐዋርያው ለቆሮንቶስ ክርስቲያኖች
ሲናገር «ይህን ሥራ የሠራው ከመካከላችሁ ይወገድ። እኔ
ምንም እንኳ በሥጋ ከእናንተ ጋር ባልሆን፥ በመንፈስ
ከእናንተ ጋር ነኝ፥ ከእናንተም ጋር እንዳለሁ ሆኜ ይህን
እንደዚህ በሠራው ላይ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም
አሁን ፈርጄበታለሁ፤ እናንተና መንፈሴም ከጌታችን
ከኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል ጋር ተሰብስበን፥ መንፈሱ በጌታ
በኢየሱስ ቀን ትድን ዘንድ እንደዚህ ያለው ለሥጋው ጥፋት
ለሰይጣን እንዲሰጥ ፍርዴ ነው።» ይላል።
ይህ የቅዱስ ጳውሎስ ቃል ስለ ውግዘት ሦስት ዋና ዋና
ነገሮችን ያሳየናል። አንደኛ፥ ይህ ነገር በጉባኤ በጥንቃቄ
የሚታይ ነው። ጉባኤው የክርስቶስ ጌትነት የከበረበት
ጉባኤ መሆን አለበት። የሐዋርያው ሥልጣን የከበረበት
መሆን አለበት። « እናንተና መንፈሴም ከጌታችን ከኢየሱስ
ክርስቶስ ኃይል ጋር ተሰብስበን» በዚህ ዘመን ያለውን
በውግዘት ዙሪያ የሚከናወነው፥ ተመሳሳይነቱ ከፖለቲካ
አደባባዮች ጋር ነው። አንደኛ ከብሮ የሚታየው ክርስቶስ
ሳይሆን የሰዎች የተንኮለኛነት ችሎታ ነው። ለምሳሌ
ባለፉት ሃያ አምስት አመታት በኢትዮጵያ ያሉት አባቶች
በአመት ሁለት ጊዜ ሲሰበሰቡ፥ ከስብሰባቸው በፊት፥
የተቃውሞ ሰልፍ፥ የክስ ደብዳቤዎች፥ ዘመቻዎች፥
ይካሄድባቸዋል። ወደስብሰባው የሚሄዱ አባቶች
ስብሰባው ከመጀመሩ በፊት ተወጋዡ ማን
እንደሚሆን፥ውሳኔው ምን መሆን እንዳለበት ተነግሮአቸውና
ተጽእኖ ተደርጎባቸው ነው የሚገቡት። ነገሮችን ከምንም
ነገር ነጻ በሆነ መንገድ ለማየት የሚሞክሩ አባቶች፥
በስድብ በስም ማጥፋት ጥላሸት ይቀባባቸዋል። በዚህ
ምክንያት አንዳንዶች ዝምታን ሲመርጡ አንዳንዶች
ለተጽእኖው ያጎበድዳሉ። ቅዱስ ጳውሎስ « ከኢየሱስ
ክርስቶስ ኃይል ጋር ተሰብስበን» ሲል « ብርታታችንና
ጉልበታችን የሚሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ይሆናል» ማለቱ
ነው። እውነት የምትነግሠውና ሐሰት ሥፍራን የምታጣው፥
በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ኃይልና በመንፈስ ቅዱስ
መሪነት ስንጓዝ ነውና።
ቅዱስ ጳውሎስ ሌላ ታላቅ ነገር ያነሣል። ይኸውም
ውግዘት ምን ያህል አስፈሪ ነገር እንደሆነ የሚያመለክት
ነው። አንድ ሰው ከእድር ቢለይ፥ ሌላ እድር ውስጥ
ይገባል። ወይም በዘመናዊው ዓለም ሌላ ዘዴ ሊጠቀም
ይችላል። ( ላይፍ ኢንሹራንስ ሊገባ ይችላል።)

Sunday, August 7, 2016

ሕይወት የሆነን የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ ብቻ ነው!


ቅዱሳንን ማክበር እንደሚገባ ምንም ጥያቄ የለንም። መታሰቢያን በተመለከተም የድርጊቶቻችን አፈፃፀም የሁሉ ነገር ባለቤት የሆነውን እግዚአብሔርን ስምና ክብር እስካልጋረደና  እስካልተካ ድረስ የሚደገፍ ነው። ነገር ግን  «ጥቂት አሻሮ ይዞ፤ ዱቄት ወዳለው መጠጋት» የሚለውን ብሂል ለመተግበር መሞከር ግን አደገኛ ነገር ነው። በተለይም በሃይማኖታዊ አስተምህሮ ወቅት ወንጌል እንደዚህ ስለሚል፤ እኔም እንደዚህ ብል ችግር የለውም የሚለውን ራስን መሸሸጊያ ምክንያት በማቅረብ ለመከለል መሞከር ፀረ ወንጌል ነው። በእግዚአብሔር ሁሉን ቻይነት ሥር ኑፋቄና ክህደትን ማስተማር በአምላክ ፊት ያስጠይቃል። እግዚአብሔር ሁሉን ማድረግ ስለሚችል የኛን ተረት ሁሉ ይሰራልናል ማለት አይደለም። ብዙ ጥያቄዎች የሚነሱትና እነዚህ የመሳሰሉ የስህተት ችካሎች አልነቀል ያሉት በምክንያት ስር በመደበቃቸው ነው።
ቅዱሳንን በማክበርና በመውደድ ሽፋን ወደአምልኮና ተገቢ ያልሆነ ሥፍራ ወደማስቀመጥ ያደገው መንፈሳዊ በሚመስል ማሳሳት ተሸፍኖ ነው።
ለክርስቲያኖች ድኅነት ዋናው ቁልፍ የክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ነው። ከዚህ ውጪ ያለው የማንም ሰው ሞትና ትንሣኤ ለመዳናችን ላይ የሚያመጣው ለውጥ የለም። አይጨምርልንም፣ አይቀንስልንም። ማዳን የእግዚአብሔር ነውና
ኢሳይያስ 43፣11
"እኔ፥ እኔ እግዚአብሔር ነኝ፥ ከእኔ ሌላም የሚያድን የለም"
ይህ የተሠጠን የቃሉ እውነት እንደተጠበቀ ሆኖ የጌታ እናት የድንግል ማርያም ሞትና ትንሣኤ ለክርስቲያኖች ዘላለማዊ ድኅነት መስጠት ይችላል? ወይ ብለን ብንጠይቅ መልሱ አይችልም ነው። ታዲያ በድንግል ማርያም ሞትና ትንሣኤ ላይ ጥንታዊያን የሚባሉ አብያተ ክርስቲያናት የተለየ ሃይማኖታዊ ትኩረት የሚሰጠው ለምንድነው? ልዩ ልዩ ሃይማኖታዊ ትርጉምና ትረካ የሚገልፁበትስ ምክንያት ለምን ይሆን?

እንኳን እኛ ጠያቂዎቹ ራሳቸው በትክክል ምክንያቱን የሚያውቁ አይመስለንም። የሆኖ ሆኖ ትርክታቸውን ለመዳሰስ እንሞክራለን።

ስለማርያም እረፍት፤ ትንሣኤና እርገት አብያተ ክርስቲያናት አንድ ዓይነት የእምነት አቋም የላቸውም። ካቶሊኮች በጥር ሞቶ በነሐሴ መቀበር የሚለውን ታሪክ አይቀበሉም። በየዓመቱ ነሐሴ 8 ያከብራሉ። በሌላ መልኩ ንዲያውም ስለማርያም ሞትና የእርገት ዕለት በግልጽ የሚታወቅ ማስረጃ እንደሌለ በ5ኛው ክ/ዘመን  የኖረው የሳላሚሱ ኤጴፋንዮስ   ተናግሯል።  ዕረፍቷና እርገቷ በኢየሩሳሌም እንደሆነ  የሚናገሩ ቢኖሩም  ይህንን አባባል የማይቀበሉ አብያተ ክርስቲያናትና የቴኦሎጂ ምሁራን ሞልተዋል። በኢየሩሳሌም አርፋለች የሚለውን አባባል የማይቀበሉበትን ማስረጃ ሲያቀርቡም ዮሐንስ በወንጌሉ ላይ እንደተናገረው «እናትህ እነኋት አለው። ከዚህም ሰዓት ጀምሮ ደቀ መዝሙሩ ወደ ቤቱ ወሰዳት»  ዮሐ19፤27 ባለው መሠረት ማርያም እስከ ሕይወቷ ፍጻሜ ድረስ ከዮሐንስ ጋር ስለኖረችና ወንጌላዊው ዮሐንስም ከጌታ ሞት በኋላ በኢየሩሳሌም  ጥቂት ዓመታትን ከቆየ በኋላ በ37 ዓ/ም ገደማ ወደ ቤዛንታይን ከተማ ኤፌሶን ሄዶ ወገኖቹን ወንጌል እያስተማረ መቆየቱንና  ማርያም በሞት እስከተለየችው ድረስ  ከ48-52 ዓ/ም እዚያው እንደነበር ብዙ ተጽፏል። ሌሎቹ ደግሞ ኤፌሶን መኖሯን ይቀበሉና ያረፈችው በኢየሩሳሌም ነው ይላሉ።
 ከዮሐንስ ጋር በኤፌሶን ነበረች ባዮች በቅርብ ርቀት ባለችው ደሴተ ፍጥሞም  በግዞት መኖሩ መኖሩና ከዶሚኒሽን አገዛዝ ቀደም ብሎ የራእይ መጽሐፉን  ከ55-65 ዓም ገደማ ስለፃፈ የማርያምም ቆይታ እስከዚያው ድረስ በኤፌሶን ነበር ይላሉ።
እንደዚህ ከሆነ  ማርያም በኤፌሶን ከዮሐንስ ጋር ኖራለች  ወይስ አልኖረችም ነው ጥያቄው።  በኢየሩሳሌም አርፋለች የሚሉ ሰዎች አንድም ጊዜ ከዮሐንስ ጋር በኤፌሶን ኖራለች ሲሉ አይደመጥም። ለምን?  ዮሐንስ ማርያምን እንደእናት ሊይዛት አደራ ተሰጥቶታል የሚባል ከሆነ ከዮሐንስ ጋር ኤፌሶን ስለመቀመጧ የማይነገረው ለምንድነው?  ዮሐንስ እስከ 96 ዓመቱ ድረስ ከኤፌሶንና ከደሴተ ፍጥሞ ውጪ ስለመኖሩ የተነገረ ነገር የለም። ማርያም ከዮሐንስ ጋር በኤፌሶን አልኖረችም ብሎ በመከራከርና ከኤፌሶን መጥታ ኢየሩሳሌም  ማረፏን በግልጽ በመናገር  መካከል ልዩነት አለ።  «እነኋት እናትህ» ባለው መሰረት አብረው ኤፌሶን ኖረው እዚያው ማረፏን የማይቀበሉና  የለም፣ ኢየሩሳሌም  አርፋለች የሚሉ ሰዎች የታሪክም፣ የጊዜም ልዩነት አላቸው።

 ወይ ደግሞ ኤፌሶን ላይ እድሜውን ሙሉ የኖረው ዮሐንስ ከማርያም ጋር ተለያይተው ነበር ሊሉ ይገባል።
ሮበርት ክሬው የተባለ የነገረ መለኮትና የታሪክ ጸሐፊ ዮሐንስ ወንጌላዊ ዘመኑን ሁሉ በኖረበት ከኤፌሶን ከተማ 8 ኪሎ ሜትር ወጣ ብላ ባለች ኰረብታ ላይ በተሰራ ቤት ውስጥ እንደኖረና ማርያምም እዚያ ማረፏን ጽፏል።  ይህንን በኤፌሶን ያለውን የማርያምን መቃብር የዓለም ክርስቲያኖች እንዲሆም ሙስሊሞች ሳይቀሩ ይጎበኙታል፤ ይሳለሙታል።  በቱርክ ግዛት ያለው ይህ ስፍራ በቱርካውያን ሙስሊሞች ዘንድ «ሜሪዬ ማና» ተብሎ ይጠራል።

ቅድስት ድንግል ማርያም ከዚህ ዓለም የተለየችው መቼ ነው? በሚለውም ጥያቄ ላይ ጥንታዊያን አብያተ ክርስቲያናት የሚባሉት የምሥራቁና የምዕራቡ ጎራዎች የተለያየ አመለካከት አላቸው።
 በተወለደች በ58 ዓመቷ ዐርፋለች የሚሉ አሉ። በ72 እና 63 እድሜዋም አርፋለች የሚሉ መረጃዎች አሉ። እንደ ግብጽ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ግን የሚታመነው በ64 ዓመት እድሜዋ ማረፏ ነው።  ኖረችበት ተብሎ ከሚገመተውና አርፋለች ከሚባለው ቦታ ያለው ልዩነት እንዳለሆኖ በጥር ወር ከዚህ ዓለም በሞት ተለይታ በ40ኛው ቀን ማረጓን የሚናገሩ አሉ። በነሐሴ ወር አርፋ ከተቀበረች በኋላ ትንሣኤዋን ሳያዩ መቃብሯ ባዶ ሆኖ ስላገኙት ሐዋርያት ሱባዔ ይዘው በሦስተኛው ቀን ተገለጸችላቸው የሚሉም አሉ። እንደኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ደግሞ በጥር ሞታ፤ በነሐሴ ተቀበረች የሚል ትምህርት አለ። በጥር ወር አርፋ፤ በነሐሴ ተቀብራለች የሚሉ ሰዎች ሥጋዋ በገነት ዛፍ ስር ለስምንት ወራት መቀመጡንና በሱባዔ ጸሎት በተደረገው ልመና የተነሳ ለመቀበር መቻሏን አስፋፍተው ይነግሩናል። ከጥር እስከ ነሐሴ ድረስ ለ8 ወራት ማርያም አልተቀበረችም።

 በጥር ወር እንዳረፈች፤ ለመቀበር ያልተቻለውም ታውፋንያ የሚባል ሽፍታ፤ ጎራዴ ሲመዝባቸው ወደ ቀብር ሥጋዋን ተሸክመው ይሄዱ የነበሩት ሐዋርያት በመፍራት ጥለዋት በመሸሻቸውና ዮሐንስ ብቻውን ቀርቶ ወደ  መቃብር ሳትገባ ወደ ገነት ዛፍ ስር በመወሰዷ ይባላል።  ነገር ግን የገነት ዛፍ ማለት ምን ማለት እንደሆነና በገነት ዛፍ ስር የሰው ሬሳ እንዴት ሊቀመጥ እንደሚችል አንድም ጽሑፍ በአስረጂነት ሲቀርብ አላየንም።

 ይህ በጥያቄነቱ ይቆየንና ታሪኩን እንቀጥል። ዮሐንስም ወደቤቱ ማምራቱንና ሸሽተው የነበሩትም ሐዋርያት ሥጋዋስ የታለ? ብለው ቢጠይቁት በገነት ዛፍ ስር መቀመጧን  ስለነገራቸው ዮሐንስ ገነት ዛፍ ሥር ሬሳዋ መቀመጡን አይቶ  እኛስ ለምን ይቀርብናል በማለት ነሐሴ 1 ቀን 49 ዓ/ም የጾም፣ የጸሎት ሱባዔ አውጀው በ15ኛው ቀን ትኩስ ሬሳ ከገነት ዛፍ ስር እንደመጣላቸውና በጌቴሴማኒ እንደቀበሯት ይናገራሉ።  ዮሐንስ በገነት ዛፍ ሥር ስትቀመጥ አያት የሚለውን ተረት እውነት አድርገን ብንቀበለው እንኳን ዮሐንስ ሀገረ ስብከቱ የሆነውንና እስከ መጨረሻው ጊዜውም የኖረበትን ኤፌሶንን ትቶ ወደኢየሩሳሌም መጥቶ ነበር ወይ? እንድንል ያደርጋል።

ሌላው ጥያቄ የሚያስነሳው ነገር  በጥር ወር አርፋ  ለቀብር ሲሄዱ ሽፍታ በፈጠረው ሁከት ሐዋርያቱ ስለሸሹ ወደገነት ዛፍ ስር ስለመወሰዷ ዮሐንስ ለሐዋርያቱ ከነገራቸው በኋላ ለስምንት ወራት የመቆየታቸው ምክንያትና ዮሐንስ ያየውን ማየት አለብን ያሉበት የጊዜና የሃሳብ አለመገጣጠም ጉዳይ አስገራሚ ይሆንብናል።
ዮሐንስ እንደነገራቸው ማየት አልፈለጉም ነበር? ከስምንት ወራት ቆይታ በኋላስ ማየት የፈለጉት ምንድነው?
ይህ ሁሉ ሲሆን የማርያም ሥጋ በተባለው የገነት ዛፍ ሥር ተቀምጧል። ሐዋርያቱ ሱባዔ ባይገቡ ኖሮ ሥጋዋ ምን ሊሆን ነበር? አይታወቅም። ዘግይቶም ቢሆን የሐዋርያቱ ሱባዔ ችግሩን ለማቃለል ችሏል።

የሚያስገርመውና የሚያስደንቀው ትርክት በጥር ወር አርፋ ሳይቀበር የቀረውን የማርያምን ሥጋ በስምንተኛው ወር ከገነት ወጥቶ ከተሰጣቸውና ከቀበሯትም በኋላ ማርያም ከመቃብር ተነስታ ስታርግ ሐዋርያቱ ለማየት አለመታደላቸው ነው።  ሐዋርያቱ ቀብረዋት ወደ ቤታቸው  ከገቡ በኋላ ከሐዋርያቱ አንዱ የነበረውና በቀብሯ ላይ ያልተገኘው ቶማስ የተባለው ሐዋርያው በደመና ተጭኖ ከህንድ ወደ ኢየሩሳሌም ሲመለስ ማርያምን ሐዋርያት በቀበሯት በሦስተኛው ቀን ወደ ሰማይ ስታርግ የዳመናው ጎዳና ላይ ያገኛታል።  መላእክት አጅበዋት ሲሄዱ ያገኛት ቶማስ ቀድሞ የልጅሽን ትንሣኤ ሳላይ ቀረሁ፣  አሁን ደግሞ ያንቺን ትንሣኤ ሳላይ ልቀር ነው? ብሎ ራሱን ከዳመናው ሠረገላ ላይ ወደመሬት ሊወረውር ሲል ቶማስ አትዘን፣ ትንሣኤዬን ያላንተ ማንም አላየም ካለችው በኋላ ለማየቱ ማስተማመኛ እንዲሆነው የተገነዘችበትን ጨርቅ እራፊ ሰበን ለምልክት ሰጥታው እንዳረገች ሰፊ ታሪክ ይነገራል።

ሰዎቹ ነገሩን ሁሉ ለማጣፈጥ የሚጠቀሙበት ነገር አስገራሚ ነው። የሰው ልጅ ከትንሣኤው በኋላ የዚህን ዓለም ጨርቅና ልብስ እንደተሸከመ ወደ ሰማይ ይገባል? ብለን እንድንጠይቃቸው ይጋብዙናል። እንደዚህ የሚናገር ክርስቲያናዊ አስተምህሮስ አለ ወይ? የሚል ጥያቄን ያስነሳል። ወንጌል ከትንሣኤ በኋላ ክርስቶስን ይመስል ዘንድ  ይለወጣል ይላል እንጂ የመቃብሩን ልብስና ሰበን እየተሸከመ ያርጋል የሚል ትምህርትን አይነግረንም።
« 2ኛ ቆሮ 3፤18
እኛም ሁላችን በመጋረጃ በማይከደን ፊት የጌታን ክብር እንደ መስተዋት እያብለጨለጭን መንፈስ ከሚሆን ጌታ እንደሚደረግ ያን መልክ እንመስል ዘንድ ከክብር ወደ ክብር እንለወጣለን»

ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን በመቃብሩ የተገነዘበትን ጨርቅ ትቶ መነሳቱን እንጂ  ያንኑ ለብሶ መነሳቱን አላነበብንም።
ዮሐ 20፤6-8. «ስምዖን ጴጥሮስም ተከትሎት መጣ ወደ መቃብሩም ገባ፤ የተልባ እግሩን ልብስ ተቀምጦ አየ፥ ደግሞም በራሱ የነበረውን ጨርቅ ለብቻው በአንድ ስፍራ ተጠምጥሞ እንደ ነበረ እንጂ ከተልባ እግሩ ልብስ ጋር ተቀምጦ እንዳልነበረ አየ»
የሁላችን አማኞች ትንሣኤ የክርስቶስን ትንሣኤ መምሰል ካለበት በቀብር ወቅት ከዚህ ዓለም ጉድጓድ የገባ ጨርቅ ወደ ሰማይ አብሮን የሚያርግበት ምንም መንገድ የለውም። ስለዚህ ከምድራዊ ማንነት ወደተለየ ሰማያዊ ማንነት እንሻገራለን እንጂ እንደሀገር ጎብኚ ጓዝ ይዘን የምንሄድበት ታሪክ ፀረ ወንጌልና ፈጠራ ላይ የተመረኮዘ ተረት ከመሆንአአያልፍም።
ስለዚህ ተጠራጣሪ እንደሆነ ሁል ጊዜ የሚነገርበት ቶማስን በማርያም ትንሣኤ ላይ ግን የተለየ ተጠቃሚ እንደሆነ አድርጎ ለማቅረብ  ሲባል ማርያም ወደ ሰማይ ስታርግ የመቃብሯን ከፈን ተሸክማ የሄደች በማስመሰልና ለምልክት ይሆን ዘንድ ከፍላ  ሰጠችው የሚለው አባባል በአንዳችም ነገር  ከወንጌል እውነት የተጠጋ አይደለም።
ሌላው ነገር በመንፈስ ቅዱስ በመነጠቅ፤  በሌላ ስፍራ ወዲያውኑ መገኘት ስለመቻል ለሐዋርያው ፊልጶስ  ከተነገረው የወንጌል ቃል  በተለየ በዳመና ላይ ተቀምጦ ስለመሄድ ግልጽ የሆነ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ቃል ባይኖርም የቶማስን ጉዞ ከህንድ ወደ ኢየሩሳሌም መመለስ እንደፊልጶስ መነጠቅ አድርገን ብንቆጥረው እንኳን የቶማስ ሰብአዊነትና የማርያም የትንሣኤ እርገት የተለያየና ፈጽሞ የማይገናኝን ነገር ለማቀራረብ መሞከር ነው።  የቶማስን የዳመና ላይ ውይይትን ከረቂቅ  ክርስቶሳዊ አዲስ ፍጥረት ጋር ለማገናኘት መሞከር የጥንቶቹን የግሪክ ወጎች/fable story/ እንድናስታውስ ያደርገናል። በግሪኮች የተረት ታሪክ "ጁፒተርና ሳተርን ተጋብተው ቬነስን ወለዱ" የሚል ታሪክ አለ። ይህ ታሪክ የገሀዱ ዓለም ተቃራኒ መሆኑን ማንም አይስትም። ቶማስና የማርያም ነፍስ የዳመናው ሜዳ ላይ ሰፊ ውይት አደረጉ. የተሸከሟት መላእክትም ጉድ፣ ድንቅ እያሉ ውይይቱን ይከታተሉ ነበር ዓይነት አባባል ከግሪኮች ጥንታዊ የተረት የተቀዳ ይመስላል።
በሞትና በትንሣኤ እንዲሁም በእርገት መካከል እንደዚህ ዓይነት ነገሮችን እግዚአብሔር በሰውኛ ትረካ ይጫወታል ማለት እግዚአብሔር ስለሞትና ትንሣኤ በተናገረው መቀለድ ይሆናል።
ከሁሉ የሚገርመው ደግሞ ማርያምን በጥር ሞታለች ያሉ ሰዎች፤  በመጀመሪያው ሞት ዮሐንስ ብቻ እድለኛ ሆኖ በገነት ዛፍ ስር ለማየት መቻሉ አንዱ ክስተት ሲሆነረ በኋለኛውም ቀብር ቶማስ ብቻ ተጠቃሚ የሆነበትን የእርገት እድል፤  ሌሎቹ ሐዋርያት ለማግኘት ባለመቻላቸው ሐዋርያቱ ሁለተኛ እድል ያመለጣቸው መሆኑ ነው።   ተረቱን የሚያቀናብሩት ሰዎች ለዚህም መላ አስቀምጠዋል።
ሐዋርያቱ ቶማስ በዳመና ላይ ያገኘው እድል ለምን ያምልጠን ብለው በቀጣይ ዓመት ነሐሴ1 ቀን 50 ዓ/ም ጀምረው ሱባዔ ለመያዝ መገደዳቸውንና በ16ኛው ቀን ኢየሱስ ክርስቶስ ማርያምን ከገነት አምጥቶ አሳያቸው።
ሁለተኛ  ትንሣኤና እርገትን ለማየት የመቻላቸው ነገር  አስደናቂ ትርክት ነው።
ቀብር ሳይኖር ትንሣኤዋንና  እርገቷን እንዴት ማየት እንደቻሉ ግልጽ አይደለም። በምሳሌ ይሁን በምትሃት እርግጠኝነቱን ያብራራ ማንም የለም።  ሁለት ጊዜ ትንሣኤና እርገትስ ማለት ምን ማለት ነው?
ዛሬም ድረስ ትንሣኤና እርገቷን የተመለከተውን ሱባዔ በማሰብ በየዓመቱ የሱባዔ ጺም ይደረጋል። የዘንድሮውም ነሐሴ 1/2008 ዓ/ም ተጀምሯል። የድሮውን ለማሰብ ነው ወይስ እንደገና ለማየት?

ሌላው  ደግሞ  ማርያምን መንበር፤ ጴጥሮስን ንፍቅ ቄስ፤ እስጢፋኖስን ገባሬ ዲያቆን አድርጎ በመቀደስ አቁርቧቸዋል የሚለው  ትረካ እርገቷን ተከትሎ የመጣው አባባል ነው። የማርያም ነፍስ እንዴት መንበር መሆን እንደሚችል? ምን የሚባለው ቅዳሴ እንደተቀደሰ? ለማወቅ አልተቻለም።   ሰራዔ ካህኑ ክርስቶስ የማንን ሥጋ  እንደቆረበ? እንዲነግሩን ግን እንጠይቃቸዋለን። ለየትኛው ድኅነት/መዳን/ እሱ ይቆርባል?  ክርስቶስ ቀደሰ እንጂ አልቆረበም ማለት አንድ ነገር ነው።  ቆርቧል የሚባል ከሆነም ምክንያትና ውጤቱን የሚተነትን ትምህርት አያይዞ ማቅረብ የግድ ይላል። እሱማ የሕይወት ምግብ ሰጪ እንጂ ተቀባይ አይደለም የሚባል ከሆነም  ሰራዔ ካህናት በዚህ ምድር መቅደስ ውስጥ ከመቀደስ ባሻገር መቁረብ አይጠበቅባቸውም በማለት አብነታዊ የክህነት አስተምህሮን አያይዞ ማቅረብ  የተገባ ይሆናል። ቀድሶ አለመቁረብን ከክርስቶስ አብነት መውሰድ ይቻላል እያሉ ነው።
እንግዲህ ማርያምን እንዴት መንበር አደረጋት፤ ክርስቶስ ሰራዔ ካህን ሆኖ  ያልታወቀ ቅዳሴ ቀደሰ ማለትስ ምንድነው?
  ስለማርያም  ትንሣኤና እርገት ማጠናከሪያ በማቅረብ ትዕይንቱን  ተአማኒ ለማድረግ ካልሆነ በስተቀር አንድም እውነትነት የለውም። እንደተለመደው አባባል ቅዳሴ እግዚእ ነው የተቀደሰው የሚል  ካለም ክርስቶስ ራሱን በሁለተኛ መደብ አስቀምጦ « ነአኩተከ አምላክ ቅዱስ፤ ፈጻሜ ነፍስነ፤ ወሀቤ ሕይወትነ ዘኢይማስን»  ሲል አይገኝም።  ራሱ ሕይወት ሰጪ ሆኖ ሳለ ሕይወት ይሰጠው ዘንድ አይለምንምና ነው። እንደዚህ ዓይነቱ አደገኛ ክህደት፤ ሰዎች ለማርያም ባላቸው ፍቅር ውስጥ ተደብቆ ለዘመናት ቆይቷል።

በጉ መስዋእቱን ለሕይወታችን ሰጥቷል። ከዚያ ውጪ እሱ  በመንግሥቱ የፍርድ ሰዓት ዳግመኛ ሊመጣ ካልሆነ በስተቀር ከማእዱ አይካፈልም።«ሰዓቱም በደረሰ ጊዜ ከአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ጋር በማዕድ ተቀመጠ። እርሱም፦ ከመከራዬ በፊት ከእናንተ ጋር ይህን ፋሲካ ልበላ እጅግ እመኝ ነበር፤ እላችኋለሁና፥ በእግዚአብሔር መንግሥት እስኪፈጸም ድረስ፥ ወደ ፊት ከዚህ አልበላም አላቸው። ጽዋንም ተቀበለ አመስግኖም። ይህን እንካችሁ በመካከላችሁም ተካፈሉት» ሉቃ 22፤14-17

ወደዋናው ሃሳባችን ስንመለስ ለመሆኑ በማርያም ላይ ስንት ቀብር፤ ስንት ትንሣኤና ስንት እርገት ተደረገ? ብለን ብንጠይቅ እንደሚነገረው  ከሆነ ፤
1/ዮሐንስ ያየውና አፈር ያልነካው እርገት በገነት ዛፍ ስር
2/ አፈር የነካው የሐዋርያቱ ቀብር በነሐሴ 14 ቀን /ከስምንት ወር በኋላ/
3/ ቶማስ ያየው የትንሳኤ እርገት፤ ከቀብር በኋላ በሦስተኛው ቀን ነሐሴ 16
4/ ከአንድ ዓመት በኋላ ሐዋርያት ያዩት የነሐሴ 16 ትንሣኤና እርገት ናቸው።
እንግዲህ በማርያም ሞትና እርገት መካከል አራት ትእይንት መከሰቱን ዛሬም ድረስ ከሚሰጡት የቃል አስተምህሮዎችና የተዘጋጁ ጽሁፎች ውስጥ በግልጽ እናገኛለን። ማርያምን መውደድ አንድ ነገር ነው። ማርያምን ግን እየቀበሩና እያነሱ ለማረጋገጥ መሞከር ደግሞ ሌላ አሳዛኝ ክስተት ይሆናል። እንዲያውም  ለዓለሙ ሁሉ መድኃኒት መሆን ከቻልኩ ሰባት ጊዜም ቢሆን እሞታለሁ ብላ ለልጇ ተናግራለች የሚልም  ተረት ተያይዞ ይነገራል።  የእሷ መሞት የዓለሙ ሁሉ መድኃኒት መሆን ከቻለ የክርስቶስ ከእሷ መወለድ አስፈላጊ አይደለም የሚል ሃሳብን የሚያንጸባርቀው ይህ አባባል ከአሳሳች ትረካዎች ውስጥ የሚደመር ከመሆን አያልፍም።
እኛ  ማርያምን ብንወዳትና ብጽእት ብንላት «እናትህንና አባትህን አክብር»  ያለውን  የአምላክ ቃል መጠበቅ ብቻ ሳይሆን ለእርሷ  የተነገረ ቃል ስላለም ጭምር ነው። ነገር ግን የዘላለማዊ አምላክ የክርስቶስ ፤ እናቱ ስለሆነች  በማዳላት ወይም አምላካዊ ባህርይውን በሰውኛ ጠባይ በመለወጥ ከፍርድ ሚዛኑ በማጉደል  የእሷን ሞትና ትንሣኤ የተለየ ያደርጋል ብሎ ማሰብ የዋሕነት ይሆናል። የእሷ ሞትም የመድኃኒትነትን ውክልና ለሰው ልጆች የያዘ እንደሆነ ማሰብ ክህደት ነው። ብቸኛው መድኃኒት አንዱ በግ ኢየሱስ ብቻ ነው። ማርያምም ይህንን ስለምታውቅ « ነፍሴ በአምላኬና በመድኃኒቴ ተስፋ ታደርጋለች» ብላ ነግራናለች።የትንሣኤ በኩር የሆነው ሁላችንም በሞቱ እንድንመስለው እንጂ የተለየ አድሎአዊ ጥቅምን/ faver/ ለተለዩ ሰዎች በመስጠት አይደለም።ወንጌል የሚናገረው ይህንን ነውና።
ሮሜ 6፥5
«ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን»
 ስለዚህ ደጋግሞ መሞት፤ መነሳትና ደጋግሞ ማረግ አለ ከተባለ ያ ነገር ከክርስቶስ ትንሣዔ ጋር ያልተባበረ ስለሆነ አንቀበለውም። እንዲያውን ይህ ኑፋቄና ወንጌልን መካድ ነው።  ሐዋርያው ጳውሎስም የተናገረው ስለክርስቶስ ወንጌል በሞቱም ክርስቶስን እንዲመስል ነበር።
ፊልጵ 3፥10-11  «እርሱንና የትንሣኤውን ኃይል እንዳውቅ፥ በመከራውም እንድካፈል፥ ወደ ሙታንም ትንሣኤ ልደርስ ቢሆንልኝ፥ በሞቱ እንድመስለው እመኛለሁ»
ማርያምን እንወዳለን እያሉ በጥር ሞተች፤ ገነት ዛፍ ስር ስምንት ወር በሬሳ ቆየች፤ በስንት ሱባዔ ስጋዋ መጥቶ ነሐሴ ተቀበረች፤ እስከነ ምድራዊ ልብሷ አረገች፤ በዳመናው ጎዳና  ላይ ከቶማስ ጋር ጨርቅ ተለዋወጠች፤ እድል ላመለጣቸው ሐዋርያት ዳግመኛ በስንት ሱባዔ በሌላ ትንሳኤና እርገት ተረጋገጠች፤ መንበር ሆና ተነጠፈች ወዘተ  በማለት እየገደሉና እያነሱ በማርያም ላይ መጫወት ተገቢ ነው ብለን አናምንም። የክርስቶስን ሞትና ትንሣኤንም ማፋለስና መካድ ይሆናል።

የማርያም ሞትና ትንሣኤ እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ካዘጋጀው የትንሣኤው በኩር አንድያ ልጁ የተለየ አያደርገውም።  ሞትም አንድ ነው ትንሣኤ ዘሙታንም አንድ ነው።  በትንሣኤ ዘሙታንና በእርገት መካከል ልዩነት አለ። ባልሆነ ጭንቁር ሃሳብ ተረቱን እያጋነንን ሕይወት የሆነንን የኢየሱስ ክርስቶስን ትንሣኤ መጋረድ ተገቢ አይደለም።

Friday, April 1, 2016

ያገር ያለህ ወይም የዳኛ ያለህ!!!


ከእውነቱ ( ክፍል ሁለት)

በማህበሩ መንፈሳዊ እንቅስቃሴ ላይ ያስተዋልኩት ድካም፡

 የግብጽ ቤተ ክርስቲያን የጫነችብንን ኢመጽሐፍቅዱሳዊ የባእላት አከባበርን ሕዝቡ በበለጠ
መልኩ እዲቀጥልበት ለማድረግ ሰምተናቸው ለማናውቃቸው ሰዎች የቅድስና ማእረግ
በመስጠት/በማሰጠት ሕዝቡ ከሥራ ይልቅ ባእል አክባሪ እንዲሆን መደረጉ፣
 በሌለ የጉልበትና የገንዘብ አቅም ሕዝቡ ለጽድቅ እየተባለ ወደ ተለያዩ ስፍራዎች በመጓጓዝ
እንዲደክም መደረጉ /ፈጣሪ በቦታ የሚወሰን ይመስል/
 በዓለም አብያተ ክርስቲያናት ታሪክ ውስጥ ታይቶና ተሰምቶ የማይታወቅ የጽላት ቀረጻና
የታቦት ተከላ ሥራ መሥራት፣
 እግዚአብሔርን ተርቦና ተጠምቶ በአውደ ምህረቱ ዙሪያ ለተሰበሰበው የዋህ ሕዝብ ፍቅር
የሚያስተምረውን የወንጌል ቃል ከመስበክ ይልቅ በእለቱ የሚከበረውን የጻድቅ ገድልና ታሪክ
ከሃይማኖትህን ጠብቅ የማስፈራሪያ መርገም ጋር በማሰማት ለጦርነት ማዘጋጀት፣
 ሕዝቡ በራሱ መረዳት ማን ምን እንደሆነ በእግዚአብሔር ቃል እውቀት እየመዘነ ሃሰቱንና
እውነቱን በመለየት የሚጠቅመውን እንዳይዝ መረጃ በሌለው አሉባልታ ተሞልቶ በውስጡ
ጥላቻና ቂም አዝሎ የራሱን ወገን እንዲጠላ በልዩ ወንጌል ሰባኪዎች መሰበኩ፣
 የበጉ ሐዋርያትና ሌሎች የቤተ ክርስቲያን ቀደምት የእምነት አባቶች አድርገውት የማያውቁትን
መጽሐፍ ቅዱሳዊ ያልሆነ በጸበል ተገኘ ጋጋታ ሕዝቡን ማንገላታታቸው፣
 በአጠቃላይ ሕዝቡን በቃል እውቀት ሳይሆን በቅርስና በባንዲራ ፍቅር የራሱን ወንድም
በጭፍን ወግሮ የሚያሳድድ ሃይማኖተኛ እንዲሆን እየተደረገ መሆኑን ይህ ጸሐፊ በራሱ ቤተ
ሰብ መካከል ባደረገው አጭርጥናት ሊያረጋግጥ ችሏል።

2/ ኦርቶዶክስ ተሐድሶ ማነው?

በኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተወልደው በማደግ ባህሏንና ትምህርቷን ጠንቅቀው የሚያውቁ
የቤተ ክርስቲያኒቷ ልጆች ነን ይላሉ፤ የኦርቶዶክስ ተሐድሶ ማህበር በሚል መጠሪያ ስም፡ ኦርቶዶክስ
ቤተ ክርስቲያናችን ከውጭና ከውስጥ በደረሱባት ልዩ ልዩ ተጽእኖ ምክንያት ከተመሰረተችበት
የክርስቶስ ኢየሱስ ወንጌል ርቃ ልዩ ወንጌል በመስበክ የመስቀሉን የማዳን ሥራ ቸል ብላለች፤ ስለዚህ
ወደ ቀደመ የወንንጌል ጅማሬዋ ትመለስ፤ በእግዚአብሔር ቃል /መጽሐፍ ቅዱስ/ መስተዋት ፊቷን
በማየት ክፉ ሰዎች ያለበሷት የደብተራዎች፣ ያስማተኞችና የደጋሚዎች ልብስ በንጹሁና እንከን የለሽ
በሆነው በእግዚአብሔር ቃል ልብስ /በክርስቶስ/ ይተካ በማለት ይጮሃሉ።

እንዲያውም እነዚህ ሰዎች የቤተ ክርስቲያናችን ወይም ያገራችን ታሪክ ይፈተሽና ይመርመር፤ ይዘነው
የተነሳነውንም የተሐድሶ ጥያቄና ሃገራዊ አጀንዳ ያገራችን ሽማግሌዎች፣ ጳጳሳት፣ ምሁራን፣ ተማሪዎች
በአጠቃላይ ሕዝቡ ይስማውና ማን የኦርቶዶክስ ጠላትና ወዳጅ እንደሆነ ጠቅላላ ምእመኑ እውነቱን
ይረዳ በሚል ግልጽነት በይፋ እየተንቀሳቀሱ መሆናቸውን መረዳት ችያለሁ።
እኔም እነዚህን አንዳንድ የኦርቶዶክ ቤተ ክርስቲያንን የተሀድሶ ሥራ አራማጆችን ጠጋ ብየ በመጠየቅ
የሚከተሉትን መረጃዎችን አግኝቻለሁ፡

1. የቤተ ክርስቲያናችን ጅማሬ ከኢየሩሳሌም ቀጥሎ በወንጌል ላይ ብቻ የተመሰረተች መሆኗን፣

2. በመጀመሪያው ጳጳስ በወንጌል ላይ የተጀመረው ክርስትናችን ግን እኒሁ ጳጳስ ከሞቱ በኋላ፡
 በእስክንድርያ ቤተ ክርስቲያን ቁጥጥር ስር በመውደቅ ለ1600 ዓመታት ከ110 በላይ በሚሆኑ
የውጭ ሀገር ጳጳሳት /የግብጽ የፖለቲካ ሠራተኞ/ መንፈሳዊ ቅኝ ተገዢዎች በመሆን አባይን
በመገደብ ሥራ ሠርተን እንዳንበላ እስካሁን ድረስ የ30 ቀናት ባእላት ባሪያዎች መደረጋችንና
ከእነዚህ መካከል አንዱ የካሊፋው ዋና ወኪል /አቡነ ሳዊሮስ/ እነደነበረ፣
 የዮዲት ጉዲት የ40 ዓመታት ግዛትና የቤተ ክርስቲያኗ መጽሐፍትና ካህናት መቃጠል፣
 የግራኝ ሙሐመድ የ15 ዓመታት ግዛትና የሙስሊም ክርስቲያኑ ሬሽዮ 9፡1 መድረሱና የቤተ
ክርስቲያኒቷን ውበት ማበላሸቱ፣

 ዘርዓ ያእቆብ በንግስናው ወራት በመጽሐፍ ቅዱስ ያልተመዘኑ የድርሰት ጽሑፎችን በቤተ
ክርስቲያኒቷ ውስጥ ያለገደብ ማስገባቱና የተሃድሶን ጥያቄ ያነሱ መነኮሳትን መጨፍጨፉ
/የፕ/ር ጌታቸውን ደቂቀ እስጢፋኖስን መጽሐፍ መረጃ ይጠቅሳሉ/፣
 የቤተ ክርሰቲያኒቷ ሲሦ መንግሥት ውል መዋዋልና ከዚህ ጋር በተያያዘ መልኩ መንግሥትን
ከሰሎሞንና ከዳዊት ጋር በማያያዝ የታቦትና የጽላት መጥቷል አፈታሪክ ጅማሬ /አቡነ ተክለ
ሐይማኖትን ተጠያቂ ያደርጋሉ/፣

 የደብተራ ቡድን በቤተ ክርስቲያኒቷ ውስጥ ተነስቶ የመናፍስት አሠራር እስካሁን ድረስ
በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ በሰፊው መለመዱ ……….. ወዘተ።
የመሳሰሉትን ነጥቦች በድፍረትና በማስረጃ በማቅረብ ቤተ ክርስቲያኒቷ ከተመሰረተችበት የወንጌል
መሰረቷ ፈቀቅ ብላለችና ወደ ቀደመ የወንጌል ጅማሬዋ ትመለስ በማለት አጥብቀውና በነፍሳቸው
ተወራርደው ለዚህ ሥራ እንደተነሱ ጨክነው ይሟገታሉ። ይህም መንፈሳዊ መታደስ በአገሪቱ ውስጥ
ላለው ሁለንተናዊ ችግር /ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ሃይማኖታዊ ችግር/ ዋና መፍትሄ ይሆናል
ብለው በማስራጃ ለማሳመን ይሞክራሉ።
ይህን ጉዳይም የኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ ተረድቶና ማን ምን እንደሆነ ተገንዝቦ ለመንፈሱ፣ ለነፍሱና
ለሥጋው የሚበጀውን በመጽሐፍ ቅዱስ/በወንጌል ሚዛን መዝኖ የሚረባውን ይይዝ ዘንድ
ራእያቸውንና ዋና ተልእኳቸውን ለሕዝብ በይፋ ያቀርባሉ፡

የተሐድሶ ራእይ፡

‘‘ጥንታዊና ሐዋርያዊት የነበረች ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያናችን በየዘመናቱ ከደረሰባት ውስጣዊና
ውጫዊ ተጽዕኖ የተነሳ ከተተከለችበት የእውነት ወንጌል በማፈንገጥ አሁን ላለችበት ውድቀት
በመዳረጓ ይህን ሁኔታዋን በከበረው የጌታችንና የመድኃኒታችን ቅዱስ ወንጌል በመመዘንና ወደ ቀደመ
የወንጌል ክብር በመመለስ በእጇ የሚገኘውን ተከታይና የተቀረውን የኢትዮጵያ ሕዝብ ክርስቶስ
ኢየሱስን በማወቅና በማመን የሚገኘውን የዘላለም ሕይወት በማግኘት ለጌታችን ቀን ያለነውርና
ያለነቀፋ ሆኖ እንዲገኝ በማዘጋጀት ለአፍሪቃና ለተቀረው ዓለም የሚላኩ ቅዱሳን አገልጋዮችን
በማፍራት የሚጠበቅባትን የወንጌል አደራ ስትወጣ ማየት ነው’’

የተሐድሶ ተልዕኮ፡

1. የቤተ ክርስቲያኒቷን አንድነትና የሀገራችንን ጥቅም በጠበቀ መልኩ ምዕመናን በጌታችንና
በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል ትክክለኛና እውነተኛ ተሀድሶ በማድረግ ለዘላለም
ሕይወት እንዲዘጋጁ መርዳት፣

2. በየደረጃው የሚገኙ የቤተ ክርስቲያኒቱ አገልጋዮች እንደ የደረጃው በተዘጋጁ የወንጌል
ትምህርቶች በማሰልጠንና በማሳወቅ ለስብከተ ወንጌል ሥራ ማዘጋጀትና የአገልግሎት ቦታዎች
ሁሉ እውነትን በተረዱ አገልጋዮች እንዲሸፈኑ ማድረግ፣

3. በየዘመናቱ ወደ ቤተ ክርስቲያኗ የገቡትን የስህተት ትምህርቶች ሥርዓቶችና ባሕሎች በቅዱሱ
ወንጌል በመዳኘት ከሕዝባችንና ከቤተ መቅደስ ዕቃ ቤቶቻችን እንዲወገዱ ማድረግ፣

4. ለአገራችን ኢትዮጵያ ዕድገትና ለዓለማችን ጥቅም በክርስቲያናዊ አስተሳሰብ ከመልካም ዜጋ
ግንባታ ጀምሮ ለልማትና ለመልካም አስተዳደር መስፈን ግዴታቸውን የሚወጡ ትጉህ
ሠራተኞችን ማፍራት፣

5. ጸረ ወንጌል ያልሆኑና ለክርስቶስ ወንጌል መስፋፋት ጠቀሜታ ያላቸውን ሥርዓቶች፣ ባህሎችና
ልማዶች ለክርስቶስ ወንጌል መሰበክ እንዲያገለግሉ መጠበቅና ማስጠበቅ።

Tuesday, March 22, 2016

እነሆ ሁለቱ ኪዳናት!!!


ከእውነቱ (ክፍል ሁለት)

መግቢያ

ስለ ሀልዎተ እግዚአብሔርና ስለ ትምህርተ ድነት በኛ ቤተ ክርስቲያን ተረስቶ ኖሯል፤ አሁንም እንደ ተረሳ ነው፡፡ አምስቱ አዕማደ ምስጢር የሚባል የዶግማ ትምህርት አለ፡፡ ግን እንኳንስ ለህፃናትና ላልተማሩ ሰዎች ዕድሜ ልኩን በቤተ ክርስቲያን ትምህርት ኖርኩ ለሚልም በቀላሉ ሊረዳ አይችልም፡፡ ዋናውና የሕይወት ትምህርት ወደ አንድ ጎን ተጥሎ ነው የኖረው፤ አሁንም ቢሆን ያሰበበት የለም፡፡ ከቃል ትምህርቱ ከዜማው፣ ከቅኔውና ከአንድምታው መቅደም የነበረበት የክርስቶስ ቤዛነት ትምህርት ነው፡፡ ትምህርተ መለኮትን (ቲኦሎጂን) ተማረ ቢባል ትምህርቱ ተንሳፋፊ ነው፡፡ መሠረቱን ለቆ አየር ላይ እየተንጠለጠለ የሚሄድ ነው፡፡ በቤተ ክርስቲያን የአመራር መንፈሳዊ አገልግሎትና በምእመናን መካከል እውነተኛው የእግዚአብሔር ፍቅር ፈጽሞ ተረስቷል፡፡ እኔነት፣ ትዕቢት፣ ትምክሕት፣ መናናቅ፣ መገፋፋት፣ መጠላላትና ርኩሰት በክርስቲያኖች መካከል ሰፍኗል፡፡ ቤተ ክርስቲያን የወንበዴዎች ዋሻ ሆናለች (በጌታችን እንደ ተነገረው)፡፡ ከላይ በጥቂቱ እንደተጠቆመው ከህፃናት ጀምሮ በየዕድሜ ክልሉ ስለ ሀልዎተ እግዚአብሔርና ትምህርተ ድነት መስጠቱ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ፈጽሞ አይታወቅም፡፡ ባሁኑ ጊዜ ሰባክያን ተብዬዎች በየደብሩ ተቀጥረው ምንም ፍሬ የሌለው ጩኸት ያስተጋባሉ፡፡ በሌላ በኩል እያወቁ ዝም ከማለት አሁንም ቢሆን በየደረጃው ትምህርት ለመስጠት የሚያስችል ትምህርትን ብናዘጋጅ ኃላፊነታችንን እንድንወጣ ያስችለን ነበር (ገብረዮሐንስ 2002፡ መግለጫ)፡፡ ይህንን መልእክት የጽሑፌ መንደርደሪያ እንዲሆን የመረጥኩት በውስጤ የሚመላለሰውን የ‹‹ችላ ተብሏልና ወደ እግዚአብሔር ሃሳብና ዓላማ እንመለስ›› ጥያቄ አጭርና ግልጽ በሆነ መንገድ ስለሚያስረዳልኝ ነው፡፡
 ደግሞም ቤተ ክርስቲያናችን ያለችበትን መንፈሳዊና አስተዳደራዊ ድክመት እንዲሁም በሰባክያኑ ውስጥ ሳይቀር ተንሰራፍቶ የሚገኘውን ፍሬ አልባነት በማሳየቱ ረገድ በዐይን ያየንና በውስጡ አልፎ ያገናዘበን ሰው ያህል ማስረዳት ስለሚያስቸግር፥ ከእኔ ይልቅ ረዘም ላለ ዘመን ባለፉበት የሕይወት ተሞክሮ ውስጥ ያከማቹትን እምቅ ትዝብት እጥር ምጥን አድርገው ያስተላለፉልንን የእኚህን አባት ቃል ቃሌ አድርጌ መናገር የተሻለ ብቻ ሳይሆን ተገቢም ነው ብዬ ስላመንኩ ነው፡፡ ይህም የሆነው እንደተባለው በውስጡ ላለፉት ሳይቀር ግልጥ ያልሆነ የትምህርት አቅርቦትን፣ ትኩረት ያልተሰጠውንና ወደ አንድ ጎን ተጥሎ የኖረውን ደግሞም አሁንም እንኳ ያሰበበት የሌለውን መንገድ እየተከተልን ይህን ያህል አማኝ አለን እያሉ መመካቱ ገበናችንን ሊሸፍንና በትምህርትና በአስተዳደር ዘርፍ ያለብንን ሥር የሰደደ መንፈሳዊ ችግር ሊሸሽግልን ባለመቻሉ በብዙ ወገኖች ተደጋግሞ እየተነሳ ያለውን ‹‹የትምህርትና የአስተዳደር ተሐድሶ›› ያስፈልጋል ጥያቄ ተገቢነት የበለጠ ትኩረት እንድሰጠውና እኔም እንዳስተጋባው በመገደዴ ነው፡፡ ይህ እንደ ተጠበቀ ሆኖ በክርስቲያናዊ ትምህርት ተኮትኩቶ ያላደገውን ምእመን ግራ እያጋቡ እነርሱ ጭምር በውል ወዳልተረዱትና በምናልባት ወደሚጓዙበት ፍልስፍና ሲጎትቱት የሚስተዋሉት ‹‹ፍሬ የሌለው ጩኸት የሚያስተጋቡት ሰባኪያን ተብዬዎች›› ሁኔታዎች ያስገኙላቸውን ክፍተቶች ተጠቅመው እየዘሩት ያለውን የትምህርት እንክርዳድ ነቅቶ ሊጠብቅና በወቅቱ ሊያስተካክል የሚችል ቢያንስ አንድ መንፈሳዊ አባት ማጣት ያስከተለው ችግር ውስብስብነትም ምንቸገረኝ የሚያሰኝ ሆኖ አላገኘሁትም፡፡

ከዚህ የተነሳ የእነዚያ ‹‹የሁለቱ ኪዳናት›› መጽሐፍ ጸሐፊ፣ አርታኢና አሳታሚ ማኅበር ቅንጅታዊ ተግባር ይህንን ለዘመናት እውነቱን እንዳያይና በዕውቀት እንዳይመራ የተደረገ ሕዝብ በባሰ የጨለማ ሕይወት እንዲዳክር ለማድረግ በቃልና በጽሑፍ የሚከናወን ጥረት አካል በመሆኑ ይህንኑ ለማሕበረሰባችን ገልጦ በማሳየት የደረሰውንና ሊደርስ ያለውን ብርቱ ችግር መከላከል አስፈላጊ ሆኗል፡፡ በእኔ እምነት ትውፊትንና ልማድን መከለያ አድርጎ የእግዚአብሔርን ቃል መቃወም ከተወቃሽነትና ከተጠያቂነት አያድንም፡፡ በክርስትና ስም ተሰባስቦና ታሪክና ቅርሳ ቅርስ እንጠብቃለን ወደሚል ዝቅታ ዝቅ ብሎ ለባሕልና ለቅርሳ ቅርስ በመወገን የእግዚአብሔር ሃሳብና ፈቃድ እንዳይፈጸም መከላከልም ተቀባይነት የለውም፡፡ ቅርሳ ቅርስ መጠበቁና ማስጠበቁ የሚያስከፋ ባይሆንም ከታሪክና ከቅርሳ ቅርስ በፊት ለእነርሱ መገኘት ምክንያትና ባለቤት የሆነው ክርስቶስ የሞተለት ሕዝብ መንፈሳዊ ሕይወት ቅድሚያ ሊሰጠው ይገባል፡፡ እስከ ዛሬም ድረስ ትኩረት የተነፈገው ምእመን ከሁሉ አስቀድሞ የእምነቱን ቀዳሚ ፍሬ (ድኅነተ ነፍሱን) እንዲያረጋግጥ የሚያስችለውን እውነተኛ የክርስትና ትምህርት ሊገነዘበው በሚችለው መንገድ ግልጥልጥ አድርጎ ማስተማር ያስፈልጋል፡፡ አቡነ መልኬ ጼዴቅ እንዳሉት ሕዝባችን በእምነቱ ፍጹም መታመን ኖሮት ‹‹… ኢየሱስ ክርስቶስ ብለን ጌታችንን ስንጠራው የዳንን ወገኖች መድኅንም ያለን ሕዝቦች መሆናችንን፤ ክርስቶስ ከግብርናተ ዲያቢሎስ ነጻ ያወጣን መሆናችንን ማመናችንና መናገራችን ነው›› ወደሚልበት እውቀትና ድፍረት መድረስ አለበት (መልከ ጼዴቅ 1984፡37)፡፡
 የክርስቲያን መመዘኛው የተጠለለበት ተቋም ህንጻ ውበት አሊያም ተቋሙ የኖረበት ዘመን ርዝማኔና የምእመናን ብዛት ሳይሆን በክርስቶስ ኢየሱስ በማመኑ ያገኘውን ዘላለማዊ ድኅነትና የሕይወት ዋስትና በእርግጠኛነት ተገንዝቦ እንደ ቀደሙት አባቶቹ፡- ከሰማይ የመጣ የእግዚአብሔርን ቃል በሥጋው ብቻውን ከሙታን ተቀድሞ እንደ ተነሳ እናውቃለን፤ በተነሳ ጊዜ አባቱ በሀብት ስቦ በረድኤት አቅርቦ ለእርሱ የሰጣቸው ምእመናን በትንሳኤ ይመስሉት ዘንድ እንግዲህ ወዲህ በቀድሞው ሰው አዳም ትእዛዝ ማፍረስ ምክንያት ፈርሰው በስብሰው አይቀሩም፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እሺ በጄ ብሎ እስከ ሞት በመድረሱ እነርሱ ፈጽመው ይድናሉ እንጂ (ዘቄርሎስ 1982፡309 ቁጥር 52) እና ያን ጊዜ በዚያ ወራት ነፍሳት ከሥጋቸው በተለዩ ጊዜ ከምድር በታች ወደ ሲዖል ይወርዱ ነበር፤ የሞት ቤቶችም እስኪመሉ ድረስ ወደ ገሃነም ይሄዱ ነበር፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአባቱ ሥልጣን ነፍሱን ከሥጋው በለየ ጊዜ ግን ወደ መንግስተ ሰማያት ለመግባት አዲስ መንገድ አዘጋጀልን፤ እንግዲህ ወዲህ ወደ ገሃነም አንሄድም፤ ፈጣሪያችንን እንከተለዋለን እንጂ … (ዘቄርሎስ 1982፡80 ቁጥር 17)፡፡ እያለ በሚያውጀው የእምነት ቃሉ፥ በሚመራበት የክርስቶስ መንግሥት ትምህርትና ሥርዓት በመኖሩ (በፍሬው) (ዮሐ 15፥16) እንዲሁም የመንግሥቱን ዜጎች በማብዛት ሥራው ሊሆን የተገባ ነው (ማቴ 28፥20፤ ማር 16፥15)፡፡ ለዚህ መጽሐፍ መጻፍም ድምር ምክንያቶቹ እነዚሁ እንደ ዘመን አመጣሽ ትምህርት እየተቆጠሩ ያሉትና ቸል የተባሉ የእምነት ቃሎችና ፍሬዎች አማኝ በሚባለው ሕዝብ ውስጥ ስፍራ ማጣታቸው የፈጠረው ስጋት ነው፡፡ ‹‹ስለ ሀልዎተ እግዚአብሔርና ስለ ትምህርተ ድነት በኛ ቤተ ክርስቲያን ተረስቶ ኖሯል፤ ዋናውና የሕይወት ትምህርት ወደ አንድ ጎን ተጥሎ ነው የኖረው አሁንም ቢሆን ያሰበበት የለም፤ በቤተክርስቲያን የአመራር አካላትና በምእመናን መካከል እውነተኛው የእግዚአብሔር ፍቅር ፈጽሞ ተረስቷል፤ ከህፃናት ጀምሮ በየዕድሜ ክልሉ ስለ ሀልዎተ እግዚአብሔርና ትምህርተ ድነት ትምህርት መስጠቱ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ፈጽሞ አይታወቅም፤ ባሁኑ ጊዜ ሰባክያን ተብዬዎች በየደብሩ ተቀጥረው ምንም ፍሬ የሌለው ጩኸት ያስተጋባሉ›› በሚለው የገብረ ዮሐንስ ገለጻ ተስማማንም አልተስማማን፥ ነቀፍነውም ደገፍነው በእኔ እምነት ደግሞም እውነትን በሚፈልጉና በሚከተሉ ዘንድ ያለንበትን ተጨባጭ ሁኔታ ገልጦ የሚያሳይና የዘነጋነውን የቀደመችውን ቤተ ክርስቲያን ሕይወትና ተልዕኮ እንድናስብ የሚያነቃ ደወል ነው፡፡ በቅንነትና ሽንገላ በሌለበት ኅሊና ከመዘንነው የተጠራንበትን ትክክለኛ ተግባር መፈጸም በሚያስችለን የትምህርት፣ የአስተዳደር፣ የሥርዓትና የአምልኮ ሂደት ላይ አለመሆናችንን የሚያስገነዝብና ልባዊ ተሐድሶ እንድናደርግ የሚያሳስብ ሕያው መልእክት ነው፡፡ ‹‹ማን ያርዳ …›› እንዲሉ ከነበሩትና አሁንም ካሉት በላይ አስረጅ አይገኝምና መስማት ለሚችልና እውነትን ለሚፈልግ ሁሉ የ‹‹ተሐድሶ››ን ማለት የእምነት ለውጥ ሳይሆን እውነቱን ፈልጎ የማግኘትን፣ በፈጸሙት በደል ተጸጽቶ ንስሃ የመግባትንና በከበረው እውነትና መሠረት ላይ ጸንቶ የመኖርን አስፈላጊነት የሚያሳይ ፋና ነው፡፡

 ይህንን የተንደረደርኩበትን የገብረ ዮሐንስን አባባል የትምህርት ተሐድሶ አያስፈልግም በሚለው ግትር አቋሙ የሚታወቀው ማኅበረ ቅዱሳን ሳይቀር ይጋራዋል፡፡ ይህንንም በራሱ መንገድ እንዲህ በማለት ይገልጸዋል፡፡ … በሥነ ምግባር የተዋበ ዜጋን የማፍራት አቅሙ እያላት አልሰራችበትም (እንዲያውም ምግባረ ብልሹነት፣ ሙስና ወዘተ አሁን አሁን በቤተ ክርስቲያን ተንሰራፍቷል) የሚሉ ትችቶችና ዘለፋዎች ከየማዕዘኑ ሲሰነዘሩ ተደምጠዋል፡፡ ትችቱ የተጋነነ ቢሆንም እውነትነት የጎደለው ግን አይደለም፡፡ … ከዚህም በተጨማሪ ቤተ ክርስቲያን ወጣቱን በትምህርትና በሥነ ምግባር ኮትኩታ ለማሳደግና ለመያዝ አለመቻሏ ሳይነሳ የሚታለፍ አይደለም፡፡ … እንደዚሁም በ1982 እና በ1983 ዓ.ም በመናፍቃን (በተሐድሶ) እንቅስቃሴ ምክንያት በቤተ ክርስቲያን በቅንዓት የተሰበሰበውን ወጣት ተገቢውን የቤተ ክርስቲያን ትምህርት በመስጠት በሃይማኖትና በምግባር እንዲጎለምስ፣ አገልግሎቱም እንዲፋጠን አልሆነም፡፡ … ለእረኛነት ተመርጠው በጎቹን በለመለመ መስክ እንዲያሰማሩና ከተኩላ እንዲጠብቁ የተላኩ ካህናት ከተኙበት እንዲነሱ በየዕለቱ ከሚተረከው ዓለም አቀፋዊነት ሌላ የተሻለ ቀስቃሽ ከቶ ሊመጣ አይችልም፡፡ (ሐመር 1999፡53-54) የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ሀብተ ብዙ በመሆኗ ብዙ ሥራዎች ይጠብቋታል፡፡ … በዚህ መሠረት ቢያንስ ሁለት መሠረታዊ ሥራዎች ይጠብቁናል፡፡ አንደኛ እውነተኛውን ትምህርት መስጠት … የዋሕ ልጆቿም በእምነት ቢቀበሉትም ዕውቀቱ አላቸው ማለት አይቻልም፡፡ በዕውቀት ያልተደገፈ እምነት ደግሞ እየቆየ መላላቱ አይቀሬ ነው፡፡ ስለዚህ ለአማኞቿ የሚሆንና ችግሮቿን የሚፈታ ለሚጠይቋቸውም መልስ በመስጠት የሚያስጨንቁበት አንዳንዶችንም ከእሳት የሚያድኑበት ትምህርት ከቤተ ክርስቲያኒቱ ልጆች ይጠበቃል፡፡ ሁለተኛ መለየትና ማዘጋጀት፡- ምንም እንኳ ቀደም ብለን እንዳየነው የአዋልድን ቁጥር መወሰን ባይቻልም የመለየትና ለአገልግሎት የመለየት ሥራው ግን ለአራተኛው ሺህ ዓመት ሊገፋ አይገባውም፡፡ … እኛ ደግሞ በመግለጽ ጊዜ ስርዋጽ የገባባቸው ካሉ በማጥራት የተጓደሉትን በማሟላት ዲቃሎቹንና እውነተኞቹን አዋልድ በመለየት ለአገልግሎት ማዘጋጀት ያስፈልጋል፡፡ … ጌታ በሚገለጥ (ዳግመኛ በሚመጣ) ጊዜ በቀኝ የሚቆም መጽሐፍና ቅርስ የለም፡፡ የሚቆሙት ሰዎች ናቸው፡፡ …ካለበለዚያ ቆፍሮ በመቅበር መጠየቃችን አይቀርም፤ እንደ ገብረ ሀካይ (ሐመር 1999፡71)፡፡

ይህንን መሠረተ ሃሳብ መነሻው አድርጎ ትክክለኛውንና ቸል የተባለውን የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ገልጦ ለማሳየትና ከአጥፊዎች ለመከላከል የተዘጋጀው ይህ መጽሐፍ በሰባት ምዕራፎች የተከፈለ ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ኪዳናት›› የሚል ርዕስ የተሰጠው የመጀመሪያው ምዕራፍ ስለ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ኪዳናት ምጥን፣ ነገር ግን አሁን ለደረስንበት አዲስ ኪዳናዊ ሕይወት መሠረት የሆኑ ሃሳቦችን ያስዳስሳል፡፡ ኪዳናቱ ከአንዱ ወደ ሌላኛው እየተሸጋገሩ ፍጹም ወደ ሆነው የመጨረሻው ኪዳን (አዲስ ኪዳን) እንዴት እንደ ደረሱ ያሳያል፡፡ በተለይም ሁለቱ ኪዳናት (ብሉይና ዐዲስ) ከተሰጡበት ዓላማና ከተመረቁበት ደም አንጻር በክብርም ሆነ በአገልግሎት እንደሚበላለጡ (አንዱ ከሌላው እንደሚለይ) ማሳየት የምዕራፉ ዋነኛ ዓላማ ነው፡፡ ምዕራፍ ሁለት ‹‹የሁለቱ ኪዳናት ቅኝት›› በሚል ርዕስ ላይ የተመሠረተ ነው፡፡
ምዕራፉ ከዚህ በፊት ‹‹ሁለቱ ኪዳናት›› በሚል ርዕስ በማኅበረ ቅዱሳን ታትሞ ለሕዝብ በተሰራጨ መጽሐፍ መግቢያ ውስጥ የሚገኙ የእውነተኛው ኦርቶዶክሳዊ ተዋሕዶ ትምህርት ይዘት የሌላቸው ሁለት ሃሳቦችን ነቅሶ በማውጣት በመጽሐፍ ቅዱስና በቀደሙት አባቶች አስተምህሮ የሚመዘንበት ክፍል ነው፡፡ በተለይም የመጽሐፉ አርታኢና የመግቢያው ጸሐፊ የ‹‹ሁለቱ ኪዳናት››ን (የብሉይና የአዲስን) ውሕደት አስመልክቶ ያስተላለፈውን መልእክት መነሻ በማድረግ ኪዳናቱ ሊዋሐዱ የማይችሉበትን መሠረታዊ ነጥቦች በስፋት ይዳስሳል፡፡ የማይዋሐዱትን ለማዋሐድ የሚደረገውንም መደፋፈር በብርቱ ይሞግታል፡፡ ድርጊቱም ክርስቲያናዊ ተግባር እንዳልሆነ ያስገነዝባል፡፡ ምዕራፍ ሦስት ‹‹ታሪካዊ ስህተትን ላለመድገም›› የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ ይህ ክፍል መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት ያደረጉ ውሳኔዎች የተላለፉባቸውን የመጀመሪያዎቹን ሦስት ዓለም አቀፍ ጉባኤያት መንስዔና የተደረሱባቸውን ውሳኔዎች ያስታውሳል፡፡ በዚህ ክፍል የሚነሳው ሃሳብ መጽሐፍ ቅዱሳዊውን እውነት በ‹‹ሁለቱ ኪዳናት›› መጽሐፍና መሰል የኅትመት ውጤቶች እየተሰራጩ ከሚገኙት ኢ-ክርስቲያናዊ ትምህርቶች ጋር በማነጻጸር ያሳያል፡፡ ይህም አንባቢው ትክክለኛውን መሠረተ እምነት ተገንዝቦ ትክክለኛ ውሳኔ እንዲሰጥ የሚያስችል ዕድል ይፈጥራል፡፡ ለመግለጽ እንደሞከርኩት ይህ ክፍል ይህንን መጽሐፍ ጨምሮ ማናቸውንም በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ስም ተጠልለው የሚሠራጩ ትምህርቶችን በተለይም በቀጣዩ ምዕራፍ የሚዳሰሱትን ከ17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ጎልተው የታዩትን ሦስት ቡድኖች አስተምህሮ ለመመዘንና የየትኛው ወገን ትምህርት ከሦስቱ ዓለም አቀፍ ጉባኤያት ውሳኔዎች ጋር እንደሚስማማና እንደማይስማማ ለመለየት ያስችል ዘንድ እንደ ቱንቢ ሆኖ ተቀምጧል፡፡ እነዚህ ሶስት ዋነኛ ጉባኤያት ሲነሱ ሊታለፉ የማይገባቸው ሁለተኛው የኤፌሶን ጉባኤ (ምዕራባውያን የወንበዴዎች ጉባዔ የሚሉት) እና በምዕራባውያኑ አራተኛው ዓለም አቀፍ ጉባኤ በመባል የሚታወቀው የኬልቄዶን ጉባኤ (በኦርየንታሎቹ ጉባኤ ከለባት የሚባለው) የመጀመሪያዎቹ ሶስቱ ጉባኤያት ያስተላለፏቸውን የእምነት ድንጋጌዎች በግልጽ ለመረዳት ከሚያደርጉልን እገዛ አንጻር ጥቂት ስፍራ ተሰጥቷቸዋል፡፡ በዚህም ከእነዚሁ ጉባኤያት ጋር የተያያዙ ዋና ዋና ሃሳቦች ይዳሰሳሉ፡፡ ምዕራፍ አራት ‹‹የግጭቶቻችን ማጠንጠኛዎች - ቅባት፣ ካራ፣ ጸጋ›› በሚል ርዕስ የቀረበ ነው፡፡ ይህ ክፍል ከ17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አንስቶ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የርስ በርስ ግጭቶችና ደም መፋሰስ ያስከተሉትን ሦስት በአመለካከት የተለያዩ ቡድኖች አስተምህሮ አስመልክቶ ምጥን፥ ነገር ግን ጠቃሚ መረጃዎችን የያዘ ነው፡፡ ክፍሉ ዛሬ ዛሬ የ‹‹ተዋሕዶ›› አማኝ ነኝ የሚሉን ቡድኖች አስተምህሮ (ማኅበረ ቅዱሳንን ጨምሮ) ከእነዚህ ከሦስት ቡድኖች (ካራ፣ ቅባት፣ ጸጋ) ቢያንስ ከአንዱ ተቀድቶ አለበለዚያም የአንዱ ቡድን ትምህርት ከሌላው ቡድን ትምህርት ጋር ተዳቅሎ ሲወርድ ሲወራረድ የመጣ በመሆኑ አስተምህሯቸውን አዳምጦና መዝኖ ከየትኛው ወገን እንደሆኑ መገምገም እንደሚያስችል ይታመናል፡፡ በተለይም በቀዳሚው ምዕራፍ የተዳሰሱትን ዓለም አቀፍ ጉባኤያት ውሳኔዎችና ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች ከእነዚህ ቡድኖች አስተምህሮ ጋር በማነጻጸር የትክክለኛውን ተዋሕዶ ባህለ ትምህርት ለመገንዘብ የሚኖረው ጠቀሜታ ከፍ ያለ ነው፡፡ በምዕራፍ አምስት ‹‹ልዩነቶቻችን በመጽሐፍ ቅዱስ ሲዳኙ›› የሚል ሃሳብ ይነሳል፡፡ የዚህ ክፍል ዓብይ ዓላማ በዘመናት ሁሉ ለተነሱት ሃይማኖታዊ ችግሮች (ልዩነቶች) መንስኤው ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ያለን አመለካከት መለያየት መሆኑን በማስቃኘት የ‹‹ሁለቱ ኪዳናት›› መጽሐፍ አዘጋጅ መሪጌታ ኃየሎምና አሳታሚው ማኅበር ማኅበረ ቅዱሳን የሚያራምዱት የእምነት አቋም በመጽሐፍ ቅዱስ ከተገለጸው የእግዚአብሔር ሃሳብ የሚቃረንና ጤነኛ የተዋሕዶ ትምህርት አለመሆኑን ማስረጃዎች ጠቅሶ ያሳያል፡፡
በአንጻሩም ቤተ ክርስቲያናችን የምትቀበላቸው ቀደምት ኦርቶዶክሳውያን አባቶች ያስተላለፉትን ትምህርት በእማኝነት በማቅረብ ጥንታዊውንና እውነተኛውን የተዋሕዶ ትምህርት ያስገነዝባል፡፡ ምዕራፍ ስድስት ‹‹ሕግና ትእዛዝ›› በሚል ሃሳብ ላይ የሚያጠነጥን ነው፡፡ ሕግጋትና ትእዛዛት ለጸጋ ስፍራቸውን እንዳልለቀቁና እነርሱን መጠበቅ የጽድቅ ምንጭ እንደሆነ ሊሰብኩን ለሚሞክሩት ‹‹የሙሴ ደቀ መዛሙርት›› ሕግን የምንጠብቀው ገና ለመጽደቅ እያሰብን ሳይሆን በክርስቶስ ኢየሱስ የመስቀል ላይ ሥራ ስለ ጸደቅን መሆኑን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ እያቀረበ ያስረዳል፡፡ ምዕራፍ ሰባት ‹‹መቅደስ - የእግዚአብሔር መገለጫ›› የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ ይህም መቅደስ የተባለውና ክርስቶስ የገባበት ሰማያዊ ስፍራ ‹‹መስቀል›. ነው ለሚለው የስህተት ትምህርታቸው መልስ የተሰጠበት ክፍል ነው፡፡ ከብሉይ ኪዳን የቤተ መቅደስ ጅማሬ አንስቶ ክርስቶስ የገባባት ተብላ እስከ ተገለጸችው ቤተ መቅደስ ድረስ ያለውን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሃሳብ በአጭሩ በማቅረብ ‹‹ቤተ መቅደስ የተባለው ጌታ የተሰቀለበት መስቀል ነው›› የሚለውን ኢ-ክርስቲያናዊ ፍልስፍና ይፋለማል፡፡ በአጠቃላይ መጽሐፉ ጤናማውን የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ባህለ ትምህርት ከጥፋት ለመከላከልና እውነቱን ገልጦ ለማሳየት መጽሐፍ ቅዱስንና የቀደሙ አባቶችን ትምህርት መሠረት አድርጎ የተጻፈ በመሆኑ ስለ እምነቱ ተገቢውን ግንዛቤ ለማግኘትና እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ለመኖር የሚፈልግ ሁሉ ጠቃሚ ትምህርት እንደሚያገኝበት እምነቴ ነው፡፡

Sunday, March 20, 2016

በከበሮና በዘፈን አመስግኑት፤ በአውታርና በእምቢልታ አመስግኑት!

መዝ 150
ሃሌ ሉያ። እግዚአብሔርን በመቅደሱ አመስግኑት፤ በኃይሉ ጠፈር አመስግኑት።
በችሎቱ አመስግኑት፤ በታላቅነቱ ብዛት አመስግኑት።
በመለከት ድምፅ አመስግኑት፤ በበገናና በመሰንቆ አመስግኑት።
በከበሮና በዘፈን አመስግኑት፤ በአውታርና በእምቢልታ አመስግኑት።
ድምፁ መልካም በሆነ ጸናጽል አመስግኑት፤ እልልታ ባለው ጸናጽል አመስግኑት።
እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን፦ ሃሌ ሉያ።



Saturday, March 19, 2016

ያገር ያለህ ወይም የዳኛ ያለህ!!!


ከእውነቱ /ለውይይት የቀረበ/

 1/ መግቢያ

በድሮ ጊዜ ሰው በሰው ሲበደልና ፍትሕ ሲጓደል ‘ያገር ያለህ’ ወይም ‘የዳኛ ያለህ’ በማለት ይጮህ ነበር፤ ይህ ዓይነቱ የተበዳይ ጮኸትም ለትውልድ መርገም እንዳይሆን ተብሎ በአካባቢው በሚኖሩ እድሜና ልምድ ጠገብ ሺማግሌዎች ገላጋይነት/ዳኝነት የበደለ እንዲክስ የተበደለ ደግሞ እንዲካስ በማድረግ ጉዳዩ እልባት እንዲያገኝ ይደረግ ነበር፤ እኔም ዛሬ በዲሞክራሲ ስም በምድራችን ውስጥ እየሆነ ያለውን አጠቃላይ እንቅስቃሴ /በተለይ ባለውለታ በሆነችው በኦርቶዶክስ ቤ/ክ ውስጥ/ ቀረብ ብየ ስመለከት ይህ እውነተኛ የፍትህ ፈላጊዎች ያገር ያለህ ጩኸት ትዝ ብሎኝ ለኢትዮጵያውን በሙሉ ለውይይትና ለመፍትሄው ፍለጋ ጭምር የሽማግሌ ዳኞች ያለህ በማለት ጮኸቴን ላቀርብ ተገደድኩ። መቸም ለተወሰኑ ዓመታት ከአገሩ ራቅ ብሎ ለኖረ ኢትዮጵያዊ የአዲስ አባባ ገጽታ ቀየር እንደምትልበት ይታመናል፤ በርካታ ሕንጻዎችና መንገዶች ተሠርተዋል፤ ባቡርም ተጀምሮ ሕዝቡ እየተጠቀመበት መሆኑን በግልጽ ማየት ይቻላል፤ ለራሴ ሕሊና ታማኝ መሆን ስላለብኝ የሚታዩትን መልካም ነገሮች እሰየው በማለት፣ ደስ የማይሉትንና ደካማ የሆኑትን ደግሞ ለእርምት በግልጽነት ብጠቁም ሰውነቱን የሸጠ ካልሆነ በስተቀር ቅር የሚሰኝ እውነተኛ ሰው የሚኖር አይመስለኝም። እዚህ ላይ የሕንጻዎችና የመንገዶች መገንባት መልካም ቢሆንም፤ በራሳቸው ግን ያንድ አገር እድገት ዋና መስፈርቶች ናቸው ብሎ መውሰዱ ተገቢ አይመስለኝም፤ ሕንጻ ያለሰው ከንቱ የድንጋይ ክምር ብቻ ስለሚሆን! በሌላ መልኩ ደግሞ አብዛኛው ሕዝብ በኑሮ ችግር እየተጠበሰና ያገሪቱ ሃብት በጥቂቶች እጅ ውስጥ ሆኖ እያለ ኢኮኖሚስቶች በነፍስ ወከፍ የገቢ ስሌት ተመስርተው አድገናል ማለታቸው በሕዝቡ አጠቃላይ የኑሮ ምጥ ላይ የሚታየውን የህይወት ማቃሰት በግልጽ መካድ ነው የሚሆነው፤ የተመጣጠነ የሃብት ክፍፍል በሌለበት አገር ውስጥ ይህ ዓይነቱ የሂሳብ ቀመር እንዴት ሆኖ እውነተኛ ሚዛን እንደሚሆን ፈጽሞ አይገባኝም። ማየት ከመስማት የበለጠ ጥሩ መረጃ እንደሆነ ይታመናል፤ በመሆኑም አገራችን ኢትዮጵያ ምን እየሆነችና ወዴት እየተጓዘች እንደሆነ ከዚህ በፊት በጆሮዬ የሰማሁትን ዛሬ በዓይኔ አይቼ ለራሴ ህሊና ያገኘሁትን መረዳት በሚከተሉት ርእሶች ላይ ያለኝን ስጋት በትንሹ ላካፍል፡

 1. ፖለቲካውና ኢኮኖሚው በሕዝቡ ኑሮ ላይ ያስከተለው አውንታዊና አሉታዊ ተጽእኖ፣ /በሁለተኛ ደረጃ የሚታይ ይሆናል/

 2. በሐይማኖታዊ ተቋማት /በተለይ አብዛኛው ሕዝብ ችግሩን ለፈጣሪው የሚያቀርብባትና ለመጽናናት የሚሞክርባት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን/ ውስጥ እየሆነ ያለው መተራመስ፤ በምድራችን ውስጥ በርካታ የሃይማኖት ተቋማት ይገኛሉ፤ ሆኖም ግን ከአገሪቱ ታሪክ ጋር ከፍተኛ ትስስር ያላትና በበርካታ ጠንካራ ጎኗ ጉሉህ ስፍራውን ይዛ የምትገኘው ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ስለመሆኗ የሚክድ ኢትዮጵያዊ ያለ አይመስለኝም፤ ካለ ግን ልሟገተውና ጣሊያንን በምስክርነት ጠርቸ ላስመሰክርበት እችላለሁ፤ ይህ የሚሆነውም በራሳቸው ሙያ የሚተማመኑ እውነተኛ ዳኞች ከተገኙ ብቻ ነው። ስለዚች ቤተ ክርስቲያን ታሪካዊ አጀማመር፣ ላገር ስላበረከተችው መልካም አስተዋጽኦ፣ በረጅም የታሪክ ሂደቷ ውስጥ ስለገጠሟት በርካታ ተግዳሮቶችና ስለከፈለችው ከፍተኛ መስዋትነት ማወቅ ለሚፈልግ /የራሱን ታሪክ ማወቅ ለሚፈልግ/ ወደ ኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ጎራ እንዲል እየጠቆምኩ፤ የዛሬውን መልእክቴን ግን በቤተ ክርስቲያኒቷ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ በስፍራው ላይ ተገኝቼ ያየሁትን እውነት ብቻ ጥንቃቄ ባለው መልኩ በዚህ የመጀመሪያ ጽሑፌ ላይ ለማቅረብ እሞክራለሁ።

   በዚች ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከላይ ከፓትሪያሪኩ ጀምሮ በተዋረድ ወደታች የሚፈስ ያስተዳደር መዋቅር አለ፤ በተጨማሪ በርካታ መንፈሳዊ የትምህርት ማሰልጠኛዎች እያስመረቁ የሚያወጧቸው ወጣቶች ዐውደ ምህረቱን ሞልተውት የሰንበት ትምህርት የማስተማሩን ሥራ በሰፊው ተያይዘውታል፤ እኔን የገረመኝና የማላውቅበትን ብእር እንዳነሳ ያደረገኝ ግን በዚህ ግራና ቀኙን በማያውቅና እግዚአብሔርን በሚፈራ የዋህ ወገናችን መካከል በተለያየ መንፈሳዊ ስያሜ ተመስርተው የሚያካሂዱት የእርስ በርስ ጦርነት ነው፤ በዘመናት መካከል እኔ ‘አውቅልሃለሁ የሚልለት ተቆርቋሪ አጥቶ የማያውቅ’ አሳዛኝ ሕዝብ፤! በዚህ መሰረት ለዛሬ ማህበረ ቅዱሳንን እና ኦርቶዶክስ ተሐድሶ የሚባሉትን መንፈሳዊ ማህበራትን ከሥራቸውና ከሚያራምዱት ዓላማ አኳያ በማየት ፍርዱን ለእውነት ፈላጊዎችና ለወገን ተቆርቋሪ ወገኖች ስተወው፤ ለበለጠ መፍትሄ ፍለጋ ግን ቤተ ሰብ ከቤተሰብ፣ ጓደኛ ከጓደኛ፣ ባል ከሚስት፣ ጎረቢት ከጎረቢት፣ አንዳችን ከሌላው ጋር በእውቀትና በቅንነት ግልጽ ውይይት በማድረግ ለአገርና ለሕዝብ የሚጠቅመውን መደገፍ ለሁላችንም ይበጃል።

1/ ማህበረ ቅዱሳን ማነው?

ከማሕበረ ቅዱሳን አጠቃላይ እንቅስቃሴ ሁላችንም ልንማረው የሚገባ ቁምነገር እንዳለ አምናለሁ፤ ዋና ዓላማው ግልጽ ባይሆንልኝም የአባላቱ ስብጥር፣ አባላት ለማህበራቸው የሚከፍሉት ዋጋና የርስ በርስ መደጋገፍ ይበል የሚያሰኝ ነው። እንዲሁም በየደብሩና በየገዳማቱ ለወደቁ ምስኪን ወገኖቻችን ከሚያደርገው መልካም ሥራ ባሻገር /እውተኛው ክርስትና የመስቀሉ ሥራ ውጤት እንጂ የመልካም ሥራ ውጤት አይደለም ወይም በሌላ አባባል የጽድቅ ሥራ ለመሥራት በመጀመሪያ በጸጋው አምኖ መጽደቅ አለበት ይላሉ ተሐድሶዎች/ ለባህልና ለቅርስ ጥበቃው ሥራ የሚከፍለው ዋጋም በቀላሉ የሚታይ ጉዳይ አይደለም። የዚህ ማህበር ሌላ መገለጫ ባህሪው የተለያየ የጉዞ ፕሮግራም በማዘጋጀት ሕዝቡ ገንዘቡን ከፍሎ በነጭ ልብስና በኢትዮጵያ ባንዲራ ከቦታ ቦታ እንዲንቀሳቀስ በማድረግ የሕዝቡ ማህበራዊ ትስስር እንዲበረታታ ያደርጋል፤ ሌላው አብዛኛው ሕዝብ አዲስና ልዩ ፈዋሽ ጸበል ተገኘ በተባለበት ስፍራና በየገዳማቱ ሁሉ አብዝቶ እንዲንቀሳቀስ ያደርጋል።
ማህበሩ በተጨማሪ ከሚያከናውናቸው ተግባራት መካከል ጥቂቶቹ፡- ሕንጻ መገንባትን፣ ንግድ መነገድን፣ የራሳቸውን አባላት ማሰልጠንን፣ አዳዲስ ታቦታት መትከልንና ስነጽሁፎችን በሰፊው አውጥቶ ማሰራጨት ሲሆኑ በእነዚህ ጽሁፎቻቸውም ላይ በዋናነት ተሐድሶን የሚያጥላላና የሚያወግዝ መልእክት በትኩረት ያወጣል። የማህበሩን እንቅስቃሴ ለማጠቃለልም፡  የውስጣቸውን/የልባቸውን ባላውቅም አለባበሳቸው በባንዲራ የታጀበ ነጭ ልብስ በመሆኑ የየዋሁን ሕዝባችንን ልብ ለዓላማቸው በቀላሉ ማማለል ይችላሉ፤ ችለዋልም፣  ለቅርስና ባህላዊ እሴቶቻችን ከፍተኛ ትኩረት በመስጠታቸውም ለአገር ብቸኛ ተቆርቋሪ ከነሱ ሌላ ፈጽሞ የሌለ አስመስሏቸዋል፣  ባህላዊ የቆሎ ትምህርት ቤቶች የበለጠ እንዲጠናከሩ ድጋፍ ያደርጋል፣ የገዳምና የምንኩስናን ኑሮ በማበረታት ምሁራን ሳይቀሩ ወደገዳም እንዲገቡ ያበረታታል፤ እንዲያውም ከውጭ አገር ኑሯቸው ተመልሰው ገዳም እንዲገቡ የተደረጉ እንዳሉ ይነገራል፣  ዘርዓ ያዕቆብን የቤተ ክርስቲያኒቱ ባለወለታ በማድረግ ያወድሱታል፤ታሪኩንም ሕዝቡ እንዲያውቀው ለማድረግ የተደጋገመ ወርክሾፕ በስሙ አድርገውለታል/እያደረጉለትም ነው፣  መጽሐፍ ቅዱስ የማያውቃቸውን አዳዲስ ቅዱሳንን ሳይቀር ሕዝቡ እንዲያውቃቸውና ጽላት/ታቦት እንዲቀረጽላቸው ያደርጋል፤ አድርጓልም /ምሳሌ አርሴማ የምትባልን ነጭ ሴት/፣  ለአባላቱ ሁለንታዊ ድጋፍና ስልጠና በትጋት ከማድረጉም ባሻገር በምረቃና በሰርግ ላይ ከበሮና ጸናጽን ይዞ በመገኘት በሚያደርገው ሞቅ ያለ የሽብሸባ አምልኮ ከጴንጤዎች ጋር ውድድር የገባ አስመስሎታል፣  ሕንጻ ይገነባል፣ ንግድ ይነግዳል፣ ገንዘብ ይሰበስባል፣ አባላትን ያደራጃል /ከቀን ሰራተኛ እስከ ምሁር ባለስልጣናት ድረስ/፣  በዩኒቨርስቲዎችና ኮሌጆች ውስጥ የሚማሩትን ተማሪዎች በማሰልጠንና በእረፍታቸው ወቅት ወደየቤተ ሰቦቻቸው በመላክ ዓላማቸውን በሰፊው እንዲያስተዋውቁላቸው ያደርጋል //ይህን በተመለከተ አንድ በመንፈሳዊም ሆነ በታሪክ በቂ እውቀት የሌለው /ከስሜታዊነት በስተቀር/ የወንድሜ ልጅ መሳተፉን አጫውቶኛል//፣  ማህበሩ በሚያደርገው አጠቃላይ እንቅስቃሴ አባላቶቹንና የዋሁን ሕዝብ ፍጹም የጉልበት ሃይማኖተኛ እያደረገው እንደሆነ በአንዳንድ ደብር በስሜታዊ አባላቱ በኩል የሚታዩት የደም መፋሰስ ግጭቶች ይመሰክራሉ፣  አዳዲስ የቤተ ክርስቲያን ሕንጻ ሥራ ላይ በሙያተኞቹ በኩል በሰፊው ይሳተፋል፣  ጎልቶ የሚታየው ሌላው ሥራው በቤተ ክርስቲያኒቷ ውስጥ ከሚገኙ አገልጋዮች መካከል አንዳንዶችን በመክሰስና ከሥራ በማሳገድ እስከ ቤተሰባቸው ችግር ላይ እንዲወድቁ ያደርጋል /ይህ በደል የደረሰባቸውን አንድ ሊቅ ይህ ጸሐፊ አናግሯል/፣  ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ተሃድሶ ያስፈልጋታል የሚሉትን ጳጳሳት፣ ካህናት፣ መሪጌቶች፣ መነኮሳት፣ ዲያቆናትና አባላትን በሙሉ የፕሮቴስታንት ቅጥረኞችና ጸረ ኦርቶዶክስ ናቸው በማለት በመጽሄታቸው፣ በጋዜጣቸውና በአውደ ምህረት ላይ በማውጣት ከፍተኛ ዘመቻ ያደርጋል።
ይቀጥላል


Sunday, March 13, 2016

እነሆ ሁለቱ ኪዳናት!

መቅድም
 ‹‹እነሆ ሁለቱ ኪዳናት›› በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ይህ መጽሐፍ በ2002 ዓ.ም ‹‹ሁለቱ ኪዳናት›› በሚል ርዕስ በመሪጌታ ሃየሎም ተዘጋጅቶ በማኅበረ ቅዱሳን አሳታሚነትና አከፋፋይነት በተሠራጨው መጽሐፍ ውስጥ ለተላለፉት ኢ-ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮዎች መልስ ለመስጠት ቢሆንም በችግሮቹ ላይ ብቻ ከማትኮር ይልቅ አንባቢያን ሃሳቤን በቀላሉ እንዲረዳልኝ ያስችላሉ ያልኳቸውን መሠረታዊ የመጽሐፍ ቅዱስና የታሪክ እውነታዎች በማሰባጠር በማስረጃ አስደግፌ ለማቅረብ ሞክሬያለሁ፡፡ የዚህን ጽሑፍ ረቂቅ ያሳየኋቸው አንዳንድ ወንድሞች የሁለቱ ኪዳናትን ጸሐፊ፣ አርታኢና አሳታሚ ማኅበር የእምነት አቋም ተወራራሽነት ለመግለጽ የተጠቀምኩባቸውን የወል ዐረፍተ ነገሮች ባስተካክላቸውና በጸሐፊው ላይ ብቻ አትኩሬ መልእክቴን ባስተላልፍ እንደሚሻል አስተያየት ሰጥተውኛል፡፡ ሃሳባቸውን በሃሳብነቱ ብቀበለውም እንዳሉት ሶስቱን አካላት ነጣጥዬ ማየት ግን አልሆነልኝም፡፡ ለዚህም ምክንያቴ አርታኢው ከአርትዖት ተግባሩ ባሻገር የመጽሐፉን መግቢያ በማዘጋጀትና በመጽሐፉ የተካተተውን አስተምህሮ ‹‹ትክክለኛነት›› አጽንኦት ሰጥቶ በማስተጋባት እንዲሁም ማኅበሩ በሐመረ ተዋሕዶ 2001 ዓ.ም ልዩ እትሙ‹‹እቅበተ እምነት (አፖሎጂ) በቅድስት ቤተ ክርስቲያን›› በተሰኘ አምድ ሥር ‹‹ሁለቱ ኪዳናት ማኅበረ ቅዱሳን በተለያየ ጊዜ በመጻሕፍትና በመጽሔት በቃል ትምህርትም መናፍቃን ለዘሩት የጥርጥር ትምህርት መልስ የሰጠበት መጽሐፍ›› ነው ብሎ መገለጹ በመጽሐፉ ውስጥ የሚገኘው የእምነት አቋም የጸሐፊው ብቻ ሳይሆን የአርታኢውና የማኅበሩ ጭምር መሆኑን የሚያረጋግጥ መሆኑ ነው፡፡ ስለዚህ በዚህ መጽሐፍ በተገለጠው የትምህርት አቋማቸው ብርሃኑ፣ ሐየሎምና ማኅበረ ቅዱሳን የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ናቸውና ብርሃኑንም ሆነ ሐየሎምን ሳመሰግን ሶስቱንም ማመስገኔ፣ እንዲሁም የብርሃኑንም ሆነ የሐየሎምን ሃሳብ ስቃወም ሁሉንም መቃወሜ መሆኑን ማስገንዘብ ተገቢ ሆኖ አግኝቸዋለሁ፡፡ በእኔ እምነት ብርሃኑ ስለማያምንበት ነገር መንደርደሪያ አልጻፈም፤ ማኅበረ ቅዱሳንም የእምነት አቋሙ ያልሆነን ትምህርት አሳትሞ አላሰራጨም፤ ለመናፍቃኑ የተሰጠ መልስ ነው እያለም አልፎከረምና ከምስጋናውም ሆነ ከወቀሳው ሊጎድሉ አይገባም ብዬ ሁሉንም ያለ ልዩነት እንዲጋሩት አድርጌያለሁ፡፡

እንደማምነው ካራ፣ ቅባት እና ጸጋ ሁሉም የተዋሕዶ አማኞች ናቸው፡፡ እንግዳ አመለካከት ሊመስል ቢችልም እንኳ ንስጥሮስ፣ አቡሊናርየስ፣ አውጣኬና ፓፓ ሊዮም ሳይቀሩ የዚሁ የተዋሕዶ ጽንሰ ሃሳብ አራማጆች ናቸው፡፡ ልዩነቱ የተፈጠረው ተዋሕዶን ለመግለጽ በተጠቀሙበት ቃል ትንታኔ ላይ ነው፡፡ አውጣኬ ተዋሕዶውን ያስረዳበት መንገድ መለኮት የሥጋን ባሕርይ መጥጦታል የሚል በመሆኑ መጠፋፋትን እንጂ የሁለቱን ባሕርያት መገናዘብ አያስረዳም መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረትም የለውም ተብሎ ተወገዘ፡፡ አቡሊናርየስ ክርስቶስ የሰው ነፍስ የለውም፤ በነፍሱ ምትክ ነፍስ የሆነለት መለኮት ነው አለ፡፡ በዚህም የክርስቶስን ፍጹም ሰውነት አጎደለ ተብሎ ተተቸ፤ ተለየ፡፡ ንስጥሮስም በበኩሉ የቃልና የሥጋ ተዋሕዶ ሁለቱ አካላት የየግል አቋማቸውን ጠብቀው የየራሳቸውን ሥራ እየሠሩ የሚኖሩበት ስምምነት (moral union) ነው አለ፡፡ እንደ እርሱ አባባል መለኮት በሥጋ ውስጥ አደረ እንጂ ባሕርያዊም ሆነ አካላዊ ተዋሕዶን አላስከተለም፡፡ ታዲያ ይህም ቢሆን የክርስቶስን አሐዱነት በተገቢው መንገድ አይገልጥም ተብሎ ተነቀፈ፡፡ በግልጥ እንደሚታወቀው የፓፓ ሊዮ አቋም ሁለት ባሕርያት በአንድ አካል የሚል ነው፡፡ ይህም ቢሆን ተዋሕዶን ምሉዕ በሆነ መንገድ አይገልጥም፡፡ አካል ያለ ባሕርይ ባሕርይም ያለ አካል ሊኖሩ አይችሉምና አንዱ የክርስቶስ አካል የማን ነው? የሚል ውዝግብ አስነሳ፡፡ ይህም አስተምህሮው በኦርየንታሎቹ ዘንድ ጥያቄ ላይ ወደቀ፡፡ በዚህም እንደሚታየው ፓፓ ሊዮም በሁለቱ ባሕርያት መኖር ላይ ከማትኮሩና የክርስቶስ አካል የመለኮት ነው ከማለቱ በቀር ተዋሕዶን አልተቃወመም፡፡ በመጀመሪያው የኤፌሶን ጉባኤ ተቀባይነት ያገኘው የቅዱስ ቄርሎስ የ‹‹ተዋሕዶ›› አስተምህሮ (ምንም እንኳ ምዕራባውያኑ በትክክል ባይረዱትና ከፓፓ ሊዮ የአንድ አካል ሁለት ባሕርይ፣ አልፎ ተርፎም ከአውጣኬ የመጠፋፋት ትምህርት ጋር ሊያመሳስሉት ቢሞክሩም) ሁለቱ አካላትና ሁለቱ ባሕርያት ሳይጠፋፉ፣ ሳይነጣጠሉ፣ ሳይቀላቀሉ አንዱ የሌላውን አካልና ባሕርይ ገንዘብ የተደራረጉበትን ከሁለት አንድ የመሆን ምስጢር (አንድ አካል፣ አንድ ባሕርይ፣ አንድ ፈቃድ፣ አንድ ግብር) የሚያስገነዝብ ነው፡፡ ይህም በተዋሕዶ የተገለጠው ኢየሱስ ክርስቶስ ያከናወናቸው ተግባራት ሁሉ ይህ የሥጋ ነው ያኛው ደግሞ የመለኮት ነው ተብለው ሳይከፈሉ በአንዱ በክርስቶስ (ሥግው ቃል) የተከናወኑ ናቸው የሚል ነው፡፡ በዚህ አስተምህሮ መሠረት እንደ ንስጥሮሳውያንና እንደ ኬልቄዶናውያን (ፓፓ ሊዎ) ድካሙን ለሥጋ ብርታቱንና ማዳኑን ለመለኮት የመስጠት ሙከራ በብርቱ የተነቀፈ ነው፡፡ ከዚህ የተነሳ ከአውጣኬያውያንና ከነፓፓ ሊዮ የተዋሕዶ ሃሳብ በእጅጉ ይለያል፡፡ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንም በአቋም ደረጃ ይህንን ትቀበላለች፡፡

እንግዲህ በቤተክርስቲያናችን የሚታወቁት ሶስት ቡድኖች ምንም እንኳ ‹‹ተዋሕዶ›› ነን ቢሉም የተዋሕዶ አስተምህሯቸው ከላይ ከተገለጹት ተዋሕዶ ነን ባዮች ከየትኛው ምንጭ እንደተቀዳ በጥንቃቄ መፈተሽ ቀዳሚውንና ትክክለኛውን የተዋሕዶ እምነት ተገንዝቦ ለመከተልና ያለ እውቀት ከሚሰነዘር ትችት ለመታቀብ ያስችላል፡፡ ከዚህ የተነሳ የጥንቷ ቤተ ክርስቲያን በመጀመሪያው የኤፌሶን ጉባኤ ያጸደቀችውን የተዋሕዶ ጽንሰ ሃሳብ ከነአውጣኬና ከነንስጥሮስ የተዋሕዶ ትርጓሜ ለመለየትና አንባቢያንን ከድንጋሬ ለመጠበቅ ‹‹ትክክለኛው›› የሚል ገላጭ ቃል ተጠቅሜያለሁ፡፡ በኢትዮጵያውያኑ የእምነት ጎራዎች (ካራ፣ ቅባት፣ ጸጋ) አስተምህሮዎች ላይ የመጻፉ ጉዳይ ብዙም አልታየኝ ነበር፡፡ ሆኖም የአንዳንድ ጊዜ የገጠማቸው ግለሰቦችና ቡድኖች አስተምህሮ ምንጭ በብዙሃኑ ስለማይታወቅ ከነሰባልዮስና ከነአውጣኬ ወገን ተሰልፈው የነቄርሎስን እምነት እንከተላለን እያሉ እውቀቱ የሌለውን ምእመን ከማደናገር አልፈው በመጽሐፍ ቅዱስ የተገለጠውን የእግዚአብሔር ቃል በመቃወም ላይ ስላሉና የእነርሱን ፈለግ ያልተከተሉትን ሁሉ እያሳደዱ እውነተኛ መስለው ለመታየት ሌት ከቀን እየተጣጣሩ ስለሚገኙ የአሳዳጆቹም ሆነ ተሐድሶ ናቸው በሚል ሽፋን እየተሳደዱ ያሉት ወገኖች ማንነት በግልጽ ይታወቅ ዘንድ እንዳልኩት ብዙም ትኩረት ላደርግባቸው የማልፈልጋቸውን ሶስት ቡድኖች አስተምህሮ ከመረጃ መጻሕፍት አሰባስቤ ለማቅረብ ተገድጃለሁ፡፡ በተለይ ማኅበረ ቅዱሳን የነቄርሎስን የተዋሕዶ ለምድ ለብሶ የሚያቀነቅነው ‹‹ሰባልዮሳዊ›› እና ‹‹አውጣኬያዊ›› ተዋሕዶ ፍንትው ብሎ ይታይና ትክክለኛው ማንነቱ ይገለጥ ዘንድ ይህንን ማድረጌ ተገቢ እንደሆነ አምናለሁ፡፡ በተረፈ ወደ መሠረታዊው ሃሳቤ ለመሸጋገር አንድ ጸሐፊ በተናገሩት ቁም ነገር ሃሳቤን ልቋጭ፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ይህ ትውልድ የሚፈልገውን እውነት በውስጧ ይዛለች፡፡ ነገር ግን እውነቷን ባልተዛባና ትውልዱ በሚፈልገው መንገድ ገልጣ ልታቀርብ አልቻለችም አብዛኛዎቹ የስብከት መድረኮቿ የተሞሉት ሌላውን በመንቀፍ ወግና ሥርዓትን ታሪክን በመተረክ ላይ በተመሠረቱ ስብከቶች ነው፡፡ በማኅበርና በግል ደረጃ በጽሑፍ የሚተላለፉ መልእክቶችም ይኸው ገጽታ ነው ያላቸው፡፡ ያለባትን ችግር በመረዳት በሚፈለገው ሁኔታ ወንጌልን የሚሰብክ አንድ ሰው ቢነሳ እንኳ በጥርጣሬ መንፈስ እየታየ በተለያዩ ውንጀላዎች ከመድረክ የሚወገድበት መንገድ ይፈለጋል (አግዛቸው ቀ.አ፡5)፡፡

ለእኔም እውነታው ይኸው ነው፡፡ የዚህም ምክንያቱ የአውጣኬያዊውና የሰባልዮሳዊው ተዋሕዶ ትምህርት በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ ሠርጎ መግባቱ ነው፡፡ እንደ ተባለው የከበረ እውነት አለን፤ ነገር ግን በዘመናት ሂደት ውስጥ ተቀብሯል፡፡ ስለዚህ የተቀበረው እውነት ተፈልፍሎ ሊወጣና ምእመኑ በግልጥ እንዲያውቀው ሌሎችም ቢሆኑ መሠረታዊውን የተዋሕዶ አስተምህሮ ተገንዝበው አጓጉል ነቀፋዎችን ከመሰንዘር እንዲቆጠቡ ማድረግ ይገባል፡፡ ለዚህም ብርቱ ትግል፣ ለመታገልም እውነቱን ከሃሰቱ መለየት ያስፈልጋል፡፡ ለዚህ ደግሞ ከጥላቻ በጸዳ መንፈስ ከማንበብና ከመወያየት የተሻለ መንገድ የለም፡፡ አለመደማመጥና ምን ያመጣሉ ለሮም ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያንም እንዳልበጃት ከታሪክ መማር ይገባል፡፡ ስለዚህ ንባብዎ እውነቱን ለመፈለግና በመመካከር መልካሙን መንገድ ለመከተል ይሆን ዘንድ ከልቤ እመኛለሁ፤ እጸልያለሁም፡፡ ሌላው ምናልባት ላሳውቀው የሚገባኝ መልሱ የዘገየበትን ምክንያት ነው፡፡ እንደ ክርስቲያን የእግዚአብሔር ጊዜ እስኪደርስ ነው ብዬ ባስብም ይህ ጽሑፍ ከታሕሣስ 2003 ዓ.ም ጀምሮ እስከዚህ ጊዜ ድረስ በእጄ ላይ እየተንከባለለ ድፍን አምስት ዓመታት ማስቆጠሩን ሳስበው በጥቂቱ አዝናለሁ፡፡ በሌላ መልኩ ምንም እንኳ እንዲታተም ብዙ ጊዜ ተመኝቼ ባይሳካልኝም እንደ ቀልድ ባለፉት በእነዚያ ዓመታት ውስጥ እኔ ባደግሁበት ዕድገት ልክ የማደግና የመብሰል ዕድል አግኝቷልና ደስ ይለኛል፡፡ ምናልባትም ቀድመውና ዘግይተው ከተጻፉ ጓደኞቹ ይልቅ የመታተሙን ቅድሚያ እንዲያገኝ የረዳው ይኸው ሳይሆን አይቀርም፡፡ እንዲህም ሲሆን ፍጹም ነው ማለቴ አይደለም፡፡ ይልቁንም ገና ‹‹ሁ›› ስለሆነ ከስህተትና ከችግር የጸዳ ላይሆን ይችላል፡፡ ስለዚህ አንብባችሁ በምትሰጡኝ ምክርና ተግሳጽ ታግዤ ስህተቴን በማረም የተሻሉ ሥራዎቼን ይዤ እንደምቀርብ ተሥፋ አደርጋለሁ፡፡ እስከዚያው መልካም ንባብ!!!
                         ጸሐፊው

Tuesday, June 30, 2015

ክርስትናን አጋድመው ያረዱት..."


(ያሬድ ሹመቴ)

ከዚህ በታች የማስነብባችሁን ጽሁፍ ከዚህ ቀደም በጨርቆስ ተገኝቼ የሰማውትን በዚሁ መገናኛ መድረካችን ላይ አስነብቤያችሁ ነበር።
ከሰሞኑን በአሜሪካን ሀገር በግብረ ሰዶም ተግባር ላይ እጅግ አስነዋሪ የጋብቻ ህግ መጽደቁን ተከትሎ ልንነጋገርበትና መንፈሳዊ ምግብ እንሰንቅበት ዘንድ የመጋቢ ሀዲስ እሸቱን ስብከት ከመድረኩ የሰማውትን ለንባብ እንዲመች አድርጌ በማቀናበር በድጋሚ እነሆ ብያለው።
"ሰው ብቻ አትሁኑ" መ.ሀ.እሽቱ
"...ሰው ብቻ ማለት ምንድን ማለት ነው? ብዬ ሳስብ፤ የሚበላ፣ የሚጠጣ፣ በሚለብሰው ልብስ፣ በሚነዳው መኪና የኑሮን ስኬት የሚለካ ማለት ነው። እስከ ሞት የሚኖር ማለት ነው፦ እንደ እንስሳ።
"...ታላቁ ሊቅ ዮሀንስ አፈወርቅ እንዲህ ይላል 'ሰው እግዚአብሄር ሲለየው' ይላል። ሰው እግዚአብሄ ሲለየው፤ ጠባዩ እንደ አራዊት፤ አመጋገቡ እንደ እንስሳ፣ ሆኖ መልኩ ብቻ የእግዚአብሄር ሆኖ ይቀራል። በጣም ቀለል ባለ አገላለጽ ሲም ካርዱ የወጣ ሞባይል ማለት ነው። ጥሪ የማይቀበል። ለጉትቻ ማንጠልጠያ ብቻ የተሰራም ጆሮ አለ።"
"...እኔ በዕውነቱ ከተማው ፈርሶ እየተሰራ ነው እየተባለ አይናማዎቹ ሲያወሩም ሲያስወሩም እሰማለው። ፈርሶ መሰራት ያለበት የሰዉ አስተሳሰብ ነው።... የሰዉ አስተሳሰብ ፈርሶ ካልተሰራ፤ የተሰራ ከተማ ይፈርሳል። ጃፓንና ቻይና ሀገራቸውን ያለሙት መጀመሪያ አስተሳሰባቸውን አልምተው ነው። አስተሳሰቡ ያልለማ ህዝብ የለማውን ያወድማል።"
"...ምንድነው አሁን ያሳየሁዋቹ? (ትንሽ ጣታቸውን አውጥተው ወደላይ እያሳዮ) ይህች ጣት ብትታምም ሀኪም ቤት ብቻዋን ነው የምትሄው?... የማይመለከታቸው እነ ጉበት፣ እናፍንጫ፣ እነ እግር፣ አብረው ነው የሚሄዱት።"
"...ከረባት የሚታሰረው የት ላይ ነው?... አንገት ላይ የታሰረ ከረባት አካሄድን ይቀይራል። አሁን እግር ምን አገባው እውነት ለመናገር? (ከፍተኛ ሳቅ) ውድ መነጽር አይናቸው ላይ ያደረጉ ሰዋች አካሄዳቸውን ሁሉ ነው የሚቀየረው። አይን መነጽር ያደረገው መላ የሰውነት አካላትን ተክቶ ነው። ለዚህ ነው ታላቁ ሊቅ ዮሀንስ አፈወርቅ "እኛ የሰውነት ክፍሎች ነን ክርስቶስ ግን ራስ ነው" ያለው። ሰው እጁ ተቆርጦ ይኖራል፤ አይኑ ጠፍቶ ትኖራል። እራሱ ተቆርጦ ግን አይኖርም። እራስ ክርስቶስ ነው። እኛ ብንሞት (የሰማይ ህይወት) ይቀጥላል። የክርስትናው እራስ ክርስቶስ ስለሆነ።"
"ቤታችሁ ገብታችሁ እንድታጤኑት ነው። እነዛ... (ምንትስ) የምንላቸው ክርስቲያኖችን አርደዋል... ምዕራባውያኑ ደግሞ ክርስትናን እራሱን አርደውታል።....ወንድ ለወንድ፣ ሴት ለሴት፣ በቤተክርስቲያናቸው እያጋቡ፤ ክርስትናን አጋድመው ያረዱ ምዕራባውያን ናቸው። (ይህን ሁሉ ያመጣውም) የምዕራባውያን ልክ ያጣ ነጻነትና ገደብ ያለፈ ዝርክርክነት ነው።"
"እንደምታዩት እኔ አይነ ስውር ነኝ። ቀላል አይደለም.... እንክዋን ዘውትር ዓይን አጥቶ አንድ ቀን መብራት ሲሄድ ስንት እንደምታማሩ ታውቅታላችሁ። አንድ ቀን ግን አልቅሼ አላውቅም። ከሞት ወዲያ መብራት አለ። ከመቃብር በላይ መብራት አለ። ... ወደ መቃብር ሲወርድ ማንም ዓይነ ስውር ነው። ማንም አይኑ እያየ የተቀበረ የለም። ተስፋችን ግን ምንድን ነው? ከሞት ወዲያ ህይወት አለ። ከሞት ወዲያ ብርሀን አለ።"
"...አንድ አንድ ጊዜ እመኛለሁ። እማይረባ እማይረባ ነገር ስናይ (ዓይናችንን) የሚያጠፋ ቆጣሪ ቢኖር... መልካም ነገር እስክናይ ድረስ ለጊዜው የሚያጠፋ ቆጣሪ ቢኖር።
"አሁን እንደው ጆሮ በካርድ የሚሰራ ቢሆን ሀሜት እንሰማ ነበር?(ከፍተኛ ሳቅ)... የምንፈልገውን (ብቻ) አውርተን ስዊች ኦፍ እናደርገው ነበር። ስንት ዞማ ጸጉር ይዞ አስተሳሰቡ የከረደደ አለ።
"ጀርመን ሀገር ሄጄ ሲነግሩኝ፤ ባለ አምስት ኮከብ የውሻ ሆቴል አለ ተባለ። እኛ ሀገር አምስት ኮከብ ሆቴል ገብተው የበሉ ትንሽ ዝና (ሀብት) እና ትንሽ ስልጣን ያላቸው ናቸው። ማን ይገባል ከነሱ ውጪ። ግን ሰዋች ነን። የጀርመን ውሻ ዛሬም ውሻ ነው ለዘላለምም ውሻ ነው። እኛ ግን ሰው ነን።
እንደ ሰው አስቡ (ምዕመናን) በማርያም።"
" እስኪ እንደው ትዳራችሁን ገምግሙት ደስተኛ ናችሁ? እንደሰው እየኖራችሁ ነው? ሚስቶቻችሁን ታከብራላችሁ? ፖለቲከኞቹ የኪነጥበብ ሰዎቹ (እዚህ) አላቹ ሲባል ሰምቻለሁ። ቆም ብላችሁ ልታስቡ ይገባል።"
" እኛም የሀይማኖት ሰዎች ሰበክን ሰበክን፤ ስብከቱ የህዝቡን አመለካከት መቀየር ትቶ የኛን ኑሮ ቀየረ።(ከፍተኛ ሳቅ)... የሰበክነው ክርስቶስ ሳይታወቅ እኛ እንታወቃለን። ማስታወቂያ ሰርተው ዝነኛ የሆኑ ሰዎች አሉ። ምርቱ ተሽጠ? ወይስ አልተሸጠም?" (ከፍተኛ ሳቅ)
" ተርቦ ያበላን፣ በክራይ ቤት እየኖረ እኛን በቪላ ቤት ያኖረን፣ እሱ በግሩ እየሄደ ለኛ መኪና የገዛልንን፤ ዝነኛ ያደረገንን ህዝብ እኛ አመለካከቱን ልንቀይረው ይገባል። አለባበስን መቀየር ቀላል ነው አስተሳሰብን መቀየር ግን ዋጋ ያጠይቃል።"
"የግሪክ ፈላስፎች እነ ሶቅራጥስ የህዝቡን አመለካከር ለመቀየር ደከሙ። ዛሬ በኢኮኖሚ ውድቀት የምትንገላታ ግሪክ ናት፦ የነ ሶቅራጥስ ሀገር። 'ሀገር ሲያረጅ ጃርት ያፈራል' ይባላል። እኛ እንክዋን ይክበር ይመስገን ኢትዮጵያውያን ነን።"
"አሁንም ደግሜ እናገራለው። ይሄን ችግር ያደረሱብን ኢትዮጵያውያን አይደሉም። (እዚህ ያሉት) ጎረቤቶቻችንን እነ መሀመድ እነ ከድጃ... ስጋዎቻችን፣ ደሞቻችን፣ አካሎቻችን ናቸው።"
"ልብ ካለ ሊቢያ ሄዶ እናዛን መፋለም ነው። '... ቢያሸንፈው ወደ ሚስቱ ሮጠ' ይባላል። አንድ አንድ አባ ወራ አለ ቡና ቤት ሄዶ ከዚያ መልስ ቅዳ (ሂሳብ በኔ ነው) ይላል። (ሚስቱ) የወር ወጪ ስትጠይቀው፤ ጥጦ እንደተነጠቀ ህጻን የሚያለቅስ።"
"...ወቀሳ አበዛሁ?(የተሰበሰበው ህዝብ ከሳቅ ጋር አላበዙም አለ) ማርያምን?... ኮሶ የሚጠጣው ስለሚጣፍጥ አይደለም ስለሚያሽር(ስለሚያድን) ነው። ለመጣፈጥማ ስኩዋር ይሻል ነበር ግን ወስፋት ነው ትርፉ።" (ሳቅ)
"...የንጉሰ ነገስቱ የክርስቶስ አልጋ ወራሾች ነን... የደስታችሁ ልኬት የደስታችሁ ሚዛን ምግብና መጠጥ አይሁን፤ መኪናና ቤት ዝናንም አታርጉ። እኛ መለኪያችን ጽድቅ ነው። መከኪያችን መንግስተ ሰማያት ነው። ያ የምንገባበት ቤት ደግም የተዋበ፣ የደመቀ፣ መብራት ውሀ የማይሄድበት፤ 24 ሰኣት ክርስቶስ የሚያበራበት፤ 24 ሰኣት የህይወት ውሀ የሚጠጣበት፤ ሀብታም፤ ደሀ፣ተራሰው የማይባልበት፣ እገሌ ግባ እገሌ ውጣ የማይባልበት ቦታ ነው። ደህና እደሩ"
መጋቤ አዲስ እሸቱን ቃለ ህይወት ያሰማልን...
አሜን!

Wednesday, November 5, 2014

ማኅበረ ቅዱሳን ለቤተ ክርስቲያን መድኅን? ዋስትና? ጠባቂ? ወይስ ምንድነው?



1/ ማኅበረ ቅዱሳን ማነው? 

ከማኅበረ ቅዱሳን መሥራቾች አንዱ እንደሆነ የሚናገረው የሜሪላንዱ ኤፍሬም እሼቴ  ስለማቅ ጥንስስ እንደተረከው ብላቴ ጦር ካምፕ ውስጥ ተቀፍቅፈን፤ ዝዋይ ላይ በመፈልፈልና አዲስ አበባ ላይ ኅልውና አግኝተን ሕይወት ዘራን ሲል ይተርክልናል። የኅልውናቸውም መስራቾችና ፈልፋዮች ማንነት ኤፍሬም ዘለግ አድርጎ ሲናገር በኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ በመንደር ምሥረታ ታሪክ ውስጥ ብዙ ድርሻ የነበራቸው ሰዎች ባሉበት ሁኔታ የዳቦ ስም ወጥቶላቸው «ማኅበረ ቅዱሳን» እንደተባሉ «አደባባይ» በተሰኘው መካነ ጦማሩ እንዲህ እያለ ያወጋናል።
«ተማሪው በጋምቤላ፣ በመተከል፣ በወለጋ … ጎጆ ቤት ሲሠራ፣ ተፈናቃዩን ሲያቋቁም ቆይቶ ተመለሰ። በደህና ወጥቶ ለመመለስ ያልቀናውም ነበር። እነዚያ መንደር ሊመሠርቱ የወጡት ታላላቅ ወንድሞቻችን በየዛፉ ሥር፣ በየመንገዳቸው ጸሎተ ማርያም ማድረሳቸውን፣ ሲችሉም ተገናኝተው ቃለ እግዚአብሔር መስማታቸውን እንዳላስታጎሉ ሲናገሩ ሰምቻለሁ። እኛን ቃለ እግዚአብሔር ያስተማሩን የዚያ “መንደር መሥራች ትውልድአካላት የሆኑ ወንድሞች ናቸው። ወደ ዝዋይም የላኩን እነርሱ ናቸው። እኛ እና እነርሱ በአንድ ላይ ስንሆን ጊዜ በጋራ “ማ/ቅዱሳን” ተባልን።»
በእርግጥ የዚያን ዘመን መንደር መሥራች ትላልቅ ወንድሞች የተባሉት ማኅበሩን የመሠረቱበት ዓላማ ግልጽ ባይሆንም ኤፍሬምን ጨምሮ አብዛኛው የማኅበሩ አባላትን ግን ያሰባሰባቸው እምነታቸው ስለመሆኑ ከጥርጣሬ የሚወድቅ አይደለም። ያሳደጋቸውም የቤተ ክርስቲያን ቅናት ብቻ ነበር። ሲመሰረትም የወንድሞች ማኅበር «ማኅበረ ቅዱሳን» ከዚያ ከትንሹ ጅምር ተነስቶ ይህንን ያህል በመግዘፍ ሀገራዊ ማኅበርና የሲኖዶስ ጉባዔ የየዓመቱ የመነጋገሪያ አጀንዳ ይሆናል ብሎ የገመተ አይኖርም ይሆናል። ምናልባት ትላልቅ ወንድሞች የተባሉት እግር በእግር እየተከታተሉና እየኮተኮቱ ያሳደጉበትን  ኅቡእ አጀንዳ ራሳቸው ያውቁ እንደሆን እንጂ ዛሬም ድረስ ከጥቂቶች በስተቀር አብዛኛው የማኅበሩ አባላት እያገለገሉ ያሉት ቤተ ክርስቲያናቸውን እንደሆነ መገመት ይቻላል።
 ነገር ግን ግዝፈቱ እውን እየሆነ ሲሄድ ወደ ረጅም ህልምና ራእይ የመድረስ ስንቅ ሳይቋጥር አልቀረም። ኅልውናውን የሚያስጠብቅበትን የሕግ ማዕቀፍ መጎናጸፍ፤ የድርጅት ኃይል ማሳደግ፤ የገንዘብ አቅም ማጎልበት፤ የዓላማና ግብ ስትራቴጂ መቅረጽ ወዘተ ራሱን የሚያስጠብቅበት ቅርጽና መዋቅር እየያዘ እንደመጣ እርምጃዎቹ ዋቢዎቻችን ናቸው። ዓላማና ግብ ሳይኖረው ኅልውናውን ማስጠበቅ እንደማያስፈልገው ይታወቃል።  እዚህ ይደረሳል ብለው ያልገመቱ ቢገኙም ሂደት ራሱ በሚፈጥረው ስኬት ከተነሳበት ሃሳብ ወጣ ባለ መልኩ ወደሚፈልጉበት አዲስ ግብ ለመድረስ  ስትራቴጂ ቢኖራቸው አያስገርምም።  ትንሹ ትንሣዔው ስኬትን ሲያጎናጽፈው መድረስ የሚፈልገው ዓላማ ሊኖረው የግድ ስለሆነ ለዚህ ደግሞ ሁሉን መስዋዕትነት እንደሚከፍል አይጠረጠርም።
ማኅበረ ቅዱሳን በጥቂቶች አስተሳሰብ በእቅድ የተመሠረተ፤ በተራው አባል ግን በአጋጣሚ እግዚአብሔር ፈቅዶ የተቋቋመ ያህል የሚታሰብ ድርጅት ነው። መቋቋሙ በቀና ዓይን ቢታይ ባያስከፋም በተግባር ግን እየታየ የቆየው የተገላቢጦሽ መሆኑ እርግጥ ነው።

2/ ማኅበረ ቅዱሳን ለማኅበረ ካህናቱ ምንድነው?

ዛሬ ላይ ማኅበሩ ያለው ስትራቴጂ  የተነሳበት ነበር ወይ? ብለን ብንጠይቅ መልሳችን አይደለም ነው።  ከላይ እንደተመለከትነው ማኅበሩ ሲነሳ አብሮ ለመዘመርና ለማማር የተሰባሰበ እንጂ የዚህን ያህል ስፋት ያለው ርቀት እሄዳለሁ ብሎ አልነበረም። ይህ ሲባል ግን የሚሄድበትን ርቀት እየለኩ የሚመሩት ሰዎች አልነበሩትም ማለት አይደለም። በዚህም የተነሳ ጉዞውን ለማሳካት የሚሄድበት ርቀት ከተነሳበት ዓላማ ጋር በእጅጉ የሚጣረስ ሆኖ ይታያል።  ተወዳጅነት ያገኘውን ያህል የተቀባይነት ማጣት ግጭትና ዓላማን ለማሳካት የሚደረገው ስልት ከፊት ለፊት ተቃውሞ መፍጠሩ አልቀረም። ለዚህም ነው ማኅበሩን ባልተቀበለው የቤተ ክህነቱ አባላት ዘንድ እርቅ ወደሌለው ቅራኔ እየከተተው የሚገኘው። ማኅበሩ አብዛኛውን በሚል ደረጃ በአባልነት የያዛቸው የየአጥቢያውን ሰንበት ተማሪዎች፤ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች እንዲሁም በራሳቸው ተነሳሽነት ተሰባስበው በዓመታዊው የጥምቀት በዓል ላይ ታቦታት ሲወጡና ሲገቡ ቄጠማ በመጎዝጎዝ ይሳተፉ የነበሩትን ወጣቶች ማኅበሩ መልክና ቅርጽ በመስጠት ወደራሱ ዓላማ በመሳብ «የጥምቀት ተመላሾች ማኅበር» በሚል ያደራጃቸው ናቸው። ማኅበሩ የፖለቲካ ድርጅት የሆነ ያህል አሁን በሥልጣን ላይ ያለውን መንግሥት በሚጠሉ ፖለቲከኞች ሁሉ እንደ አንድ አስፈላጊ አካል መቆጠሩ ሳይዘነጋ መሆኑንም ያስተውሏል። የዚህ አብሮነት ያገናኛቸው የእምነት ስምምነት ውል መኖሩ ሳይሆን ፖለቲካዊ ስልት መሆኑን ለማወቅ ብዙም ምርምር አይጠይቅም።
 ከዚያ በተረፈ ማኅበረ ቅዱሳንን ከጥቂት የጥቅም ተጋሪዎችና በፍርሃት ቆፈን ከተያዙት በስተቀር አብዛኛው የቤተ ክህነቱ ሰው ግን «ዓይንህን ላፈር» እንዳለው ይገኛል። የማኅበረ ቅዱሳን ኅልውና እንደሪፈረንደም በቤተ ክህነቱ አባላት ድምጽ የሚወሰን ቢሆን ኖሮ አንድም ቀን ኅልው ሆኖ ሊኖር እንደማይችል በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል።  ምንም እንኳን ማኅበረ ቅዱሳን የቤተ ክህነቱን ኃይል ማሳኝና አማሳኝ እያለ በደፈናው ንቆ ቢጨፈልቅም ማኅበሩ እንደሚገምተው በቀላሉ እጁን የሚጠመዘዝ ኃይል አይደለም። የቤተ ክህነቱ ሰው  በክህነት አገልግሎት ላይ ስለሚገኝ  ሕዝበ ክርስቲያኑ ሁሉ ያለው በመንፈሳዊው የክህነት አገልግሎት ስር ነው።  ስለሆነም የማኅበረ ካህናቱን ኃይል ከህዝበ ክርስቲያኑ መነጠል አይቻልም። ስለዚህ የዚህ ኃይል ማኅበረ ቅዱሳንን መቃወም መቻሉ የማኅበሩን የወደፊት ኅልውና የመወሰን አቅም አለው። ማኅበሩ ደግሞ ከዚህ ከክህነት አገልግሎቱ ኃይል ጋር ዓይንና ናጫ ሆኗል። በማኅበሩ የሚደረገው የስለላ፤ የመረጃ፤ የስም ማጥፋት፤ የአድማ፤ ከስራ የማስባረር፤ ዋስትና የማሳጣት፤ መተማመንን የማዳከም ተግባራቱ በክህነት አገልጋዩ ዘንድ በሰፊው ስለታወቀ መቼም ቢሆን መተማመን እንዳይኖር አድርጎታል።

 በማኅበረ ቅዱሳንና በማኅበረ ካህናቱ መካከል ያለው የዓላማ ቅራኔ የሚፈጥረው ሽኩቻ ቤተ ክርስቲያኒቱን ከማዳከም በዘለለ አንዳችም ትርፍ አላስገኘም። ማኅበረ ቅዱሳን ዓላማው አጠቃላይ ማኅበረ ካህናቱን በራሱ ፖሊሲና ስትራቴጂ ማጥመቅ ሲሆን ማኅበረ ካህናቱ ደግሞ ይህ ማኅበር ከቤተ ክርስቲያን ተወግዶ ማየት በመሆኑ ልዩነቱን የማይታረቅ አድርጎታል።
ማኅበረ ቅዱሳን በካህናቱ በኩል የሚታየው እንደፍልስጣ ኃጢአትን መዝግቦ እንደሚከስ ባላንጣ እንጂ እንደቅዱሳን ስብስብ አይደለም። ማኅበረ ቅዱሳን ለማኅበረ ካህናቱ የፈየደው አንዳችም ነገር አለ ተብሎ አይታሰብም። ምክንያቱም ማኅበሩ በክህነት አገልግሎት አያግዝም። በምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ከማኅበረ ካህናቱ የተሻለ ዕውቀት የለውም። ከሕዝበ ክርስቲያኑ ጋር ከካህናቱ በተሻለ ሁኔታ በዕለት ዕለት ቅርርብ አይመሰከርለትም። ስለዚህ ማኅበረ ቅዱሳን ማለት ለካህናቱ ምንም ማለት ነው።

ይህ ባለበት ሁኔታ ሳለ መልካም ግንኙነት መመሥረት የሚችልበትን ዕድል በማበላሸት የካህናቱን ሥነ ምግባር በማጉደፍ፤ አደባባይ ላይ በማዋልና ስም በማጥፋት ላይ በመሰማራቱ ከካህናቱ ጋር ለመተሳሰር ምንም ድርሻ የሌለው ማኅበር ሆኖ ቀርቷል።  ሁሉም ሰው «ነግ በኔ» በሚል ፍርሃት በአንድነት በተቃርኖ የቆመበት ማኅበር ነው። ይህ  የቅራኔ ግንኙነት መቼ ይሻሻላል? ቢባል መቼም የሚታረቅ አይደለም እንላለን። የማኅበሩ ዓላማና ግብ በራሱ ጳጳሳት የሚመራ ሲኖዶስ አቋቁሞ፤ በራሱ ጳጳሳት የሚሾሙ ማኅበረ ካህናትን መስርቶ አሁን ያለውንና የማይቀበለውን የማኅበረ ካህናት አስወግዶ የራሱን መዋቅር መዘርጋት በመሆኑ አሁን ካለውና ከሚቃወመው ጋር መቼም ቢሆን እርቅ ይኖረዋል ተብሎ አይጠበቅም።ስለሆነም ማኅበሩ ከአጠቃላይ ማኅበረ ካህናት ጋር ሰላም ሊመሰርት አይችልም ብሎ መደምደም ይቻላል። ማኅበሩም ራሱ ዓላማውን ለማሳካት የሚሄድበት መንገድ ከቤተ ክርስቲያኒቱ ካህናት ጋር ለመስማማት የሚያስችል ተፈጥሮ ላይ የተመሠረተ አይደለም። 

3/ ማኅበረ ቅዱሳን ለቤተ ክርስቲያኒቱ ምዕመናን ያበረከተው ምንድነው?

ከላይ ለመጥቀስ እንደተሞከረው ማኅበረ ቅዱሳን በቤተ መቅደሱ የክህነት አገልግሎት ላይ የተሰማራ ባለመሆኑ ለምዕመናኑ ከካህናቱ በተሻለ የሚሰጠው አገልግሎት ይኖራል ተብሎ አይታሰብም።
 በየአድባራቱ ወይም በየገዳማቱ ከምዕመናን አባላቱና ከሰንበት ትምህርት ቤቶች ወጣቶች ጋር ያለውን ቅርርብ በመጠቀም ዓላማና ግቡን ለማስረጽ በሚያደርገው ትግል ውስጥ ከካህናቱ በኩል ያለውን  ተቃውሞ ለመከላከል ሲል ለቤተ ክርስቲያን የሚቆረቆር በመምሰል ስም በማጥፋት፤ በአድማና በህውከት ከቦታቸው እንዲነሱ፤ እንዲጠሉ በማስደረግ ወይም ዝም ጭጭ ብለው፤ አንገታቸውን ደፍተው እንዲኖሩ በሚያደርገው ተግባሩ ያተረፈው ነገር ቢኖር የቤተ ክርስቲያኒቱ አባላት ወደሌሎች ቤተ እምነቶች መኮብለል ብቻ ነው። በሐረር፤ በድሬዳዋ፤ በደቡብ፤ በምዕራብና በምሥራቅ የሀገሪቱ አካባቢዎች ያሉ የቤተ ክርስቲያኒቱ አባላት እንደጎርፍ ቤተ ክርስቲያኒቱን ትተው የኮበሉለት ማኅበረ ቅዱሳን በየቦታው በፈጠው ሁከትና ብጥብጥ የተነሳ ነው።

   በእርግጥ አንዳንዶች ማኅበረ ቅዱሳን ለቤተ ክርስቲያኒቱ አባላት ባሉበት መርጋት ትልቅ ሚና ተጫውቷል ቢሉም ተረትና እንቆቅልሽ ለማስተማር ካልሆነ በስተቀር ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንን የመተካት አንዳችም አቅም የሌለው ድርጅት ነው።
መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ከ1960 ዓ/ም በፊት ከ1% በታች የነበሩት የፕሮቴስታንት ቤተ እምነቶች እስከ 1984 ዓ/ም ድረስ 5.5% ሲደርሱ እስከ 1994 ዓ/ም ድረስ በዐሥር ዓመት ውስጥ ብቻ 10.2% ለመድረስ በቅተዋል። አሁን ባለው ስታስትስቲክ የፕሮቴስታንቱ ቁጥር ከሀገሪቱ ሕዝብ ውስጥ 18.6% ፐርሰንት መድረሱን ያሳያል። በተቃራኒው ደግሞ ከሀገሪቱ ሕዝብ 60% ገደማ የኦርቶዶክስ ቤተ እምነት ተከታይ የነበረው ቁጥር በአስደንጋጭ መጠን ወደ 43.5% ያሽቆለቆለው ባለፉት ዐሥርተ አመታት ውስጥ መሆኑ የሚያሳየን ነገር የማኅበረ ቅዱሳንን የስብከትና እንቅስቃሴ ምዕመናኑን ከመበተን ይልቅ በቤታቸው የማቆየት አቅም እንዳልነበረው አረጋጋጭ ነው። 
ወደፕሮቴስታንቱ ጎራ ከኮበለለው 17% ገደማ የሚሆነው ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የወጣ መሆኑ እርግጥ ነው። ማቅ እንኳን ከሌላ ቤተ እምነት ሰብኮና አሳምኖ ሊያመጣ ይቅርና ያሉት ተረጋግተው እንዳይኖሩ ሲሰራ የቆየ መሆኑ አይታበልም። የማኅበረ ቅዱሳን የተረትና እንቆቅልሽ አስተምህሮ ማንንም ሰብኮ መመለስ እንደማይችል ይታወቃል።

  የሁሉም ነገሮች ችግር መነሻው ማኅበረ ቅዱሳን ነው ባይባልም ምዕመናን በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ሲሳሳቱ በቤተ ክርስቲያኒቱ ሊቃውንት በኩል አስተምሮና ናዝዞ ከመመለስ ይልቅ ተሐድሶ፤ጴንጤ፤ መናፍቅ፤ ሌባ፤ ዘማ፤ ነፍሰ ገዳይ እያለ በመፈረጅ በፍርሃት እንዲኮበልሉና እንዲሰደዱ በማድረግ በኩል የማኅበረ ቅዱሳን ድርሻ ወደር የለውም። ማኅበረ ቅዱሳን ኖሮ ቤተ ክርስቲያን ከተጠቀመችው ይልቅ ማኅበሩ በየቦታው በሚፈጥረው ሁከትና ግርግር የተጎዳችበት ይልቃል።

4/ ማኅበረ ቅዱሳን ለቤተ ክርስቲያኒቱ ያበረከተው አገልግሎት እውነት እንደሚወራው ነው?

ሲጀመር ጀምሮ ማኅበረ ቅዱሳን የካዝና ቋቱንና ኪሱን ለቤተ ክርስቲያኒቱ አያሳይም። በሞዴላ ሞዴል ተጠቀም! ሂሳብህን አስመርምር! በምትሰራው ነገር ሁሉ የቤተ ክርስቲያኒቱን ፈቃድ ጠይቅ! መባሉ በቤተ ክርስቲያኒቱ ሥር የመሆኑ ማረጋገጫ  ካልሆነ በስተቀር ሀብትና ንብረቱን ስለመውረስ የሚያውጅ ድርጊት አልነበረም።  ከአባ ሠረቀ ብርሃን ጋር ያጋጫቸው ይኸው ዘራፍ ባይነቱ እንጂ አባ ሠረቀ ብርሃን ማኅበሩን የማፍረስ ዓላማ ስላላቸው አይደለም። ማኅበሩ የትኛውንም የቤተ ክርስቲያኒቱን ቁጥጥር መቀበል አይፈልግም። ለምን?

   ማኅበሩ ፈቃደኛ አለመሆኑ የሚያመለክተው ቢኖር አንድም ራሱ ብቻ አዋቂ ስለሆነ የቤተ ክርስቲያኒቱን አሠራር ይንቃል፤ አለያም ምን እየሰራ እንዳለ እንዲታወቅበት አይፈልግም። ስለዚህ ማኅበረ ቅዱሳንለቤተ ክርስቲያን  አበረከትኩት የሚለው አገልግሎት የስም፤ የዝናና ራስን ለማሳበጥ የሚጠቅምበት ስልታዊ እንቅስቃሴ ከመሆን የዘለለ አልነበረም ማለት ነው። 
ለምሳሌ ጣሊያን ኢትዮጵያን ከወረረች በኋላ በመንገድ ሥራ፤ በውሃ ቧንቧ ግንባታ፤ በመብራት ዝርጋታ ላይ ተሰማርታ ነበር። ኢጣሊያ ያንን ማድረጓ ወረራዋን ፍትሃዊ ሊያሰኘው እንደማይችለው ሁሉ ማኅበረ ቅዱሳን ፈጸምኳቸው የሚላቸው አንዳንድ እንቅስቃሴዎች  የማኅበሩን ኢፍትሃዊ እርምጃዎችን ፍትሃዊ ሊያሰኙት በጭራሽ አይችሉም። ስለዚህ ማኅበረ ቅዱሳን ተመስርቶ ከተከናወኑት ሥራዎች ይልቅ ቤተ ክርስቲያኒቱ በማኅበሩ የደረሰባት ወከባና ሁከት ዐሥር እጅ ይልቃል። ደግሞስ በ22 ዓመት ዓመት እድሜው «ጧፍና ሻማ ረዳሁ» ከሚል በስተቀር የጧፍና ሻማ ማምረቻ ሲገነባ አልቆየም። ይልቁንም ቤተ ክርስቲያኒቱን መስሎና አክሎ የሚንቀሳቀስበትን የግሉን ሕንጻና ሀብት ሲገናባ ኖሯል።  ሠራሁ የሚለውም ቢሆን በአካፋ ከዛቀው በማንኪያ እያካፈለ ላለመሆኑ ቤተ ክርስቲያኒቱ ባደረገችው ምርመራ አልመሰከረችለትም።  ያለውን የካዝና አቅም ከቤተ ክህነቱ መሸሸጉ የሚያስረዳን ነገር ቢኖር በአካፋ የዛቀውን በማንኪያ መስጠቱን እንጂ ሐቀኛነቱን አይደለም። አመራሮቹ እስከ 500 ሺህ ብር እየተበደሩ ሳይከፍሉ የውሃ ሽታ የሆነውን የገንዘብ ወጪ መረጃ በምን ሂሳብ ሊያወራርዱት? ተብሎ ለሚቀርበው መጠይቅ ሕጋዊ መልስ የለውም።  ስለዚህ ማኅበሩ ቤተ ክርስቲያኒቱ ጋሻዬ፤ መከታዬ ልትለው የምትችልበት ምንም ምክንያት የላትም።

5/ ለማኅበረ ቅዱሳን አሠራር ሁሉ ዋና ተጠያቂዎች ደጋፊ ጳጳሳቱ ናቸው!

ጳጳስ አይጠየቅም የሚል ልምድ አለ። መታወቅ ያለበት ነገር ጳጳስ ሰው መሆኑን ነው። እንደማንኛውም ሰው መሰናክል የሚገጥመውና ሰውኛ ድክመት ሊታይበት የሚችል ፍጡር መሆኑን መረዳት አለብን። እንዲያውም ቤተ ክርስቲያኒቱ በቀየረችው የጵጵስና ትርጉም የተነሳ የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳደር እየተበላሸ ሄደ እንጂ ጳጳስ መሆን የሚችለው በቤተሰብእ አስተዳደር ልምድ ያለውና የአንዲት ሴት ባል የሆነ ሰው መሆኑን ጳውሎስ ለጢሞቴዎስ በጻፈው መልዕክቱ በግልጽ ተቀምጧል። ጳውሎስ «ቤተ ሰብኡን በመልካም በማስተዳደር ያልተመሠከረለት፤ ቤተ ክርስቲያንን እንዴት ይመራታል?» በማለት መጠየቁ ጳጳሳት ስለተባሉት የቤተ ክርስቲያን መሪዎች እንጂ ዛሬ እንደሚነገረው በተናጠል ስለቀሳውስት አይደለም። በዚህ ዘመን ቀሳውስቱ መቼ የቤተ ክርስቲያን መሪዎች ሆኑ? መነኮሳቱ መሪነቱን ተረክበው ይዘውት አይደለም እንዴ ያሉት?
ወደርዕሰ አሳባችን ስንመለስ ጳጳሳት እንደማንኛውም ሰው ሊሳሳቱ ይችላሉ። በኃጢአትም ሊወድቁ ይችላሉ። እንኳን በዚህች ምድረ ፋይድ ያለው የሰው ልጅ ቀርቶ በገነት የኖረው አዳምም ተሳስቷል። ስለዚህ ጵጵስና ማዕርግ እንጂ ከኃጢአት የመንጻት ማረጋገጫ አይደለም። ሁለት ፓስፖርት ይዘው የሚኖሩ፤ በሚሊዮኖች ብር የሚገመት ቤት የሚገነቡ፤ እንደውሃ የሚፈስ መኪና በሚነዱበት ሀገርና ገንዘባቸው ባንክን ማጨናነቁ በሚነገርበት ዓለም ስለብቃት መናገር አይቻልም። የዘር ቆጠራውና የወንዜ ልጅ ዜማው የሚገነው በነዚሁ በጳጳሳቱ ላይ ነው። የሚነገረውና የሚወራው ሁሉ እውነት ባይሆንም ስለሥጋ ድክመትና ስለኃጢአት መኖር ግን ማንም ሊያስተባብል አይችልም። ስለዚህ ማኅበረ ቅዱሳንን በማወቅም ይሁን ባለማወቅ በማሳደግ፤ በማግነን አሁን ላለበት ደረጃ በማድረስ በኩል ጳጳሳቱ ኃላፊነት አለባቸው። የትውልድም፤ የታሪክም ተጠያቂነት እንዲሁም በሆነውና በሚሆነው ነገር ሁሉ በእግአብሔር ፊት ተጠያቂዎች ናቸው።
ጳጳሳቱ በተቀመጡበት የቤተ ክርስቲያን አመራር ወንበር ላይ መንፈሳዊ ይሁን ቁሳዊ ልማት የማምጣት፤ ሕዝቡን ወደ እድገትና ራስን ወደመቻል የሥራ አቅም የማሳደግ ኃላፊነት የተጣለባቸው ቢሆንም ይህንን ሲያደርጉ አይታዩም። ከዚህ ይልቅ በማኅበረ ቅዱሳን ባላ እየተደገፉ ስሙን ጳጳሳቱ ተሸክመው ሥራውን ለማኅበሩ በመስጠት ቤተ ክርስቲያኒቱ ከነበረችበት ፈቀቅ እንዳትል አድርገዋታል። ቤተ ክርስቲያኒቱ ካሏት ሁለት ኮሌጆች በስተቀር በሀገረ ስብከት ደረጃ አንድም ጳጳስ ኮሌጅ ወይም ሴሚናሪ ት/ቤት ከፍቶ አልታየም። የጧፍ ወይም የሻማ ማምረቻ ሠርቷል የሚል ዜና አልሰማንም። 
ምናልባት ወደፊት ቤተ ክርስቲያኒቱ የጳጳሳትን ሹመት ይሁን ያሉትን የማዘዋወር ሁኔታ ማከናወን ያለበት ከፈጸሙት ልማትና የሥራ ብቃት አንጻር መሆን እንዳለበት ሊሰመርበት ይገባል። ጵጵስናን በተመለከተ ከማዕርጉ የሚያስሽሩ ሁኔታዎችም ትኩረት ተሰጥቶባቸው የሕግ ማዕቀፎች ካልተሰራባቸው ቤተ ክርስቲያኒቱ የበለጠ ፈታኝ ሁኔታ እንደሚገጥማት ለማወቅ ነብይ መሆንን አይጠይቅም። ከካህናቱና ከሕዝቡ ዓይን የተሰወረ አንዳችም ነገር አይኖርም።
 ቤተ ክርስቲያኒቱ ለሁለት የተከፈለችውም ይሁን ክፍፍሉ ባለበት ቦታ ሁሉ ውስጧ የሚታወከው በጳጳሳቱ በራሳቸው መሆኑን ያየናቸው ተሞክሮዎች ያስረዱናል።

6/ ማኅበረ ቅዱሳንና የቤተ ክርስቲያኒቱ አስተምህሮ አይገናኙም!

ቤተክርስቲያን በመዋቅር የሊቃውንት ጉባዔ እንዳላት ይታወቃል። ይሁን እንጂ ይህ የሊቃውንት ጉባዔ የቤተ ክርስቲያኒቱን በዘመኑ ያሉ አስተምህሮዎች እየመረመረ ስህተቶችን እየለየ፤ በሐዋርያት መሠረት ላይ ያሉትን እያጸና እውነታኛውንና የቀደምት አበውን ትምህርት ሕዝቡን መመገብ ሲገባው እስከመኖሩ በማይታወቅበት ደረጃ ላይ መገኘቱ ያሳዝናል። ዛሬ ላይ የሊቃውንት ጉባዔውን ጉባዔ በአጅ አዙር በመረከብ በመመርመር ለስደትና ለውግዘት ተሰልፎ የሚገኘው ይህ ማኅበረ ቅዱሳን የተባለው ያልተማረው ሊቃውንት ጉባዔ ነው። በዚህ ማኅበር የተነሳ እውነት ተደፍቆ ተቀብሯል። ሊቃውንት ተሰደዋል። እነ ሆድ አምላኩና እነልጆቼን ላሳድግበት ብቻ ወንበር ይዘው ቀርተዋል። ይሁን እንጂ ይህ ድርጊት መቀጠሉ መልስ ያልተገኘላቸውን ጥያቄዎች ማስቀረት አልቻለም።ወደፊትም አይችልም። የተለመደው ባህላዊ እምነት ሳይነካ ባለበት ተሸፍኖ እንዲቀመጥ ማድረጉ ኩብለላውን አላቆመም።  ሊያቆምም አይችልም። ትውልዱ የሚነገረውን ብቻ እየሰማ የሚነዳ ሳይሆን የሚጠይቅም በመሆኑ ከፊት እየሄደ የሚመራ ሊቃውንት ጉባዔ ያስፈልግ ነበር። እንዳለመታደል ሆኖ ይህ አልሆነም። አሁን በሚታየው ሁኔታም መቼም ይሆናል ተብሎ አይጠበቅም። በዚህ ላይ የተረት አባትና የአፄው ዘውግ አንጋች ማኅበረ ቅዱሳንና ጳጳሳቱ እያሉ የወንጌል እውነት ተገልጦ፤ የአበው አስተምህሮ አደባባይ ላይ ይነገራል ማለት ዘበት ነው። ተረትና እንቆቅልሽ፤ ባህልና ወግ እምነት መሆናቸው ያበቃል ተብሎ አይታሰብም። ተኃድሶ የባህሪው የሆነው እግዚአብሔር ነገሮችን በሆነ መንገድ ይለውጥ እንደሆነ ወደሰማይ ማንጋገጥ የወቅቱ አማራጭ ሆኗል። በአጠቃላይ ሲታይ ማኅበረ ቅዱሳን ሳይፈለግ የተገኘ፤ ሳይወደድ የቆየ፤ እየተጠላ ለመኖር የሚታገል በጥቂት አንጃ ጳጳሳት የሚደገፍና ለቤተ ክርስቲያኒቱ ሸክም የሆነ ድርጅት ነው።
ኤር 29፥12
እናንተም ትጠሩኛለችሁ፥ ሄዳችሁም ወደ እኔ ትጸልያላችሁ፥ እኔም እሰማችኋለሁ።ኤር 29፥12 «እናንተም ትጠሩኛለችሁ፥ ሄዳችሁም ወደ እኔ ትጸልያላችሁ፥ እኔም እሰማችኋለሁ» ያለ እግዚአብሔር ሁሉን እስኪለውጥ በትዕግስት መጠበቅ ብልኅነት ይመስለናል።

Wednesday, October 22, 2014

ማኅበረ ቅዱሳንን ክርስቲያናዊ ብራዘር ሁድ የሚያሰኙ ማስረጃዎችና መመሳሰሎች!

ሙስሊም ብራዘር ሁድ ወይም የሙስሊም ወንድማማቾች ማኅበር የተባለው ድርጅት በ1928 ዓ/ም በግብጽ ተመሠረተ። ከሰማንያ ዐመታት በኋላ በጄኔራል አልሲሲ መንግሥት በአሸባሪነት ተፈርጆ ድምጥማጡ እስኪጠፋ ድረስ በ70 ሀገሮች ውስጥ ቅርንጫፎቹን ከፍቶ በዘመናዊና ሃይማኖታዊ ትምህርት ቤቶች፤ በገበያ ማዕከላት፤ በንግድ ሱቆች፤ በማከፋፈያ ድርጅቶች፤ በሚዲያ ተቋማት ወዘተ የሀብት ማግበስበሻ መንገዶች እየተሳተፈ ክንዱን በማፈርጠም ለእንቅስቃሴው የሚጠቅመውን የገንዘብ ምንጭ ሲፈጥር ቆይቷል። ይህ የግብጹ ሙስሊም ብራዘር ሁድ በዐረብ ሀገራት ውስጥ ተመሳሳይ የሙስሊም ወንድማማች ማኅበራትን በማደራጀትና በማሰልጠን መንግሥታቱን ሲያስጨንቅ የቆየ ሲሆን አሁንም እያስጨነቀ ይገኛል።

የሙስሊም ብራዘር ሁድ ለተባለው ሃይማኖታዊ-ፖለቲካዊ ድርጅት ዋነኛ ተቀባይነት ማግኘት ዋናው ምክንያት የሆነው በእስላሙ ሕብረተሰብ ውስጥ ቶሎ ሰርጾ እንዲገባ የሚያካሂደው ሃይማኖታዊ አስተምህሮቱና  ለዚህ እምነት መክፈል የሚገባውን ዋጋ ሁሉ በመክፈል ከአላህ ዘንድ የሚከፈለውን ምንዳ ለመቀበል ቶሎ መሽቀዳደም ተገቢ መሆኑን አበክሮ በመስበኩ የተነሳ ነው።

1/ የሙስሊም ብራዘር ሁድ መዋቅራዊ እንቅስቃሴ 

 ሙስሊም ብራዘር ሁድ መዋቅሩ በሀገሪቱ የመንግሥት ሲቪላዊ መዋቅር ደረጃ የተዘረጋ ነው። ይህም ከማዕከላዊ ቢሮው ተነስቶ አባል በሆኑ በእያንዳንዱ ቤተሰብ ውስጥ በሰንሰለት የተያያዘ ነው። ቤተሰባዊውን የአባልነት ማኅበር «ኡስራ» ይሉታል። አንድ «ኡስራ» አምስት አባላት ሲኖሩት ከአምስት በላይ ከሆነ በሁለተኛ የኡስራ ስያሜ ደረጃ ይዋቀራል። በቤተሰቡ ያሉትን ኡስራዎች የሚመራ ደግሞ የቤተሰቡ አባል የሆነ በእስልምና ሃይማኖቱ የበሰለና የብራዘር ሁድ አስተምህሮት በደንብ የገባውን ሰው የቤተሰቡ ጉባዔ ይመርጠውና «ናቂብ» ተብሎ ይሰየማል። ይህ «ናቂብ» የተባለው ሰው የቤተሰቡ አባላት በእስልምናው ደንብ ዘወትር ስለመንቀሳቀሱ ይቆጣጠረዋል፤ ያስተምረዋል፤ ይነግረዋል። ያልተመለሰውን በማኅበረሰቡ ደረጃ ለተቀመጠውና ከፍ ላለው ሃይማኖታዊ መሪ ያቀርበዋል። ይህ ሁሉ ሲሆን ስለእስልምናው የሚደረግ እርምጃ በመሆኑ በደስታ ከሚቀበል በስተቀር ማንም በተቃውሞ አያንገራግርም፤ ሊያንገራግርም አይችልም። ምክንያቱም ጸረ እስልምና እንደሆኑ ራሳቸውን አስገዝተዋልና። በዚህ ዓይነት አደረጃጀት የሙስሊም ወንድማማቾች ማኅበር ከላይ ወደታችና ከታች ወደላይ የተሳሰረ መዋቅር አለው።

2/   የገንዘብ ምንጮቹን ማሳደግ

ገንዘብ የዚህ ዓለም እንቅስቃሴ የደም ሥር ነው። አባላት ለመመልመል፤ እንቅስቃሴውን ለማስፋፋት፤ የሽብር ተግባሩን ለመፈጸም፤ ለመደለል፤ ለመሰለል፤ ሃይማኖታዊ ዶክትሪኑን ለማስተማር  እጅግ ጠቃሚ ነገር መሆኑን ጠንቅቆ የተረዳው ብራዘር ሁድ የገንዘብ አቅሙን ለሀገር ውስጥና ድንበር ዘለል ተግባሩ ያውለው ዘንድ ተግቶ ይሰራል።

የእስላም ወንድማማቾች ማኅበር ሁለት ዓይነት የገንዘብ ምንጮች አሉት። አንዱ በውጪ ሀገራት ካሉ አባላቱ በመዋጮ የሚሰበሰብ እንዲሁም ብዙ ሃብት ካላቸው የድርጅቱ ደጋፊ ሚሊየነሮች  የሚደረግለት የገንዘብ ፈሰስና በእስላማዊ መንግሥታት ስር ከተሸሸጉ ባለስልጣናት የሚዋጣለት ገንዘብ ነው።  ሁለተኛው ደግሞ በተራድዖ ስም ከውጭ የሚያሰባስበውን ገንዘብ ወደልማት ካዝና በመቀየር በአካባቢ ልማት፤ በትምህርት ቤቶችና መድራሳ ማቋቋም፤ ሥራ አጥ ህብረተሰብን በማደራጀት፤ የራስ አገዝ እንቅስቃሴን በመመሥረት የሚሳተፍ ሲሆን ለዚህም ሀገር በቀል የእርዳታ ስልት በመቀየስ መዋጮውን ቅርጹን ለውጦ ያግበሰብሳል። ይህም፤

ሀ/ ከአባልነት መዋጮ
ለ/ ከንግድ ድርጅቶቹና ከሚዲያ ተቋማቱ የሚገኝ ገቢ ነው።


ይህንን ገንዘብ በተለያየ የገንዘብ ማስቀመጫ ስልቶችና በብዙ የሂሳብ አካውንቶች ቋት ውስጥ በተለያየ ስም በማስቀመጥ ለሚፈልገው ዓላማ በፈለገበት ሰዓት ማንም ሳያውቅበት ያውለው ነበር። በተለይም የእስልምና ባንኮች ተመራጭ መንገዶቹ ነበሩ።

3/ በመንግስታዊ ተቋማት ውስጥ ሰርጎ መግባት

ብራዘር ሁድ አባላቱን ሲመለምል ነጻና ገለልተኛ የሆኑትን ብቻ አይደለም። ከሚኒስትሮች እስከፍርድ ቤቶች፤ ከመከላከያ እስከ ፖሊስ መምሪያዎች፤ ከድርጅት ሥራ አስኪያጆች እስከ አስተዳደር ኃላፊዎች ድረስ በአባልነት መልምሎ፤ አሰልጥኖና ሃይማኖታዊ ትጥቅ አስታጥቆ የሚንቀሳቀስ ድርጅት ነበር። እነዚህ የመንግሥታዊ አካላት ክፍሎች ድርጅታቸው ለሚነሳበት ተቃውሞና ኅልውናውን ፈታኝ ለሆኑ ችግሮች የግብዓት ምንጭ ሆነው ያገለግላሉ። አስፈላጊ በሆነ የመረጃ፤ የፋይናንስና የአፈና ሥራው በትጋት ይሰራሉ።
ይህ ድርጅት እንደሃይማኖታዊ ተቋም አራማጅነት ተነስቶ ወደፖለቲካዊ ሥልጣን መቆናጠጥ እርምጃው ለማደግ መሠረት አድርጎ የሚነሳው የእስልምና ሃይማኖትን ነው። ይህም ብራዘር ሁድን መቃወም እስልምናን እንደመቃወም እንዲቆጠር በሕብረተሰቡ ዘንድ የኅልውናውን ስዕል በማስቀመጥ እንዳይነካ ወይም እንዳይጠፋ ረድቶታል። የእስልምናውን አስተምህሮ መነሻ በማድረጉ የማይነቃነቅ ፖለቲካዊ ግብ ለማስረጽ ያገዘው ሲሆን የዚህም መገለጫው በአልሲሲ መንግሥት ላይ በአንድ ጊዜ እስከ 33 ሚሊዮን ተቃዋሚ ሰልፈኞችን በመላ ሀገሪቱ ማንቀሳቀስ የሚችል ድርጅት አድርጎታል።
 ይሁን እንጂ የጀነራል አልሲሲ መንግሥት እርምጃ ስልታዊ በመሆኑ በአንድ ቀን ብቻ ከሁለት ሺህ በላይ ከፍተኛና ዝቅተኛ አመራሩንና የሃይማኖታዊ ተፍሲር መምህራኖቹን ለቃቅሞ ወደማጎሪያ ካምፕ በመክተቱ ድርጅቱ በ85 ዓመት እድሜው አይቶት የማያውቀውን ውድቀት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እንዲያስተናግድ አድርጎታል። በአልሲሲ መንግሥት የተተገበረው «ወፎቹ እንዲበተኑ ቅርንጫፉን መቁረጥ» የሚለው አባባል ብቻ ሳይሆን ግንዱን መንቀል በመሆኑ የብራዘር ሁድ ዋና መሪ መሐመድ ሙርሲን ጨምሮ ከፍተኛውን የሹራ ካውንስል ሳይቀር ከስር ገርስሶታል። በሺዎች የሚቆጠሩ አባላቱም የሞትና የእስራት ፍርድ ተከናንበዋል። አልሲሲ በቲቪ ቀርበው "ብራዘር ሁድን ከስረ መሠረቱ ነቅለን ካላጠፋን ሰላም የለንም" በማለት ድራሹን አጥተውታል። ዛሬም ድረስ የተቃውሞ ሰልፎች ያሉ ቢሆንም በሃይማኖት ካባ ስር በተሸፈነው ድርጅት በኩል የአእምሮ አጠባ ተደርጎ የተታለለው ሕብረተሰብ እንጂ ብራዘር ሁድ እንደተቋም በግብጽ ታሪክ ግብዓተ መሬቱ ተፈጽሟል። ያ ማለት ግን ብራዘር ሁድን የሚደግፍ፤ የሚጠባበቅና እንዲያንሰራራ የሚፈልግ የለም ማለት አይደለም።

4/ማኅበረ ቅዱሳን እንደክርስቲያን ብራዘር ሁድ ስንል ምን ማለታችን ነው?

1/ ተቋማዊ አደረጃጀቱ ከመንግሥትም፤ ከቤተ ክህነትም ቁጥጥር ነጻ መሆኑ
2/ የራሱን አባላት የሚመለምልና የሚያደራጅ መሆኑ
3/ የራሱ የሆነ የገቢ ምንጭ ያለውና የንግድ ተቋማትን የሚያንቀሳቅስ መሆኑ
4/ ከአባላቱ ልዩ ልዩ መዋጮዎችና የስጦታ ገቢዎችን በመሰብሰብ በልማት ውስጥ እየተንቀሳቀሰ እንዳለ የማሳየት ብልሃት ያለው መሆኑ
5/ በመንግሥት ተቋማትና መሥሪያ ቤቶች፤ ፍርድ ቤቶች፤ ፖሊስ መምሪያዎች፤ በኮሌጆችና ዩኒቨርሲቲዎች ስውር መዋቅር ያለው መሆኑ
6/ በቤተ ክርስቲያኒቱ ላዕላይ መዋቅርና እስከ አጥቢያ ድረስ በተዘረጋው አስተዳደር የራሱ አደረጃጀት የዘረጋ መሆኑ
7/ በቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ውስጥ የራሱን ጳጳሳት በመመልመል ማስሾም የቻለ መሆኑ
9/ ከሀገር ውጭ ዓለም አቀፍ ቢሮዎችን ከፍቶ የሚንቀሳቀስና አባላት ያሉት መሆኑ
10/ ከዓለም አቀፍ የገቢ ፈጠራው ውስጥ በልማት ሰበብ የሚያጋብስ መሆኑ
11/ የመረጃ፡ የስለላና የትንተና መዋቅር ያለው መሆኑ
12/ የቤተ ክርስቲያኒቱን አደረጃጀቶች ለራሱ ዓላማ የመጠቀም አቅም ያለው መሆኑ
( ሰንበት ት/ቤቶችን፤ የጥምቀት ተመላሽና የጽዋ ማኅበራትን)
14/ የግለሰቦችን ስም በማጥፋት ወይም ራሳቸውን በማጥፋት፡በማባረር፡በመደብደብ ወይም ግለታሪካቸውን ለራሱ ዓላማ ጠምዝዞ በማዋል እርምጃ መውሰድና ማስወሰድ የቻለ መሆኑ
15/ ስሙን ለማግነን፤ ክብሩን ለማስጠበቅ የሚያስችል በራሱ የሚመራ እንዲሁም በፖለቲካ የተቃውሞው ጎራ የተሰለፉ ደጋፊዎችና በስውር መረብ የሚንቀሳቀስ የሚዲያ ተቋም ያለው መሆኑ፤
ማኅበረ ቅዱሳንን ክርስቲያናዊ ብራዘር ሁድ እንድንለው ያስችለናል።

እስካሁንም ማንም ምላሽ ሊሰጥበት ያልቻለው ዋናው ነጥብ ማኅበረ ቅዱሳን ከመንግሥት እይታ ውጪ መሆን ባይችልም ከመንግሥት ቁጥጥር ውጪ የሆነ ክርስቲያናዊ ማኅበር መሆኑ ሲሆን እንደክርስቲያናዊ ተቋምነቱ  ደግሞ ቤተ ክርስቲያኒቱ በማኅበሩ ላይ ቁጥጥርና ክትትል የማድረግ ችሎታ አንዳችም አቅም የሌላት በመሆኑ ያሳዝናል:: በመንግሥትም፤ በቤተ ክህነቱም ማንም ጠያቂ የሌለው ሆኖ መቆየቱን ለማመን ያለመፈልግ ዝንባሌ መኖሩም ያስገርማል::  ማኅበሩ እንደምክንያት ሁልጊዜ የሚያቀርበው ሲኖዶስ በሰጠኝ ደንብ እመራለሁ ቢልም እውነታው ግን ብራዘር ሁድ በሆኑ ጳጳሳት አባላቱ በኩል የሚመቸውን ደንብ አስጸድቆ ያለጠያቂ በነጻነት ከሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ የገቢ አቅሙን እያሳደገ፤ የቤተ ክርስቲያኒቱን አባላት ለራሱ አባላት እየመለመለ፤በቤተ ክርስቲያኒቱ ቁመናና መልክ የራሱን አደረጃጀት፤ መዋቅርና እንቅስቃሴ እያከናወነ ያለ ማኅበር መሆኑ የማይካድ እውነታ ነው። ለምሳሌ የማኅበሩ ብራዘር ሁድ አባላት ጳጳሳቱ አባ ማቴዎስ፡አባ ቀውስጦስ፡ አባ ቄርሎስ፡ አባ ያሬድ፡አባ አብርሃም፡አባ ሳሙኤል፡ በአባ ማቴዎስ አደራዳሪነት የትግሬን መንግስት በጋራ መዋጋት በሚል ፈሊጥ ከማኅበሩ እግር ላይ ወድቀው የታረቁት አባ ፋኑኤል ተጠቃሾች ናቸው:: አባ ገብርኤል ግን ከአቶ ኢያሱነታቸው ጀምሮ የተጠጋቸው የውግዘት በሽታ  መቼም አይለቃቸውም::

5/ ለመሆኑ አሁን ያለው ማኅበረ ቅዱሳን አደረጃጀት፤   

የሰንበት ት/ቤት ስብስብ ነው? እርዳታ ድርጅት ነው? የልማት ተቋም ነው? የበጎ አድራጎት ማኅበር ነው? ራሱን ከሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ውጪ አስደርጓል። በዋና ሥራ አስኪያጅ ሥር የሚተዳደር ነገር ግን የቤተ ክህነቱ መምሪያ ያልሆነ መምሪያ ነው?
በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ ሥፍራው ከየት ነው? በምንስ እንመድበው? ማኅበሩ በምን ሂሳብ እንደተቋቋመና በምን አደረጃጀት ኅልውና እንዳገኘ አይታወቅም::

እስከሚገባን ድረስ እንቅስቃሴውንና ያለውን አደረጃጀት ተመልክተን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማኅበረ ቅዱሳናዊ ብራዘር ሁድ ብንለው ተግባሩ ያረጋግጣል።
በሌላ መልኩ መንግሥት በኢትዮጵያ የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች ዘንድ እንዲህ ዓይነት ማኅበር ከእስልምና ምክር ቤቱ ውጪ እንዲቋቋም ይፈቅዳል ወይ ብለን እንጠይቃለን? መልስ የሚያሻው ጥያቄ ነው።

Wednesday, October 15, 2014

«እርስዎም በአማካሪዎችዎ የተነሳ ዕድሜዎ እንዳያጥር ያስቡበት!» ያሉት አባ ማቴዎስ ጠንቅ ዋይ ወይስ የሞት መንፈስ?



ዋና ሥራ አስኪያጁ ‹‹ውድቀት እንዳይደረስብዎ አማካሪዎችዎ ሊያዝንልዎ ይገባል፤›› ማለታቸውን የገለጹት የስብሰባው ተሳታፊዎች አያይዘውም ‹‹ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ በአማካሪዎቻቸው ክፋት ከዕድሜያቸው ዐሥር ዓመት አሳጥረዋል፤ እርስዎም በአማካሪዎችዎ የተነሣ ዕድሜዎ እንዳያጥር ያስቡበት፤›› ሲሉ መምከራቸውን ጠቅሰዋል፡፡ ( ሐራ)

«እርስዎም በአማካሪዎችዎ የተነሳ ዕድሜዎ እንዳያጥር ያስቡበት!» ያሉት አባ ማቴዎስ ጠንቅ ዋይ ወይስ የሞት መንፈስ ናቸው?

የሁላችንም ዕድሜ ያለው በእግዚአብሔር እጅ ነው። ማንም የማንንም ዕድሜ አያውቅም። ነገር ግን የሰውን ዕድሜ እናውቃለን የሚሉ ጠንቅ ዋዮችና መናፍስት ጠሪዎች ቢኖሩም አታላዮችና አጭበርባሪዎች ናቸው። ታዲያ አባ ማቴዎስ የፓትርያርክ አቡነ ማትያስን እድሜ በዐሥር ዓመት ማሳጠር የሚችሉት በምን ጥበባቸው ነው? ደግሞስ ነፍስ ኄር አቡነ ጳውሎስ ሊቆዩ ከሚችሉበት ዕድሜ በዐሥር ዓመት ያሳጠሩትስ በምን ኃይል ነው? አባ ማቴዎስ ስለሟቹ ፓትርያርክ አሟሟት የሚያውቁትን ምሥጢር በፓትርያርክ ማትያስ ላይ ለመድገም እንደሚችሉ «እርስዎም ዕድሜዎ በዐሥር ዓመት እንዳያጥር ያስቡበት!» ሲሉ ማስጠንቀቃቸው የሚነግረን አንድ ምሥጢር አለ። እግዚአብሔር ማኅበረ ቅዱሳንን የማይወደውን ሁሉ ይገድላል እያሉን ነው ወይም ማኅበረ ቅዱሳንን የማይወደውን ሁሉ እኛ እንገድላለን ማለታቸው ነው። እንደዚያ ካልሆነ ማኅበረ ቅዱሳንን ባለመውደድና በሞት መካከል ምን ግንኙነት አለ?

    አባ ማቴዎስ በግልጽ ቋንቋ የተናገሩት ዐረፍተ ነገር እንደሚያስረዳው ስለፓትርያርክ ጳውሎስ አሟሟት በትክክል እንደሚያውቁ ነው። ይህንኑ ዕውቀት በፓትርያርክ ማትያስ ላይ እንደሚደግሙት ማስጠንቀቂያቸው ያስረዳናል።
«የአቦን ግብር የበላ ይለፈልፋል» እንዲሉ በማኅበሩ ላይ የደረሰው የማኅበረ ካህናቱና የፓትርያርኩ ግልጽ አቋም ያበሳጫቸው ሸዌው እጩ ፓትርያርክ አባ ማቴዎስ በንዴት ሳያውቁት ድብቁን አደባባይ ላይ አዋሉት። «አቡነ ጳውሎስን የገደልናቸው እኛ ነን» ሲሉ ራሳቸው መሠከሩ። እኛም በመጠየቅ ጨምረን እንዲነግሩን የምንፈልገው እንዴት አድረገው እድሜአቸውን ማሳጠር እንደቻሉ ምስጢሩን ከቻሉ በጀመሩበት መንገድ በፈቃዳቸው እንዲነግሩን፤ እምቢ ካሉ ደግሞ በሕግ ፊት እንዲዘከዝኩልን ለሚመለከታቸው ክፍሎች እናሳስባለን። 

በአንድ ከፍተኛ የቤተ ክርስቲያኒቱ አመራር ላይ «ዕድሜህን በዐሥር ዓመት እናሳጥራለን!» የሚለው ዛቻ «ልብስ አጥበን እንተኩሳለን» እንደሚባለው የሠፈር ማስታወቂያ ተነቦ በቀላሉ የሚታለፍ ጉዳይ አይደለም። በተዘዋዋሪ «እንገድልሃለን» ማለት ነው። የግድያ ዛቻ ደግሞ በምድራዊው ሕግ ወንጀል ነው።  በሰማያዊውም ቃል ዐመጻና ክፋት ነው።

«አስበው ክፉ ነገርን ተናገሩ። ከፍ ከፍ ብለውም በዓመፃ ተናገሩ» መዝ 73፤8 

አስበው የተናገሩት ቃል ከፍ ያለ የግድያ ዐመጻ ነው። አባ ማቴዎስ ቀድመው እንደማይሞቱ ያረጋገጡ ይመስል የአቡነ ማትያስን በፍጥነት በሞት መወገድ በአደባባይ እንደማወጅ ነውረኛና የከፋ አነጋገር ይኖር ይሆን? እግዚአብሔር አምላክነቱ ለአባ ማቴዎስና ለማኅበረ ቅዱሳን ብቻ የሆነ ያህል አቡነ ማትያስን ቶሎ እንደሚገድል መናገር አሳፋሪ ነው። እንግዲህ እነዚህ ናቸው፤ ቤተ ክርስቲያንን የሚመሩት!

በማኅበረ ካህናቱ ስብሰባ ላይ የነበሩ አንድ ካህን ከተናገሩት አንድ ቃል እዚህ ላይ ልዋስ። « እነዚህ እኮ መንግሥትን ከአንድ ክ/ሀገር ወደሌላ ክ/ሀገር ያመጡ ሰዎች ናቸው እኮ፤ በዚያን ዘመን እንዲህ ማድረግ የቻሉ ዛሬ «አቢሲዲ ቆጥረውማ ማን ይችላቸዋል?» ማለታቸው አንድ ነገር ያሳስበናል። ለሥልጣን ሲሉ ሰው እስከመግደል ሊደርሱ መቻላቸውን ይገልጻል። እንደዚያ ካልሆነ አባ ማቴዎስ እስከዕድሜ ማሳጠር እብደት ቀመስ ንግግር ባልደረሱም ነበር። ምንም እንኳን የሰው ልጅ ዕድሜ በእግዚአብሔር እጅ ያለ ስለሆነ ሁሉም ሰው መሞቱ ባይቀርም አሟሟቱ ግን ልዩ ልዩ ነው።

 በጎርፍ፤ በመሬት መንቀጥቀጥ፤ በመኪና አደጋ፤ ገደል በመውደቅ፤ ውሃ ውስጥ በመስመጥ፤ በሕመም፤ በሰው እጅ በመገደል ወዘተ መንገድ ሕይወቱ ሊያልፍ ይችላል። የአቡነ ማትያስ አሟሟት በእነ አባ ማቴዎስ እጅ ይፈጸም ዘንድ ከፈጣሪ የታዘዘ ካልሆነ በስተቀር ካልጠፋ ወቀሳና ሌላ የማሳሰቢያ ንግግር «እንደአቡነ ጳውሎስ ዕድሜዎት በዐሥር ዓመት ያጥራል» ባለሉም ነበር። እግዚአብሔር የነፍሳት ሁሉ ጌታ ስለሆነ  አሟሟታቸውን ልዩ ልዩ አድርጓል።  በእርግጥም የሰውን ነፍስና ሥጋ ይለዩ ዘንድ ምክንያት ከሚሆኑት መካከል ክፉ መናፍስቶች አንዱ ናቸው። አባ ማቴዎስን ከክፉው መንፈስ እንደአንዱ እንቁጠራቸው? ሞትን ያህል ዜና በአደባባይ ያወሩት የክፉው መንፈስ መልዕክት ቢደርሳቸው ይሆናል። እውነታው ግን እግዚአብሔር ለአባ ማቴዎስና ለማኅበራቸው ብቻ የቆመ አምላክ አይደለም። ኃጢአተኞችን ሁሉ በመታገስ ዕለትን በዕድሜአቸው ላይ የሚሰጥ ሁሉን ቻይ አምላክ ነው።
ነገር ግን አባ ማቴዎስ እንደጻድቅ ራሳቸውን ቆጥረው በሌላው ሰው ላይ ሲፈርዱ ለዚህ ክፉ አሳባቸው የሞት መልአክ ቀድሞ ወደእርሳቸው ቢመጣስ?

«ክፉ ሰው ዓመፃን ብቻ ይሻል ስለዚህ ጨካኝ መልአክ ይላክበታል» መዝ 17፤11 ይላልና መጽሐፉ።

አቡነ ማትያስም ከክፉ ሰዎች እጅ እንዲድኑ አብዝተው መጸለይ የሚገባቸው ይመስለናል። ዳዊት በዝማሬው እንዳለው

 « አቤቱ፥ ከክፉ ሰው አድነኝ፥ በልባቸውም ክፉ ካሰቡ ከዓመፀኞች ሰዎች ጠብቀኝ ቀኑን ሁሉ ለሰልፍ ይከማቻሉ» መዝ 140፤1

የዕድሜ ወሰን ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው።

«የሰው ዕድሜ የተወሰነ ነው፥ የወሩም ቍጥር በአንተ ዘንድ ነው፥ እርሱም ሊተላለፈው የማይችለውን ዳርቻ አደረግህለት» ኢዮ 14፤5
አባ ማቴዎስ ማኅበረ ቅዱሳንን የሚነካ ሁሉ ይሞታል እያሉ ይናገራሉ።  ታዲያ አባ ማቴዎስ ጠንቅ ዋይ ናቸው ወይስ የሞት መንፈስ???? የምታውቁ ንገሩን!!