Sunday, March 20, 2016

በከበሮና በዘፈን አመስግኑት፤ በአውታርና በእምቢልታ አመስግኑት!

መዝ 150
ሃሌ ሉያ። እግዚአብሔርን በመቅደሱ አመስግኑት፤ በኃይሉ ጠፈር አመስግኑት።
በችሎቱ አመስግኑት፤ በታላቅነቱ ብዛት አመስግኑት።
በመለከት ድምፅ አመስግኑት፤ በበገናና በመሰንቆ አመስግኑት።
በከበሮና በዘፈን አመስግኑት፤ በአውታርና በእምቢልታ አመስግኑት።
ድምፁ መልካም በሆነ ጸናጽል አመስግኑት፤ እልልታ ባለው ጸናጽል አመስግኑት።
እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን፦ ሃሌ ሉያ።