Monday, April 9, 2012

በብፁዕ አቡነ ፋኑኤል የሚመራው የዋሽንግተን ዲሲና ካሊፎርኒያ አህጉረ ስብከት ጽህፈት ቤት በምዕራብ አሜሪካ ካሊፎርኒያና አካባቢው የተቋቋመውን የስቴት ቤተ ክህነት ሊቃነ ካህናቱን አስታወቀ

ከአባ ሰላማ ብሎግ ያገኘነው መረጃ እንደሚያሳየው ብጹእ አቡነ ፋኑኤል ከዚህም ቀደም በየእስቴቱ ሊቃነ ካህናትን በመመደብ የአስተዳደር መዋቅራትን እያደራጁ እንደነበረው ሁሉ በተቀሩት  ስቴቶችም መዋቅራቸውን በማስፋት ተጨማሪ ሊቀካህናትና የአስተዳደር አካላትን የመደቡ መሆናቸውን ታውቋል።
ከዚህም በተጨማሪ የአህጉረ ስብከቱን ጽ/ቤት መንፈሳዊ የአስተዳደር ጉባዔ አባላትን በአዲስ መልክ እንዳዋቀሩ ዘገባው በተጨማሪ ያመለክታል። የመንፈሳዊ አስተዳደር ጉባዔ አባላትን በአዲስ መልክ ማደራጀቱ ለአህጉረ ስብከቱ የሥራ እንቅስቃሴ የተሻለ እንደሚሆን ቢታመንም ለአንዳንድ ወገኖች ይህ ፈጽሞ ሊሆን እንደማይችል ታስቦ እንቅፋት ሊዘጋጅለት ይችላል። በተለይም እነዚህ የአህጉረ ስብከቱ ጽ/ቤት መንፈሳዊ የአስተዳደር ጉባዔ አባላት በአዲስ መልኩ መዋቀር እጀ ረጅም ለሆነው ማኅበረ ቅዱሳን ትልቅ መርዶ ብቻ ሳይሆን ራስ ምታት እንደሚፈጥርበት «ደጀ ብርሃን» ብሎግ ታምናለች። ለዚህም መዋቅር መፍረስ የሚቻለውን ሁሉ ኃይልና በጀት እንደሚመድብ ከማኅበሩ ተፈጥሮ የተነሳ ግምት ይወሰዳል። ከዚያም ባሻገር  ሊቀ ጳጳሱ ምድረ አሜሪካ ከገቡ ጊዜ ጀምሮ በማኅበረ ቅዱሳን የጥላቻ ፈንገስ (Fungus) የተጠቃው አሮጌው ቡድን ይፈጽም የነበረው የህውከት በሽታ በዚህ ፍቱን የመዋቅር መድኃኒት የተነሳ እየመረዘ እንዳይቀጥል  ፈውስ የተሰጠበት ስለሆነ   ፈንገሱ ለመመለስ የሚያደርገውን መፍጨርጨር አብሮ መከላከያውን በመፍጠር መዋቅሩን ማጠናከር እንደሚገባ «ደጀ ብርሃን» አጥብቃ ታሳስባለች።
በተሰጠው የሊቀ ጳጳሱ የአስተዳደር መዋቅር ድንጋጤና ንዴት የተነሳ የአፈ ማኅበሩ ብሎጎች ፈንገሱን በምረዛው ለማስቀጠል ዘመቻቸውን እንደሚከፍቱ ይጠበቃል። ይህንን ዘመቻ መቋቋም የሚቻለው  መዋቅሩ ከደብዳቤ ባለፈ መሬት ላይ የሚታይ መሆን ሲችል ብቻ በመሆኑ ብሎጋችን ስለምታምን ከማሳሰቡ ጋር በጸሎት ጭምር የምታግዝ መሆኑን አቋሟን ትገልጻለች።
እስከዚያው ድረስ በሊቀጳጳሱ የተሰጠውን የአስተዳደር መዋቅር ደብዳቤዎችን ለመመልከት፤
                                           ( እዚህ ላይ ይጫኑ )