Sunday, April 1, 2012

የአቡኑ ገዳም



ቡኑ ገዳም
ተራራ ወጥቼ፣ ቡኑ ዘንድ ሄጀ መስቀል ለመሳለም
ክረምቱ በረታ፣ ምንም  ልተቻለ፣ ያሰብኩት ሳይሞላ፣ ሳይሆንልኝ ቀረ
ዳመናው ዝናቡ፣ ጉምና ጭጋጉ፣ ይህ የዛሬ ክረምት መች ያነቃንቃል!
ደጁን ጨቀይቶት፣ ወንዙም ጐርፍ ሞልቶት፣ ጅጉን ስፈሪ፣ በጣም ያስጨንቃል
በታምር በፀሎት፣ ከተራራው ፋፍ፣ ከዳመናው በላይ የገደሙት ገዳም
ደካማው ጉልበቴ፣ ንደምን ይቻለው፣ ጭቃውን ሸርተቴ፣ የኖኁን ዝናም
ዛሬ፣ ነገ ያልኩ ሰማዩና ምድሩን ሳስስ ስመለከት፣ ስቃኝ ድማሱን
ዓይኖቼም ደከሙ፣ ለቀ ጉልበቴ፣ መቃብር ቁፋሮ፣ ሰርክ መማሱን!
ማለዳ-ማለዳ ደረትዋን ገልብጣ፣ ድምጿንም ከፍ ደርጋ የምትጮኸው ወፍ
የቀሰቀሰች  ንቅልፍ ነሳችኝ፣ ሽፍንፍን ብዬ፣ ተኝቼ በሰላም በደህና ንዳላርፍ!
ምድር-ዓለሙ ክዶኝ፣ ሁሉም ጥሎኝ ሄዷል፣ ጠያቂም የለኝም ከቶ ሚያጽናናኝ
ወፊቱስ የት ሄደች? ከጠፋች ቆይታለች፣ ድምጿንም ልሰማሁ፣ ንዳታዝናናኝ
ደጋግሞ የቆየ የሚነፍሰው ነፋስ ለው መጥፎ ጠባይ፣ ኃይለኛ ዙሪት
የጐጆየን ክዳን በትኖ ያነሳ፣ ምን ዓይነት ተንኮል ነው፣ ምን ዓይነት ብሪት!
መቸ ይኸ ብቻ! ሰማዩን ተርትሮ ስደንጋጭ ብልጭታ መብረቅ ሲፈነጥቅ
ከታትሎ ይሏል የሰማይ ነጐድጓድ ቤቱን ንቀጥቅጦ ጆሮ ስኪሰነጥቅ
ተራራ ልወጣህ፣ ታቡን ዘንድ ልደረስኽ፣ መስቀል ልተሳለምክ ብሎ ነው መሰለኝ
ከዚያ ላይ ስወጣ ገደል ከምገባ፣ ወድቄ ከምሞት፣ ወይም ንሸራትቶኝ ከሚሰባብረኝ
ከዚሁ ከቤቴ ካልጋዬ ተኝቼ፣ በንፋስ፣ በመብረቅ ነጉዶ ንጐዳጉዶ እንዳሻው ያድርገኝ!
                              
 ገ/ኢ ጎርፉ