Monday, February 13, 2012

የአቡነ ገብርኤል ተልዕኰ!


በሲዳማ፣ ጌዴኦ፣ አማሮና ቡርጂ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ሀገረ ስብከት በተለይም በሀዋሳ ለአንድ ዓመት ከስምንት ወራት ያህል የቆየው ውዝግብ እስካሁን መቋጫ አለማግኘቱን መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ ለውዝግቡ መባባስ የአቡነ ገብርኤል አንዱን አቅርቦ አንዱን የማራቅ አድሏዊ አመራር ትልቁን ድርሻ ሲወስድ፣ ቅዱስ ሲኖዶስ፣ የመንበረ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤትና ጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት ተገቢውን እርምጃ ባለመውሰዳቸው የምዕመናኑ ሰቆቃ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መምጣቱን ከተለያዩ ምንጮች ለመረዳት ችለናል፡፡

አቡነ ገብርኤል በሁለንተናዊ የስብዕና ቀውስ ውስጥ ያሉ ሰው ናቸው ያሉ ታዛቢዎቻችን እንዳስረዱን፣ ሊቀጳጳሱ የሚናገሯቸውና የሚፈጽሟቸው ድርጊቶች የትላንቱ ከዛሬው፣ የዛሬው ከነገ የማይጣጣሙ ርስ በርሳቸው የሚምታቱ ናቸው ብለዋል፡፡ በተከበረውና በተቀደሰው ዐውደ ምሕረት ላይ አንድ ጊዜ በድያለሁ ይቅርታ ሲሉ፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ በግል መጽሔት ጭምር በአምሳለ ሥላሴ የተፈጠሩትን ምዕመናንንና ምዕመናትን ቀበሮዎች እያሉ የሚሳደቡ መሆናቸው ተገልጿል፡፡  ሰውየው በዚህ ብቻ ሳያበቁ በቅዱስ ሲኖዶስ ፊት ከቤተክርስቲያን የተለየ እና የተከፈለ ሕዝብ የለም ጥቂት ተሃድሶአውያን ናቸው እያሉ የ"ማኅበረ ቅዱሳን"ን የውሸት አሉባልታ ያስተጋባሉ፡፡ ሌላ ጊዜ ደግሞ አዎን የተሰደደ ሕዝብ አለ፡፡ ዕድሉ ይሰጠኝና ሁለቱንም አስማማለሁ እያሉ ሲማጸኑ ይታያሉ፡፡

አቡነ ገብርኤል በግል ቀርቦ ለሚያነጋግራቸው አሁን ያለው የቤተክርስቲያን ቀውስ በዋነኛነት በ"ማኅበረ ቅዱሳን" የተንኮልና የጥፋት ዕቅድ እንደሚመራ፣ እንዲሁም አገልጋዮች ያለ ጥፋታቸው እንደሚሰደቡና በግላቸውም አገልጋዮቹን እንደሚያደንቋቸው ሲመሰክሩ፣ በአደባባይ ሲሆን ግን ከማኅበሩ ብሰው ሽንጣቸውን ገትረው ይራገማሉ፡፡ አቡነ ገብርኤል የማስመሰል ድርጊታቸው ከውስጥ ባህርያቸው የሚመነጭ ነው ያሉ እነዚህ ወገኖች፣ እንደማሳያ የሚሆነን በዕድሜ ያረጁ ሆነው ሳለ ወጣት ለመምሰል ጥቁር ሂና (የፀጉር ቀለም) መቀባታቸው ራሳቸውን በወጣትነት ውስጥ ደብቀው ከሁኔታዎች ጋር ለመመሳሰል መሞከራቸው ነው ብለዋል፡፡ ቤተክርስቲያንንም የሚያጠቁት የዋህና ምንም የማያውቅ ቅን ክርስቲያን በመምሰል ነው ብለዋል፡፡

ምክራችሁን እሻለሁ!

 ጥያቄ፦

እባካችሁ ወገኖች ምክራችሁን እሻለሁ!

በጌታ የተወደዳችሁ ወገኖቼ ሰላም ለናንተ ይሁን!

ባለትዳርና የልጆች እናት ነኝ፡፡ ባለቤቴ እጅግ የሚወደድና ምስጉን ባህርይ ያለው ሰው ነው፡፡ ስራው የግሉ ንግድ ላይ ሲሆን ብዙውን ጊዜ ለስራው ሲሮጥ ከወዲህ ወዲያ ሲል ለስኬቱም ሲለፋ ነው የሚውለው፡፡ ለኔም ሆነ ለልጆቹ ያለው ፍቅር ሰው የሚቀናበትና እጅግ የሚገረምበት ነው፡፡ ትልቁ ህልሙ ልጆቹን ውጤታማ አድርጎ ለማየት ሲሆን ብዙውን ጊዜም እኔ ባለፍኩበት ልጆቼ እንዲያልፉ አልፈልግም ብሎ ይናገራል፡፡

እኔ ደግሞ በስነ ጥበብ ስራ ላይ ስገኝ ከስራዬ ባህርይ የተነሳ ከብዙ አለማውያን ወንዶች ጋር እገናኛለሁ፡፡ በስራዬ ደግሞ ስኬታማና ስም ያለኝ ሴት ነኝ፡፡ በሃገር ውስጥም ሆነ ከሃገር ውጪ የተለያዩ ግለሰቦችም ሆኑ ድርጅቶች እያዘዙኝ እሰራለሁ፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በአንድ የውጪ ድርጅት ውስጥም ተቀጠሬ እየሰራሁ ነው፡፡

ከኢትዮጵያ ውጪ ካሉት አሰሪዎቼ ውስጥ አንደኛው ግለሰብ ብዙውን ጊዜ ወደሃገር ቤት ይመላለሳል፡፡ የስራ ትእዛዞችን ሰጥቶኝና የተሰሩትንም ይዞ ለመሔድ እዚህ በመጣ ጊዜ በተደጋጋሚ እንገናኛለን፡፡ ይሄ ሰው ዳጎስ ያለ ክፍያ የሚከፍለኝ ሲሆን ከውላችን ውጪም ተጨማሪ ገንዘብ በስራዬ መደሰቱን በመግለጽ አልፎ አልፎ ይሰጠኛል፡፡ ባለበት ሃገር ሆኖም ለሰላምታ ይደውልልኛል አልያም ኢሜይል አልፎ አልፎ እንጻጻፋለን፡፡

ከቅርብ ጊዜ ውዲህ ደግሞ በፌስቡክ ላይ ተገናኝተን ቻት እየተደራረግን ቀረቤታችን ለየት ያለ ወሬን ወደማውራት እና ወደመነፋፈቅ ተሸጋገረ፡፡ በወሬያችን እንደሚወደኝ እና ለኔ ለየት ያለ ስሜት እንዳለው ሲገልጽልኝ ባለትዳርና የልጆች እናት መሆኔን እያወቀ እንዲህ አይነቱን ነገር ማሰብ እንደሌለበት ደጋግሜ እናገረዋለሁ አኩርፎኝ እንለያያለን፡፡ (ሳልገልፀው የማላልፈው ጉዳይ ቢኖር እርሱ ትዳሩን ከጥቂት አመታት በፊት የፈታ ሲሆን የልጆች አባትም ነው)፡፡

የሄንን ሰው በስራየ ማጣት የለብኝም ባይሆን ረጋ ብዬ አስረዳዋለሁ እልና በሌላ ጊዜ ኦን ላይን ሳገኘው ረጅም ሰዓት ወስጄ ሃሳብ እንለዋወጣለን፡፡ በሃላም የተረዳኝ መስሎ ለጥቂት ጊዜ ተወኝ፡፡ የምናወራውም እነዴት ነህ እንዴት ነሽ ብቻ ሆነ፡፡ መጻጻፉንም እንደድሮው ሳይሆን ቀነስ አደረገ፡፡

እኔም በራሴ ወስኜ ፌስ ቡክ የሚባለውን ነገር ከስንት አንዴ ከመጠቀም በቀር በአብዛኛው ተውኩት፡፡ የምከፍተውም ከሃገር ውጪ ያሉ አብሮ አደጎቼን ለማግኘትና ከክርስቲያን ወገኖቼ ጋር መንፈሳዊ ነገሮችን ለመዋወጥ ብቻ ነው፡፡ እርሱንም ሊያገኘኝ የማይችልበትን ሰዓት እየተጠቀምኩ ነበር፡፡


በቅርቡ በግል ኢሜይሌ የተላኩልኝን መልእክቶች በማየትና ምላሽ በመስጠት ላይ እያለሁ በዚያም ቻት ማድረጊያው ላይ መልእክት መጣልኝ፡፡ ከዚህ በፊት በዚህ ተጠቅሜ ስለማላውቅ በመገረም ሳነበው የእርሱ እንደሆነ ገባኝ፡፡ በመጥፋቴ እንደተጨነቀና እንዳጋጣሚ እንዳገኘኝ ገልጾልኝ ተቀይሜው እንደሆነ ጠየቀኝ፡፡ በፍጹም ቅያሜ በኔ ልብ ውስጥ እንደሌለ ገልጬለት ስለ ስራችን አውርተን ተለያየን፡፡

በሳምንቱ ይመስለኛል ስልክ ደውሎ ለየት ላለ ስራ እንደሚፈልገኝ ገልጸልኝ ስለሁኔታውም አስረድቶኝ ለኔ ቀላልና ልሰራው የምችለው መሆኑን ገለጽኩለት፡፡ እግረ መንገዱንም ስለነበረው ያለፈው ሁኔታ አንስቶብኝ ፈጽሞ እንዲረሳውና ግንኙነታችን እንደቀድሞ እንዲሆን ገልጨለት በዚሁ ተለያየን፡፡ በማግስቱ ኢሜይል አድርጎልኝ አገኘሁ፡፡ ለኔ የተለየ ልብ እንዳለው፤ ፈጽሞ ሊያጣኝ እንደማይፈልግ ፤የሚያጣኝ መስሎት ተጨንቆ እንደነበርና አሁን ግን እረፍት እንዳገኘ የሚገልጽ ነበር፡፡ ምላሽ ግን አላኩለትም፡፡

Sunday, February 12, 2012

መመለስ አቃተኝ!

 ጠያቂ፦ አብርሃም እባላለሁ፤ በኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል አምናለሁ፡ ቃሉንም ዘወትር አነባለሁ፡ ነገር ግን በአሳፋሪ የዝሙትና የስንፍና ሃጢአት ባሪያ ሆኝለሁ....ብዙ ጊዜ ለመመለስ ብሞክርም በተደጋጋሚ ወደቅኩ። እባካችሁ ይህንን ጥያቄ ያነበባችሁ ሁሉ ባላችሁበት ቦታ ጸልዩልኝ። ምክራችሁንም ለግሱኝ።
 መልስ፦
የዝሙት ኃጢአት ባሕርያት

ከሁሉ አስቀድሜ እየተለማመድክ ስላለኸው ኃጢአት ምንነትና ባህርይ የበለጠ መረዳት እንድትችል አንዳንድ ነገሮችን ለማለት እወዳለሁ።

እንደዚህ አይነት ኃጢአቶች ብዙ ጊዜ በትንሹ የሚጀመሩና ከጥቂት ጊዜ በኋላ የራሳቸው የሆነ ሕይወት አበጅተው በራሳቸው ጉልበትና ኃይል የሚንቀሳቀሱ ኃጢአቶች ናቸው። ብዙ ጊዜ የሚጀመሩት በፈተና ነው። የሚፈትኑና የፍትወት ፍላጎትን የሚያነሳሱ ሁኔታዎች ይገጥሙና የመጀመሪያውን ፈተና መቋቋም ባለመቻል ይጀመራል። ብዙ ጊዜ ይህንን አይነት ኃጢአት የሚለማመድ ሰው (ቀድሞውኑም ጤናማ የክርስትና ሕይወት የነበረው ሰው ከሆነ) ኃጢአቱን ለማሸነፍና ፈተናውን ለመቋቋም የተወሰኑ ትግሎችን ያደርጋል። የሚፈትን ነገር ይኖራል፤ እናም ያንን ለመቋቋም ይሞከራል፡ ነገር ግን ይወደቃል። እንደ ማንኛውም ኃጢአት ከመደረጉ በፊት የነበረው "ደስታ"ና ግፊት ኃጢአቱ ከተደረገ በኋላ ከመቅስበት ጠፍቶ ወደ ጸጸትና ሃፍረት ስለሚለወጥ፤ ፈተናውን ሳይቋቋሙ ቀርተው በዚህም ኃጢአት ሲወድቁ ሰዎች በመጀመሪያ አካባቢ ይጸጸታሉ፤ ሁለተኛም ደግመው ላለማደረግ ይወስናሉ። ነገር ግን ከጥቂት ጊዜያት በኋላ ተመሳሳይ ፈተና ይመጣል፤ ትንሽ ያንገራግራሉ ደግመውም ያንኑ ኃጢአት ሲለማመዱ ራሳቸውን ያገኙታል ወዘተ።

እንዲህ እንዲህ ይልና መጀመሪያ ፈተና ከዚያም ማንገራገር በመጨረሻም መውደቅ የሚለው አዙሪት እየተደጋገመ ይሄዳል። ይህ ድግምግሞሽ ግን ወደሚቀጥለው የኃጢአት ደረጃ ይሻገራል። ይህም ከጊዜ በኋላ ኃጢአቱ እየተወደደና እየተደጋገመ ስለሚሄድ በራሱ ሕይወት ያለው ልምድ ይሆናል። ልምድ ደግሞ የሕይወት አካል ከሆነ ኃጢአቱ የሚደረገው ፈተና ስላለ ብቻ ሳይሆን ደስ ስለሚልና ስለ ለመድነው ነው። ከፈተና አልፎ የራሱ የሆነ ሕይወት አበጀ ማለት ነው። ከፈተና አልፎ በየጊዜው የምንለማመደው የሕይወታችን አካል ሆነ ማለት ነው። በዚህ ደረጃ ከደረሰ ደግሞ ኃጢአቱን ለመለማመድ ግዴታ የሚፈትኑ ነገሮች መኖር የለባቸውም። እኛው ራሳችን፤ በራሳችን ተነሳሽነት እንደ ልማዳችን ኃጢአቱን መለማመድ እንጀምራለን። መጀመሪያ ላይ ፈተናው የሚመጣው ከውጪ ነበር፤ በኋላ ልምድ ሲሆን ግን ያለ ወጪያዊ ፈተና ኃጢአቱ መጥፎ ልማድ ስለሆነብን ተነሳሽነቱ ከእኛው ውስጥ ነው የሚመነጨው። ይህ አደገኛ አካሄድ ላይ እንዳለን የሚያሳይ ምልክት ነው። ኃጢአቱ በሕይወታችን ቤቱን እየሠራና የእኛ አንዱ አካል እየሆነ የሚያመልክት ትልቅ ማስጠንቀቂያ ነው

ያልገባኝ ነገር አለ!

ጥያቄ፦ እኔ ያልገባኝ ነገር አለ፤ እሱም ጌታ ፍቅር ነው እና ኃጢአት የሚሠራ ሥጋ ነው እና እሱ ራሱ ካልቅደሰኝ እንዴት ራሴ ልቀደስ እችላለሁኝ? ራሴ የምቀደስ ከሆነ ሕግ ይሆንብኛል እና እወድቃለሁ። አታድርግ ከሆነ ሰው በኋላ አይበርታም፡ ሰለዚህም ግራ መጋባት ላይ ነኝ።
 መልስ፦
ጸጋና ኃጢአት

በቅድሚያ አዲስ ኪዳን ስለ ሁለት ኃጢአቶች ይናገራል። አንደኛው ሳናውቅና ሳናስብ አንዳንዴ ስለምናደርገው ኃጢአቶች። እንደዚህ ያሉትን ኃጢአቶች ካደረግን፤ ንስሐ ገብተን ኃጢአታችንን እግዚአብሔር ይቅር እንደሚለን ተጽፎአል።

Quote:
1ኛ የዮሐንስ መልእክት 1
8 ኃጢአት የለብንም ብንል ራሳችንን እናስታለን፥ እውነትም በእኛ ውስጥ የለም።
9 በኃጢአታችን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው።

Saturday, February 11, 2012

የጤናማ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ!

ጠያቂ፦ ስለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ዶክትሪን ብታስረዱኝ?

መልስ፦
በኢትዮጵያ ውስጥ ብዙ አብያተ ክርስቲያናት አሉ። የእያንዳንዳቸውን ዶክትሪን ልዩነት ለመጻፍ አስቸጋሪ ነው። ቢሆንም ግን አንዲት ቤተ ክርስቲያን ጤነኛ መሆንዋን የሚያመለክተን ዶክትሪንዋ (አስተምህሮትዋ) ነው። ጤነኛ ዾክትሪን ያላትን ቤተ ክርስቲያንን ለመለየት የሚከተሉትን መስፈርቶች መጠቀም ያስፈልገናል፦

1. ስለመጽሐፍ ቅዱስ ያላት አመለካከት ምን ነው - Bibliology
- መጽሐፍ ቅዱስ የ እግዚአብሔር ቃል ነው ብላ የማታምን፤ እንዲሁም ለቀደመው ዘመን እንጂ ለዚህ ዘመን አልተጻፈም ብላ የምታምን ከሆነ ወይንም ከመጽሐፍ ቅዱስ ሌላ አግንና የምትጠቀምበት ሌላ አይነት መጽሐፍት ያላት ከሆነ ይህች አይነቱ ቤ/ክ ጤናዋ ትክክል አይደለም። ከመጽሐፍ ቅዱስ ይልቅ ሌላ ነገር የምታስተምር ከሆነ መስመር የሳተች ናት።
2. ሰለ ስነመለኮት (ስለ እግዚአብሔር) ያለት አስተምህሮት ምንድነው? - Theology
- አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በሦስትነት አንድነትን የማታስተምር ከሆነች ጤነኛ አይደለችም።
3. ስለ ክርስቶስ ያላት እምነት ምንድነው?- Christology
-ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ መሆኑን የምታምን ቤ/ክ ጤነኛ ቤ/ክ ናት
4. ስለመዳን ያላት እምነት ምንድነው? እንዴትስ ይዳናል ብላ ታምናለች? - Soteriology
- በክርስቶስ ከማመን ውጪ ሌላ ወይንም ተጨማሪ የመዳኛ መንገድ የምታመለክት ቤ/ክ ጤነኛ አይደለችም።
5. ስለመንፈስ ቅዱስ ምን ብላ ታምናለች? - Pneumatology
- መንፈስ ቅዱስ ከስላሴ አካላት አንዱ እንደሆነ ፣ ለቤተ ክርስቲያንን በሃይል የሚያጠምቅ፣ወደ እውነት የሚመራና አስተማሪ መሆኑን ወዘተ. የምታምን ቤ/ክ ጤነኛ ናት።
6. ስለመላዕክት ምን ብላ ታምናለች? - Angelology
- መላዕክት የእግዚአብሔር ፍጥረትና አገልጋይ መልዕክተኞች እንደሆኑ እንጂ አማላጅ እንዳልሆኑ የምታምን ቤ/ክ ጤነኛ ናት። መላእክት ከምድር እስከሰማይ በተዘረጋው መሰላል ላይ ይወጣሉ፣ ይወርዳሉ እንጂ ራሳቸው መውጪያና መውረጃ መሰላል አይደሉም። ናቸው የምትል ከሆነ በክርስቶስ ቦታ መላእክትን ተክታለችና ጤናማ አይደለችም።
7. ስለርኩሳን መላዕክትስ ምን ብላ ታምናለች - Demonlogy
- ርኩሳን መናፍስቶች የ እግዚአብሔርን አላማ አሰናካዮች፣ የሰውም የ እግዚአብሔርም ጠላቶች እንደሆኑ፤ በመንፈስ ቅዱ ኅይል በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ከሰዎች መውጣት እንዳለባቸው የምታምን ቤ/ክ ጤነኛ ናት። ከክፉ መናፍስት መካከል ክርስቲያን መሆን የሚችሉ እንዳለ የምታስተምር ከሆነ ጤናማ ቤ/ክ አይደለችም።
8. ስለቤተ ክርስቲያንስ ምን ብላ ታምናለች - Ecclesiology
- ቤተ ክርስቲያን የክርስቶስ አካል፤የክርስቶስ ሙሽራ የምታምን ቤተ ክርስቲያን ጤነኛ ናት።
9 ሰለመጨረሻው ዘመን ምን ብላ ታምናለች? - Eschatology
- ቤ/ክ እንደምትነጠቅ፣የመከራው ዘመን  በምድር ላይ  እንደሚመጣ የምታምን፣ ከክርስቶስ ጋር እንደገና በክብር እንደምትገለጥና  ከንጉሡ ጋር በክብር ነግሳ እንደምትኖር የምታምንም ቤ/ክ ጤነኛ ቤ/ክ ናት።

እንግዲህ የዶክትሪን ልዩነቶች ከላይ በተጠቀሱት ዙሪያ በሁሉም አብያተ ክርስቲያናት ሊኖር ይችላል። በወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያን ውስጥ በአብዛኛው ተቀራራቢ መረዳት አለ ብዬ አምናለሁ። በዚህ ምሳሌ ነገሬን ልደምድም.... ጊታር የሚጫወቱ ሰዎች ይህ ምሳሌ በቀላሉ ይገባቸዋል። ጊታር ስድስት ክሮች አሉት የሁሉም ድምጽ ይለያያል። ሁሉም አይጠብቁም ሁሉም ደግሞ አይላሉም። ከሚገባው በላይ የጠበቀ ድምስ ዲስኮርድ ይፈጥራል፤ ከሚገባው በላይም የላላ እንዲሁ። በዶክትሪንም ዙሪያ ከላይ የዘረዘርኩት የሚጠብቁ ናቸው.... ይህንን ማላላት አይቻልም። ስለዚህ የሚጠብቀውን አጥብቀን የሚላላውን እናላላ። በሚያጨቃጭቁ ዶክትሪን ዙሪያ ከመናቆር አንድነታችንን ጠብቀን ወንጌልን እናሩጥ!
ከኢየሱስ.ኮም ድረገጽ የተገኘና በጥቂት ማስተካከያ የቀረበ

Friday, February 10, 2012

«ኢያሱ ወልደ ነዌ በአባቶች እግር»



«ኢያሱ ወልደ ነዌ በአባቶች እግር»

ምድራችን አንዱን በአንዱ እየተካች እዚህ ዘመን ላይ ደርሳለች። ቀድሞ የነበረው ዛሬ የለም። ዛሬ ያለው ደግሞ ነገ ላይኖር ይችላል። በለውጥ ሂደት ውስጥ እንዳለን እንገነዘባለን። ዓለም እንኳን እየተለወጠች ነው። ድሮ የሌለ እምነት ዛሬ ተፈልስፏል። የነበረውም ቢሆን ገሚሱ ረስቶታል ወይም ከልሶታል አለያም ጥሩ አድርጎ አክርሮታል። ዝናባማው ዘመን በፀሐይ ተተክቷል። የሙቀት ጨምሯል ጩኸት፣ የዕለት ከዕለት ዜና ከሆነ ውሎ አድሯል። ሉላዊነት(Globalization) የሚሉት ስልጥንና በመንፈሳዊ ሀብት የሚታይ አብሮነትና አንድነት ባይኖረውም የሳይንስ ቁስ ዓለምን አቀራርቧል። ዓለምን ለመቃኘት ማጄላንን ወይም ኢብን ባቱታን መምሰል አይጠበቅብንም። ቁርስ አዲስ አበባ፣ ምሳ አቴንስ ለመመገብ ተችሏል። ድምፀትን ለመቀበል ወይም ለመስጠት ዛሬ ሁሉ ነገር የዓይንና የጆሮ ያህል ቀርቧል። ሲሰየጥኑ ይሁን ሲሰለጥኑ «ገንዘብ ካለ በሰማይ መንገድ አለ» የሚለው ትረካ ዓለምን እየነዳት ይገኛል። ይህ እንግዲህ ዓለም ደርሼበታለሁ የምትለው ግኝቷ ሲሆን የተቆላለፈው ችግሯ ደግሞ የትየለሌ ሆኗል።
ኤድስ የሚሉቱ አይድኔ በሽታ ብዙዎችን ወደ መቃብር ሸኝቷል። ኢቦላና የአእዋፍ ጉንፋን(BIRD FLU) ስንቱን ፈጅቶ የታገሰ ቢመስልም ጨርሶ እንዳልጠፋ ይወቃል። ካንሰር፣ ወባ፣ ስኳር፤ ግፊትና ብዛት፣ ማነስና ድክመት ልዩ ልዩ ህመሞች በርክተዋል፣ ወይም ህመምተኞችን አበራክተዋል። ከቺሊ እስከጃፓን፣ ከግሪንላንድ እስከ አንታርክቲካ የመሬት መንቀጥቀጡና የበረዶ መደርመሱ፣ የመሬት መናዱና ጎርፉ ብዙዎችን አጥፍቷል።
ሀይቲ 230,000 ሰው ሲሞትባት፤ሱናሚ ከኢንዶኔዢያ እስከ ሶማሊያ ጠረፍ ከ280,000 በላይ ሰዎችን መጥረጉን ሰምተናል። ጃፓንም ሀገር አማን ባለችበት ሀብቷን ሳይጨምር10 ሺዎችን ዜጋ አጥታለች።
ጦርነቱ፣ ፍጅቱ፣ የስልጣን ሽኩቻው፣ የሃይማኖት ፉክክሩ፣ የአሸናፊና ተሸናፊ ግብግቡ አይሏል። ያም ሆኖ ዓለም አለሁ፣ ማለቷን አልተወችም። ያለፈውን እየረሳች፣ መጪውን ትኖር ዘንድ ትጥራለች። «ገንፎ እየሞተ፣ ይተነፍሳል» እንዲሉ መሆኑ ነው። አዎ ዓለማችን እየሞተች መተንፈሷን አላቋረጠችም። ባለውና በሚታየው ነገር ለመጽናናት ትሻለች። ቁም ነገሩ ባለውና በሚታየው ነገር ፍጹም መጽናናትን ማግኘት አለመቻሏን አለማወቋ ነው። የተነገረውን አልሰማችም ወይም አልሰምቶም ሆኖባታል።
ማቴ 243-8
እርሱም በደብረ ዘይት ተቀምጦ ሳለ፥ ደቀ መዛሙርቱ ለብቻቸው ወደ እርሱ ቀርበው። ንገረን፥ ይህ መቼ ይሆናል? የመምጣትህና የዓለም መጨረሻ ምልክቱስ ምንድር ነው? አሉት።
ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፦ ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ።
ብዙዎች። እኔ ክርስቶስ ነኝ እያሉ በስሜ ይመጣሉና፤ ብዙዎችንም ያስታሉ።
ጦርንም የጦርንም ወሬ ትሰሙ ዘንድ አላችሁ፤ ይህ ሊሆን ግድ ነውና ተጠበቁ፥ አትደንግጡ፤ ዳሩ ግን መጨረሻው ገና ነው።
ሕዝብ በሕዝብ ላይ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣልና፥ ራብም ቸነፈርም የምድርም መናወጥ በልዩ ልዩ ስፍራ ይሆናል፤
እነዚህም ሁሉ የምጥ ጣር መጀመሪያ ናቸው።
እናም ዓለም የምትወልደውን በምትወልድበት በመጨረሻው ወር ውስጥ ነው ያለችው። እንደነፍሰ ጡር ሴት በምትወልድበት በ9ኛው ወር ውስጥ እንዳለች ልትረዳና «ወልደ አብ፣ ኢየሱስ» 9ነኛው ሰዓት ያስተማራትን ጸሎት ልታሰማ ይገባታል። «
ማቴ2746
ዘጠኝ ሰዓትም ኢየሱስ፦ ኤሎሄ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ? ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ። ይህም። አምላኬ አምላኬ፥ ስለ ምን ተውኸኝ? ማለት ነው።

በዚህ ጽሁፍ ስለዓለም የዳሰስኩት ጽሁፌን በዚያ ላይ ለማንተራስ እንጂ ስለዓለም ለማስተማር ስላለሆነ ዋናው ነጥቤ ዓለም ያለችበትን ደረጃ በማሳየት የዓለም አንድ ክፍል የሆንን እያንዳንዳችን ከዚህ የዓለም ጣር ለመዳን ምን ማድረግ እንዳለብን «የኢያሱ ወልደ ነዌ»ን አብነታዊ መንገድ ለማሳየት ነው። ኢያሱ እንደልጅ ልጅ ሆኖ ኅሊናውን ሳያባክን፣ መንፈሳዊ ልቡናውን በጊዜው ከነበረው መሳሳቻ ጠብቆ የአባቶቹን እግር እንደተረከበ በማሳየት እኛም በዚያ መሠረትነት ላይ ቆመን ዛሬ ዓለምን ከሚንጣት ወጀብ በመዳን የኃጢአት ከተማ ኢያሪኰን አፍርሰን ርስታችንን ለመውረስ እንድንችል ለማስገንዘብ ነው። ፍየል በኃጢአተኛ የምትመሰልበት ዋናው ምክንያት፣ ግልገሎቿን አድፍጦ ወደበላባት የቀበሮ ጫካ ቅጠል ለመቀንጠስ ዳግመኛ የምትመለስ በመሆኗ ነው። እንዲሁ ሁሉ ከጎናችን ብዙዎች ንስሐ ሳይገቡ መሞታቸውን እያየን፣ በቅጽበታዊ አደጋ ዓለም ብዙዎችን እንደሸኘች እየተመለከትን፣ እኛ ዘንድ እንደማይደርስ አስበንና ለእነርሱ እያዘንን በመቆየት ሰንበትበት ሲል ሁሉን ነገር ረስተን እንደነበረው የምቀጥል መሆናችን ነው።

ይቀጥላል.............

Tuesday, February 7, 2012

ሞርሞኒዝም ምንድነው?


ካለፈው የቀጠለ
ክፍል 3
በባለፈው ጽሁፋችን ሞርሞኒዝም የብዙ አማልክት እምነት ቦታ ሆኖ የእምነቱ ተከታዮችም ወደዚህ ወደአማልክትነት ለመቀየር ብዙ መታገልና መጣር እንደሚገባው ተመልክተናል። የዚያኑ ቀጣይ ክፍል ደግሞ እነሆ አቅርበናል።
«እስራኤል ሆይ ስማ አምላካችን እግዚአብሔር አንድ እግዚአብሔር ነው»ዘዳ6፣4
እግዚአብሔር አንድ አምላክ ሆኖ ሳለ ብዙ አማልክት አድርጎ ማቅረብን ጆሴፍ ስሚዝ ከየት አመጣው? ብለን ብንጠይቅ መልሳችን አጭር ነው። ከሔዋን ጀምሮ ሲያሳስት የኖረው ሰይጣን በመኖሪያ ቤቱ ውስጥ የብርሃንን መልአክ መስሎ ከሰጠው መገለጥ የተገኘ ትምህርት ነው። መሐመድ በ7ኛው ክ/ዘመን «ሂሩ»ዋሻ እየሄደ ከአላህ መልአክ ከጅብሪል አገኘሁት ባለው በሚያንዘፈዝፍና በሚያንቀጠቅጥ መገለጥ አላህ አይወርድም፣አይወለድም፣ ዒሳ(ኢየሱስ) ነብይ እንጂ የእግዚአብሔር ልጅ አይደለም፣አልተሰቀለም፣ አልሞተም የሚል የክህደት ትምህርትን ከሰይጣን ተቀብሎ ለዓለም አስተላለፈ። እነሆ እልፍ አእላፋት ይህንኑ አምነው ይገኛሉ።
እግዚአብሔር አንድ አካል፣አንድ ገጽ ነው በማለት በመሐመድ በኩል ሲያሳስት የኖረው ሰይጣን በጆሴፍ ስሚዝ በኩል ደግሞ የለም «አምላክ ቁጥር ስፍር የለውም» ሲል መገኘቱ ሰይጣን የሰውን ልጅ ለማሳሳት መቼም ቢሆን አርፎ እንደማያውቅ ነው። እሱ ስራው ሰው የሚጠፋበት መንገድ ማዘጋጀት፣ ከእውነት ጋር የስህተት ትምህርቶችን አቀላቅሎ መስጠትና ለጥፋት ማዘጋጀትን መደበኛ ስራው አድርጎ ይንቀሳቀሳል። የሚገርመው ግን እስላሞች ይሁኑ ሞርሞኖች ያለእነርሱ ሌላው እንደማይጸድቅ፣ ሲኦል እንደሚወርድና ፈጣሪ የወደድኩት ሃይማኖት የእናንተን ነው እንዳላቸው አድርገው ራሳቸውን አሳምነው መገኘታቸው ነው።

Saturday, February 4, 2012

ማኅበሩ አያንቀላፋም!

« ማኅበሩ አያንቀላፋም»

እንቅልፍ ለሰዎች የተሰጠ የሥጋ እረፍት ነው። «ቀን ለሰራዊት፣ሌሊት ለአራዊት»እንዲሉ! ዛሬ ግን ዓለማችን ቀንና ሌሊቱን አቀላቅላው ሰውም አራዊቱም ጉዞአቸው ባንድ ሆኗል። በሌሊት! ከነዚህ ቀኑንም ሌሊቱንም ከማያንቀላፋው ሀገርኛ ድርጅት አንዱ ራሱን በራሱ የቅዱሳን ማኅበር ነኝ የሚለው «ማኅበረ ቅዱሳን» በቁልምጫ ስሙ «ማቅ» የተባለው ድርጅት ነው። በቤተክርስቲያን ውስጥ ስፍራውና ድርሻው ለጊዜው ባይገባንም ረጅምና ስውር እጁ የሌለበት ቦታ የለም በሚባል ደረጃ ያለእረፍት ይንቀሳቀሳል። ለዚህም ነው የጽሁፋችንን ርእስ «ማኅበሩ አያንቀላፋም» ያልነው። አዎ! ማኅበረ ቅዱሳን አያንቀላፋም። የማያንቀላፋው ራሱን የቤተክርስቲያን ተጠሪ በማድረግና ሲኖዶሱ ባልሰጠው ውክልና በቤተክርስቲያኒቱ መዋቅር ውስጥ ስውር እጁን እንደአባጨጓሬ እያርመሰመሰ በመገኘቱ ነው። ማኅበሩ በሲኖዶስ መሃል ቁጭ ብሎ በስውር እጁ ጳጳስ ሆኖ ይወስናል፣ ያስወስናል፣ይከራከራል፣ይሞግታል። ለሲኖዶሱ አጀንዳ ይቀርጻል፣ የማይስማማውን ይጥላል፣ የፓትርያርኩ የራስ ህመም እስኪነሳ ያሳብዳል። ምክንያቱም ማኅበሩ ጳጳስ ስለሆነ አያንቀላፋም። በአምሳለ ጳጳስ «ማኅበረ ቅዱሳን ባይኖር ቤተክርስቲያን ምን ተስፋ አላት» ያሰኛል። በአድባራትና ገዳማትም መካከል ሳያንቀላፋ በአለቃነት ወይም በሀገረ ስብከት ደረጃ በሥራ አስኪያጅነት ወይም በመምሪያ ኃላፊነት ውስጥም ኅቡእ መንፈስ ሆኖ ይንቀሳቀሳል። የሰባኪዎችን፣የሰንበት ት/ቤቶችን ወይም የምእመናንን ማንነት ይቆጣጠራል፣ ይመረምራል፣ ይሰልላል። ማኅበረ ቅዱሳን አያንቀላፋምና እዚህም ቦታ አለ። ንግዱ ውስጥ! ይነግዳል፣ያስነግዳል። ግብርና ታክስ የማይከፍል የንግድ ተቋም ሆኖ በሆቴሎች፣ በሱቆች፣ በንዋያተ ቅድሳት መሸጫዎች፣በኢንኮርፖሬትድ ድርጅቶች፣ በህትመት፣ በሚዲያ ውጤቶች ውስጥ ሁሉ አለ።

ሞርሞኒዝም!

 

በዳኒ ይትባረክ የተጻፈ( በደጀብርሃን ለብሎጉ እንዲያመች የቀረበ)
.... ክፍል ሁለት

                            ሞሮኒ ማነው?

ስለዚህ ሰው በመጽሐፍም ይሁን በታሪክ ምንም ዓይነት መረጃ አናገኝም። መዝገበ ቃላትም ቢሆን ሞሮኒ(MORONI)የኮሞሮስ ዋና ከተማ መሆኗን እንጂ ሌላ የሚሰጠን ፍንጭ የለም። ታዲያ ይህ ሞሮኒ የተባለው የጆሴፍ ስሚዝ ሰው ማነው?
በመጽሐፈ ሞርሞን (THE BOOOK OF MORMON) መግቢያ ላይ «,,አ በ421 /ም ገደማ መጨረሻ አካባቢ የኔፊ(*) ባለታሪክና ነብይ የነበረ «ሞሮኒ» በጥንታዊ ነብያት አማካይነት በእግዚአብሔር ድምጽ በኋለኛው ቀን እንደሚመጣ እንደተተነበየው ቅዱሱን መዝገብ አተመው፣ እናም በጌታ እንዲጠበቅ ደበቀው» ካለ በኋላ በጌታ ተደብቆ የተቀመጠው ሞሮኒ ከሞት ተነስቶ በ1823 /ም በቤቱ እየጸለየ ሳለ የተገለጠለትና እጅግ በሚደንቅ ግርማ እንደታየው የጆሴፍ ስሚዝ መጽሐፍ ያትታል።
እንግዲህ ሞሮኒ ማለት እንደተከታዮቹ አባባል በ421 /ም ሞቶ በ1823 /ም ትንሳዔ በማግኘት ለጆሴፍ ስሚዝ የተገለጠ መልአክ ነው ማለት ነው።
ከዚህ አባባል የምንረዳው ነገር ሰይጣን በኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወት የታየውን መለኮታዊ መልክ በሚመስል ነገር በሞሮኒ ስም ለጆሴፍ ስሚዝ በመገለጥ እንደሆነ እንረዳለን።
ሰይጣን ጆሴፍ ስሚዝን እንዳታለለው ዛሬም ቢሆን ህልም አለምኩ፣ ራዕይ አየሁ፣ መልዕክት መጣልኝ፣ እመቤታችን ታየችኝ፣ እሳት ከሰማይ ወረደ፣ በዘንዶ የሚጠበቅ ቤተክርስቲያን፣ በእባብ የታጠረ ጸበል በሚል ሰበብ በክርስትናው ውስጥ ዛሬም ብዙ ጆሴፎች አሉ።)
ሰይጣን መቼም አይተኛም። ጆሴፍ ስሚዝን እንዳጭበረበረው እኛንም ሊያጭበረብረን ይፈልጋል። ምክንያቱም ለሞርሞኖች ተስፋቸው አዲስቱ ኢየሩሳሌም ሳትሆን አሜሪካ ነች። ከድርሳናቸው አንዱ ክፍል ኔፊ እንዲህ ይላል።
«የያዕቆብ ቅሪት የሆኑትም ጌታ አምላካቸውን ወደማወቁ ይመጣሉ፣ እናም አሜሪካንን ይወርሳሉ» 3ኔፊ201
ጆሴፍን አሜሪካ የርስት ምድር እንደሆነችና አሜሪካንን የሚናፍቁ ሕዝቦች የሚፈጠሩበት ዘመን እንደሚመጡ ያኔም ሞሮኒ የተነበየላት ስለሆነ እንደሚባረኩ መዋሸቱን ስንመለከት ይህ ሰይጣን በኢትዮጵያም ውስጥ መልኩንና ማሳሳቱን ለውጦ «ደጅህን የረገጠ ኢየሩሳሌምን እንደተሳለመ እቆጥርለታለሁ ብሎ ቃል ገብቶለታል፣ ፍርፋሪህን የበላ የ40 ቀን ህጻን አደርግልሃለሁ ብሏል፣ በስሜ የተጠራ ዘው ብሎ ገነት ይገባል፣ የቅዳሴዬን ጸበል የቀመሰ 30 ትውልድ ሰተት አድርጌ ገነት አገባልሃለሁ ወዘተ ሞርሞናዊ ማሳሳቻዎች ከሰይጣን የወጣ ስለመሆኑ የታወቀ ነው። ሰይጣን ምን ጊዜም ክርስቶስ ያደረገልንን የሕይወት ስጦታ በመቀየር ወደሌላ የማዳኛ ምክንያቶች ለመለወጥ ሳይደክም እንደሚሰራ እንረዳለንና ነው።
ሐዋርያው እንዲህ ብሏል።« ስለዚህም ምክንያት፥ በእውነት ያላመኑ ነገር ግን በዓመፅ ደስ ይላቸው የነበሩ ሁሉ ፍርድን እንዲቀበሉ፥ ሐሰትን ያምኑ ዘንድ እግዚአብሔር የስሕተትን አሠራር ይልክባቸዋል»2ተሰ 211-12


               ሞርሞኖች ስለእግዚአብሔር ያላቸው አስተምህሮ

ሞርሞኖች በአጽናፈ ዓለም ላይ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ፕላኔቶች እንዳሉ፣ በነዚህም ፕላኔቶች ላይ በአንድ ወቅት ሰዎች ይኖሩበት እንደነበረና አሁን ግን አማልክት በሆኑ ኃይሎች እንደሚተዳደሩ ያምናሉ። ከዚህም በተጨማሪ እግዚአብሔርን በተመለከተ 4 ዓይነት አስተምህሮዎች አላቸው።
1/ እግዚአብሔር ሥጋና ደም አለው ይላሉ።
2/እግዚአብሔር አምላክም ሰውም ሆኖ በሰማይ አለ ይላሉ።
3/አማልክት አባት፣ እናት፣ አያት ወዘተ ሆነው በዘር ሐረግ በየፕላኔቶቹ አሉ ብለው ያምናሉ።
4/ እያንዳንዱ ሞርሞናዊም ወደአማልክትነት ለመቀየር መጣር አለበት ይላሉ።
(Mormon doctrine, page 557 &, Doctrine & covenantes section 130. verse 22)

.....ይቀጥላል
(*) የተመለከተው «ኔፊ» የሞርሞኖች ድርሳን ነው።

Friday, February 3, 2012

ሞርሞኒዝም !

            ሞርሞኒዝም ምንድነው? 

በዳኒ ይትባረክ

ሞርሞኒዝም የሞርሞንን የእምነት ፍልስፍና መከተል ማለት ሲሆን የዚህ የእምነት ፍልስፍና መስራቹ ደግሞ ጆሴፍ ስሚዝ ይባላል።

                 ጆሴፍ ስሚዝ ማነው? 

ጆሴፍ ስሚዝ ኒዮርክ ውስጥ ሻሮን ቬርሞንት በሚባል አካባቢ ይኖር የነበረ ሰው ሲሆን የተወለደውም እ,ኤ,አ በ1805 ነው። በሚኖርበትም አካባቢም ማዕድን ለማግኘት ሲል አስማታዊ ልምምድን ያደርግ እንደነበር የብሪንግሃም ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ፕሮፌሰር ሚካኤል ኪውን «Early Mormonizm in the Magic World» በሚለው መጽሐፋቸው ላይ ጠቁመዋል። ብሪንግሃም ዩኒቨርሲቲም የሞርሞኖች ዩኒቨርሲቲ ነው። ስለዚህ እኛ ከዚህ ፍንጭ በመነሳት ጆሴፍ ስሚዝ መተተኛ ወይም ድግምተኛ ነበር ብንል ስህተት አይሆንም።

            ሞርሞኒዝም መቼ ተጀመረ? 

ሞርሞኒዝም የተጀመረው በነጮቹ አቆጣጠር በ1830 ሲሆን የተጀመረውም ጆሴፍ ስሚዝ ተገለጠልኝ ባለው መገለጥ አማካይነት ነው። ጽሁፋቸውን ስናነብ ጆሴፍ ስሚዝ ከ14 ዓመቱ ጀምሮ «የትኛዋ ቤተክርስቲያን ትሆን ትክክል?» የሚል ጥያቄ እንደነበረውና አንድ ቀን «አብና ወልድ» ተገልጠው እውነተኛይቱ ቤተክርስቲያን ምድር ላይ እንደሌለችና በእርሱ( በጆሴፍ በኩል) እንደሚያስተካክሏት ከነገሩት በኋላ ወደየትኛዋም ቤተክርስቲያን እንዳይሄድ እንደከለከሉት «the testimony of the prophet Joseph Smith, page, 1» ላይ ተቀምጦ ይገኛል።

                      የጆሴፍ ስሚዝ ራዕይ

ጆሴፍ ስሚዝ በ1823 መስከረም 21 ቀን ምሽት ላይ አምላክ ነው ወደሚለው እየጸለየ ሳለ የተገለጠለትን ራዕይ እንዲህ በማለት ተናግሯል። «እግዚአብሔርን በመጥራት ላይ ሳለሁ ብርሃን በነበርኩበት ክፍል ሲመጣ አየሁ፣ ብርሃኑም ከቀትር ጸሀይ ይበልጥ ነበር፣ ወዲያውም አንድ ሰው በአልጋዬ አጠገብ እግሩ መሬት ሳይነካ በአየር ላይ ተገለጠልኝ,,» ሲል ከተናገረ በኋላ የተገለጠለት ሰው መልክና ማንነት ከመነገር በላይ እንደነበር ተርኳል። አንዳንድ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መገለጦችን መነሻ አድርገን ለጆሴፍ የተገለጠለት ኢየሱስ ክርስቶስ ይሆን እንዴ? ብለን ብንገምት ግምታችን ግምት ሆኖ የሚቀረው ጆሴፍ ስሚዝ የተገለጠለትን ሰው ማንነት ሲነግረን ነው። እሱም «ሞሮኒ» የተባለ ነው።

               ሞሮኒ ማነው?

ይቀጥላል.................

Thursday, February 2, 2012

በጋሻውን ለማጥቃት፤ሕሙምን መበቀል?

ከደጀብርሃን፤
ለልብ ሕመምተኛው የድረሱለት ጥሪ ማቅረብ ተሀድሶን መደገፍ ነው! አንድ አድርገን ብሎግ(እዚህ ላይ ይጫኑ)
በጠቅላይ ቤተክህነት አዳራሽ የቤተክርስቲያን በዓላት ሲከበሩ ከካቶሊክ ፣ ከግሪክ እና ከሌሎች ተቋማት በእንግድነት እንደሚጠሩ ይታወቃል። ምነው ያኔ በሃይማኖት የማይመስሉን ተገኝተዋል የሚል ተቃውሞ ያልቀረበ?
ጉዳዩና ቂም በቀሉ ያለው ለህመምተኛው የእርዳታ ጥሪ ለማድረግ የተንቀሳቀሱት እነትዝታው ሳሙኤል፣ እነምርትነሽ ጥላሁን በመሆናቸው ብቻ ነው። ምርትነሽ በመዝሙሯ ያስተማረችውንና ያነጸችውን የክርስትና ምግባር ዋጋ ማሳጣት ለምን?
እነምርትነሽ ካልጠፉ የልብ ህሙምም የእርዳታ በሩ ድርግም ይበልበት ክርስትና ነው? ወይስ ጸረ ክርስትና?
ያገኘነውን መረጃ እናካፍላችሁ! መልካም ንባብ!
ለእንዳለ ገብሬ የተዘጋጀው የዕርዳታ ገቢ ማሰባሰቢያ ጉባዔ በቀሲስ ሳሙኤል እሸቱ የግል ውሳኔ ታገደ ዕገዳው ቀሲስ ሳሙኤል በሰው ሕይወት ላይ ያስተላለፉት ውሳኔ በመሆኑ፣ በወንጀል ሊያስጠይቃቸው ይችላል ቤተክርስቲያን የበላይ ኃላፊ ሲያዝ፣ የበታች ኃላፊ የሚሽርበት ሥርዓት አልበኝነት የነገሠባት ተቋም ሆናለች በከፍተኛ የልብ ሕመም ለሚሰቃየው እንዳለ ገብሬ ማሳከሚያ የሚውል ገቢ ለማሰባሰብ ጥር 20 ቀን 2004 ዓ.ም የተዘጋጀው ጉባዔ በቀሲስ ሳሙኤል የግል ውሳኔ መታገዱ ከጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ አመለከተ፡፡ ታማሚው አቶ እንዳለ ገብሬ ቤተክርስቲያን ድጋፍ እንድታደርግለት ባቀረበው ማመልከቻ ላይ ብፁዕ አቡነ ፊሊጶስ በስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ በኩል አስፈላጊው የገቢ ማሰባሰቢያ ጉባዔ እንዲዘጋጅለት መርተውለታል፡፡ የመምሪያው ኃላፊ መምህር አዕመረም በግል ከታማሚውና ከልዩ ልዩ ክፍሎች ጋር በመነጋገር ጉባዔውን የሚያዘጋጁት መምህራን የስብከት አገልግሎት ማስረጃዎችን ከመንፈሳዊ ኮሌጆችና ከአጥቢያ ቤተክርስቲያናት አቅርበው እንዲያካሂዱለት ከመወሰናቸውም በላይ አንድ የፕሮግራም መሪ እና የስብከት መምህር ከጠቅላይ ቤተክህነቱ በማከል ጉባዔው በተጠቀሰው ዕለትና ቦታ እንዲካሄድ ወስነው ወደ ባህርዳር አካባቢ መጓዛቸው ታውቋል፡፡ ይሁን እንጂ ጉባዔው ካልታገደ ተኝተን አናድርም ያሉት የ"ማኅበረ ቅዱሳን" ሠራዊት አባላት መምህር አዕመረ አለመኖራቸውን አይተው የመምሪያውን ምክትል ኃላፊ ቀሲስ ሳሙኤል እሸቱን በመወትወትና በማስፈራራት ጭምር አለቃው የወሰኑትን በመሻር የዕገዳ ማስታወቂያ እንዲያወጡ ያዟቸዋል፡፡ ቀሲስ ሳሙኤል እሸቱም ያለአንዳች ማቅማማት የአለቆችን ትዕዛዝ በመሻር ጉባዔው መታገዱን ዓርብ አመሻሽ ላይ ማስታወቂያ የለጠፉ ሲሆን፣ የአዳራሽ ቁልፍ የያዘውን አቶ በሪሁንን ቁልፉን ይዞ ከአካባቢው እንዲሰወር በመንገር ጉባዔ አለብኝ በማለት ወደ ድሬዳዋ ተጉዘዋል፡፡ ቅዳሜና እሁድ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ኃላፊዎች ሆን ብለው ይሁን በአጋጣሚ በሥፍራው ባለመኖራቸው ጉባዔው እንዲካሄድ ማስደረግ ባለመቻሉ አስተባባሪዎች ፕሮግራሙን ለመሠረዝ መገደዳቸው ታውቋል፡፡ የዕርዳታ ጥሪውን በመስማት ወደ ጠቅላይ ቤተክህነት አዳራሽ የተመመው ሕዝብ በርካታ ሲሆን፣ ለምን ይታገዳል በሚል ብሶት ውስጥ ስለነበር ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ለሌላ ቀን መተላለፉ በማስታወቂያ እንዲነገረው ተደርጓል፡፡ ታማሚው አቶ እንዳለ ታክሞ ለመዳን የቀረው ከአንድ ወር ያነሰ ጊዜ ሲሆን እስከ መጨረሻው ሰዓት ከቀሲስ ሳሙኤል እሸቱ ዘንድ በመሄድ "ስለ እግዚአብሔር ብለው አይጨክኑብኝ" ብሎ ቢማፀንም፣ ቀሲሱ ከ"ማኅበረ ቅዱሳን" ለሚሰጣቸው ድርጎ ልባቸው ተሸንፎ ክርስቲያናዊ ግዴታቸውን ሊወጡ አልቻሉም፡፡ ቤተክርስቲያን የዕርዳታ እጆቿን ስትዘረጋ ዕርዳታው በአግባቡ እንዳይደርስና የታማሚው ሕይወት አደጋ ላይ እንዲወድቅ ማድረግ በኃላፊነት የሚያስጠይቅ ከመሆኑም በላይ አደጋ ላይ ያለን ሰው በቸልተኝነት (ምን አገባኝ በሚል ስሜት) ተገቢውን አለማድረግ ራሱን የቻለ ወንጀል መሆኑ በወንጀለኛ መቅጫ ሕጉ ተደንግጓል፡፡ ጉዳዩ በዚህ ብቻም የሚታለፍ ሳይሆን ቤተክርስቲያናችን ዘርና ቋንቋ፣ ሃይማኖትና ጾታ ሳትለይ ለማንኛውም ሰብዓዊ ፍጡር ዕርዳታ የምትሰጥ ከመሆኑ አንፃር የቤተክርስቲያናችንን መልካም ገጽታ የሚያጎድፍ እኩይ ተግባር ነው፡፡ የጉባዔው አስተባባሪዎችም አስፈላጊውን መረጃዎች አሟልተው በቤተክርስቲያን ልጆች አገልግሎቱ የሚሰጥ በመሆኑ፣ ጉባዔው የሚታገድበት አንዳች ምክንያት አልነበረም፤ የለምም፡፡ በቤተክርስቲያናችን፣ በተለይም "ማኅበረ ቅዱሳን" እንደልብ ጣልቃ እየገባ ማተረማመስ ከጀመረ ወዲህ ሥርዓት ታውኳል፡፡ ማንም ማንንም ከማይሰማበት ደረጃ ላይ ተደርሷል፡፡ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ፣ ቅዱስ ሲኖዶስና የጠቅላይ ቤተክህነት ሥራ አስኪያጁ የሚያስተላልፉት መመሪያና ትዕዛዝ በተራ የበታች ሠራተኞች ይሻራል፤ ይቀለበሳል፡፡ የአቶ እንዳለን ጉዳይ እንደማሳያ ብንቆጥረው የመንበረ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት፣ የጠቅላይ ቤተክህነት ሥራ አስኪያጅ ጽ/ቤትና የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ የሰጡት ትዕዛዝ በአንድ ቀሲስ ሳሙኤል እሸቱ ተሽሯል፡፡ በሪሁን የተባለው የአዳራሽ ቁልፍ ያዥ ቁልፉን ይዞ ተሰውሯል፡፡ ይህ በቤተክርስቲያን የተካሄደ ውንብድና እንጂ አገልግሎት ሊባል አይችልም፡፡ ዓለም በግልፀኝነትና በተጠያቂነት ዘመን ስትራመድ ቤተክርስቲያን ግን ርስ በርስ መጠላለፍ በበዛበት እና የጨለማው ዓለም ተንኮል ተተብትባ ስትታይ ይህንን ትውልድ በእጅጉ ያሰቅቀዋል፡፡ ውሳኔዎች የሚመሩት በእምነትና በሥርዓት መሆኑ ቀርቶ፣ ገንዘብ የዳኝነቱን ቦታ ሲረከብ ማየት ያለንበትን አሳዛኝ ሕይወት ያመላክታል፡፡ የእግዚአብሔር ምሕረትና ጥበቃው ከእኛ አይለይ!!! አሜን!!! Posted by Dejeselaam at 1:48 AM
source' dejeselaam blog

Sunday, January 29, 2012

«ገና በመንገድ ሳለህ ከባላጋራህ እንድትታረቅ ትጋ»ሉቃ 12፣58

ከዚህ ቀደም ስለእርቅ ጉዳይ በተነሳ ሃሳብ ዘመድኩንን ኃያልና የማይንበረከክ ክንድ ባለቤት እንደሆነ አጋኖ ደጀሰላም ብሎግ ዘግቦ ነበር። ዘመድኩንም ሲኦል ብወርድ እንኳን ከበጋሻው ጋር እርቅ አይሞከርም በማለቱም ተገርመን አስተያየት ጽፈን በደጀሰላም ላይ አስነብበናል። ሰጥተን የነበረውም አስተያየት ከላይ የሰጠነውን ርእስ መሰረት ያደረገ ነው። በወቅቱ የሰጠነውን አስተያየት እንዳለ አቅርበነዋል፣
«Anonymous said... ከሳሽንም ተከሳሽንም በደንብ አውቃቸዋለሁ። ወደ ዝርዝር ብንገባ ከአምላክ የሚያጣላ ይሆናልና ተከድኖ ይብሰል። የሆኖ ሆኖ ፍርድ ቤት ስለምስጢረ ሥላሴ ሳይሆን ስለስመ ማጥፋት ወንጀል የቀረበ ክስን እያየ እንደሆነ ከክሱ ጭብጥ ስንረዳ ከሳሽና ተከሳሽ ክርክሩን በእርቅ ቢጨርሱት 1/ የእግዚአብሔር ልጆች ይባላሉ ። 2/ሃይማኖተኞች ሃይማኖት በሌላቸው(ዓለማውያን) ፍርድ ቤቶች የሚያደርጉት ክርክር ሃይማኖቱን ያስነቅፋልና ይህንን ለማስቀረት 3/የበደሉንን ይቅር ማለት ስለሚገባን ዘመድኩን ዕርቅ አልቀበልም ማለቱ እውነተኛ ኦርቶዶክሳዊ መሆኑን ሳይሆን የሚያመለክተው አለማወቁን፤ ግብዝነቱንና የታይታ ክርስቲያን መሆኑን እንጂ የክርስቶስ ልጅ መሆኑን አይደለም። ክርስቶስ ፍርድ ቤት ይለያችሁ ሳይሆን ያለው ከባላጋራህ ጋር አስቀድመህ ታረቅ ነው ያለው። እኔ ከአንድ እስላም ጋር ብጣላና ብታረቅ በሰውነቱ እንጂ የሱን ሃይማኖት ለመቀበል ስላልሆነ ዘመድኩን እሱ ከበጋሻው ጋር ታረቀ ማለት እሱ እንደሚለው ተሃድሶ ሆነ ማለት አይደለም። የሚያሳብቅ ውሸት መሆኑ ደግሞ ሲዖልም ቢሆን እወርዳለሁ በማለት አንድ ክርስቲያን በህይወት ዘመኑ ዕድል ፈንታውና የፍርድ ዕጣው በፍጹም ሊሆን ቀርቶ ሊመኝ የማይገባውን መናገሩ አሳዛኙ አባባል ነው። እውነተኛ ክርስቲያን ነኝ ለማለት ማረጋገጫና ሌላውን የማሰመኛ ቃል አድርገን ሲዖልም ቢሆን እወርዳለሁ ማለት ከየት የተገኘ ትምህርት ነው። እኛ እድል ፈንታችንና መንፈሳዊ ፍላጎታችን መቼም ቢሆን ከክርስቶስ ጋር መኖር ነው እንጂ ሲዖልም ቢሆን ወርደን የምናረጋግጠው እውነተኛነታችን ስለሌለ ይህንን ቃል ከመጠቀም(ሎቱ ስብሐት)እንላለን። ሳጠቃልል ዘመድኩን የምትረታ መሆንህን ብታውቅ እንኳን ከፍርድ ቤት ክርክርና ጭቅጭቅ በኋላ ከምታገኘው የረቺነት ኃላፊ ጠፊ ዝና ይልቅ ለክርስቶስ ብለህ ሁሉን ትተህ የምታደርቀው እርቅ ብዙ ኃጢአትህን ይሸፍናል፤ ሰማያዊ ክብርንም ያስገኝልሃልና ከልብህ መክረህ ታረቁ የሚሉ ሽማግሌዎች ካሉ ወደመጡበት አትመልስ ወንድማዊ ምክሬ ነው። September 10, 2011 12:37 PM የሚል አስተያየት ሰጥተን የሰማን የለም።
የያኔውን የደጀሰላም ብሎግ «ወደፊት በሉለት ይለይለት» ሙሉ ጽሁፍን ለማንበብ ከፈሉጉ (እዚህ ላይ ይጫኑ)
  አሁን ደግሞ «ደጀሰላአም» የተሰኘ ብሎግ በወቅቱ ብለነው የነበረውን አስተያየት የሚያጠናክርና የክሱ ሂደት የፈራነው ግምት የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ መድረሱን ከታች አስነብቦናል። መልካም ንባብ!

Friday, January 27, 2012

ሕሙም እንዳይረዳ የተቃውሞ ዘመቻ!


የአቶ እንዳለ ገብሬን ሕይወት ለመታደግ የገቢ ማሰባሰቢያ መንፈሳዊ ጉባዔ ሊካሄድ ነው
"ማኅበረ ቅዱሳን" ጉባዔው እንዲካሄድ በመፍቀዳቸው ብፁዕ አቡነ ፊሊጶስን ስም አጠራራቸው እስኪረሳ እንዲያልፉ እርግማን አወረደባቸው
ባደረበት የልብ ሕመም ምክንያት ውጭ ሀገር ሄዶ ካልታከመ በስተቀር የመዳን ተስፋው የመነመነው የአቶ እንዳለ ገብሬን ሕይወት ለመታደግ ከ450 ሺህ በላይ ወጪ የተጠየቀ ሲሆን፣ ቤተክርስቲያንን በማገልገል ላይ ያሉት መምህራንና ዘማርያን፣ በጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት አዳራሽ ጥር 20 ቀን 2004 ዓ.ም ከቀኑ ሰባት ሰዓት የሚጀምርና ገቢው ለዚሁ ወንድም መታከሚያ የሚውል መንፈሳዊ ጉባዔ አዘጋጅተዋል፡፡
ይህንን የተቀደሰና ሁሉም ወገን ሊረባረብበት የሚገባ ዕርዳታ በወንጌሉ ቃል መታጀቡና መመራቱ በዘልማድ ማኅበረ ሰይጣን የሚባለውና ራሱን "ማኅበረ ቅዱሳን" እያለ የሚጠራው ፈሪሳዊ ማኅበርን በማስኮረፉ ጉባዔውን ለማደናቀፍ በመውተርተር ላይ ይገኛል፡፡ ካለ እኔ በስተቀር ቤተክርስቲያን ልጅ የላትም የሚለው ይኸው ማኅበር፣ ልዩ ልዩ አቃቂሮችን በማውጣት ራሱ ፈራጅ፣ ራሱ ፈጻሚ በመሆን በምዕመናንና በቤተክርስቲያን መካከል እንደ ግድግዳ ቆሞ ማወክ ከጀመረ ዓመታት ያስቆጠረ ሲሆን፣ ይህንኑ ጉባዔ ያዘጋጁት ለእርሱ ዓላማ አንገዛም ያሉ ሰባክያነ ወንጌልና መዘምራን በመሆናቸው፣ እንደተለመደው የተሃድሶ ታፔላውን ከፍ አድርጎ በማንሳት ያዙኝ ልቀቁኝ እያለ ነው፡፡(ዘመቻውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ)
ዘወትር ስድብና ዕርግማን ከአፉ የማይጠፋው "ማኅበረ ቅዱሳን" የወንድማችንን ሕይወት ለመታደግ ማንኛውም ሰብዓዊ ፍጡር ዕርዳታ እንዲያደርግለት በመማጸን ፈንታ በሲኖዶስ ያልታገዱትና ያልተከለከሉት ሰባክያንና ዘማርያን እንደታገዱና እንደተወገዙ አስመስሎ በማውራት ጠቅላይ ቤተክህነት አዳራሽ ለምን ተፈቀደላቸው ብሎ በመጮህ ላይ ነው፡፡ ይባስ ብሎም፣ "አንድ አድርገን" በተባለው ብሎጉ፣ ". . . ፈቃጆች ነገ ስም አጠራራቸው እስኪረሳ ድረስ ያልፋሉ. . ." በማለት ሆን ብሎ በስም ባይጠራቸውም ጉባዔው እንዲካሄድ የፈቀዱትን እነአቡነ ፊሊጶስን ወርፏል፡፡

Thursday, January 26, 2012

መግደልና ማቃጠል!!





በሀላባ ቁሊቶ አክራሪ ሙስሊሞች ለጥምቀት በዓል በወጡ ክርስቲያን ምዕመናን ላይ ጉዳት አደረሱ

የሀላባ እና አካባቢው ምዕመናን ከፍተኛ ክርስቲያናዊ ገድል በመጋደል ሃይማኖታቸውን መከላከላቸው ተሰማ

ጉባ በተባለች አነስተኛ መንደር ለገበያ በወጡ ክርስቲያኖች ላይ የማኅተም መበጠስና የገንዘብ ዝርፊያ ተካሂዷል

መንግሥት ተገቢውን እርምጃ ካልወሰደ መጪው ጊዜ እጅግ አስቸጋሪ እንደሚሆን ተገምቷል


በደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ከሻሸመኔ በስተምዕራብ በግምት 75 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምትገኘው በሀላባ ቁሊቶ ከተማ ጥር 12 ቀን 2004 ዓ.ም ለጥምቀት በዓል በወጡ ክርስቲያኖች ላይ ጥቃት መድረሱን ከዚያው አካባቢ የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡

ሆን ተብሎ እና ታቅዶ በተሰነዘረው በዚህ ጥቃት በርካታ ክርስቲያን ወንዶችና ሴቶች፣ ሕፃናትና ዐዋቂዎች ከፍተኛ የመፈንከትና የመቁሰል አደጋ ደርሶባቸዋል፡፡ ጉዳቱ የደረሰው ምዕመናን የቅዱስ ሚካኤልና የመድኃኔዓለም ታቦታትን ወደ ቤተመቅደስ ለመመለስ አጅበው በሚጓዙበት ወቅት መሆኑን ምንጮቻችን አረጋግጠዋል፡፡ በዕለቱ በክርስቲያኖች በኩል ከወትሮው የተለየ ግጭትን የሚያነሳሳ ምንም ነገር አለመፈጸሙንና ታቦታቱ ተጉዘው በከተማዋ አደባባይ ለዕረፍት በቆሙበት ወቅት፣ አድፍጠውና ተዘጋጅተው ምቹ ሰዓትና ቦታ ይጠብቁ በነበሩ ሙስሊሞች በኩል የድንጋይ እሩምታ መጀመሩን እማኞቻችን አስረድተዋል፡፡

Thursday, January 19, 2012

በጥምቀትም ከእርሱ ጋር ተቀበራችሁ!



(ከእንግሊዝኛ ማጣቀሻ ጋር)

ቆላስ ፪፥፲፪ (Colossians2:12) « በጥምቀትም ከእርሱ ጋር ተቀብራችሁ፥ በጥምቀት ደግሞ፥ ከሙታን ባስነሣው በእግዚአብሔር አሠራር በማመናችሁ፥ ከእርሱ ጋር ተነሣችሁ»
ኦሪቱ የአዲስ ኪዳኑን ጥምቀት በማንጻትሥርዓት ታከናውነዋለች። ከኃጢአት ማንጻት! ማንም ቅድስናንና ንጽሕናን ሲሻ ይህንን የማንጻት ልማድ መፈጸም ግዴታው ነው። እንደሕጉ የታዘዘውን መስዋዕት አቅርቦ የሥርዓቱ ማጠቃለያ በምንጭ ውሃ ሰውነቱ መታጠብ አለበት። የማንጻት ልማዱ የሚከናወነው ከሰፈር ውጭ ነው።
«ንጹሕም ሰው የጊደሪቱን አመድ ያከማቻል ከሰፈሩም ውጭ በንጹሕ ስፍራ ያኖረዋል ርኵሰትም ለሚያነጻ ውኃ ለእስራኤል ልጆች ማኅበር ይጠበቃል ከኃጢአት ለማንጻት የሚሆን ነው» ዘኁ ፲፱፣፱ (Numbers19:9)
ፈሳሽ ያለበት ይሁን ለምጽ የወጣበት ወይም ቆረቆር የታየበት ይሁን የመርገም ወራቷ የመጣባት ሴት ሁላቸውም እንደሕጉ የታዘዘውን የኃጢአት መስዋዕት አቅርበው ሲያበቁና ሥርዓቱ ከተከናወነ በኋላ ለመንጻት በምንጭ ውሃ መታጠብ የግድ ነው። ያኔ ነጽተው ወደሕዝቡ ይቀላቀላሉ። አለበለዚያ ከሕዝቡ ጋር ሕብረት አይኖቸውም።ፈሳሽ ነገር ያለበት ሰው ከፈሳሹ ነገር ሲነጻ ስለ መንጻቱ ሰባት ቀን ይቈጥራል ልብሱንም ያጥባል፥ ገላውንም በምንጭ ውኃ ይታጠባል፥ ንጹሕም ይሆናል» ዘሌ ፲፭፣፲፫ (Leviticus15:13)
«የሞተውን ወይም አውሬ የሰበረውን የሚበላ ሰው ሁሉ፥ የአገር ልጅ ወይም እንግዳ ቢሆን፥ ልብሱን ያጥባል፥ በውኃም ይታጠባል፥ እስከ ማታም ርኩስ ይሆናል ከዚያም በኋላ ንጹሕ ይሆናል። ልብሱንና ገላውን ባያጥብ ግን ኃጢአቱን ይሸከማል» ዘሌ ፲፯፣፲፭-፲፮ (Leviticus17:15-16) ያ ማለት ኦሪት የምታነጻውና መስዋዕቱን ፍጹም የምታደርገው በውሃ በመታጠብ ነው።
የዚህ የማንጻት ልማድ የድንጋይ ጋኖች አብነት ሆነው በዘመነ ሐዲስ ከአንድ ሰርግ ቤት ተቀምጠው እናገኛቸዋለን። ቦታው ቃና ዘገሊላ ነው። እነዚህ የድንጋይ ጋኖች በኦሪቱ ለማንጻት ሥርዓት የምንጭ ውሃ የሚጠራቀምባቸው ነበሩ። ወንጌሉ አገልግሎታቸውን ለይቶ አስቀምጦልናል።
«አይሁድም እንደሚያደርጉት የማንጻት ልማድ ስድስት የድንጋይ ጋኖች በዚያ ተቀምጠው ነበር፥ እያንዳንዳቸውም ሁለት ወይም ሦስት እንስራ ይይዙ ነበር» ዮሐ ፪፣፮ (John2:6)
እነዚህ የማንጻት ሥርዓት የድንጋይ ጋኖች የመጀመሪያውን የአዲስ ኪዳን ተአምርም አስተናግደዋል። የእውነተኛው የወይን ግንድ ደም ለዓለሙ ሁሉ እንደሚፈስ ምሳሌ ሆነዋል። ቅድስት ማርያም ወይን እንዳለቀባቸው ባሳሰበች ጊዜ ጌታም እውነተኛው ወይን ለዓለሙ ሁሉ የሚፈስበት ጊዜ ገና መሆኑን ሲያስረዳ «ኢየሱስም፦ አንቺ ሴት፥ ከአንቺ ጋር ምን አለኝ? ጊዜዬ ገና አልደረሰም አላት» ዮሐ ፪፣፬ (John2:4)እውነተኛ ወይን እስኪሰጥ የኦሪቱ የማንጻት ሥርዓት የድንጋይ ጋኖች ጊዜው እስኪደርስ ድረስ ተአምር አስተናግደዋል። እነሱ ሲፈጽሙ የቆዩበትን የማንጻት ሥርዓት አዲስ ኪዳን በማይደጋገምና አንዴ በሚፈጸም የኃጢአት ሥርየት ለውጣዋለች። እሱም «ጥምቀት» ነው። ኦሪት ከሰፈሩ ውጭ ሁልጊዜ በሚፈጸምና በሚፈሰው የደም መስዋዕት ማሳረጊያ የሚሆን የመንጻትን ሥርዓትን ታዛለች።
አዲስ ኪዳን ደግሞ ከሰፈሩ ውጭ በተሰቀለውና አንዴ በሞተው የበጉ መስዋዕት ምሳሌ የውሃ ጥምቀትን በመቀበሩ ጠልቀው፣ ከውሃው በመውጣት ትንሳዔውን መስክረው፣ አንዴ በፈጸሙት ሥርዓት የኃጢአት ስርየት ታስገኛለች።
ለዚህም ነው ሐዋርያው ጳውሎስ እንዲህ ያለው።
ቆላስ ፪፣፲፪ (Colossians2:12) «በጥምቀትም ከእርሱ ጋር ተቀብራችሁ፥ በጥምቀት ደግሞ፥ ከሙታን ባስነሣው በእግዚአብሔር አሠራር በማመናችሁ፥ ከእርሱ ጋር ተነሣችሁ»
ጥምቀት ከንስሐ በኋላ የምትፈጸም ስለመሆኗ መገንዘብ ያስፈልጋል። ንስሐ ደግሞ ስላለፈው ተጸጽቶ፣ በጥምቀት ስለሚገኘው ጸጋ አምኖ መቀበልን ይጠይቃል። መጥምቁ ዮሐንስ በዮርዳኖስ ዙሪያና በሄኖን ማጥመቂያው ሁሉ ሲናገር የነበረው የቅድሚያ አዋጅ «ንስሐ ግቡ» እያለ ይሰብክ እንደነበር እንያለን።
«ዮሐንስ በምድረ በዳ እያጠመቀ የንስሐንም ጥምቀት ለኃጢአት ስርየት እየሰበከ መጣ» ማር ፩፣፬ (Mark1:4)
«ከመምጣቱ በፊት ዮሐንስ አስቀድሞ ለእስራኤል ሕዝብ ሁሉ የንስሐን ጥምቀት ሰብኮ ነበር» የሐዋ ፲፫፣፳፬ (Acts13:24)
«እኔስ ለንስሐ በውኃ አጠምቃችኋለሁ፤ ጫማውን እሸከም ዘንድ የማይገባኝ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ግን ከእኔ ይልቅ ይበረታል፤ እርሱ በመንፈስ ቅዱስ በእሳትም ያጠምቃችኋል»ማቴ ፫፣፲፩ (Matthew 3:11)
ሐዋርያው ጴጥሮስም በበዓለ ሃምሳ ተሰብስበው ለነበሩት ነፍሳት ሁሉ አዲሱን የምስራች ከሰበከ በኋላ «ምን እናድርግ?» ብለው በጠየቁት ጊዜ የሰጣቸው መልስ ቅድሚያው ንስሐ ግቡ ነው። ቀጥሎም ኃጢአታችሁ ይሰረይ ዘንድ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ ነው። ከዚያም የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ ትቀበላላችሁ ነበር ያላቸው ንግግሩን በማያያዝ።
«ጴጥሮስም፦ ንስሐ ግቡ፥ ኃጢአታችሁም ይሰረይ ዘንድ እያንዳንዳችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ፤ የመንፈስ ቅዱስንም ስጦታ ትቀበላላችሁ» የሐዋ ፪፣፴፰ Acts2:38
«እምነት ከመስማት ነው፣ መስማትም ከእግዚአብሔር ቃል ነው» ሮሜ፲፣፯ Rome10:7 የሚለው ትምህርት በመጀመሪያ ገቢር ላይ ሲውል የተነገራቸውን ቃል አመኑ፣ ያመኑበትን ተቀበሉ፣ በተቀበሉት ተጠመቁ፣ ከዚያም ወደ መዳን ሕይወት ተጨመሩ ይለናል መጽሐፉ።
« በብዙ ሌላ ቃልም መሰከረና። ከዚህ ጠማማ ትውልድ ዳኑ ብሎ መከራቸው። ቃሉንም የተቀበሉ ተጠመቁ፥ በዚያም ቀን ሦስት ሺህ የሚያህል ነፍስ ተጨመሩ» የሐዋ ፪፣፵-፵፩ Acts40:41
ታዲያ እኛስ ምን ማድረግ ይጠበቅብናል?
፩/ « እነሆም፥ ድምፅ ከሰማያት መጥቶ። በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው አለ» እርሱን ስሙት ያለውን ብቻ ተቀብለን በማመን አንዲት ጥምቀት በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም መጠመቅ! ማቴ ፫፣፲፯,Matthew3:17 ኤፌ ፬፣፬, ማቴ ፳፰፣ ፲፱
፪/ ከተጠመቅን ደግሞ «ከእንግዲህስ ወዲያ ለኃጢአት እንዳንገዛ የኃጢአት ሥጋ ይሻር ዘንድ አሮጌው ሰዋችን ከእርሱ ጋር እንደ ተሰቀለ እናውቃለን፤ የሞተስ ከኃጢአቱ ጸድቋልና» ሮሜ ፮፣፮ እንዳለው ዳግም ወደኃጢአት አለመመለስ!
፫/ ያመነና የዳነ የክርስቶስ ፍሬ ይታይበት ዘንድ ግድ ነው። «በመልካም መሬት የተዘራውም ይህ ቃሉን ሰምቶ የሚያስተውል ነው፤ እርሱም ፍሬ ያፈራል አንዱም መቶ አንዱም ስድሳ አንዱም ሠላሳ ያደርጋል» ማቴ ፲፫፣፳፫ Matthew13:23
ከዚህ ከሦስቱ የወጣ ሁሉ ይህን ሆኗል ማለት ነው።
«አውቀዋት ከተሰጣቸው ከቅድስት ትእዛዝ ከሚመለሱ የጽድቅን መንገድ ባላወቋት በተሻላቸው ነበርና። ውሻ ወደ ትፋቱ ይመለሳል፥ ደግሞ። የታጠበች እርያ በጭቃ ለመንከባለል ትመለሳለች እንደሚባል እውነተኞች ምሳሌዎች ሆኖባቸዋል» ፪ኛ ጴጥ ፪፣፳፩-፳፪ 2 Peter2:21-22
ስለሆነም ጥምቀትን ከእውቀት ጋር ስለመዳናችን እንጂ ስለበዓል ጭፈራና የጭፈራ ስርዓት አከባበር እንዳይውል እንጠንቀቅ!
መልካም በዓለ ጥምቀት!!!!!!!!!




የጥምቀት በዓል መታሰቢያ ስዕሎች

Friday, January 13, 2012

የተስፋው ቃል!





«እኛ በመንፈስ ከእምነት የጽድቅን ተስፋ እንጠባበቃለንና» ገላ ፭፣፭
በተስፋ የሚጠብቅ ክርስቲያን ትክክለኛ እምነትን የያዘ ነው። ፍጹም የሆነ እምነት በሌለበት የጽድቅን ተስፋ መጠባበቅ የለም። ስለሚጠባበቁት ተስፋ ፍጻሜ እምነት ሊኖር የግድ ነው።
ወንድና ሴት ሊጋቡ ሲወስኑ በጋብቻ ውስጥ ሳሉ ስለሚሆነው ነገር ሁሉ አስቀድመው በተስፋ አምነው ይፈጽማሉ። በጋብቻቸው ልጆችን ይወልዱ ዘንድ ተስፋ አድርገው ያምናሉ እንጂ እየወለዱ አይጋቡም። ሴትም በጽንሷ መጨረሻ ወራት ልጇን ትወልድ ዘንድ በተስፋ ትጠብቃለች እንጂ የጽንስ ውጤት ምን እንደሆነ ሳታውቅ ጽንስን አትለማመድም። ስለሚሆነው ነገር ባለው ጽኑ እምነት የተነሳ ውጤቱን በተስፋ መጠበቅ የግድ ይሆናል ማለት ነው።
አንድ ሰው ቃል ከገባለት ሌላ ሰው የተገባለትን ቃል ፍጻሜ በተስፋ ይጠብቃል። የገባለት ቃል ፍጻሜው ምንም ይሁን ምንም የተስፋውን ቃል ያይ ዘንድ በልቡ አስቀምጦ ይጠብቃል።
እንደዚሁ ሁሉ የተበደለ እንደሆነ የሚያምን ማንም ቢኖር ወደፍርድ አደባባይ ቢሄድ የበደሉን ዋጋ መልካም ፍርድን በተስፋ ይጠብቃል። በተስፋ ስለሚጠብቀው ነገር የጸና እምነት ባይኖረው ወደፍርድ አደባባይ በደሉን ይዞ ሊሄድ አይችልም።
ኦርቶዶክስ ይሁን እስላም፣ ይሁዲ ይሁን ጄሆቫ ዊትነስ፣ ፕሮቴስታንት ይሁን ካልቪኒስት የሁሉም ሃይማኖት ተከታይ በሚያምነው ሃይማኖት ውስጥ የመጨረሻ ግቡን በተስፋ ይጠባበቃል። ውጤቱ ምንም ይሁን ምንም የሚጠባበቀውን ተስፋ በእምነት ሳይቀበል ሃይማኖታዊ ልምምዱን በኑሮው ሁሉ ሊተገብር አይችልም።
ተስፋውን የሚጠባበቀው ከማመን ነው። ማመን ደግሞ ከመስማት ነው። በተስፋው ነገር ላይ እምነት ሳይኖረው ተስፋ አያደርግም። የሚያምነው ደግሞ ስለሚጠባበቀው ተስፋ በደንብ በመስማት ነው። ሳይሰማ እንዴት ያምናል? መጽሐፉም «እምነት ከመስማት ነው» ያለውም ለዚህ አይደል!!

Friday, January 6, 2012

እኔ ማነኝ?



(by dejebirhan)

«እኔ ማነኝ? አንተስ ወንድሜ ማነህ?»

እኔ አበባ ነኝ ፣ የማለዳ ጤዛ ያረፈብኝ፣

ፍካት፣ ድምቀት የከበበኝ፣

ያይን ስስት፣መዐዛ ሽታ፣ የሞላብኝ፣

የንብ ቀሰም፣ ጣፋጭ ማር ነኝ፣

የከበርኩኝ፣ ውበትን የታጠርኩኝ፣

አበባ ነኝ፣ አበባ ነኝ፣

«እኔ ማነኝ፣ እንዴት አልኩኝ?

«አንተስ ማነህ፣ ለምን አልኩኝ?።

                                  ጠያቂ አዋቂ፣ ያ'በው ወግ፣

                                 ጸገየ እጽ ፣ የፍጥረት ሕግ፣

                              ለካስ ነበር-ወደማታው፣ መጠውለግ፣

                                      የመፍረስ ጫፍ ፣ ሌላ ጥግ፣

ታዲያስ እኔ ማነኝ?

ፍካት ድምቀት፣ የማይዘልቀኝ፣

ውበት ጤዛ፣ የሚያረግፈኝ፣

ከሰሎሞን የተሻልኩኝ፣ውበት የደረብኩኝ፣

ሆኜ ሳለሁ፣ ባዶ ገላ ያሸነፈኝ፣ እኔ ማነኝ?

                                   መልስ አገኘሁ፣ የራሱ ካደረገኝ፣

                                    ሳልፈልገው ከፈለገኝ።

                                   እኔ የኔ አይደለሁም፣

                               ውበቴን ሽንፈት አይጥለውም፣

                               መርገፍ ልብሴ፣ ወልቆ አይቀርም፣

አበባዬ ክርስቶስ ነው፣

እርቃኔን የሸፈነው፣

የኔን ከለሜዳ የለበሰው፣

ክብሩን ለኔ ያወረሰው፣

ሞት ሸማዬን የገሰሰው፣

እኔ ማነኝ? ብዬ ስለው፣

አበባህ ረግፎ የማትቀረው፣

አንተ የኔ ነህ፣ ሲለኝ ሰማሁ፣

እኔም ያንተ፣ ቃሌን ሰጠሁ፣

ዛሬም አለሁ፣ ነገም አለሁ፣

አበባዬ አይረግፍም፣ ዛሬም አብባለሁ፣

ነገም በሰማይ አብቤ፣ አብሬው እኖራለሁ።

                                አንተስ ወንድሜ ማነህ? ያለኸው የትነው?፣

                                  የወደቅኸው፣ ከወዴት ነው?፣

                                  ስታበዛ ሩጫ፣ ልብስ ስትሻ፣

                                 የትም የለ፣ ማካካሻ፣

                                     የዚህ ዓለም ማረሳሻ፣

                                ይልቅ ና አበባ ሰው፣

                                መርገፍ ገላ፣ ከሚፈርሰው፣

                               አዲስ አርጎ፣ የሚያድሰው፣

                                 ክርስቶስን ልበሰው!!!!
«ለእውነትም በሚሆኑ ጽድቅና ቅድስና እንደ እግዚአብሔር ምሳሌ የተፈጠረውን አዲሱን ሰው ልበሱ» ኤፌ 4፣24



Thursday, January 5, 2012

የአባታችሁን ምኞት ልታደርጉ ትወዳላችሁ!



ደጀሰላምና አንድ አድርገን የተባሉ ብሎጎችን እንጠይቃለን
 

                              ወንጌል ደግሞ«የአባታችሁን ምኞት ልታደርጉ ትወዳላችሁ» ይላችኋል።ዮሐ ፰፣፵፬

(by dejebirhan)ይህንን ቃል የተናገረው የዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ለፈሪሳውያን ካህናት ነበር። ጌታ የመጣው የታሰሩትን እንዲፈቱ፣ በሞት ጥላ ስር ያሉ ወደሕይወት እንዲመጡ ነበርና የመንግሥቱን ወንጌል በቃል እያስተማረ፣ ኃይሉንም በግብር እየገለጠ የመጣ የይቅርታና የምህረት ባለ ቤት መሆኑን አሳይቷል። ከዚህም ውስጥ አንዱ የሆነው ጉዳይ ፈሪሳውያን በዝሙት የተያዘችውን ሴት በክስ ወንበር አቁመዋት እንደሕጋቸው በድንጋይ ተወግራ የምትገደል መሆኑን ቢያውቁም ጌታችንን ሊፈትኑትና የሚከሱበትን ምክንያት ሲሹ ፈታኝ በሆነው መንፈስ እየተነዱ ዘማዊቷን ከፊቱ አቅርበው የሙሴ ሕግ ተወግራ ትገደል ይላል፣ አንተስ በሕግህ ምን ትላለህ? ብለው ሲጠይቁት «መላልሰው በጠየቁት ጊዜ ግን ቀና ብሎ። ከእናንተ ኃጢአት የሌለበት አስቀድሞ በድንጋይ ይውገራት አላቸው» ዮሐ ፰፣፯
ኃጢአት ያልሰራ ማንም ፈሪሳዊ ካህን አልነበረምና ውልቅ ፣ውልቅ እያሉ እሱና ሴትየዋ በመቅረታቸው ፣ ከሳሾችሽ ወዴት አሉ? ሲላት «አንድም» ብላ መለሰች፣ እሱም «ሂጂ፣ ከአሁን ጀምሮ ኃጢአት ደግመሽ አትስሪ» ብሎ በፈውስና በሰላም እንዳሰናበታት እናነባለን።
ጌታ ብርሃን በመሆኑ በጨለማ ላሉ ሊያበራ እንጂ በአንድም ስንኳ ሊፈርድ እንዳልመጣ፣ የሚፈርድበት በልጁ ባላመኑ ሁሉ ላይ አብ መሆኑን፣ ኢየሱስ ቢፈርድም እንኳን ፍርዱ እውነት እንጂ በዘማዊቷ ላይ ህግ ጠቅሰው ለመፍረድ እንደሚሹ ፈሪሳውያን እንዳይደለ፣ ለራሱ የሚመሰክር አባቱ መሆኑንና ራሱም ቢመሰክር ምስክሩ እውነት መሆኑን የሚገልጸው የወንጌል ቃል በሰፊው ተጽፎልን እናገኛለን።
ስለራስህ ራስህ እንዴት ትመሰክራለህ? እውነት አርነት ያወጣኋችል እንዴት ትለናለህ? አንተ አባቴ ብትል እኛስ አብርሃምን የሚያክል አባት አለን ብለው ሲሞግቱ በየዘመናቱ እንደተነሱት ፈሪሳውያን በዘመናችንም በተነገረው ዘላለማዊ ቃል ትንቢት ሆኖ የሚመሳሰሉበትን አንድነት  እንረዳለን። ይኸውም፣
1/ ስለኢየሱስ የሚመሰክረው አብ ነው። ራሱ ቢመሰክርም ምስክሩ እውነት ነው። ፈሪሳውያኑ ራሳቸው ህግ ጠቃሽ፣ ራሳቸው ፈራጅ፣ ራሳቸው ፈታኝ ሆነው ከሚታዩ በስተቀር አንድም የእውነት ምስክር የሌላቸው የኃጢአት ባሪያዎች ናቸው። ዮሐ ፰፣፴፬
2/ኢየሱስ በኃጢአት ላሉ መፈታትንና በሞት ጥላ ስር ላሉ መዳንን ሊሰጥ መጥቷል። ዘማዊቷን «ሂጂ፣ ደግመሽ ኃጢአት አትስሪ »ሲላትና በነጻ ከእስራት ሲያወጣት የያኔው ፈሪሳውያንም ይሁኑ የዘመኑ፣ በጨለማ የኃጢአት ዓለም ሳሉ አንድ ዘማዊ፣ ወይም በስጋ ድካም የሚሰራውን ብዙ ብዙ ኃጢአት እየጻፉ የሚከሱ፣ በድንጋይ ወግረው ለመግደል አደባባይ የሚቆሙ ናቸው። ምክንያቱም እነሱ «እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ የአባታችሁንም ምኞት ልታደርጉ ትወዳላችሁ። እርሱ ከመጀመሪያ ነፍሰ ገዳይ ነበረ፤ እውነትም በእርሱ ስለ ሌለ በእውነት አልቆመም። ሐሰትን ሲናገር ከራሱ ይናገራል፥ ሐሰተኛ የሐሰትም አባት ነውና» ዮሐ፰፣፵፬ በማለት ማንነታቸውን ገልጿል። ይባስ ብለውም ራሳቸው የሰይጣንን ስራ እየሰሩ ሳለ በተቃራኒው የራሳቸውን ግብር ለኢየሱስ ሰጥተው «አንተ ሳምራዊ እንደሆንክና ጋኔን እንዳለብህ እናያለን» ሲሉ ሰድበውታል። በእነሱ ዘንድ ሳምራዊ የሆነ ሰው ሁሉ ጋኔን አለበት፣ ከእነሱ ውጪ የተለየ ሃሳብም ያለው ጋኔን የያዘው ነው ማለት ነው። ዛሬም የዘር ውርስ ፈሪሳዊነትን የተረከቡት የሚጠሉትን አንተ ርኩስ ሳምራዊ ብለው ጎራ ይለዩበታል፣ ያለ የሌለ ኃይላቸውን ይዘው ይዘምቱበታል።
ከዚህ በላይ ያየነው የእግዚአብሔር ምርጦች ነን፣ የአብርሃም ልጆች ነን፣ የሙሴን ሕግ የምንጠብቅ ጥንቁቆች ነን እያሉ ነገር ግን እገሌ ተሃድሶ፣ እገሌ ሳምራዊ፣ እገሌ ሰዱቃዊ፣ እገሌ ደግሞ ኦርቶዶክሳዊ ነው በማለት እራሳቸው መርምረው፣ እራሳቸው መጽሐፍ ገልጠው፣ እራሳቸው በፍርድ ወንበር ተቀምጠው ከፈረዱ በኋላ አንደኛውን ወገን በድንጋይ ወግረው ለመግደል፣ የራሳችን የሚሉትን ወገን ደግሞ ከፍ ከፍ ሲያደርጉ ይታያሉ።
ያዕቆብ ፬፣፲፬«ሕግን የሚሰጥና የሚፈርድ አንድ ነው፤ እርሱም ሊያድን ሊያጠፋም የሚችል ነው፤ በሌላው ግን የምትፈርድ አንተ ማን ነህ? »የሚለው ቃል እነርሱ ዘንድ አይሰራም።
ዛሬም በዚህ ዘመን ክርስቶስ የሞተለትን አንድ ደካማ ወይም ኃጢአት ያሸነፈውን ወይም እነሱ ላቆሙት ህግ አልገዛም ያለውን ሰው ክስ መስርተውበት በሕጋቸው ወግረው ለመግደል፣ ራሳቸው ለኃጢአት ባሪያ ሆነው ሳሉ፣ ሌላውን ጋኔን አለብህ የሚሉ፣ የአብርሃምን ስራ ሳይሰሩ አብርሃም አባት አለን የሚሉ፣ የአባታቸውን የዲያብሎስን ስራ እየፈጸሙ በክስ አደባባይ የሚያቆሙ፣ ስም የሚያጠፉ፣ የሚደበድቡ፣ የሚወነጅሉ፣ የሀሰት አባት ልጆች መሆናቸውን የሚመሰክሩ ፈሪሳውያን በዚህ ዘመንም ሞልተዋል። ከእነዚህም ውስጥ ግንባር ቀደሞቹ ማኅበረ ቅዱሳን፣ እንደዚሁም ዓይንና ጆሮ ሆነውለት የሚሰሩ ደጀሰላምና አንድ አድርገን የተባሉ በስም ስለሰላምና አንድ መሆን የሚመስሉ፣ በግብር ግን ሰላምና አንድነት እንዳይመጣ ሌሊትና ቀን የሚደክሙት ተጠቃሾች ናቸው። ይህም በማስረጃ ይረጋገጣል።ውድ አንባቢያን አስተዋይ ልቦና ኖሮን እንደእግዚአብሔር ቃል እውነቱን በማወቅ ለወንጌሉ ምስክር ልንሆን እንደሚገባን በአጽንዖት አሳስባለሁ!!
ከታች ያለውን አስረጂዎች ይመልከቱ።

Thursday, December 29, 2011

እውነትም ፍቅር ትቀዘቅዛለች!


ሩቅ ሳንሄድ ኢትዮጵያ ውስጥ እስላሙ በክርስትያኑ ላይ «የአላሁአክባር» ዘመቻውን በደንብ እያስፋፋው ስለመገኘቱ ከታች ባለው ርእስ የተመለከተው የቪዲዮ ምስል ማሳያ ነው። እራሱ ክርስቲያን ነኝ የሚለው ኦርቶዶክሱ እርስ በእርሱ እየተባላ፣ እየተካሰሰ፣ የአሸናፊነት ከበሮ ለመደለቅ በአንድ ወገን ሲኖዶሱ እርስ በእርስ፣ በሌላ ወገን ማኅበረ ቅዱሳንና ደጋፊዎቹ በእነ በጋሻው ላይ የተያዘ የሞት ሽረት ትንቅንቅ፣ በእስልምናው በራሱ የሱኒና የሐነፊ ሽኩቻ በመጨረሻው ዘመን የተነገረው ትንቢት እየደረሰ ይሆን? ያስብላል። «ሕዝብ በሕዝብ ላይ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣልና፥ ራብም ቸነፈርም የምድርም መናወጥ በልዩ ልዩ ስፍራ ይሆናል» ማቴ 24፣7ከሁሉ የሚገርመውና ትንቢቱን በትክክል የሚያረጋግጥልን ነገር ክርስቶስ በተወለደበት ቤተልሔም መቅደስ የፈረንጆቹ ገና በሁለት ወገን ጦርነት ደምቆ መዋሉ ነው። ኳኳታና የሰው ግንባር ፍንዳታ በተሰማበት አዲስ ዜማ በቤተክርስቲያኑ ውስጥ ክርስቲያን ቀርቶ አረሚ የማያደርገውን ፈጽመው አክብረው ዋሉ። እውነትም «ከዓመፃም ብዛት የተነሣ የብዙ ሰዎች ፍቅር ትቀዘቅዛለች» ማቴ24፣12 ያለው ደርሷል። ግሪኮችና አርመኖች ተፈጣፈጡ!!



Wednesday, December 28, 2011

የኢየሱስ ክርስቶስ አስታራቂነትና አምላክነት

«ክርስቶስ ማለት በቁሙ ወደአማርኛ የተገለበጠው የግሪኩ(ጽርእ)ቃል «Χριστός»«ክሪስቶሽ ሲሆን ትርጉሙም «የተቀባ» ማለት ነው። መቀባት « χριστῷ» የሚለውን ብቻውን የሚያመለክተው ከሌላ መቀበልን ሲሆን «ክርስቶስ» የሚለው ቃል ግን የቅብእ ባለቤትነትንና የመቀባት ግብርን አያይዞ የሚጠራ ስም ነው። (ኢሳ 45፣1) ይመልከቱ። «ክርስቶስ» በእብራይስጡ «המשיח» ሀመሺያኽ ቅቡእ፣ የተቀባ ሲሆን ግእዙ «መሲህ» በሚለው ይተካዋል። የቤተክርስቲያን ሊቃውንትም «የክርስቶስን መቀባት ወይም ቅቡእ መሆን ለማመልከት ሲያስተምሩ «አብ ቀባኢ፣ ወልድ ተቀባኢ፣ መንፈስ ቅዱስ ቅብእ» በማለት ይገልጻሉ። በእርግጥ ይህ ትምሕርተ መለኰት ሰፊና ጥልቅ እንደመሆኑ መጠን በዚህ ዙሪያ የተነሱ ትምህርቶችና ክርክሮች ብዙ ሲያምሱ ቆይቷል፣ ዛሬም ቢሆን ጨርሶ የጠፋ ስለመሆኑ የሚታወቅ ነገር የለም። እኛም ያንን ላለመድገም እንደመንደርደሪያ ይህንን ያህል ካልን ወደተነሳንለት ዓላማ እናምራ!
«ክርስቶስ» የተቀባ ማለት ነው ብለናል። እንደዚሁ ሁሉ «ኢየሱስ» የሚለውን ስንመለከት የእብራይስጡ «ישוע» የሹአ ሲሆን ትርጉሙም «መድኃኒት» ማለት ነው። ግሪኩም «Ιησούς» መድኃኒት፣( ማዳን)፣ አዳኝ የሚለውን ትርጉም ይሰጣል። ከዚህ የተነሳ «ኢየሱስ ክርስቶስ» ማለት «የተቀባ፣ቅቡእ እና መድኃኒት፣ አዳኝ» የሆነ ማለት ነው። ይህንን የስም ትርጉም ካገኘን ለሚቀጥሉት ሃሳቦቻችን መረዳት መጠነኛ ግንዛቤ ጨብጠናል ማለት ነው።
የሚቀባው ማነው? የሚቀባውስ ለምንድነው?
እነዚህን ነገሮች አጥርቶ ማወቅ የብሉይ ኪዳን አስተምህሮዎችን መመርመር ግድ ይላል። ያንንም ማድረግ አስፈላጊ የሚሆነው «ስለመሲሁ» ክርስቶስነት ላይ በሚነሱ ልዩ ልዩ አመለካከቶች ከብዥታ የወጣ እይታ እንዲኖረን ይረዳናል።
ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ........>>>(እዚህ ላይ ይጫኑ

Thursday, December 22, 2011

መጋቤ ሀዲስ በጋሻው ደሳለኝ የአራዳውን ምድብ ችሎት በመሳጭ ስብከቱ አስደመመ


ጽሁፉን በፒዲኤፍ ማንበብ ከፈለጉ ........>>>To read in PDF click here


ታህሣሥ 9 ቀን 2004 ዓ.ም በዋለው የአራዳው ምድብ ችሎት የዐቃቤ ሕግ አንደኛ ምሥክር ሆኖ የቀረበው መጋቤ ሀዲስ በጋሻው ደሳለኝ ችሎቱን ፍጹም ወደ ሆነ መንፈሳዊ ድባብ ለውጦ አስተምሮ መውጣቱን የዜና ምንጮቻችን አረጋገጠዋል፡፡ ዘመድኩን በቀለ በግሉ አርማጌዶን ቁጥር አንድ እና ቁጥር ሁለት ሲዲና ቪሲዲ በማሠራጨት እና የተሳሳተ መልዕክት በማስተላለፍ ምዕመናንን በማወናበዱና በወንድሞች ላይ የስም ማጥፋት ዘመቻ በመክፈቱ በአራዳው ምድብ ችሎት ላይ ክስ የተመሠረተበት ሲሆን እርሱ ራሱ የ"ማኅበረ ቅዱሳን" አባል የሆነ ጠበቃ አቁሞ ለመከላከል ሞክሯል፡፡ በዚሁ ዕለት ከቀኑ 8፡00 ሰዓት እስከ 10፡25 በቆየው የክርክር ሂደት የዘመድኩን ጠበቃ የተልፈሰፈሰ መስቀለኛ ጥያቄ ለማቅረብ ሞክሮ በታዳሚው ሲሳቅበት እንደዋለ እነዚሁ ምንጮቻችን አስታውቀዋል፡፡

ጠበቃው ባቀረበው መስቀለኛ ጥያቄ ቤተክርስቲያንን "አሮጊቷ ሣራ" ብለህ ተሳድበሃል፤ ታዲያ ቤተክርስቲያንን በምንፍቅና ጥለው ከሄዱት ከእነ አባ ዮናስ በምን ትለያለህ? ብሎ የጠየቀው ሲሆን፣ መጋቤ ሀዲስ በጋሻው በሰጠው ምላሽ፣ እናታችን ሣራ በዕድሜ ብታረጅም፣ እግዚአብሔር አከበራት፤ ልጆችን ሰጣት፡፡ እኔም፣ ጥንታዊት ቤተክርስቲያናችን በአሁኑ ሰዓት በማገልገል ላይ ያሉትን ወንድሞችና እህቶች አገልጋዮችን አፍርታለች ነው ያልኩት፡፡ የእኛ ሣራ ልጆችን ወልዳለች፤ የእነ አባ ዮናስ ሣራ ግን ስለመወለዷ አይታወቅም፤ በዚህ እንለያለን በማለት መመለሱ ታውቋል፡፡

መጋቤ ሀዲስ በመቀጠል የቀረበለት ጥያቄ፣ ራስህን በራስህ ሰባኪ አድርገሃል፤ የቤተክርስቲያን ትምህርት ሳይኖርህ ታስተምራለህ፤ ለመሆኑ ዲቁናውን ማን ሰጠህ? መጋቤ ሀዲስ የሚለውንስ ማዕረግ ከወዴት አገኘኸው? የሚል ነበር፡፡ እርሱም በበኩሉ ሲመልስ፣ ዲቁናውን የተቀበልኩት ከብፁዕ አቡነ በርተለሜዎስ የቀድሞው የሲዳማ፣ ጌዴኦ፣ አማሮና ቡርጂ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ነው፡፡ የስብከት መምህርነት ኮርስም ተከታትዬ የተሰጠኝ የምሥክር ወረቀት አለኝ፡፡ የመጋቤ ሀዲስነት ማዕረጉንም ሰባ ሺህ ያህል ሕዝብ ባለበት የሰጡኝ ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል በዚያን ወቅት የሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ ናቸው፡፡

መምህር በጋሻው ሌላው የቀረበለት ጥያቄ የእኛ ጌታ ተኝቶ ይገዛል ብለሃል፡፡ ይህ አባባልህ ልክ ነው? የሚል ነበር፡፡ እርሱም ሲመልስ ታዲያ ይሄ ምን ስሕተት አለው? ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከደቀመዛሙርቱ ጋር በጀልባ ሲጓዝ፣ ተኝቶ ነበርና ማዕበሉ በተነሳ ጊዜ ሲቀሰቅሱት፣ እምነት የጎደላችሁ ስለምንድርነው አላላቸውም? በከርሰ መቃብር ሦስት መዓልትና ሦስት ሌሊት ባደረበት ወቅት ዓለምን አልገዛም? ጌታችን፣ አምላካችን በሰው አስተሳሰብ የተኛ ፣ የሞተ ቢመስልም እርሱ ግን ሁሉንም በኃይሉ ይጠብቅ ነበር፤ በማለት መልሷል፡፡ መጋቤ ሀዲስ በጋሻው ሌሎችንም ተጨማሪ ማብራሪያዎችን የሰጠ ሲሆን፣ እርሱ ጥያቄዎችን በሚመልስበት ወቅት ሁሉም ከመመሰጡ የተነሳ የችሎቱ ሂደት ስብከተ ወንጌል አዳራሽ እስከሚመስል ደርሶ እንደነበር በስፍራው የነበሩ እማኞች ገልጸዋል፡፡

Wednesday, December 14, 2011

ማደናገር ይቁም! የሰንበት ት/ቤቶች ማ/መ ድረገጽ


«ADOBE OF GOD»በሚል ርእስ የክርስቶስ ኢየሱስን የማዳን ስራ የሚያጥላላና ፍጹም ክህደት የተሞላበት ፊልም ኢትዮጵያ ውስጥ ሊሰራ እንደነበር በባለፈው ወር የወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ። በእርግጥም ከ75% በላይ ሕዝብ ክርስትናን በአንድም በሌላ ምክንያት ተቀብሎ የሚኖርና በአብዛኛውም ይህንኑ የእለት ከእለቱ መመሪያ አድርጎ በሚቀበል ሀገር ላይ ይህንን መሰሉን ፊልም መስራት መርገም ካልሆነ በረከት ያመጣል፣ ተብሎ አይታሰብም። ክርስቶስን ለማዋረድ መፈለግ ከክርስቶስ ማንነት ላይ አንዳች የሚያጎለው ነገር ባይኖርም
«የማያምኑ ቢኖሩ አለማመናቸው የእግዚአብሔርን ታማኝነት ያስቀራልን?» ሮሜ 3፣3 እንዳለው ክርስቶስ ዛሬም፣ ነገም ያው እሱ መሆኑ ሳይጎድል አምልኰና ክብር በሚገባው ቦታ ተሳልቆና ክህደት ሲተካ ግን የረድዔትና የበረከት እጁን ላለመቀበል በፈለግነው ልክ የዚህ ዓለም ገዢን ማስተናገድ በመሆኑ ሊያስደነግጠን እንደሚገባ ለአፍታ መዘናጋት የለብንም። ይህንን ድርጊት ለምእመናንና ምእመናት በማዳረስ በመረጃው ላይ የወል ግንዛቤ ወስዶ አቋማችንን ለሚመለከተው ለማድረስ ሚዲያዎች ሰፊ ዘገባቸውን ሰጥተው ሰርተዋል። ይህ ሊመሰገን የሚገባው መንፈሳዊ ተግባር ነው። ይሁን እንጂ አንዳንዶች ራሳቸውን የዚህ ጥረትና ትግል ዋነኛ አካል አድርገው የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ማእከላዊ ጽ/ቤት ግን «ፊልሙ እንዲሰራ ፈቅዷል» በማለት ድካምና ጥረቱን ውሃ በመቸለስ ከችግሩ ጎን ለጎን የችግሩ ዋነኛ ምህዋር እንደነበር ለማሳየት መሞከራቸው አስገራሚ ሆኗል። ከነዚህም መካከል የማኅበረ ቅዱሳኑ ሌላኛው እጅ የ«ደጀሰላም» ድረገጽ ከለጠፈው በኋላ ቤተክህነቱን የወነጀለበትን ጽሁፍ ያውርድ እንጂ ወንድሙ የሆነው «አንድ አድርገን» ለማንበብ ይህን ይጫኑ
እስካሁን ያስነብበናል። «ማኅበረ ቅዱሳን የቤተክህነት እዳ» በተሰኘው መጽሐፍ እንደተጠቆመው «እንቁ» መጽሔት የማኅበረ ቅዱሳን የእጅ አዙር መጽሔት መሆኑን ለመረዳት ብንችል ሁሉም በአንዴ ተቀባብለው ቤተክህነቱን ያለስራው ስም ሰጥተው «ADOBE OF GOD» ለተሰኘው የክህደት ፊልም ትብብሩን ሰጥቷል ሲሉ መጻፋቸው ካንድ ወንዝ መቀዳታቸውን እንደሚነግሩን እንገነዘባለን። የቤተክህነቱ ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ነገሩ እጅግ ቢያስመርረው በድረገጹ ለተባለው ፊልም ከታቃውሞ ውጪ ድጋፍ አለመስጠቱን አስነብቦናል።
ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ

Friday, December 9, 2011

የጳጳሳት ጆሮ የተነፈገው የአዲስ አበባ ካህናት ጩኸት!


የጳጳሳት ጆሮ የተነፈገው የካህናት ጩኸት(to read in PDF click here)

ከደጀብርሃን፣

የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የገንዘብና የንብረት ዘረፋ ሀገር ያወቀው፣ፀሐይ የሞቀው ጉዳይ ነው። ኰሌጅ፣ ሙአለ ህጻናት፣ አውቶቡስ፣ ታክሲ፣ ሆቴል፣የተለያየ ደረጃ ያላቸው ህንጻዎች፣ ሱቆች፣ የሚከራዩ አፓርትማዎች፣ የቤትና የንግድ መኪናዎች ያላቸውን አስተዳዳሪዎች፣ ፀሐፊዎች፣ ሂሳብ ሹሞች፣ የቁጥጥር ሠራተኞች፣ገንዘብ ያዢዎችና ንብረት ክፍሎችን ማየት እንግዳ ነገር አይደለም። ይህንን ሁሉ ሀብት ሲያጋብሱ የቀድሞ ደመወዛቸው ቢበዛ የአስተዳዳሪው ከአንድ ሺህ አምስት መቶ ብር የሚበልጥ አልነበረም። የሌሎቹ ደግሞ ሺህ ብር ባልገባ ደመወዝ ነበር ይህንን ሁሉ ሃብት ማፍራት የቻሉት። የዘረፋ ቁንጮ እንደሆነ የሚነገርለትና አውቶቡስ፣ ት/ቤት፣ ትልቅ ህንጻ እንዳለው የሚነገርለት (ሊቀ ሊቃውንት)አባ እዝራ የሚባለው የሽማግሌ ማፊያ ለዚህ የሚጠቀስ አብነት ነው። ሊቀሊቃውንት ብላ ቤተክርስቲያን የምትጠራው ጡቷን ምጎ፣ ምጎ አጥንቷን ስላወጣው እውቀቱ ይሆን? ይህንን እንግዲህ እውቅና የሰጠው ሲኖዶስ የሚባለው የአባቶቹ ማኅበር ያውቃል። ሌሎቹንም የዘረፋ ሊቀ ሊቃውንት በስምና በአድራሻ ማንሳት ይቻላል። የሚያሳዝነው ግን ንቡረ እድ አባ ገ/ማርያም ገ/ሥላሴን ከአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ሥራ አስኪያጅነት ለማስነሳት የዘመቻው ፊት አውራሪዎች እነዚህ የቤተክርስቲያንን ሀብት እያገላበጡ የሚዘርፉ የቀን ጅቦች መሆናቸው ነው። ከማሳዘን አልፎ የሚገርመው ንቡረ እድ አባ ገ/ማርያም የቀን ጅቦቹን አፍ የዘጉት በየትኛውም የቤተክርስቲያን ገንዘብና የንብረት ቆጠራ ላይ አስተዳዳሪው፣ ፀሐፊውና ሂሳብ ሹሙ እጃቸውን ሳያስገቡ ቁጭ ብለው እንዲመለከቱና አገልጋይ ካህናቱ ብቻ በአንድነት ቆጥረው የተገኘውን ገንዘብ በሞዴል 64፣ የገባውን ንብረት በሞዴል 19 ገቢ አድርገው በግልጽ መጠበቅና ማስጠበቅ መቻላቸውን ሲኖዶስ የሚባለው ስብስብ እያወቀ ወይም ማወቅ ሲገባው ለዘራፊዎቹ ጩኸት ምላሽ በመስጠት ባለፈው ጉባዔ ሥራ አስኪያጁን ከቦታው እንዲነሱ አድርጓል።
ከ5 ሚሊዮን ያላለፈውን ለጳጳሳት ደመወዝና ሥራ ማስኬጃ ፈሰስ የሚደረገውን የጠቅላይ ቤተክህነት ገቢ ወደ 27 ሚሊዮን ከፍ ስላደረጉላቸው ሽልማት መስጠቱ ይቅርና ይህንን አጠናክረህ ቀጥል ማለት አቅቷቸው እንደጥፋተኛ ሰው የልማቱን አባት ለቦታው አትሆንም ብሎ ማንሳት ሲኖዶስ በእውነት በመንፈስ ቅዱስ የሚመራ ነው? የሚያስብል ነገር ነው። የአባ ገ/ማርያምን መነሳት የሚሹ ወገኖች(ፓትርያርኩን ጨምሮ) የዝውውር ጥያቄ ውድቅ ሊያስደርግ የሚችል ተግባር ለማየት ሲኖዶስ የሚባለው ክፍል በመንፈሳዊነት ደረጃ ይቅርና በመስማትና በማሽተት እንዴት ሳይረዳው ቀረ? ይልቁንም ጊዜውን በአባ ሠረቀ ጉዳይ ላይ የማኅበረ ቅዱሳንን ውክልና በማስፈጸም መጠመዱን ስራዬ ብሎ ዋለ እንጂ!! እውነትም የመንፈስ ቅዱስ ጉባዔ!!!!!!!
ከታች የቀረበው በሰዓታቱ፣በማኅሌቱ፣በቅዳሴው፣በፍትሃቱ ሌሊትና ቀን እየጮሁ ቤተሰቦቻቸውን የሚያስተዳድሩ ካህናት ጩኸትና ትዳር አንፈልግም፣ እኛ መንኩሰናል፣ እያሉ ግን ብዙውን ጊዜያቸውን ሽቶ የተለወሰ ቀሚሳቸውን አስረዝመው፣ ወለተማርያም፣ወልደ ማርያም እያሉ የመበለት ቤቶችን የሚበዘብዙ አስተዳዳሪዎች መካከል የተደረገው የአቤቱታ ክርክርና ከላይ እስከታች ረዳት የሌለውን ካህን ድምጽ የሚያሳይ ነውና መልካም ንባብ ይሁንልዎ!! ኅሊናዎትም ፍርዱን ይስጥ!!ከታች ያለውን ተጭነው ያንብቡ!(http://dejebirhan.blogspot.com)

Thursday, December 8, 2011

መጽሐፈ ሰዓታት ምን ይላል?

                               መጽሐፈ ሰዓታት.............to read in PDF click here





«ሰዓሊ ለነ ሰንበተ ክርስቲያን ቅድስት፣
ለውሉደ ሰብእ መድኃኒት፣
ወእስከ ለዓለም ሰፋኒት» ትርጉም--ለሰው ልጆች መድኃኒትና እስከዘለዓለም ገዢ የሆንሽ፣ የክርስቲያን ሰንበት ሆይ ለምኝልን ማለት ነው።
ሰንበተ ክርስቲያን የተባለችው ዕለት ለሰው ልጆች መድኃኒት በመሆኗ እንዲሁም እስከዓለም ፍጻሜ የሰው ልጆች ገዢ ስለሆነች እንድታማልደን እንጠይቃት ማለቱን መጽሐፈ ሰዓታት ይጠቁመናል።
እዚህ ላይ ጥቂት ጥያቄዎችን እናንሳ።
1/ሰንበተ ክርስቲያን የምትባለው ምናልባትም ዕለተ እሁድ ናት። ሐዲስ ኪዳን ግእዙ «ወበእሁድ ሰንበት መጽአት ማርያም መግደላዊት ኀበ መቃብር»ዮሐ20፣1 «ማርያም መግደላዊት ወደመቃብር በሳምንቱ መጀመሪያ ቀን መጣች»ይላል። ምንም እንኳን የእብራይስጡም ሆነ የጽርዑ መጽሐፍ ቅዱስ እሁድ ሰንበት የሚል ቃል ባይዝም እሁድ ብለው ያስቀመጡትን የግእዝ ተርጓሚዎች ተከትለን ብንሄድ እሁድ የተባለችው ቀን---
ሀ/እንዴት ሆና ነው የሰው ሁሉ ገዢ የምትሆነው?
ለ/ እሁድ በምን አፏ ነው የምልጃ ቃልን የምታሰማው?
ሐ/ እሷስ ከማነው የምታማልደን?
ሐ/ከሳምንቱ እለታት የተለየች ናት ካልን የጌታ እለታት ያልሆኑት የትኞቹ ናቸው?
መ/ድርሳነ ሰንበት የተሰኘው መጽሐፍ «ሰንበት» ማለት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ይለናል። ታዲያ ሰንበት የተባለው መድኃኔዓለም ያማልደናል ማለታቸው ነው?
2/ አስታራቂና አማላጅ የሆነችው እለተ ሰንበት ስለመሆኗ የተቀመጠ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ ምንድነው?
ሐዋርያው ጳውሎስ ለገላትያ ሰዎች ወንጌልን ከሰበከላቸው በኋላ ወደቀደመው ከንቱ የሆነ አምልኰ ሲመለሱ ተመልክቶ እንዲህ ብሎ ነበር።
«ነገር ግን በዚያን ጊዜ እግዚአብሔርን ሳታውቁ በባሕርያቸው አማልክት ለማይሆኑ ባሪያዎች ሆናችሁ ተገዛችሁ» ገላ 4፣8
እንደዚሁ ሁሉ እለተ እሁድ እግዚአብሔር ከቀናት እንደአንዱ የሰራት መሆኗ ተረስቶ ልክ አማልክት ወደመሆን የተቀየረች ይመስል አስታርቂን፣አማልጂን ማለት ጳውሎስ በባህሪያቸው አማልክት ለማይሆኑ ባሪያዎች ሆናችሁ የተገዛችሁ ነበረ ያለውን ቃል እኛ ዛሬም እየፈጸምን መገኘታንን ያሳያል።

Wednesday, December 7, 2011

የጴንጤ መዝሙር ያዳመጠስ?

የበጋሻው ግጥም ስህተት የለውም!
በጋሻው ደሳለኝን በተመለከተ አንዴ ጻድቅ ነው፣ አንዴ ደግሞ ኀጥእ ነው እንደሚለው ማኅበረ ቅዱሳንና ልሳኖቹ በሆኑት ደጀሰላም፣ አንድ አድርገን  በመሳሰሉት እንደሚናገሩት ኀጥኡን ለመኮነን ወይም ጻድቁን ለማጽደቅ የኛ ድርሻ ስላልሆነ እንዲሁም  ቃለእግዚአብሔር አይፈቅድልንምና በዚህ ዙሪያ የምንለው ነገር አይኖርም።
ሁለተኛው ደጀሰላም የሆነው «አንድ አድርገን» የበጋሻውን ከሀዲነት የሚገልጽ የግጥምና የመዝሙር ቅንብር በማቅረብ ለማጋለጥ ሞክሯል። እስኪ በዚያ ላይ ተንተርሰን ጥቂት ሃሳብ እንስጥ። ለፍርድ ያመች ዘንድ ግጥሙን ለማሳያነት በጥቂቱ ኮፒ አድርገነዋል።

የፕሮቴስታት                                                                  የኦርቶዶክስ
ካልባረከኝ አለቅህም ካልባረከኝ አለቅህም-                      ካልባረከኝ አለቅህም ካልባረከኝ አለቅህም
 አምላኬ ነህ ለዘላለም                                                 -አምላኬ ነህ ለዘላለም
ጌታዬ ነህ ለዘላለም                                                       ጌታዬ ነህ ለዘላለም
ለብቻዬ ልኖር ፈቃድህ ከሆነ                                           ሊነጋ ሲጀምር ሰማዮ ሲቀላ
ሌላው አይገደኝም ህይወቴ ከዳነ                                      ወዴት እሔዳለው ነፍሴ እንዲህ ዝላ
ሲሆን እስከ ንጋት ልታገልህና                                           እያለቀስሁ ሁሉ እከተልሀለሁ
ስደደኝ ጌታዬ ሆይ ሕይወቴን ባርክና                                   እጅህን ዘርጋልኝ በረከት እሻለሁ
በመንበርከክ ብዛት በጸሎት ትግል                                        ለብቻዬ ልኖር ፈቃድህ ከሆነ
ፈቃድህ ከሆነ ጉልበቴ ይዛል                                               ሌላውን አልሻም ሕይወቴ ከዳነ
እያለቀስኩ ሁሉ እከተልሀለሁ                                           ሲሆን እስከ ንጋትታግለሃልና ል                                                                              
እጅህን ዘርጋልኝ በረከት እሻለሁ                                       ስደደኝ ጌታዬ ሕይወቴን ባርክና

የግጥሙን መመሳሰል ወደኋላ ላይ እናቆየውና የሚታየውን እውነት ኢአመክንዮያዊ (fallacy)በመስጠት በጋሻውን ከሃዲ ለማድረግ የተሞከረበትን ስነ ሞገት እንመርምር።

Monday, December 5, 2011

ይከራከሩኛል!


                 ይከራከሩኛል
ይከራከሩኛል፣ እየተጋገዙ
በከንቱ ላይረቱኝ፣ አምላክን ሳይዙ።
እንዳገሩ ልማድ- ለተማረ ዳኛ፣
ቅጣት ይገዋል-ይህ ደፋር አፈኛ፣
ብሎ ፈረደብኝ- የወንጌል ምቀኛ።
ክርስቲያን የሆነ-ሲኖር በዓለም፣
መመርመር ነው እንጂ- ክፉና መልካም።
እውነት እስኪገለጽ አጥብቆ መድከም፣
እንዲሁ ቢያከፉት- የወንድምን ስም፣
እጅጉን ነውር ነው-ጌታ አይወደውም።
ማርያምን ጻድቃንን-አይወድም ያሉት፣
በምቀኝነት ነው- ስሜን ለማክፋት።
በክስ ቢጠይቁኝ- ስለሃይማኖት፣

Wednesday, November 30, 2011

ሰዶምና ገሞራ ወደኢትዮጵያ?


ማናቸውም ሰው ከሴት ጋር እንደሚተኛ ከወንድ ጋር ቢተኛ ሁለቱ ጸያፍ ነገር አድርገዋል ፈጽመው ይገደሉ ደማቸው በላያቸው ነው» ዘሌ 20፣13
በኢትዮጵያ የአራቱም ሃይማኖቶች መሪዎች በአዲስ አበባ በቅርቡ በሚካሄደው 16ኛው የአይካሳ ጉባዔን አስታክኮ በአገሪቱ ጸያፍ፣ ከሥነ ምግባር ውጭና ባህልን የሚያንቋሽሽ አጀንዳ ለማስፈጸም ተነሣሥቷል ያሉትን የአንድ ቡድን እንቅስቃሴን በመቃወም ትናንት ሊሰጡት የነበረው ጋዜጣዊ መግለጫ ላልተወሰነ ጊዜ ተላለፈ፡፡
የሪፖርተር ፎቶግራፍ ጋዜጠኛ መሪዎቹ መግለጫ ለመስጠት እንደተዘጋጁ ያነሳውም ፎቶግራፎች እንዲጠፉ ተደረገ፡፡

መሪዎቹን በመወከል መግለጫው ለሌላ ጊዜ መተላለፉን ያስታወቁት ከኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ቄስ ኢተፋ ጎበና ሲሆኑ፣ የጋዜጠኛው ፎቶ ግራፎች እንዲጠፉ ያደረገውም በሥፍራው የነበረ አንድ የደኅንነት አባል ነው፡፡

መግለጫው የሚሰጥበት ትክክለኛው ቀን መቼ ነው ተብሎ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ ‹‹ከጉባዔው በፊትም ሆነ በኋላ ሊሆን ይቻላል፡፡ ከዚህ ውጭ ትክክለኛው ቀን ይህ ነው ብዬ ለመናገር ያስቸግረኛል፤›› ሲሉ ቄስ ኢተፋ መልሰዋል፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት፣ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን፣ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ መሪዎች በተወካያቸው አማካይነት መግለጫው ላልተወሰነ ጊዜ መተላለፉን ያስታወቁት፣ የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ ዶክተር ቴዎድሮስ አጽሃኖም በተገኙበት የዝግ ስብሰባ አድርገው በጉዳዩ ላይ ለአንድ ሰዓት ያህል ከተወያዩ በኋላ ነው፡፡

ጉልበተኛው ረባሽ!!




ቦረና ሀገረ ስብከት በክብረ መንግሥት ከተማ በጽርሐ አርያም ቅዱስ ሚካኤል አጥቢያ ቤተክርስቲያን እስከ ህዳር 19 ቀን 2004 ዓ.ም ላለው ጊዜ የተዘረጋው የእግዚአብሔር መንግሥት ወንጌል ጉባዔ መቋረጡን በዚያው ያሉ ምንጮቻችን አረጋግጠዋል፡፡ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በተደጋጋሚ እንደሚደረገው የ"ማኅበረ ቅዱሳን" ቡችሎች በለኮሱት ሁከት ጉባዔው መቋረጡ ታውቋል፡፡ በተለይም የግጭቱ አስተባባሪ በመሆን ቀዳሚውን ድርሻ የወሰደው ያሬድ ውብሸት የተባለ የማኅበሩ አባል ሲሆን፣ ይኸው ግለሰብ ለማኅበሩ መረጃ በማቀበልና በመሰለል ወንድሞችን ለአደጋ የሚጥል መሆኑ ጭምር ተገልጿል፡፡ በዚሁ ጉባዔ ላይ፣ ለጊዜው ስሙና ማንነቱ ካልተገለጸ ሌላ ግለሰብ ጋር በመሆን ጠቡን እንዳስነሱት የታወቀ ሲሆን፣ ይኸው ግብረ አበር ሰዎችን ከደበደበ በኋላ ጌታዋን እንደተማመነች በግ ከተማዋ ውስጥ በነፃነት ሲንሸራሸር፣ የወንጌል መምህር የሆኑትን ቀሲስ ተስፋዬ መቆያን ለእሥራት እንዳበቋቸው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡

የክብረ መንግሥት ጽርሐ አርያም ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን፣ ቀሲስ ተስፋዬ መቆያ ከፊደል ቆጠራ እስከ ዲቁና ከዚያም እስከ ቅስና ያገለገሉባት፣ ጥርስ ነቅለው ያደጉባት እናት ቤተክርስቲያናቸው ስትሆን፣ የከተማዋ ምዕመናን የወንጌሉ የምሥራች ቃል እንዲሰበክላቸውና በመንፈሳዊ ሕይወታቸው እንዲጎለብቱ፣ የዘማሪያንንና የሰባክያንን ወጪዎች በመሸፈን ጭምር በተደጋጋሚ የወንጌል ጉባዔ ያዘጋጁ ቅን የቤተክርስቲያን አገልጋይ መሆናቸው ተገልጿል፡፡

Sunday, November 27, 2011

ታቦት በአዲስ ኪዳን እንዴት?




ታቦት በአዲስ ኪዳን እንዴት?to read in PDF

ለዚህ ጽሑፍ መነሻ የሆነው በኢቢኤስ ቴሌቪዥን በዲያቆን ዓባይነህ ካሴ የተሰጠውና ስለጽላት የአዲስ ኪዳን ዘመን አስፈላጊነት ስብከቱ የተነሳ ነው። አባይነህ ካሴ ያልገለጻቸው፣ ያልመለሳቸውና ያላብራራቸው፣ ነገር ግን በምንም መልኩ ሊታለፉ የማይገባቸው ነጥቦች ስላሉ በዚህ ጽሁፍ ይዳሰሳሉ። ምክንያቱም ለክርስቲያኖች ከየትኛውም መረጃ በላይ የእምነታቸው መሠረት መጽሐፍ ቅዱስ ሲሆን እሱም ሳይሸፋፍን ለብሉይ ኪዳኑ ሥርዓትም ይሁን ለአዲስ ኪዳኑ ዘመን እምነት መመሪያን፣ትእዛዛቱንና መንገዶቹን በግልጽ አስቀምጦት ስለሚገኝ ነው።
ዓባይነህ ካሴ ስሜቶቹን ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር እያዛመደ በዚህ የጽላት ዓለም እምነት ላሉ፣ በዚያው እንዲጸኑ፣ ይህንን ለማይቀበሉት ደግሞ ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች መልስ በመስጠት የሁለት ወገን ስራውን ለመስራት ሞክሯል። ይሁን እንጂ መረጃውን በማብራሪያ ለማጠናከር ከመሞከር ባለፈ በተጨበጠ ማስረጃ ማስደገፍ ባለመቻሉ ግልጽ እውነቶችን እያነሳንሥነ አመክንዮ «Give reasons or cite evidence in support of an idea, action, or theory, typically with the aim of persuading others to share one's view» እንሰጥበታለን።
ታቦት ለእስራኤል ዘሥጋ ያስፈለገበት ዋናው ምክንያት
ነብዩ ሙሴ ከእግዚአብሔር ቃል እየተቀበለ ለሕዝቡ መልእክቱን ያደርስ ነበር።
ዘጸ 3፣15 እግዚአብሔርም ደግሞ ሙሴን አለው። ለእስራኤል ልጆች እንዲህ ትላለህ። የአባቶቻችሁ አምላክ፥ የአብርሃም አምላክ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ እግዚአብሔር ወደ እናንተ ላከኝ ይህ ለዘላለሙ ስሜ ነው፥ እስከ ልጅ ልጅ ድረስም መታሰቢያዬ ይህ ነው።

Saturday, November 26, 2011

ይድረስ ለቀሲስ ደጀኔ!!


«እስራኤል ዘሥጋን በመንገዳቸው ሁሉ የጠበቃቸው፥ መና ከሰማይ ያወረደላቸው፥ ተአምራትን ያደረገላቸው፥ ማርና ወተት ወደምታፈስሰው ርስታቸው የመራቸው፥ በደመና መጋረጃ የጋረዳቸው፥ በክንፎቹም የሸፈናቸው መጋቤ ብሉይ የተባለ ቅዱስ ሚካኤል ነው»በማለት በብሎግዎ ላይ ጽፈዋል። ገረመኝና አንዳንድ ጥያቄዎችና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃዎችን አቀረብኩልዎ!!
ቀሲስ ደጀኔ ሽፈራው- ይህንን ከየትኛው መጽሐፍ ላይ አገኙት? ሚካኤል ነው የሚል ተጽፏል? ወይስ ነገረ ሥራው ሚካኤልን ይመስላል ብለው ያልተገለጸውን አቅኚ ሆነው ነው? እግዚአብሔር ሚካኤል ስለመሆኑ ያልገለጸው ረስቶ ወይም ተሳስቶ እርስዎ ግን በትርጉም ፈትተውት ያገኙት እውቀት ነው?
መቼም እንደማይቀበሉኝ አውቃለሁ፣ እኔን ሳይሆን ለዚያውም መጽሐፍ ቅዱስን።
ዘፍ  21፥17
    31፥11
     48፥16
ዘጸ  3፥2
    14፥19
    33፥1-3
ዘኁ  22፥22 - 22፥23 - 22፥24 - 22፥25 - 22፥26 - 22፥27 - 22፥31   -  22፥32    22፥34   22፥35  
አንድም ቦታ ሚካኤል የሚል ስም ተጠቅሶ አይገኝም። እግዚአብሔር ስሙን ያልጠቀሰው ለምን ይመስልዎታል? እኛስ ስሙን መጥቀስ ለምን ይገባናል? የኛ መጥቀስ እግዚአብሔር ያልጠቀሰውን ጉድለት ለመሙላት ነው ወይስ ስውር  የሆነውን ሚካኤል በትርጉማችን ገልጸን በማውጣት መልአኩን ለማክበር?
ለዚያውም ስሙ ባልተገለጸ መልአክ እጅ እግዚአብሔር ያደረገውን ድንቅና ተአምራት ለሚካኤል ለመስጠት «እስራኤል ዘሥጋን በመንገዳቸው ሁሉ የጠበቃቸው፥ መና ከሰማይ ያወረደላቸው፥ ተአምራትን ያደረገላቸው፥ ማርና ወተት ወደምታፈስሰው ርስታቸው የመራቸው፥ በደመና መጋረጃ የጋረዳቸው፥ በክንፎቹም የሸፈናቸው መጋቤ ብሉይ የተባለ ቅዱስ ሚካኤል ነው» ማለት በፍጹም ትልቅ ስህተትና ክህደት ነው።
 እርስዎ እግዚአብሔር ያለውን ለምን መተው ይወዳሉ?
 ዘፍ 28፣15 «እነሆም እኔ ከአንተ ጋር ነኝ፥ በምትሄድባትም መንገድ ሁሉ እጠብቅሃለሁ፥ ወደዚችም ምድር እመልስሃለሁ የነገርሁህን ሁሉ እስካደርግልህ ድረስ አልተውህምና»
 ዘጸ 6፣6 «ስለዚህም ለእስራኤል ልጆች እንዲህ በላቸው። እኔ እግዚአብሔር ነኝ፥ ከግብፃውያንም ባርነት አወጣችኋለሁ፥ ከተገዥነታቸውም አድናችኋለሁ በተዘረጋ ክንድ በታላቅ ፍርድም እታደጋችኋለሁ»

ዘጸ 6፣7ለእኔም ሕዝብ እንድትሆኑ እቀበላችኋለሁ፥ አምላክም እሆናችኋለሁ እኔም ከግብፃውያን ባርነት ያወጣኋችሁ እግዚአብሔር አምላካችሁ እንደሆንሁ ታውቃላችሁ።

ዘጸ 6፣8 «ለአብርሃምና ለይስሐቅ ለያዕቆብም እሰጣት ዘንድ ወደ ማልሁባት ምድር አገባችኋለሁ እርስዋንም ርስት አድርጌ እሰጣችኋለሁ እኔ እግዚአብሔር ነኝ»
ዘጸ 10፣3 «ሙሴም አሮንም ወደ ፈርዖን ገቡ፥ አሉትም። የዕብራውያን አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በፊቴ ለመዋረድ እስከ መቼ እንቢ ትላለህ? ያገለግሉኝ ዘንድ ሕዝቤን ልቀቅ»
ዘጸ 13፣21 «በቀንና በሌሊትም ይሄዱ ዘንድ፥ መንገድ ሊያሳያቸው ቀን በደመና ዓምድ፥ ሊያበራላቸውም ሌሊት በእሳት ዓምድ እግዚአብሔር በፊታቸው ሄደ»
ዘጸ 14፥24
ንጋትም በሆነ ጊዜ እግዚአብሔር በእሳትና በደመና ዓምድ ሆኖ የግብፃውያንን ሠራዊት ተመለከተ፥ የግብፃውያንንም ሠራዊት አወከ። 25 የሰረገሎቹንም መንኰራኵር አሰረ፥ ወደ ጭንቅም አገባቸው ግብፃውያንም። እግዚአብሔር በግብፃውያን ላይ ይዋጋላቸዋልና ከእስራኤል ፊት እንሽሽ አሉ»
ዘጸ 15፥3 «እግዚአብሔር ተዋጊ ነው፥ ስሙም እግዚአብሔር ነው»
ዘጸ 16፥15
የእስራኤልም ልጆች ባዩት ጊዜ ያ ምን እንደ ሆነ አላወቁምና እርስ በእርሳቸው። ይህ ምንድር ነው? ተባባሉ። ሙሴም፦ ትበሉት ዘንድ እግዚአብሔር የሰጣችሁ እንጀራ ነው»
ከብዙ በጥቂቱ እስራኤል ዘሥጋን የመገባቸው፣የጠበቃቸው፣ያሻገራቸው፣ የጋረዳቸው እግዚአብሔር እንጂ እርስዎ እንዳሉት ሚካኤል የሚባል መልአክ አይደለም።  
ዘሌ20፥24 ነገር ግን እናንተን፦ ምድራቸውን ትወርሳላችሁ ትወርሱአትም ዘንድ ወተትና ማር የምታፈስሰውን ምድር እሰጣችኋለሁ አልኋችሁ። እኔ ከአሕዛብ የለየኋችሁ አምላካችሁ እግዚአብሔር ነኝ»
ዘዳ 26፣8 እግዚአብሔርም በጸናች እጅና በተዘረጋ ክንድ፥ በታላቅም ድንጋጤ፥ በተአምራትም፥ በድንቅም ከግብፅ አወጣን
ዘዳ 26፣9 ወደዚህም ስፍራ አገባን፥ ወተትና ማር የምታፈስሰውንም ይህችን ምድር ሰጠን።
ቀሲስ- እርስዎ ግን በድፍረት በእግዚአብሔር ላይ ዐምፀው ላልተገለጠና ላልተጻፈ የመልአክ ስም ሰጥተው፣ ያሻገራቸው፤ መናን የመገባቸው፣ ወተትና ማር የምታፈሰውን ሀገር ያወረሳቸው ሚካኤል ነው ይላሉ። እግዚአብሔር እኔ ነኝ እያለ እርስዎ ግን የለም ሚካኤል ነው ማለትዎ ለምን ይሆን? ላልተገለጠ መልአክ ክብሩን ከእግዚአብሔር ላይ ወስደው ሲሰጡ ለእኔ እንደተደረገ ይቆጠራል የሚል ይመስልዎት ይሆን? ላልተገለጠና ላልተጻፈ የመልአክ ስም ክብሩን ሁሉ መስጠትዎ ሳያንስ ሌሎችም ይህንኑ ስህተትዎን እንዲቀበሉና ፊታቸውን ወዳልተነገረውና እግዚአብሔር ወዳልገለጸው መልአክ እንዲመልሱ ማስተማርዎ ያሳዝናል !! በዘለበ ምላስ የሚናገሩትና የሚጽፉትን ለራስዎ እንዲመች ተርጉመው የመጽሐፍ ቅዱስን ቃል ማጣመምዎ ለምንድነው?
ምናልባት እግዚአብሔር ይቅር ቢልዎ ንስሐ ይግቡበት!! ምክንያቱም እኔ ሰራሁ ያለውን ላልተጻፈ መልአክ ሰጥተው፣ አስቀንተውታልና!!
እርስዎ እግዚአብሔር ያደረገውን ተአምራት ሁሉ ለሌላ አውለው እንዳስቀኑት ሰዎች ሆነዋል።
ዘኁ 14፣22-23 በግብፅ ምድርና በምድረ በዳ ያደረግሁትን ተአምራቴንና ክብሬን ያዩ እነዚህ ሰዎች ሁሉ አሥር ጊዜ ስለ ተፈታተኑኝ፥
 ነገሬንም ስላልሰሙ፥ በእውነት ለአባቶቻቸው የማልሁላቸውን ምድር አያዩም ከእነርሱም የናቀኝ ሰው ሁሉ አያያትም» ይላልና ያስቡበት!!!!!!

Friday, November 25, 2011

እሬት የተቀባ ጡት ማን ይጠባል?



 ሁላችንም ህጻን ልጅ ሆነን አድገን አሁን ካለንበት መድረሳችን እርግጥ ነው። ህጻናትን በተመለከተም ህጻናት ወንድሞችና እህቶችም ይኖሩን ይሆናል። ምናልባትም ህጻናት ልጆች ይኖረንም ይሆናል። ባይኖረን እንኳን ስለህጻናት ያለን እውቀት ትንሽ እንደማይሆን ተስፋ አደርጋለሁ። ስለህጻናት ማንሳት የወደድኩት «ምርጥ ምርጡን ለህጻናት» የሚል አስተምህሮ ለመስጠት አይደለም። አእምሮአችሁን ለአፍታ ስለህጻናት እንዲያስብና ላነሳ ስለፈለኩት ጉዳይ ግንዛቤ እንዲኖራችሁ ነው።
ጥያቄ ላቅርብላችሁ? ህጻናት ጡት የሚተዉት እንዴት ነው? ጡት የሚጠባ ህጻን ጡት ሲያጣ ወይም ጡት ሲከለክሉት እንዴት ያደርገዋል? መቼም እንደማይስቅና እንደማይፍለቀለቅ አናጣውም። ይነጫነጫል፣ያለቅሳል፤ በአቅሚቲ እናቱን ይቧጥጣል፣ጡት አምጪ ብሎ ይማታል ብንል እውነት ነው። ሲያገኝና ሲጠግብ ደግሞ ጤነኛ እስከሆነ ድረስ ይስቃል፣ይጫወታል። እንዲህ እንዲህ እያለ ሁለትና ሶስት ዓመት ሲሞላው ደግሞ ደግሞ ጡቱን ያስጥሉታል።አራትና አምስት ድረስ የሚጠባ ልጅ እንዳለ ሳይዘነጋ መሆኑን ልብ ይሏል? ጡት የምታስጥል የገጠር እናት ያንን የለመደውን ነገር ለማስጣል ከባድ ይሆንባታል። እንዲጠላው ለማድረግ እሬት ይቀቡታል። ይቆነጥጡታል። ሌላም ነገር እያደረጉ ይከለክሉታል። ይሁን እንጂ የህጻኑ ለቅሶ ሲበረታ ልምድ አደገኛ ነውና እንደገና ያጠቡታል። እንደዚያ እንደዚያ እያደረጉ ምግብ እያቀረቡ፣ጡት እየነፈጉ ከህጻንነት የጡት መጥባት ዓለም ያወጡታል።

Monday, November 21, 2011

የሚያድን ዕይታ


የዘመኑ መስታወት.......



by Dagnu Amde on Friday, November 18, 2011 at 7:11pm

አቤቱ÷ እኔን ለማዳን ተመልከት
አቤቱ÷ እኔን ለመርዳት ፍጠን
(መዝ.69÷ 1)::

በሕይወታችን ብዙ ነገሮችን ዐይተናል፡፡ ዐይተናቸው በውስጣችን የቀሩ፣ ዐይተናቸው የረሳናቸው፣ ዐይተናቸው ደግመን ለማየት ያልፈቀድናቸው፣ ዐይተን እንዳላየ ያለፍናቸው፣ ዐይተን የታዘብናቸው ብዙ ነገሮች አሉ፡፡ ጽጌረዳን ዐይተን እሾህን እናያለን፡፡ የተንሰራፉ አበቦች በአሜከላዎች ላይ ተጐዝጉዘው እናያለን፡፡ ዐይናችን ሁለቱንም ታያለች፡፡ ኅሊና ግን አጥርታና መርጣ ታያለች፡፡ በዐይናችን ብዙ መልካምና ክፉ ነገሮችን እናያለን፡፡ ላየነው ሁሉ ምላሽ መስጠት አያስፈልገንም፡፡ ምላሻችንን የሚፈልጉ ዕይታዎች ግን አሉ፡፡ ማየት ከመስማት በላይ ነው፡፡ ሰምቶ ምላሽ ያልሰጠ ሲያይ ግን ምላሽ ይሰጣል፡፡ ማየት የተግባር አዛዥ ናት፡፡