Saturday, February 11, 2012

የጤናማ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ!

ጠያቂ፦ ስለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ዶክትሪን ብታስረዱኝ?

መልስ፦
በኢትዮጵያ ውስጥ ብዙ አብያተ ክርስቲያናት አሉ። የእያንዳንዳቸውን ዶክትሪን ልዩነት ለመጻፍ አስቸጋሪ ነው። ቢሆንም ግን አንዲት ቤተ ክርስቲያን ጤነኛ መሆንዋን የሚያመለክተን ዶክትሪንዋ (አስተምህሮትዋ) ነው። ጤነኛ ዾክትሪን ያላትን ቤተ ክርስቲያንን ለመለየት የሚከተሉትን መስፈርቶች መጠቀም ያስፈልገናል፦

1. ስለመጽሐፍ ቅዱስ ያላት አመለካከት ምን ነው - Bibliology
- መጽሐፍ ቅዱስ የ እግዚአብሔር ቃል ነው ብላ የማታምን፤ እንዲሁም ለቀደመው ዘመን እንጂ ለዚህ ዘመን አልተጻፈም ብላ የምታምን ከሆነ ወይንም ከመጽሐፍ ቅዱስ ሌላ አግንና የምትጠቀምበት ሌላ አይነት መጽሐፍት ያላት ከሆነ ይህች አይነቱ ቤ/ክ ጤናዋ ትክክል አይደለም። ከመጽሐፍ ቅዱስ ይልቅ ሌላ ነገር የምታስተምር ከሆነ መስመር የሳተች ናት።
2. ሰለ ስነመለኮት (ስለ እግዚአብሔር) ያለት አስተምህሮት ምንድነው? - Theology
- አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በሦስትነት አንድነትን የማታስተምር ከሆነች ጤነኛ አይደለችም።
3. ስለ ክርስቶስ ያላት እምነት ምንድነው?- Christology
-ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ መሆኑን የምታምን ቤ/ክ ጤነኛ ቤ/ክ ናት
4. ስለመዳን ያላት እምነት ምንድነው? እንዴትስ ይዳናል ብላ ታምናለች? - Soteriology
- በክርስቶስ ከማመን ውጪ ሌላ ወይንም ተጨማሪ የመዳኛ መንገድ የምታመለክት ቤ/ክ ጤነኛ አይደለችም።
5. ስለመንፈስ ቅዱስ ምን ብላ ታምናለች? - Pneumatology
- መንፈስ ቅዱስ ከስላሴ አካላት አንዱ እንደሆነ ፣ ለቤተ ክርስቲያንን በሃይል የሚያጠምቅ፣ወደ እውነት የሚመራና አስተማሪ መሆኑን ወዘተ. የምታምን ቤ/ክ ጤነኛ ናት።
6. ስለመላዕክት ምን ብላ ታምናለች? - Angelology
- መላዕክት የእግዚአብሔር ፍጥረትና አገልጋይ መልዕክተኞች እንደሆኑ እንጂ አማላጅ እንዳልሆኑ የምታምን ቤ/ክ ጤነኛ ናት። መላእክት ከምድር እስከሰማይ በተዘረጋው መሰላል ላይ ይወጣሉ፣ ይወርዳሉ እንጂ ራሳቸው መውጪያና መውረጃ መሰላል አይደሉም። ናቸው የምትል ከሆነ በክርስቶስ ቦታ መላእክትን ተክታለችና ጤናማ አይደለችም።
7. ስለርኩሳን መላዕክትስ ምን ብላ ታምናለች - Demonlogy
- ርኩሳን መናፍስቶች የ እግዚአብሔርን አላማ አሰናካዮች፣ የሰውም የ እግዚአብሔርም ጠላቶች እንደሆኑ፤ በመንፈስ ቅዱ ኅይል በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ከሰዎች መውጣት እንዳለባቸው የምታምን ቤ/ክ ጤነኛ ናት። ከክፉ መናፍስት መካከል ክርስቲያን መሆን የሚችሉ እንዳለ የምታስተምር ከሆነ ጤናማ ቤ/ክ አይደለችም።
8. ስለቤተ ክርስቲያንስ ምን ብላ ታምናለች - Ecclesiology
- ቤተ ክርስቲያን የክርስቶስ አካል፤የክርስቶስ ሙሽራ የምታምን ቤተ ክርስቲያን ጤነኛ ናት።
9 ሰለመጨረሻው ዘመን ምን ብላ ታምናለች? - Eschatology
- ቤ/ክ እንደምትነጠቅ፣የመከራው ዘመን  በምድር ላይ  እንደሚመጣ የምታምን፣ ከክርስቶስ ጋር እንደገና በክብር እንደምትገለጥና  ከንጉሡ ጋር በክብር ነግሳ እንደምትኖር የምታምንም ቤ/ክ ጤነኛ ቤ/ክ ናት።

እንግዲህ የዶክትሪን ልዩነቶች ከላይ በተጠቀሱት ዙሪያ በሁሉም አብያተ ክርስቲያናት ሊኖር ይችላል። በወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያን ውስጥ በአብዛኛው ተቀራራቢ መረዳት አለ ብዬ አምናለሁ። በዚህ ምሳሌ ነገሬን ልደምድም.... ጊታር የሚጫወቱ ሰዎች ይህ ምሳሌ በቀላሉ ይገባቸዋል። ጊታር ስድስት ክሮች አሉት የሁሉም ድምጽ ይለያያል። ሁሉም አይጠብቁም ሁሉም ደግሞ አይላሉም። ከሚገባው በላይ የጠበቀ ድምስ ዲስኮርድ ይፈጥራል፤ ከሚገባው በላይም የላላ እንዲሁ። በዶክትሪንም ዙሪያ ከላይ የዘረዘርኩት የሚጠብቁ ናቸው.... ይህንን ማላላት አይቻልም። ስለዚህ የሚጠብቀውን አጥብቀን የሚላላውን እናላላ። በሚያጨቃጭቁ ዶክትሪን ዙሪያ ከመናቆር አንድነታችንን ጠብቀን ወንጌልን እናሩጥ!
ከኢየሱስ.ኮም ድረገጽ የተገኘና በጥቂት ማስተካከያ የቀረበ