Saturday, February 4, 2012

ሞርሞኒዝም!

 

በዳኒ ይትባረክ የተጻፈ( በደጀብርሃን ለብሎጉ እንዲያመች የቀረበ)
.... ክፍል ሁለት

                            ሞሮኒ ማነው?

ስለዚህ ሰው በመጽሐፍም ይሁን በታሪክ ምንም ዓይነት መረጃ አናገኝም። መዝገበ ቃላትም ቢሆን ሞሮኒ(MORONI)የኮሞሮስ ዋና ከተማ መሆኗን እንጂ ሌላ የሚሰጠን ፍንጭ የለም። ታዲያ ይህ ሞሮኒ የተባለው የጆሴፍ ስሚዝ ሰው ማነው?
በመጽሐፈ ሞርሞን (THE BOOOK OF MORMON) መግቢያ ላይ «,,አ በ421 /ም ገደማ መጨረሻ አካባቢ የኔፊ(*) ባለታሪክና ነብይ የነበረ «ሞሮኒ» በጥንታዊ ነብያት አማካይነት በእግዚአብሔር ድምጽ በኋለኛው ቀን እንደሚመጣ እንደተተነበየው ቅዱሱን መዝገብ አተመው፣ እናም በጌታ እንዲጠበቅ ደበቀው» ካለ በኋላ በጌታ ተደብቆ የተቀመጠው ሞሮኒ ከሞት ተነስቶ በ1823 /ም በቤቱ እየጸለየ ሳለ የተገለጠለትና እጅግ በሚደንቅ ግርማ እንደታየው የጆሴፍ ስሚዝ መጽሐፍ ያትታል።
እንግዲህ ሞሮኒ ማለት እንደተከታዮቹ አባባል በ421 /ም ሞቶ በ1823 /ም ትንሳዔ በማግኘት ለጆሴፍ ስሚዝ የተገለጠ መልአክ ነው ማለት ነው።
ከዚህ አባባል የምንረዳው ነገር ሰይጣን በኢየሱስ ክርስቶስ ሕይወት የታየውን መለኮታዊ መልክ በሚመስል ነገር በሞሮኒ ስም ለጆሴፍ ስሚዝ በመገለጥ እንደሆነ እንረዳለን።
ሰይጣን ጆሴፍ ስሚዝን እንዳታለለው ዛሬም ቢሆን ህልም አለምኩ፣ ራዕይ አየሁ፣ መልዕክት መጣልኝ፣ እመቤታችን ታየችኝ፣ እሳት ከሰማይ ወረደ፣ በዘንዶ የሚጠበቅ ቤተክርስቲያን፣ በእባብ የታጠረ ጸበል በሚል ሰበብ በክርስትናው ውስጥ ዛሬም ብዙ ጆሴፎች አሉ።)
ሰይጣን መቼም አይተኛም። ጆሴፍ ስሚዝን እንዳጭበረበረው እኛንም ሊያጭበረብረን ይፈልጋል። ምክንያቱም ለሞርሞኖች ተስፋቸው አዲስቱ ኢየሩሳሌም ሳትሆን አሜሪካ ነች። ከድርሳናቸው አንዱ ክፍል ኔፊ እንዲህ ይላል።
«የያዕቆብ ቅሪት የሆኑትም ጌታ አምላካቸውን ወደማወቁ ይመጣሉ፣ እናም አሜሪካንን ይወርሳሉ» 3ኔፊ201
ጆሴፍን አሜሪካ የርስት ምድር እንደሆነችና አሜሪካንን የሚናፍቁ ሕዝቦች የሚፈጠሩበት ዘመን እንደሚመጡ ያኔም ሞሮኒ የተነበየላት ስለሆነ እንደሚባረኩ መዋሸቱን ስንመለከት ይህ ሰይጣን በኢትዮጵያም ውስጥ መልኩንና ማሳሳቱን ለውጦ «ደጅህን የረገጠ ኢየሩሳሌምን እንደተሳለመ እቆጥርለታለሁ ብሎ ቃል ገብቶለታል፣ ፍርፋሪህን የበላ የ40 ቀን ህጻን አደርግልሃለሁ ብሏል፣ በስሜ የተጠራ ዘው ብሎ ገነት ይገባል፣ የቅዳሴዬን ጸበል የቀመሰ 30 ትውልድ ሰተት አድርጌ ገነት አገባልሃለሁ ወዘተ ሞርሞናዊ ማሳሳቻዎች ከሰይጣን የወጣ ስለመሆኑ የታወቀ ነው። ሰይጣን ምን ጊዜም ክርስቶስ ያደረገልንን የሕይወት ስጦታ በመቀየር ወደሌላ የማዳኛ ምክንያቶች ለመለወጥ ሳይደክም እንደሚሰራ እንረዳለንና ነው።
ሐዋርያው እንዲህ ብሏል።« ስለዚህም ምክንያት፥ በእውነት ያላመኑ ነገር ግን በዓመፅ ደስ ይላቸው የነበሩ ሁሉ ፍርድን እንዲቀበሉ፥ ሐሰትን ያምኑ ዘንድ እግዚአብሔር የስሕተትን አሠራር ይልክባቸዋል»2ተሰ 211-12


               ሞርሞኖች ስለእግዚአብሔር ያላቸው አስተምህሮ

ሞርሞኖች በአጽናፈ ዓለም ላይ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ፕላኔቶች እንዳሉ፣ በነዚህም ፕላኔቶች ላይ በአንድ ወቅት ሰዎች ይኖሩበት እንደነበረና አሁን ግን አማልክት በሆኑ ኃይሎች እንደሚተዳደሩ ያምናሉ። ከዚህም በተጨማሪ እግዚአብሔርን በተመለከተ 4 ዓይነት አስተምህሮዎች አላቸው።
1/ እግዚአብሔር ሥጋና ደም አለው ይላሉ።
2/እግዚአብሔር አምላክም ሰውም ሆኖ በሰማይ አለ ይላሉ።
3/አማልክት አባት፣ እናት፣ አያት ወዘተ ሆነው በዘር ሐረግ በየፕላኔቶቹ አሉ ብለው ያምናሉ።
4/ እያንዳንዱ ሞርሞናዊም ወደአማልክትነት ለመቀየር መጣር አለበት ይላሉ።
(Mormon doctrine, page 557 &, Doctrine & covenantes section 130. verse 22)

.....ይቀጥላል
(*) የተመለከተው «ኔፊ» የሞርሞኖች ድርሳን ነው።