Wednesday, December 28, 2011

የኢየሱስ ክርስቶስ አስታራቂነትና አምላክነት

«ክርስቶስ ማለት በቁሙ ወደአማርኛ የተገለበጠው የግሪኩ(ጽርእ)ቃል «Χριστός»«ክሪስቶሽ ሲሆን ትርጉሙም «የተቀባ» ማለት ነው። መቀባት « χριστῷ» የሚለውን ብቻውን የሚያመለክተው ከሌላ መቀበልን ሲሆን «ክርስቶስ» የሚለው ቃል ግን የቅብእ ባለቤትነትንና የመቀባት ግብርን አያይዞ የሚጠራ ስም ነው። (ኢሳ 45፣1) ይመልከቱ። «ክርስቶስ» በእብራይስጡ «המשיח» ሀመሺያኽ ቅቡእ፣ የተቀባ ሲሆን ግእዙ «መሲህ» በሚለው ይተካዋል። የቤተክርስቲያን ሊቃውንትም «የክርስቶስን መቀባት ወይም ቅቡእ መሆን ለማመልከት ሲያስተምሩ «አብ ቀባኢ፣ ወልድ ተቀባኢ፣ መንፈስ ቅዱስ ቅብእ» በማለት ይገልጻሉ። በእርግጥ ይህ ትምሕርተ መለኰት ሰፊና ጥልቅ እንደመሆኑ መጠን በዚህ ዙሪያ የተነሱ ትምህርቶችና ክርክሮች ብዙ ሲያምሱ ቆይቷል፣ ዛሬም ቢሆን ጨርሶ የጠፋ ስለመሆኑ የሚታወቅ ነገር የለም። እኛም ያንን ላለመድገም እንደመንደርደሪያ ይህንን ያህል ካልን ወደተነሳንለት ዓላማ እናምራ!
«ክርስቶስ» የተቀባ ማለት ነው ብለናል። እንደዚሁ ሁሉ «ኢየሱስ» የሚለውን ስንመለከት የእብራይስጡ «ישוע» የሹአ ሲሆን ትርጉሙም «መድኃኒት» ማለት ነው። ግሪኩም «Ιησούς» መድኃኒት፣( ማዳን)፣ አዳኝ የሚለውን ትርጉም ይሰጣል። ከዚህ የተነሳ «ኢየሱስ ክርስቶስ» ማለት «የተቀባ፣ቅቡእ እና መድኃኒት፣ አዳኝ» የሆነ ማለት ነው። ይህንን የስም ትርጉም ካገኘን ለሚቀጥሉት ሃሳቦቻችን መረዳት መጠነኛ ግንዛቤ ጨብጠናል ማለት ነው።
የሚቀባው ማነው? የሚቀባውስ ለምንድነው?
እነዚህን ነገሮች አጥርቶ ማወቅ የብሉይ ኪዳን አስተምህሮዎችን መመርመር ግድ ይላል። ያንንም ማድረግ አስፈላጊ የሚሆነው «ስለመሲሁ» ክርስቶስነት ላይ በሚነሱ ልዩ ልዩ አመለካከቶች ከብዥታ የወጣ እይታ እንዲኖረን ይረዳናል።
ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ........>>>(እዚህ ላይ ይጫኑ