Thursday, February 28, 2013

የሰነበተ ዜና በሰበር፦ ብፁዕ አቡነ ማትያስ ፮ኛው ፓትርያርክ ሆኑ

ብፁዕ አቡነ ማትያስ በ500 ድምዕ

ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ98 ድምፅ
 ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል70 ድምፅ
 ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ98 ድምፅ
 ተመራጩ ፓትርያሪክ ብፁዕ አቡነ ማትያስ
 በዚህም መሠረት ብፁዕ አቡነ ማትያስ የካቲት 24 ቀን 2005 . በመንበረ ተክለ ሃይማኖት የሚሾሙ ስድስተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያሪክ ይኾናሉ፡- ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያሪክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት !!!
 በዛሬው የመራጮች መዝገብ 808 መራጮች ተመዝግበዋል፡፡  806 መራጮች መርጠዋል፡፡
 15 ድምፆች ዋጋ አልባ ኾነዋል፡፡ አንድ ባዶ የድምፅ መስጫ ወረቀት ተገኝቷል፡፡
 ተመራጩ ፓትርያሪክ ብፁዕ አቡነ ማትያስ ንግግር አድርገዋል፡፡
 ለምርጫው በአጠቃላይ ብር 3,650,000 ወጪ መደረጉን የአስመራጭ ኮሚቴው ሰብሳቢ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ ተናግረዋል፡፡