Showing posts with label ዜና. Show all posts
Showing posts with label ዜና. Show all posts

Wednesday, December 3, 2014

ሰበር ዜና፤ አባ እንባቆም ኢየሩሳሌም ገቡ፤ አባ ዳንኤል ደግሞ ሚኒያፖሊስ ከተሙ!

(ደጀ ብርሃን፤ሕዳር 24/2007 )

 አባ እንባቆም እስራኤል በሚገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ገዳማት ሊቀጳጳስ ሆነው በጥቅምቱ የሲኖዶስ ጉባዔ መመደባቸው ይታወሳል። በዚሁ መሠረት ቀደም ሲል የገዳማቱ ሊቀ ጳጳስ በነበሩትና ባለመግባባት ከቦታው እንዲነሱ በተደረጉት በአባ ዳንኤል ምትክ የተመደቡት አዲሱ ሊቀ ጳጳስ አባ እንባቆም ትናንት በ23/3/ 2007 ዓ/ም ኢየሩሳሌም መግባታቸውና ደማቅ አቀባበል እንደተደረገላቸው ተያይዞ የደረሰን ዜና ያስረዳል።

    አባ እንባቆም ቀደም ሲል በድሬዳዋ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሆነው ይሰሩ እንደነበር ሲታወቅ በቆይታቸውም ከሀገረ ስብከቱ ሠራተኞች ጋር ከፍተኛ አለመግባባት ላይ ደርሰውና ከቦታው እንዲነሱ የሕዝብ ግፊት አይሎ በነበረበት አጋጣሚ ወደኢየሩሳሌም መመደባቸው ለጊዜውም ቢሆን ትንፋሽ የመግዢያ ጊዜ ሊሆናቸው እንደሚችል ተገምቷል።

 በተመሳሳይ መልኩ ሊቀጳጳሱ በደብረ ሊባኖስ ገዳም ከፍተኛ ጥላቻና ተቃውሞ ሲደርስባቸው የቆየ ሲሆን የጉዳዩን ዝርዝር ምክንያት ለመግለጽ የተቆጠቡት ምንጮቻችን ሊቀጳጳሱ ከኢየሩሳሌም መነኮሳት ጋር ተግባብተው መስራት ይችላሉ ወይ? የሚለው ጉዳይ እንደሚያሳስባቸውና በሂደት ምን ሊፈጠር እንደሚችል ወደፊት የሚታይ ይሆናል ሲሉ አክለው ገለጸውልናል።
በሌላ በኩል ከገዳሙ አባቶች ጋር ባለመግባባት የተነሱት አባ ዳንኤል የተመደቡበትን ሀገረ ስብከት ሳይረከቡ እስካሁን አሜሪካ በሚኒሶታ ስቴት ሚኒያፖሊስ ውስጥ በምትገኘው የግላቸው ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከትመው የሚገኙ ሲሆን  ታቦተ ኪዳነ ምህረትን ከአዲስ አበባ ተሸክመው እንዲሄዱና ከመድኃኔዓለም ታቦት ጋር በደባልነት እንዳስገቡ ለመረዳት ችለናል። ሀገረ ስብከቱ በአቡነ ዘካርያስ የሚመራ ቢሆንም የሲኖዶሱን ህግ በመጻረር አንዱ በሌላው ሊቀ ጳጳስ ሀ/ስብከት ውስጥ ጣልቃ ገብቶ የፈለገውን መሥራት የለመደ አሰራር ሆኗል። በተለይም በአሜሪካ የመኖሪያ ፈቃድ ያለው ሊቀ ጳጳስ ጡረታውንና ድጎማውን እየተቀበለ በስሙ ያቋቋማትን ቤተ ክርስቲያን ደግሞ በግሉ ያለከልካይ ያስተዳድራል።



Monday, November 24, 2014

ኡጋንዳዊቷ የቤት ሠራተኛ ሕይወት ለማጥፋት በመሞከር ወንጀል ተከሠሠች!

( ዕድሜአቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ እንዲመለከቱ አይመከርም ) The film is not suitable for viewing by anyone under 18 years of age

ባለፉት ቅርብ ቀናት በኢትዮጵያ ውስጥ ሐና በተባለች ታዳጊ ወጣት ላይ አስነዋሪና እጅግ አሳሳቢ ድርጊት ተፈጽሞ የብዙዎችን ልብ እንደሰበረ ይታወቃል። ማኅበራዊ አኗኗራችን ከመተሳሰብ እያፈነገጠ፤ ሥነ ምግባራዊ አስተሳሰባችን እያደፈ የመሄዱ ምልክት ነው። ዓለም አንድ መንደር እየሆነች ነው ሲባል በመሰልጠኑ ብቻ ሳይሆን በመሰይጠኑም ጭምር በመሆኑ ስግብግብነት፤ ራስ ወዳድነት፤ ብልግናና ዐመፃንም ዓለማዊ መንደርተኝነት እያካፈለው ይገኛል። ኢትዮጵያ ውስጥ የተፈጸመው አስነዋሪ ድርጊት ትኩሳቱ ሳይበርድ አንድ መንደር የሆነችው ዓለም ከወደዑጋንዳ ሌላ ዜና ብቅ አለች። በአንዱ ጫፍ የተፈጸመው ወሬ ወደሌላ ጫፍ ለመድረስ ደቂቃ የማይፈጅባት ዓለማችን ካስተናገደቻቸው ብዙ ዜናዎች መካከል አንዱን አሳዛኝ ድርጊት አሰማችን። ጉዳዩ እንዲህ ነው።

  ድርጊቱ የተፈጸመው በዑጋንዳ፤ ኪዋቱሌ በተሰኘች አነሰተኛ ከተማ ነው። ድርጊቱን የፈጸመችው የ22 ዓመቷ ጆሊ ቱሙሂርዌ የተባለች የቤት ሠራተኛ ስትሆን በተቀጠረችበት ቤት ውስጥ እንድትንከባከብ ከአሰሪዎቿ አደራ የተሰጣትን ሕጻን በዘግናኝ ሁኔታ ስትደበድብ በቤት ውስጥ ስውር ካሜራ የተቀረጸ ቪዲዮ ያሳያል። በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ የተሠራጨው ይህ ቪዲዮ ብዙዎቹን አሳዝኗል። በጣም የሚረብሸው ይህ ምስል ማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ እንደዋለ ዓለም ዐቀፍ ትኩረት ስቧል።  የሕጻኗ ወላጅ አባት የሆነው ኤሪክ ካማንዚ ቪዲዮውን እንደተመለከተ ለኪዋቱሌ  ፖሊስ ጣቢያ በማመልከቱ ፖሊስ ደብዳቢዋን የቤት ሠራተኛ በቁጥጥር ስር አውሎ «በማሰቃየትና ለመግደል ሙከራ በማድረግ» ወንጀል የክስ ፋይል ከፍቶ ለፍርድ ቤት እንዳቀረባት የተገኘው ዜና ያስረዳል።  የቤት ሰራተኛዋ ከተቀጠረች 26 ቀናት ብቻ ያስቆጠረች ቢሆንም የፈጸመችው ድርጊት በተመሳሳይ ሁኔታ የቆየች እንደሚመስል ፖሊስ ግምቱን የሰጠ ሲሆን  ስለሰራተኛዋ ማንነትና የቀደመ ተግባር ምርመራ ለማድረግ የጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው ለፍርድ ቤቱ በማመልከቱ ለታህሳስ 8/2014 እንዲያቀርብ ፍርድ ቤቱ አዟል። ሕጻኗ በደረሰባት ጭካኔ የተሞላበት ድብደባ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባት ቢሆንም እስካሁን ህክምና እየተደረገላት በሕይወት እንደምትገኝ ታውቋል።
ሕጻናት የተለየ ክብካቤና ጥበቃ የሚያስፈልጋቸው ቢሆንም ዓለም በምታስተናግደው የሥነ ልቡና ማኅበራዊ ቀውስ የተነሳ ለጥቃት እየተጋለጡ ይገኛሉ። ፍሪሃ እግዚአብሔር የሌለው ትውልድ ከሥነ ምግባር ውጪ በመሆን ለማኅበራዊ ኑሮ የአስተሳሰብ ቀውስ መጋለጡ አይቀሬ ነው። አሳዛኝና አስነዋሪ ድርጊት የመፈጸሙ ምክንያትም ይህ ነው።  በየቤታችን ለሕጻናት፤ በየአካባቢው ለሴቶችና ለታዳጊ ወጣቶች፤ ለአረጋውያንና ረዳት ለሌላቸው የምናደርገውን ክትትልና ቀና ድጋፍ በማጎልበት «የአባቴ ብሩካን» ተብሎ የተነገረውን የሕይወት ዋጋ ለማግኘት ዛሬውኑ እንነሳ!!

«ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደ ሆነ፥ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ» 1ኛ ጴጥ 2፤2



Wednesday, October 29, 2014

«የነብር ጅራት አይዙም፤ ከያዙም አይለቁም!»

በጥያቄ እንጀምር! ማኅበረ ቅዱሳን ይፍረስ፤ ይበተን አልተባለም። ወደሕግና ሥርዓት ይገባ ነው እየተባለ ያለው። ማኅበሩ ይሁን ማፈሪያ ሊቃነ ጳጳሳቱ በዚህ አባባል የሚናደዱት ለምንድነው? «ደረጃ፤ ቦታና መጠን ተበጅቶለት መቀጠል ይገባዋል» የሚለውን የማኅበረ ካህናቱን ድምጽ ለመስማት ያለመፈለግ ምክንያት ከምን የመነጨ ነው? እኮ አሳማኝ ምክንያት አቅርቡ!!
 አለበለዚያ «እኛ ሊቃነ ጳጳሳት ስለሆንና ጉባዔው በድምጽ ብልጫ ስለሚመራ የአድማ እጃችንን ቀስረን ማኅበረ ቅዱሳን የሚደሰትበትን እንወስናለን» የሚለው ፈሊጥ የተበላ ዕቁብ ነውና ዘንድሮ አይሠራም።  በትክክል ዘንድሮ አልሠራም፤ አይሠራምም።

 ሊቃነ ጳጳሳቱ በየአህጉረ ስብከታቸው የካህናት ማሰልጠኛ ኮሌጆችን በመክፈት፤ የሴሚናሪ ትምህርት ቤቶችን በማስፋፋት የመንፈሣዊና ሳይንሳዊ እውቀት ባለቤት እንዲሆን ለቤተ ክርስቲያን እድገት እንዲሁም ፤ ለህብረተሰቡ ደግሞ በአካባቢ ልማት ተሣትፎ፤ በመንገድ ሥራ፤ በጤና ጣቢያና በንጹህ ውሃ አቅርቦት ተግባር ላይ በመትጋት ያንን ድሃ ምእመን ሕዝባቸውን መርዳት፤ መደገፍና በሥራ ማሳየት ሲገባቸው ተሸፋፍነው በመቀመጥ ሠራተኛ ሲቀጥሩ፤ ሲያባርሩ፤ ደመወዝ ሲቀንሱና ከቦታ ቦታ ሲያዘዋውሩ እድሜአቸውን ይፈጃሉ። ንቡረ እድ አባ ገ/ማርያም የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ሥራ አስኪያጅ በነበሩበት ጊዜ ሊቀ ጳጳስ አባ ቀውስጦስ ከራሳቸው ብሔርና ጎጥ ብቻ የመጣውን እየለዩ ለመቅጠር ሲታገሉ በተነሳ አለመስማማት የሙስና አፍ የዘጉትን ሥራ አስኪያጅ አይታዘዘኝም በሚል ውንጀላ ከስሰው እንዲቀየሩ ማስደረጋቸው አይዘነጋም። አሁን ደግሞ አባ ቀውስጦስ «ሞቴን ከማኅበረ ቅዱሳን ጋር ያድርገው» እያሉ ለያዥ ለገራዥ እያስቸገሩ እንዳሉ ይሰማል። ለምእመናን ልጆቹ በእኩል ዓይን አባት ይሆን ዘንድ ቃል የገባ ሊቀ ጳጳስ በዘረኝነትና በጎጠኝነት ሲታወር ሥጋውያኑማ እንዴት ይሆኑ?
የጎጃሙ ለጎጃም፤ የወሎው ለወሎ፤የጎንደሩ ለጎንደር፤ የሸዋው ለሸዋ የዘረኝነትን ገመድ የሚጎትት ሊቀ ጳጳስ ቤተ ክርስቲያንን እያወካት እንደሚገኝ ፀሀይ የሞቀው፤ አገር ያወቀው ጉዳይ ነው። እነማን? እንዴትና የት? ለሚለው በማስረጃ የተደገፈ ዝርዝር ማቅረብ ይቻላል።
ከብዙ መልካምና ጥሩ ነገሮቻቸው መካከል ሙት ወቃሽ አያድርገንና ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ የፈጸሟቸው ስህተቶች ለጵጵስና ማዕረግ ቀርቶ ለአንዲት አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪነት የማይበቁ ሰዎችን የመሾማቸው ጉዳይ ትልቁ ስህተታቸው ነበር። እሳቸውም በሕይወት ሳሉ ሊሾሙ የማይገባቸውን ሰዎች በመሾማቸው ይጸጸቱ እንደነበር እናውቃለን። ዛሬም የዚያ ስህተት ውጤት የሆኑ ሊቃነ ጳጳሳት ስንት ሥራና አገልግሎት ባለባት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ለአንድ ማኅበር ጥብቅና ቆመው «ሞታችንን ከማኅበረ ቅዱሳን ጓሮ ያድርገው» ሲሉ ይታያሉ። ከተመቻቸውና ከሞቃቸው ከማኅበረ ቅዱሳን ጋር ሞታችንን ያድርገው ያሉት ይሁንላቸው። ነገር ግን ማኅበረ ቅዱሳን ራሱ ወደሕግና ሥርዓት ካልገባ መሞቱ አይቀርም። ያን ጊዜ ምን ሊውጣቸው ይሆን?

ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ የማኅበረ ካህናቱ ሙሉ ድጋፍ እንዳላቸው ይታወቃል። ማኅበሩን ሥርዓተ አልበኛ የሚያሰኙ ተግባራቱ የማኅበሩን የመጨረሻ እድል ይወስናሉ። የጳጳሳቱ ጩኸት መነሻውና መድረሻው ከጎጥ፤ ከጥቅምና ከፍርሃት የመነጨ እንጂ ለቤተ ክርስቲያን ከማሰብ አይደለም። ምክንያቱም ማኅበረ ቅዱሳን ሳይኖር ቤተክርስቲያን ነበረችና። ማኅበረ ቅዱሳንም ባይኖር ትኖራለች።  ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ በሊቀ ጳጳሳቱ አድማ እንዳይፈቱ አደራችን ጥብቅ ነው። ከሕግና ከኃይል በላይ የሚሆን ማንም የለምና በበሉበት ለሚጮኹት ቦታ ሳይሰጡ ሥርዓትና ደንብ የማስገባት እርምጃዎትን ይቀጥሉ ዘንድ አበክረን እናሳስባለን። ዘንድሮን ነካክተው ከተዉት ይሄ የተደራጀ አውሬ እስከመጪው ዓመት ይበላዎታል። አቡነ ጳውሎስንም የበላው እንደዚሁ ነው። ዕድሜአቸውን በዐሥር ዓመት አሳጠርነው እያሉ የሚፎክሩት እስከየት የመጓዝ እልክ እንዳላቸው ማሳያ ነውና ይጠንቀቁ። ክፉ ሥራቸውን የሚጸየፍ እግዚአብሔር ይረዳዎታል።

«የነብር ጅራት አይዙም፤ ከያዙም አይለቁም!»






Friday, October 24, 2014

የቅዱስ ፓትርያርኩ የሲኖዶስ ጉባዔ መክፈቻ ንግግር (እዚህ ይጫኑ)



ሐራ ተዋሕዶ የተባለው የማኅበረ ቅዱሳን ቀኝ ክንፍ መካነ ጦማር ቅዱስ ፓትርያርኩ በሲኖዶሱ መክፈቻ ላይ ባቀረቡት ንግግር ተወገዙ፤ ውሳኔም ተላለፈባቸው ሲል ከብራዘር ሁድ ጳጳሳቱ ጋር ያለውን የምስጢር ትስስር በሚያሳብቅ መልኩ ዘገባውን አቅርቧል። ማኅበሩ የሲኖዶስ አባል ሆኖ በጉባዔው ላይ በመገኘት የጉባዔው ተካፋይ መሆን አይጠበቅበትም። በሱ ምትክ የጉባዔውን እስትንፋስ እየለኩ ምስጢር የሚያካፍሉ አባላት የሆኑ ጳጳሳት እንዳሉት ይታወቃል። ማኅበሩን ያናደደውና ደረጃውን ያልጠበቀ የፓትርያርኩ የመክፈቻ ንግግር ያሰኘው ነገር ቅዱስ ፓትርያርኩ ከመቼውም ጊዜ በላይ ስለማኅበሩ ቀጥተኛ አቋም ይዘው በመክፈቻ ንግግራቸው ላይ አበክረው ስላሳሰቡ ከደረሰበት ጭንቀት የተነሳ መሆኑ ይገባናል። የፓትርያርኩን ንግግር ደረጃ የሚያወጣና ማስጠንቀቂያ የሚሰጥ እሱ ማነው? አባ ሉቃስ? አባ ማቴዎስ?
በዚህ ዓመት ስለማኅበረ ቅዱሳን አቅምና ጡንቻ የመጨረሻ ገደብ ካልተደረገበት የነብርን ጅራት ይዞ እንደመልቀቅ ይቆጠራል። ጳጳሳቱም ቢሆን ክብራቸውን ካልጠበቁና ለማኅበሩ በአድማ ተሰልፈው ከቆሙ በተመዘገበ ግለ ታሪካቸው ቦታ ቦታቸውን እንዲይዙ ሊደረግ ይገባል። በአጭር ቃል ባለትዳሮቹና የልጅ አባቶቹ ከቤተ ክርስቲያኒቱ ከፍተኛ ማዕረግ ወርደው ከምዕመናን አንድነት ሊቀላቀሉ የሚገባው ዓመትም ይህ ዓመት ነው። ሳይገባቸው ከፍታ ላይ የተቀመጡ ሰዎች ባለበት አስተዳደር ምን ጊዜም ሁከት፤ ክፍፍልና እርስ በእርስ መለያየት መኖሩ እርግጥ ነው።
ይህ ዓመት ቤተ ክርስቲያንን የሚያምሱ፤ በአድማ የሚወስኑ ሰዎች ሰልፍ የሚሰበርበት እንዲሆን እንመኛለን።

Saturday, October 11, 2014

ፓትርያርኩም፤ ካህናቱም ስለማኅበረ ቅዱሳን በአንድ ድምጽ ተናገሩ!

ቤተ ክርስቲያን ግልጽ የሆነ መዋቅር ያላት ቢሆንም በቤተ ክርስቲያን ስም የሚደራጁ ማኅበራት፣ ከመዋቅራዊ ቁጥጥር ውጭ በመንቀሳቀስ ሀብትና ንብረት ያከማቹና እያከማቹ በመሆናቸው፣ ሕግና ሥርዓት የማይቆጣጠራቸው ከሆነ አሸባሪ የመሆን ዕድላቸው የሰፋ መሆኑን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ አስታወቁ፡፡

 

Friday, July 18, 2014

በኢየሩሳሌም ገዳም መነኮሳትና በሊቀ ጳጳሱ መካከል የተከሰተውን አለመግባባት ለመመልከት የተሰየመው አጣሪ ጉዳዩን ለማየት መጓዙ ታወቀ።




በኢየሩሳሌም ገዳም መነኮሳትና በገዳሙ ሊቀጳጳስ በአባ ዳንኤል መካከል በተከሰተው አለመግባባት ያለውን ችግር ለመፍታት ቋሚ ሲኖዶስ እንዲጣራ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል። ከዚህ በፊት እንደዘገብነው የገዳሙ ሊቀጳጳስ በመነኮሳቱ በኩል በረሃብ እየተቀጣሁ ነው ያለሁት ያሉትን ስሞታና መነኮሳቱ ደግሞ ውሸት ነው በማለት የሰጡትን ማስተባበያ ለአንባብያን መግለጻችንም አይዘነጋም። አሁን ዘግይቶ በደረሰን መረጃ ደግሞ ቋሚ ሲኖዶስ አሳልፎት በነበረው ውሳኔ መሠረት ግራ ቀኝ የተሰሙትን ክሶች ለማጣራት እንዲቻል አጣሪዎቹን ወደ ኢየሩሳሌም እንደላካቸውና ከስፍራው መድረሳቸውን የቤተ ክህነት ዘጋቢያችን ያደረሰን ዜና ያስረዳል።

ዘጋቢያችን የአጣሪዎቹን ማንነት ለማወቅ ጥረት እያደረገ ሲሆን የተላኩት የሲኖዶስ መልእክተኞች ወደእስራኤል መጓዛቸውን ግን ከተጨባጭ ምንጮች የተገኘው ዘገባ አመልክቷል።
ማጣራቱ የሚደረገው የገዳሙ መነኮሳቱ በሊቀ ጳጳሱ በኩል ተፈጽሟል የሚሉትን ክሶች መመርመርና ሊቀ ጳጳሱ ደግሞ በመነኮሳቱ በኩል ተፈጽሞብኛል የሚሉትን በደልና ግፍ አንድ በአንድ መርምሮ ለቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ ማቅረብ እንደሆነ ይታወቃል።
የአጣሪዎቹን ማንነት፤ የተደረገውን የማጣራት ሂደትና የተገኘውን አጠቃላይ ውጤት የተመለከተ የመረጃ ዘገባ ተከታትለን ለማቅረብ እንሞክራለን።

Monday, June 30, 2014

በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሊቀጳጳስ በብፁዕ አቡነ ዳንኤል ላይ የገዳሙ መነኮሳት አድመው በረሃብ እየቀጧቸው መሆኑ ተሰማ!



( ምንጭ፤ አባ ሰላማ ድረ ገጽ)



በኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሊቀጳጳስ በሆኑት በብፁዕ አቡነ ዳንኤል ላይ አባ ገብረ ወልድ በተባሉ መነኩሴ አሳዳሚነት ሊቀጳጳሱ ላይ ልዩ ልዩ የአድማ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆናቸውንና ሊቀጳጳሱ ላይ አደጋዎች መደቀናቸውን ከስፍራው የደረሰን ዜና አመለከተ፡፡ ብፁዕነታቸው የሲኖዶስን ስብሰባ ለመካፈል ከመጡ ወዲህ ተመልሰው ቢመጡ አናስገባቸውም በሚል የተጀመረው አድማ ምግብ እንዳይቀርብላቸው፣ ሾፌራቸውም መኪናቸውን እንዳያንቀሳቅስ እስከ ማሳደም የደረሰ አሳዛኝ እርምጃ እየተወሰደባቸው መሆኑን ምንጮቻችን የገለጹ ሲሆን ይህም ድርጊት በአንዳንድ ክፉ ቀን ግብጻውያን መነኮሳት ኢትዮጵያውያን መነኮሳት በበሽታና በረሃብ እንዲያልቁ ለማድረግ በራቸውን ዘግተውባቸው እርዳታ ሳያገኙ እንዲሞቱና ገዳማቶቻችን ያለ ሰው እንዲቀሩ ለማድረግ ከሚጠቀሙባቸው በጭካኔ የተሞሉ ስልቶች ጋር ተመሳሳይነት አለው፡፡ ከዚህ እርምጃ በስተጀርባ የማን እጅ እንዳለ ለጊዜው የታወቀ ነገር ግን የለም፡፡


ብፁዕ አቡነ ዳንኤል የስኳር በሽተኛ ከመሆናቸው አንጻር በረሃብ እንዲቀጡ አድማ መመታቱ እጅግ አሳዛኝ ተግባር መሆኑ እየተነገረ ሲሆን፣ በብፁዕነታቸው በኩል እስካሁን ነገሩን በትዕግስት ማሳለፋቸው የቤተክርስቲያን ስም በዚህ መንገድ እንዳይነሣ ከማሰብ እንደሆነ የተናገሩት ምንጮች፣ ብፁዕነታቸው የዲፕሎማት ፓስፖርት ያላቸውና እንደዲፕሎማት ስለሚታዩ ለሚመለከተው አካል አቤት ቢሉ ይህን ባደረጉት መነኮሳት ላይ ሕጋዊ እርምጃ ሊወሰድ እንደሚችል ስለጉዳዩ የሚያውቁ ይናገራሉ፡፡
በአባ ገብረወልድ የተመራው የአድማ ማኅበር እንዲህ ለማድረግ ያነሳሳው ምን እንደሆነ እስካሁን የታወቀ ነገር ባይኖርም ብፁዕነታቸው የኢየሩሳሌም ሊቀጳጳስ ሆነው ከተሾሙ በኋላ በዚህ ወቅት ሊሆን የማይችለውን በጎልጎታ ምዕራፍ ስምንት የተባለውን ቦታ ለቤተክርስቲያናችን በመግዛት ትልቅ ስራ መስራታቸው ይነገራል፡፡ የመነኮሳቱ ቅናትና አድማ የተነሳው ከዚህ መልካም ስራ ሳይሆን እንደማይቀር አንዳንዶች ይገምታሉ፡፡ የመነኮሳቱ ማኅበርም አይዟችሁ ያላቸው አካል ሳይኖር አይቀርም የሚል ግምት አለ፡፡

Wednesday, June 11, 2014

ማኅበረ ቅዱሳን በፓትርያርኩ ላይ የመጨረሻ የስም ማጥፋት መርዙን መርጨት ጀመረ!!

ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ ስንል እንደቆየነው ከማኅበረ ቅዱሳን ስውር መሰሪ ተግባር ውስጥ አንዱ ጉዳይ የሊቃነ ጳጳሳቱን የሕይወት ታሪክ ባለው የገንዘብና የስለላ አቅም አስቀድሞ በመሰብሰብ ለችግር ቀን ሊጠቀምበት ከመሳቢያው ውስጥ ቆልፎ የማስቀመጥ ጥበቡ ነው። ሊቃነ ጳጳሳቱ ማኅበሩ ለሚፈልገው አገልግሎት የጎበጠ ጀርባ ለማቅረብ ፈቃደኝነት ሲጎድላቸው ወይም ሲያገለግሉት ቆይተው የጎበጠ ጀርባቸውን ቀና በማድረግ የነጻነት አየር ለመተንፈስ ሲፈልጉ ያንን ከመሳቢያው ውስጥ ቆልፎ ያስቀመጠውንና ስም ለማጥፋት ይጠቅመኛል ብሎ ያሰበበትን የቆሸሸ ሥራ እንደአዲስ ግኝት ብቅ በማድረግ በሕዝብ ዘንድ እንዲጠሉ የክፋት መርዙን በልዩ ልዩ አቅጣጫ መርጨት ይጨምራል።
እነሆ « የለውጥ አባት፤ ሙስናን ለመዋጋት ቃል የገቡ ፓትርያርክ» በማለት በማሞካሸት ጉሮሮው እስኪነቃ ውዳሴ ከንቱ ማብዛቱ ሳያንስ  በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ለማስረግ ሞክሮ ያልተሳካለትን «የሕግና የለውጥ አተገባበር መመሪያ» በማለት ያንቆለጳጰሰውን የቅጥፈት ስርዋጹን ሰነድ፤ ፓትርያርኩ «በመላ ሀገሪቱ ሊተገበር የሚገባው» በማለት አድናቆት እንደቸሩት ሲደሰኩር እንዳልነበር ሁሉ ፓትርያርኩ የማኅበሩን አካሄድ አይተው ፊታቸውን ሲያዞሩበት  በመረቀበት አፉ እርግማኑን ለማውረድ የተፋው ምራቅ ገና አልደረቀም ነበር።
የማኅበሩ የክፋት ጥግ ርኅራኄ የለሽ መሆኑን የሚያሳየን ሲያገለግሉት የቆዩት ሰለቸን ማለት ከጀመሩ ወይም ፊት ሰጥተው ሲያሳስቁት የነበሩት አባቶች ቅጭም ያለ ገጽታ ወደማሳየት ከተሸጋገሩ ስማቸውን በማጥፋት የነበራቸውን ስም ከአፈር በመደባለቅ እንዳይነሱ አድርጎ የመምታት ልኬታው ከባድ ነው።
ሰሞኑን በፓትርያርክ ማትያስ ላይ በግል ጋዜጦች፤ በአፍቃሬ እንዲሁም ስውር ብሎጎቹና በመንግስት ተቃዋሚ ድረ ገጾች ሳይቀር እየተቀባበሉ «ፓትርያርኩ የደርግ አገልጋይ ናቸው» ወደሚል የጋራ የስም ማጥፋት ዘመቻ ወርደዋል። «አንድ ሰሞን ማመስገን፤ አንድ ሰሞን መራገም» የማኅበረ ቅዱሳን «ሲመች በእጅህ፤  በማንኪያ ሲፈጅህ» መፈክር መገለጫ መሆኑ ነው።
አይሆንም እንጂ ቢሆንለት ፓትርያርኩ ነገ አዲስ ሀሳብ ይዘው ብቅ ቢሉና »ማኅበረ ቅዱሳን የቤተ ክርስቲያናችን የዓይን ብሌን ነው» የሚል መግለጫ ቢሰጡ  «12 ክንፍ ያላቸው ቅዱስ ፓትርያርኩ የክፍለ ዘመኑን አዲስ መግለጫ ሰጡ» በማለት እንደ ደብረ ብርሃኑ መብረቅ በብርሃን ወረደልን የፈጠራ ዜና ይለውጠውና ለፓትርያርኩ ገድል ይጽፍላቸው ነበር።
ይሁን እንጂ ይህ እንዳይሆን ለማኅበረ ቅዱሳን ህልም በመሰለ የእውነታ ውጥረት በፓትርያርኩ ስለተያዘ እርግማኑንና ስም ማጥፋቱን ስራዬ ብሎ ገፍቶበታል። ነገሩ ሲታይ «የማያድግ ጥጃ እንትን ይበዛበታል» እንዲሉ የስም ማጥፋት ዘመቻው የእስትንፋሱ የመጨረሻ ምዕራፍ እንደሆነ አመላካች ይመስለናል።
ፓትርያርክ ማትያስ«የደርግ ተላላኪ ነበሩ፤ አሁን ደግሞ የኢህአዴግ ተላላኪ ሆነው ተገልብጠዋል» በማለት ማጣጣሉ የሚያሳየን ነገር  የማኅበረ ቅዱሳን ተላላኪ ለመሆን በጭራሽ ፈቃደኝነት ቀርቶ ሃሳብ እንደሌላቸው ስላየ እንጂ ማኅበሩን እያሞጋገሱና ከወንበራቸውም ትንሽ ከፍለው ቢሰጡት ኖሮ ይህንን ወደመሰለ የብስጭት ማሳያ ነቀፋ ባልወረደም ነበር። እውነትን ለሕዝብ ለመግለጽ ፈልጎ ቢሆንማ ኖሮ አባ ገብርኤልን የመሰሉ የማኅበሩ ደጋፊ ጳጳስ በአንድ ወቅት አቶ ኢያሱ የመባላቸውን ዜና፤ አቡነ ጳውሎስን አውግዘው ወደአሜሪካ መፈርጠጣቸውን፤ እዚያም ሄደው የኢህአዴግ የተቃውሞ ሰልፍ አስተባባሪ ሆነው በአደባባይ መጮሃቸውንና 360 ዲግሪ ተሽከርክረው ወደጠሉት ሀገር መመለሳቸውን ዜና አድርጎ ለምን አይሰራም ነበር? ይህንንማ እንዳያደርግ አባ ገብርኤል የማኅበሩ ቀኝ እጅ ሆነው ስለሚያገለግሉ  ብቻ ነው።  ነገ ተነስተው «በዚህ ማኅበር ታምሰን የምንሞተው፤ እስከመቼ ነው?» የሚል ጥያቄ አቡኑ ቢያነሱ የታወቀና ያልታወቀ ኃጢአታቸውን እንደሸረሪት ድር ይዘከዝክላቸው ነበር።
በዘንድሮውም የሲኖዶስ ጉባዔ ላይ እንዳገኘው መረጃ ከሆነ የማኅበሩ ደጋፊ መሆናቸው በደንብ የሚታሙት ጳጳሳት ሳይቀሩ የድጋፍ ቀንዳቸውን አቁመው ሊከራከሩለት አለመድፈራቸው አንድም የማኅበሩ የእድሜ ዘመን ማጠሩን ከመገመት አንጻር አለያም በማኅበሩ ጥፋት የተነሳ ከኑግ እንደተገኘች ሰሊጥ እንዳይወቀጡ ከመስጋት የተነሳ ይመስለናል። ጥቅም ዓይናቸውን ካሳወራቸው መካከል ጥቂቶች ለመንጫጫት ከመሞከራቸው በስተቀር ከዚህ በፊት ሲያደርግ እንደነበረው ማኅበሩ አጀንዳ አስረቅቆ፤ ሲያስጸድቅ የነበረውን ጉልበት ዘንድሮ ሳያገኝ መክኖ ቀርቷል። አቡነ ጳውሎስን ተባብረው በአድማ ሲያዳክሙና ለራስ ምታት ሲዳርጓቸው የነበረው የሴራ አቅም በፓትርያርክ ማትያስ ተቀልብሶ በተገላቢጦች የማኅበሩና የደጋፊዎቹ ራስ ምታት ሆኖ የጫወታው ሜዳ ተጠናቋል።
ከዚህ በፊት ስንል እንደቆየነው አሁንም ደግመን የምንለው «የማኅበረ ቅዱሳን አባል መሆን መብት ሲሆን ሊቀ ጳጳስ ሆኖ ወደማኅበር አባልነት ወይም ደጋፊነት ከወረደ ያለበትን መንፈሳዊ ሥልጣን ለቤተ ክርስቲያኒቱ አስረክቦ በተራ አባልነቱ እንዲቀጥል የማስድረጉ ነገር መዘንጋት የለበትም» እንላለን። ሊቀ ጳጳስ በቤተ ክርስቲያኒቱ ከፍተኛ መንፈሳዊ ሥልጣን ላይ ተቀምጦ ከመንጋው ውስጥ በተለየ መልኩ የሚወደው ወይም የሚንከባከበው ወይም በጥብቅና የሚከራከርለት የተወሰነ የቤት ልጅ እና የእንጀራ ልጅ የሚባል ሊኖረው አይችልም። በሀዋሳ ታይቶ የነበረው ሁከት መነሻው በአባ ገብርኤል በኩል ማኅበረ ቅዱሳንን የቤት ልጅ አድርጎ የማየትና ማኅበሩን የሚቃወሙትን ደግሞ የእንጀራ ልጅ አድርጎ በማቅረብ መንጋውን በእኩል ለማገልገል ያለመቻል የጳጳሳት አባል የመሆን ልክፍት የተነሳ ነው። ይህ ችግር በቦረና፤ በሐረር፤  በመንፈሳዊ ኮሌጆችና በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ውስጥ ሳይቀር በተግባር ታይቷል። ማኅበሩ «ከኛ ጋር ያልቆመ ጠላታችን ነው» በሚል ፈሊጥ በአባልነት የያዛቸውን ጳጳሳት እንደዱላ በክርስቶስ መንጋ ላይ እየወረወረ ይጠቀምባቸዋል።
ስለዚህ ፓትርያርክ ማትያስ በስም አጥፊው ማኅበርና ለማኅበሩ በተለየ አድረው መንጋውን በእኩል ዓይን ማየት በተሳናቸው ላይ ፍትሃዊና የተጨበጠ እርምጃ ለመውሰድ ማቅማማት እንደሌለባቸው ለማስገንዘብ እንወዳለን።
የስም ማጥፋት ዘመቻው የማኅበሩን ማንነት ገላጭ ሲሆን በንስሐ ተመልሶ ቤተ ክርስቲያን በሰጠችው ልክ ከመንቀሳቀስ ይልቅ ክፋቱን ለመተው ያለመፈለጉ ማሳያ መሆኑ ሊዘነጋ አይገባም።

Thursday, May 29, 2014

በአቡነ ጳውሎስ ላይ ሲፈጸም የቆየው የሊቃነ ጳጳሳቱ አድማና የማኅበረ ቅዱሳን ጣልቃ ገብነት በአቡነ ማትያስ ላይም ቀጥሏል!

ከሊቃነ ጳጳሳቱ ግማሾቹ የራሳቸውን የጉባዔ ላይ የድምጽ ጡንቻ በማፈርጠም ጥቅማቸውን ለማስጠበቅ ከሚመስሏቸው ጋር የመቀናጀት ጠባያቸው ከምንኩስና ጀምሮ የተዋረሳቸው እንጂ ድንገት የተከሰተባቸው ዐመል አይደለም። ገሚሶቹ ሊቃነ ጳጳሳት ደግሞ ከዚህ ፈርጣማና  ጠንካራ የቡድን  አቅም መፍጠር ከቻሉት ጋር መለጠፍ የሚፈልጉት አንድም ብቻቸውን መዝለቅ እንደማይችሉ ስለሚያውቁ፤ በሌላ መልኩም ሊመጣ ይችላል ከሚሉት ጥቃት ራሳቸውን ለመከላከል ከመፈለግ ራስን የማዳን ዘዴ የተነሳ ነው። ጥቂቶች ቢሆኑም አንዳንዶቹ ደግሞ ያልሆነ ንትርክና ጭቅጭቅ እንዲነሳ የማይፈልጉ፤ ዝም ብለው በመመልከት ታዛቢ የሚመስሉ በእድሜ የገፉ ሲሆኑ በጣት የሚቆጠሩት ደግሞ ስለቤተክርስቲያን የሚገዳቸው ነገር ግን ድምጻቸው ብዙም የማይሰማላቸው ናቸው።
 የቡድን ኃይል መፍጠር የቻሉት አብዛኛዎቹ ሊቃነ ጳጳሳት የወጣትነት ዐመል ብዙም ያልራቃቸው፤ በቂ ኃብት ማከማቸት የቻሉ፤ ለተሸከሙት ማዕርግ ሳይሆን ለስምና ለዝና የሚጨነቁ በተለይም ከማኅበረ ቅዱሳን ጋር በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ንክኪ ያላቸው ናቸው። እነዚህኞቹ ለቤተ ክርስቲያን የሚታይ፤ የሚጨበጥ፤ ለትውልድ የሚተላለፍ ቋሚ ቅርስና ሀብት መፍጠር ያልቻሉ ነገር ግን በምላስ የሰለጠኑ፤ እምቢተኝነትና ቡድንተኝነት እውቀት የሚመስላቸው ናቸው። ቤተክርስቲያን መታመስ የጀመረችው እነዚህኞቹ ቅዱስ ወደተባለው ሲኖዶስ የመቀላቀል እድል ካጋጠማቸው በኋላ ነው። ማኅበረ ቅዱሳንም ከሀገር ቤት እስከ ውጪ ሀገር ድረስ በቤተ ክርስቲያኒቱ መልክና ቁመና ስሩን የሰደደው በእነዚህኞቹ ጀርባ ታዝሎና ተንጠላጥሎ ነው።
የቀድሞውን ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስ እግር ተወርች አስረው አላሰራ ሲሉ የነበሩት እነዚህ ቡድንተኞች ዛሬም አንድ ግንባር ፈጥረው እድሜ ካላስተማራቸው አረጋውኑ መካከል ጥቂቶቹን አሰልፈው ማኅበረ ቅዱሳንን ከጀርባቸው አቁመው ፓትርያርክ ማትያስንም በተመሳሳይ መልኩ አላሰራ፤ አላንቀሳቅስ፤ አላላውስ እያሏቸው ይገኛል። በዚህ መልኩ የት ድረስ መጓዝ እንደሚቻል ለመገመት አይከብድም። ነገር ግን «ህልም ተፈርቶ ሳይተኛ አይታደርም» እንዲሉ አበው መላ መፈለግ ፓትርያርክ ማለት «ርእሰ አበው» ማለት እንደመሆኑ መጠን የተሰጠውን ሥልጣን ለቡድንተኞች አስረክቦ የተነገረውን የሚቀበል ተላላኪ ማለት ባለመሆኑ ሥልጣኑ ሙሉዕ መሆኑን ማመን የግድ ይሆናል። ስለዚህ በአድመኝነት፤ ለማኅበሩ ወግነው አላሰራ ለሚሉ ምን መደረግ አለበት?  ነገሮች እየጠሩ፤ የችግሩም ገፈት ከላይ ካልተወገደ በስተቀር ተለባብሶ የትም አይደረስም። ቤተ ክርስቲያንም አትድንም፤ ባለማዕርጎቹም በዘመናቸው ንስሐ አይገቡም። ስለዚህ የማያወላዳ እርምጃና ውሳኔ ያለምንም ማቅማማት መውሰድ የግድ ይላል። ጥቂት ነጥቦችን እናንሳ።
1/ ከአድመኞቹ ሊቃነ ጳጳሳት መካከል ብዙዎቹ ቃል የገቡበትን መሃላ አፍርሰው የቤተ ክርስቲያኒቱ ተጠሪ ነን ካሉ በኋላ ደመወዝተኛ፤ አበልተኛና የጥቅሟ ተከፋይ ሲያበቁ መንፈሳዊነቱን ክደው፤ ሀብት ንብረት አፍርተው ፤ እንደዓለማውያኑ የሚሊዮን ብር ቤቶችን የገነቡ፤ በባንክ ያከማቹ ስለመሆናቸው መረጃና ማስረጃ የሚቀርብባቸው ስለሆነ በሊቀ ጳጳስነት ማዕርግ የእግዚአብሔርን መንግሥት ብቻ ለማገልገል  ብቃት የሚጎድላቸውና «ለሁለት ጌቶች መገዛት አትችሉም» ያለውን የወንጌል ቃል ያፈረሱ ስለሆነ ከያዙት ማዕርግ ተሰናብተው ወደዓለማዊ ሀብታቸው እንዲሄዱ ሊሸኙ ይገባል።
2/ ገሚሶቹ ሊቃነ ጳጳሳት ቃለ መሃላ ከፈጸሙበት «ኩሎ ኀደግነ» ሁሉን ትተን ተከተልንህ ካሉ በኋላ በቀጥታ ያለሰማንያ ጋብቻ በትዳር ወልደው ከብደው የሚኖሩ፤ ገሚሱም በአዲሱ የቤተሰብ ህግ እንደተመለከተው « ትዳር በሚመስል ሁኔታ አብሮ መኖር ራሱ ጋብቻ እንደተፈጸመ ይገመታል» በሚል የህግ መንፈስ መሰረት አግብተው ዓለሙም፤ ሊቀጵጵስናውም ሁሉም ሳይቀርባቸው አጣምረው የያዙ ስለሆነ በእነዚህኞቹ «ጸሊማን አርጋብ»  ላይ በቂ ማስረጃ መቅረብ ስለሚችል በማያወላዳ ውሳኔ ለሌሎች ትምህርት ሊሆን በሚችል መልኩ ለትዳራቸው ታማኝ ሆነው እንዲኖሩ በክብር መሸኘት አለባቸው።
3/ ለዚህ ጥሩ አብነትና ምሳሌ ሊሆን የሚችለው በግብጽ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ከዚህዓለም በሞት የተለዩት የአቡነ ሺኖዳ አስተዳደር ተጠቃሽ ነው። ሊቃነ ጳጳሳት የራሳቸውን ሀብት ማፍራት አይችሉም። መነኮሳት ከመነኮሱበት ገዳም ውጪ ሌላ ገዳም በፍጹም አይቀበላቸውም። ከገዳሙ ከወጣ ምንኩስናውን እንደተወ ይቆጠራል። በሴት የተጠረጠረ መነኩሴ በቀጥታ ተጠርቶ ይጠየቃል እንጂ እንደኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ተሸፋፍኖ ያሻውን እንዲፈጽም እድል አይሰጠውም። መረጃና ማስረጃ ከቀረበበት ቀሚሱን ከታች አንስቶ፤ እስከ አንገቱ ድረስ መሃል ለመሃል በመቀስ ቀደው መቋቋሚያ ገንዘብ ሰጥተው ሕዝባዊ እንዲሆን ያሰናብቱታል። ይህ ለሌላው ትምህርት፤ ለቤተ ክርስቲያንም ክብር ይሆናል። ነገር ግን በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ያለው ነገር በዚህ ዘመን አሳፋሪ ሆኗል። ከሊቃነ ጳጳሳቱ ትዳር የመሰረቱ ሞልተዋል። የመነኮሳት ነጋዴ መሆናቸው ሳይታወቅ ሚሊየነር ሆነዋል። ዝሙትና ስርቆት ቤተ ክርስቲያኒቱን እንደነቀዝ እየበላት ነው። በዚህ መልኩ ከቀጠለች የቤተ ክርስቲያኒቱ ኅልውና አስጊ ነው። እዚህ ላይ ከነጋ ድራስ ገብረሕይወት ባይከዳኝ መጽሐፍ ጥቂት ቃል እንዋስ። «እግዚአብሔር መንግሥታችንን፤ ቤተክርስቲያናችንን ለባዕድ አሳልፎ አይሰጣትም እያለ ሕዝባችን በስንፍና ያለሥራ ይኖራል» እውነትም ብዙ ጊዜ እግዚአብሔር ከጥፋት ተከላከለን፤ ነገር ግን እኛ ለቸርነቱ የተገባውን ሥራ ሠርተን በተግባር አላሳየንም» ብለዋል ነጋድራስ በጽሁፋቸው ከዛሬ ሰማንያ ዓመት በፊት።  ይሁን እንጂ ዛሬም ከስንፍናችን ፈቀቅ አላልንም። እግዚአብሔር ራሱ ይጠብቅ ብለን እኛው ያጠፋናትን ቤተ ክርስቲያን እንደባለእዳ ትተንለታል።
4/ ማኅበረ ቅዱሳን ማነው? የማነው? ምንድነው? ብዙ የሚያጠያይቅ ጉዳይ ነው። የጠራና የማያሻማ መልስ ያስፈልገዋል። ተለባብሶ በበግ ለምድ ተሸሽጎ አይዘለቅም። ስለማኅበረ ቅዱሳን ጥብቅና የሚቆም ማንም ቢኖር የማኅበሩ አባል የመሆን መብቱ የተከበረ ነው። ነገር ግን ሊቀጳጳስ ከሆነ በኋላ ቤተ ክርስቲያን የሰጠችውን የሲኖዶስ አባልነት ሥልጣን ይዞ የማኅበረ ቅዱሳን አባል መሆን አይችልም። መሆን ከፈለገ ጵጵስናውን ማስረከብ አለበት።  አንድ ሚኒስትር የኢህአዴግ ምክርቤት አባልና የሰማያዊ ፓርቲ አባል በአንድ ጊዜ መሆን አይችልም። አንዱን ይተዋል፤ ወደአንዱ ይጠጋል እንጂ። ይህንን ለማስተካከል የፓትርያርኩ ሥልጣን ምሉዕ ነው። እነዚህ በሁለት ልብ ሲኖዶሱን የሚያውኩ ጳጳሳት በህግ አግባብ ካልተወገዱ የሲኖዶስ ሕውከት ማብቂያ አይኖረውም። ስለማኅበረ ቅዱሳን የሚከራከር ሊቀጳጳስ ከሲኖዶስ አባልነቱ ወደታች ወርዶ የተራ ማኅበር ደጋፊ ከሆነ ማዕርጉን ተገፎ  በማኅበር አባልነቱ እንዲቀጥል ከሲኖዶስ ሊባረር ይገባዋል።
5/ ፓትርያርክ ማትያስ ቆምጨጭ ያለና እርምት የሚሰጥ እርምጃ ከመውሰድ ውጪ በእንደዚህ ዓይነት የአድማና የቡድን ጭቅጭቅ እየተሰላቹ የትም አይደርሱም። ሊቀጳጳስ የሚባለው ማዕርግ ሊከበር የሚችለው ራሱ ማዕርጉን የተሸከው ሰው አክብሮ፤ የሚያስከብር ሥራ ሲሰራበት ብቻ ነው። ሹመትማ ይሁዳም ከሐዋርያት አንዱ ነበር። ነገር ግን ጥፋት እንጂ ልማት አልሰራበትምና ሐዋርያ መባሉ ቀርቶ «ሰያጤ እግዚኡ» ከመባል አልዳነም። ስለዚህም ቤተ ክርስቲያንን ከመሸጥ የማይመለሱ እነዚህ አድመኞች ሊቃነ ጳጳሳት ሻጮች ቢባሉ ምንም አያስነውርም። ስም መጥቀስ አያስፈልግም እንጂ እነማን ማናቸው? ምን አደረጉ? ምንሰሩ? በደንብ ይታወቃል።
6/ ቤተ ክርስቲያንን ከውድቀት ለማዳን፤ ማዕርጋት ዋጋና ክብር እንዲኖራቸው ለማድረግ ሲባል ያልተፈለገ ነገር ግን አስገዳጅ እርምጃ እስከመውሰድ የሚዘልቅ ክስተት መፈጠሩ አይቀርም።  ፓትርያርክ ከሆኑ በኋላ ከሚቆጠቁጠው የመንፈሳዊ ኅሊና ቁጭትና ከታሪክ ወቀሳ ለመዳን መስራት የሚገባውን ሁሉ ካልሰሩበት ማዕርጉን ተሸክሞ መቀመጥ በቤተክርስቲያን ውድቀት ላይ መተባበር በመሆኑ ሹመቱን አስረክቦ የራስን ነጻነት ማወጅ የተሻለ ነው።
በአቡነ ጳውሎስ ላይ ሲፈጸም የቆየው የሊቃነጳጳሳቱ አድማና የማኅበሩ ሴራ በአቡነ ማትያስም ላይ የሚቀጥለው  እስከመቼ ነው?
 አቡነ ማትያስ አርፈው የማኅበሩ አባል ሊቀ ጳጳስ ሌላ ፓትርያርክ እስኪሆን ድረስ ይህ ውጊያ አያቆምም።

Sunday, May 18, 2014

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በማኅበረ ቅዱሳንና በደጋፊ ጳጳሳቱ በኩል የጉባዔ ተግዳሮት እንደሚገጥማቸው ይጠበቃል!





የዘንድሮው የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባዔ ከመቼውም ጊዜ የተሻለ ምስጢራዊነቱን የጠበቀ እንዲሆን ተሞክሯል። ይህ ማለት ግን ከማኅበረ ቅዱሳን የተሰወረ የአጀንዳ፤ የውይይት ሂደትና የውሳኔ እልባት ነበረ ማለት አይደለም። ምስጢራዊነቱ  የቤት ልጅ ከሆነው ከማኅበረ ቅዱሳን ውጪ ለአብዛኛዎቻችን እንዲጠበቅ ያስፈለገበት ዋና ምክንያት በቅዱስ ፓትርያርኩ በተሰጠ የቅድመ ጉባዔ መመሪያ ቢሆንም በአንጻሩ ማኅበሩና ደጋፊ ጳጳሳቱም ምስጢራዊነቱ ቢጠበቅ የኅልውና ጉዳይ የባቄላ ወፍጮ እንዳይሆን ከመፈለግ የተነሳ እንደሆነ ውስጥ አዋቂ ምንጮች ግምታቸውን ያስቀምጣሉ። ምክንያቱም የዘንድሮው የጉባዔ ሂደት የማኅበሩን የሁለት ዐሥርተ ዓመታት ጉዞ ወሳኝ በሆነ መልኩ የሚመለከት ጉዳይ ከመኖሩ የተነሳ ምስጢራዊነቱ እንዲጠበቅ አስፈልጓልም በማለት ያክላሉ።
ቅዱስ ፓትርያርኩን ከገጠሟቸው ተግዳሮቶች አንዱ «ማኅበረ ቅዱሳን በምን ሕግና መንገድ ሊተዳደር ይገባዋል» በሚለው አንገብጋቢ ጉዳይ ላይና አዳዲስ ሊሾሙ በሚችሉ የእጩ ኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ላይ የተያዘው የሁለት ወገን ሰልፍ ምክንያት እንደሆነ ይነገራል።
አንዱ ሰልፍ  በቅዱስ ፓትርያርኩና በደጋፊዎቻቸው በኩል የሚነሳው ሃሳብ የማኅበሩ እንቅስቃሴ ከሰላምና ከፍቅር ይልቅ ቤተ ክርስቲያኒቱ በማኅበሩ የምትታወክበትና ያልተፈለገ እሰጥ አገባ ውስጥ የምትዘፈቅበት ምክንያት ስለበዛ እንደማኅበር መቆየት አለበት የሚያሰኝ አመክንዮ ባይኖርም እንኳን እንዲኖር ካስፈለገ አቅሙንና ደረጃውን አውቆ፤ እንቅስቃሴው ከአቅሙ ጋር ተገናዝቦ በተወሰነ ማዕቀፍ ውስጥ ብቻ ኅልው እንዲሆን የሚያስገድድ ህግ እንዲወጣለት ጥብቅ ፍላጎት ያላቸው መሆኑ ነው።
ሁለተኛው ሰልፍ ደግሞ የማኅበሩ አባላት በሆኑ ሊቃነ ጳጳሳትና ማኅበሩ ራሱ በስለላ መዋቅሩ በኩል በሚያካሂደው የሩጫ ዘመቻ የተነሳ ያለው ሰልፍ ሲሆን ይህም ሲከናወን የቆየውን ስልት ማስቀጠል የሚያችል ልዩ መብት በራሱ ሰዎች በኩል አርቅቆ ለማስጸደቅ መቻል ነው። ይኼውም ማኅበሩ እስካሁን ከሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ስር በተመሳሳይ የዘመቻ ስልት አፈንግጦ የወጣበትና በሥራ አስኪያጁ ስር እንዲቆይና የራሱን ኅልውና ለማቆየት አዲስ መተዳደሪያ ደንብ እንዲወጣ የተሰጠውን የቆይታ ጊዜ ባለመጠቀሙ በዚህ ጉባዔ ላይ በሚፈልገው የጊዜ መግዢያ መንገድ የመቋጨት ዓላማ እንዳለው ከውስጥ አዋቂ ምንጮቻችን ለማወቅ ተችሏል።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ የሚነሳው ጉዳይ የአዳዲስ ኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ሲሆን ማኅበሩና ታዛዥ ጳጳሳቱ የያዙት ስልት በሁለት መንገድ እየተሰናሰለ ለማስኬድ እየተሞከረ እንደሚገኝ መረጃዎች ያሳያሉ። ይኼውም በእነሱ ምርጫና አጽዳቂነት ተመልምለው ለሲኖዶስ መቅረብ የሚገባቸውን የመለየት ስራ ያከናወኑ ሲሆን በፓትርያርኩና በደጋፊዎቻቸው በኩል ሊቀርቡ የሚችሉ ነገር ግን ለማኅበሩ ኅልውና ስጋት ሊሆኑ እንደሚችሉ ቅድመ ግንዛቤ የተያዘባቸውን አስቀድሞ ውድቅ የማድረግ ስልት መያዙም ሌላኛው እቅድ ስለመሆኑም ይነገራል። በተለይም እንደአባ ሠረቀ ብርሃን ወልደሳሙኤልና መሰል ተቃናቃኞች በምንም ዓይነት መንገድ ቢሆን ከእጩዎች ዝርዝር ውስጥ መግባት እንደሌለባቸው በማኅበሩና ደጋፊ ጳጳሳቱ በኩል በጥቁር መዝገብ ውስጥ የሰፈሩ ናቸው። በሌላ መልኩም ንቡረ እድ አባ ገ/ማርያም ገ/ሥላሴ በሥራ ችሎታና ሙስናን በመዋጋት ጠንካራ ስለመሆናቸው ጥያቄ ባያስነሳም በማኅበረ ቅዱሳን ደጋፊ ሊቃነ ጳጳሳት ዘንድ የማያጎበድዱ፤ ለሹመት ደጅ የማይጠኑና እጅ መንሻ  የማያቀርቡ በመሆናቸው ለእጩነት ችላ ከተባሉት መካከል ናቸው።  
በፓትርያርኩ በኩል ሊቀርቡ የሚችሉና ማኅበረ ቅዱሳን ዓይናቸውን ማየት የማይፈልጋቸው እጩዎችን ላለመቀበል በደጋፊ ሊቃነ ጳጳሳቱ በኩል በሁለተኛነት የተያዘው ዘዴ  ደግሞ «እኛ ምን ሠርተን ነው፤ የአዳዲስ እጩዎች ምርጫ ለማጽደቅ እንዲህ የሚያጣድፈን ምክንያት የለም!»  የሚል ሲሆን ጊዜውን በማዘግየትና የምርጫውን በር በመዝጋት ያልፈለጓቸውን ሰዎችን ለማስቀረት እንደስልት መያዙ ነው።
በሌላ መልኩም ከፓትርያርኩ ስር የማይጠፉ ለዓመታት የጵጵስና ስካር እያንገዳገደ ያቆያቸው አንዳንድ መነኮሳት ሰርገው ለመግባት የሚያደርጉት ሩጫ ሳይጠቀስ መታለፍ የሌለበት ሆኖ ተገኝቷል። ለዚህ ማዕርግ ብቁ ስለመሆናቸው የምዕመናንና ምዕመናት ምስክርነት የሌላቸው እንዲሁም ያለደረጃቸው ካቴድራል የተሰጣቸው ጠልፎ በላዎችና ተሸክመው የመጡትን ዶላር መመንዘር የማይሰለቻቸው ደግሞ ጺማቸውን እየላጉ ጳጳስ ለመሆን ማስፈሰፋቸው ትኩረት የሚያሻው ነገር ነው።  ማኅበሩና ደጋፊ ሊቃነ ጳጳሳቱ በአንድ በኩል ሠርተው ማሰራት የሚችሉትን ወደእጩነት እንዳይቀርቡ በር በመዝጋት ላይ ሲተጉ በሌላ በኩል ደግሞ በጓሮ በር መግባት የሚፈልጉ እንደቅድስት ሥላሴው ጎረምሳ አስተዳዳሪና መሰል የሹመት ስካር የሚያንገዳግዳቸው የችሎታ ባዶዎች አሰፍስፈው መገኘታቸው ጉዳዩን አስቸጋሪም፤ አሳዛኝም፤ አሳፋሪም ያደርገዋል።

ስለዚህ ፓትርያርኩ ተግዳሮት ገጥሟቸዋል ስንል በእነዚህ ውስብስብ እንቅስቃሴዎች የተነሳ ሲሆን መወሰድ የሚገባው ርምጃም ትኩረት የሚያሻው፤ ካለፈ በኋላ የማይቆጭ መሆን ስለሚገባው አበክረን ማሳሰብ እንወዳለን።

አጭር ነገር ግን የትኩረት አቅጣጫን የሚለውጡ ግንዛቤዎች፤

1/ ማኅበሩ እንደፈለገና እንዳሻው በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ የሚናኝ ሆኖ መቀጠል የለበትም። ማኅበሩ ማኅበር እንጂ የቅዱስ ሲኖዶስ ቅርንጫፍ መሥሪያ ቤት ወይም የቤተ ክህነቱ የመምሪያ አካል አይደለም። ሲኖዶስ ስለአንድ ማኅበር ከዓመት ዓመት በአጀንዳ የሚነጋገርበት ምክንያት የለም። ስለዚህ፤
  ሀ/ ቢቻል ራሱን ችሎ ሥልጣን ባለው አካል ሕጋዊ ሰውነት አግኝቶ እንደማኅበር በሀገሪቱ ሕግ እንዲንቀሳቀስ  በነጻ መተው አለበት እንጂ ሲኖዶስ ሕግ አውጥቶለት በራሱ እጅ እየተለበለበ መቀጠል የለበትም።  «ቁጭ ብለው የሰቀሉትን ቆሞ ማውረድ» ያቃተው ለምንድነው? ስለዚህ በዚህ ጉባዔ ፓትርያርኩ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እልባት እንዲያገኝ ማድረግ አለባቸው። በቀጠሮ የነፍስ መግዢያ ጊዜ የሚጠይቁ አፍራሾችን መዋጋት አለባቸው።
 ለ/ ማኅበሩ በኛው ስር ሆኖ ቢሰራ ውጤታማ መሆን ይችላል የሚል ግምት ካለ ( ከታየው ተሞክሮ የተነሳ የተሳሳተ ግምት እንደሆነ ቢታወቅም) የማኅበሩን ያለፈ ታሪክ ገምግሞ ወደፊት ምን ሊሰራ ይችላል በሚል ግንዛቤ ስር ሰፊ ጥናት ተወስዶ በተገደበና በተወሰነ የመተዳደሪያ ደንብ  ተቀርጾ አቅሙን ለክቶ በመስጠት የማያዳግም መቋቻ ሊደረግበት ይገባል።
2/ የእጩ ኤጲስ ቆጶሳትን ምርጫ በተመለከተ፤ ማኅበሩና ደጋፊ ሊቃነ ጳጳሳቱ የያዙት ስልት የራሳቸውን የሲኖዶስ አባላት ቁጥር ከፍ የማድረግና የትኛውንም ውሳኔ በአብላጫ ድምጽ ሙሉ በሙሉ የመቆጣጠር ፖለቲካዊ ስልት ለማስፈጸም የፈለጓቸውን በጥቆማ የማቅረብ ሲሆን በዚሁ ተቃራኒ ደጋፊ ያልሆኑና ለኅልውናቸው ስጋት እንደሆኑ የሚታሰቡትን እጩዎች ደግሞ በልዩ ልዩ መንገድ የመከላከል ሁኔታ አለ። ስለዚህ ይህንን ማጤን አስፈላጊ ነው እንላለን።
3/  በሌላ መልኩም የማኅበሩንና የደጋፊዎቹን እንቅስቃሴ መቆጣጠር ብቻ ሳይሆን በእጩ ምርጫው ዝርዝር ውስጥ ያልተፈለጉ ሰዎች እንዳይገቡ ማድረግ በፓትርያርኩ በኩል እጅግ ትኩረት የሚያሻው ጉዳይ ነው። ስነ ምግባራቸው፤ እውቀታቸው፤ ችሎታቸው፤ የአስተዳደር ብቃታቸው፤ ተሞክሮአቸውና መንፈሳዊ ብስለታቸው ሳይታይ በብልጣብልጥ ዘዴና በገንዘብ አቀባባዮች የተጋነነ መረጃ የተነሳ ኤጲስ ቆጶስነትን ለማሸከም መሞከር ነገ ለሿሚው ኀፍረት፤ ለቤተ ክርስቲያኒቱም ሸክምና ውርደትን ሊያስከትል ስለሚችል የሹመት ስካር ያጠቃቸውን የጥቅምትና የግንቦት ተስፈኞች መከላከል ትኩረት ያሻዋል።

በመጨረሻም ቅዱስ ፓትርያርኩ በማኅበሩ ዙሪያ እየያዙ የመጡት ግንዛቤና ስጋት የመሆኑን ደረጃ የመገንዘብ አቋም የሚደገፍና የሚበረታታ ነው። ቤተ ክርስቲያኒቱ ከማኅበሩ ያለኪሳራ አንዳች አላተረፈችም፤ አታተርፍምም። ማኅበሩ ግን ያለቤተክርስቲያኒቱ ከባህር የወጣ ዓሳ ነው። ስለዚህ የፓትርያርኩ ስልጣን አንድን ማኅበር ጥግ ለማስያዝ የሚያንስ አይደለም። በቤተክርስቲያኒቱ ከፍተኛው የስልጣን እርከን ላይ የተቀመጠ ፓትርያርክ ከሀገሪቱ ሕግ ጋር ተቀናጅቶ የሚያስቸግረውንና ለአስተዳደር እንቅፋት የሆነውን ክፍል በህግ አደብ ለማስያዝ የማንም ጳጳስ የጩኸት እርዳታ አስፈላጊው አይደለም።  
ያለበለዚያ በማኅበሩ ተግዳሮት እየቆሰሉ እስከሞት መቀጠል አለያም አሜን ብሎ እጅ በመስጠት ታማኝ ሆኖ የማገልገል ምርጫ ብቻ ነው ከፊት ለፊት ያለው። አቡነ ጳውሎስን እያታለለ እስከኅልፈታቸው የተዋጋቸው ማኅበር ዛሬም ውጊያውን አላቋረጠም። ግን እስከመቼ?

Saturday, March 15, 2014

«ቅዱስ ኤልያስ ይዞት የመጣውን መጽሐፍ” ቤተ ክርስቲያን እንድትቀበል ተጠየቀ»

 (ምንጭ፤አዲስ አድማስ)
መጽሐፉ ለአቡነ ማትያስና ለጠ/ሚ ኃይለማርያም እንዲደርሳቸው ተደርጓል
ደብዳቤው ለእስራኤሉ ጠ/ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታናሁ እና ለተመድ ተልኳል

       ከተፃፈ ከ2 ሺህ ዓመታት በላይ አስቆጥሯል የተባለውንና ስለ ቅዱስ ኤልያስ መምጣት ምስጢር የሚተነትነውን መጽሐፍ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ተቀብላ ወደተለያዩ ቋንቋዎች በማስተርጎም ምዕመናኖችን እንድታስተምር፣ “ማህበረ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ” ለቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ በጻፈው ደብዳቤ ጠየቀ፡፡
ማህበሩ፤የመጽሐፉን ኮፒዎች ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ እና ለብፁዕ አቡነ ማትያስ  ህዝቡን እንዲያስተምሩበት ከሚያሳስብ ደብዳቤ ጋር መላኩን አስታውቋል፡፡
አርቲስት ጀማነሽ ሰለሞን አባል የሆነችበት ማህበረ ሥላሴ፤“ቅድስት ቤተ-ክርስቲያን ለሁለት ሺህ ዘመን ስትጠብቀው የቆየችውን ምስጢራዊ መጽሐፍ በአደራ የመረከብና ለዓለም ሁሉ የማሳወቅ ፅኑ ኃላፊነትን ይመለከታል” በሚል ርዕስ ለፓትርያርኩ፣ በግልባጭ ደግሞ ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ እንዲሁም ለእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔትናሁ እና ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት በፃፈው  ደብዳቤ “ማህፈድ ብርህት ዘዲዮስቆሮስ አንበሳ” በሚል ርዕስ በግዕዝ ቋንቋ የተፃፈውን መጽሀፍ፣ የቤተ-ክርስቲያኗ ሊቃውንት ተቀብለው ምእመናኑን ስለ ቅዱስ ኤልያስ እና ትክክለኛይቱ ሰንበት እንዲያስተምሩበት አሳስቧል፡፡
ደብዳቤው ለእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር የተላከው ኢትዮጵያና እስራኤል በመንፈሣዊ አሰራር አንድ ስለሚሆኑበት ሁኔታ ለማመልከት ነው ያሉት የማህበሩ አመራሮች፤ለተባበሩት መንግሥታት የተላከውም መልእክቱ ለዓለም ሁሉ እንዲዳረስ ስለሚፈለግ ነው ብለዋል፡፡
ከ2 ሺህ ዓመታት በፊት እንደተፃፈ የሚነገርለት መጽሐፉ፤ ስለ ቀዳሚት ሰንበት ምንነትና ዘለዓለማዊነት በግልፅ እንደሚያብራራ እንዲሁም የኢትዮጵያና የእስራኤልን አንድነትና ትንሳኤ ምስጢር ተንትኖ እንደሚያስረዳ ተጠቁሟል፡፡
ማህበሩ በላከው መልዕክት፣ ቅዱስ ኤልያስ ከብሄረ ህያዋን ይዞት የመጣውን መጽሀፍ፣ የቤተ-ክርስቲያኒቱ ሊቃውንት እንዲመረምሩት፣ በተለያዩ ቋንቋዎች እንዲተረጎምና እንዲታተም፣ ምዕመናንም እንዲያነቡት የማድረግ ግዴታ ፓትርያርኩ እንዳለባቸው ያሳስባል፡፡ “ይህ ሳይሆን በእንቢተኝነትና በቸልታ ለዘመናት በተስፋ የተጠበቀውን ይህን መጽሀፍ እንዳይቀርብ ቢያደርጉ፣ ከብሄረ ህያዋን የመጣው ቀናኢ ነቢይ ዓለምን ሁሉ እየገሰፀ ባለበት ኃያል፣ ስልጣኑ ፅኑ ፈራጅነቱና ቁጣው የሚፈርድ መሆኑን አረጋግጠን እንነግርዎታለን” ብሏል፡፡ “ለቤተ-ክርስቲያኒቱ ሲኖዶስ እና ካህናት ጥፋትና የመጨረሻው ውድቀት ነው” ሲልም ለመፅሃፉ ትኩረት እንዲሰጥ ማህበሩ  አበክሮ አሳስቧል፡፡
በጉዳዩ ዙሪያ የፓትርያርኩን ጽ/ቤት እና የጠቅላይ ሚኒስትሩን ጽ/ቤት በስልክ አግኝተን ለማነጋገር ያደረግነው ተደጋጋሚ ሙከራ ሳይሳካ ቀርቷል፡፡

Wednesday, March 12, 2014

የደብረ ምጥማቅ ሰአሊተ ምህረት ቅድስት ማርያም ካቴድራል የሰንበቴ ማኅበራት ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የተወከለውን ኦዲተር የኦዲት መርኃ ግብር በመቃወም ህገወጥ ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ

በአዲስ አበባ የደብረ ምጥማቅ ሰአሊተ ምህረት ቅድስት ማርያም ካቴድራል የሰንበቴ ማኅበራት ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የተወከለውን ኦዲተር የኦዲት መርኃ ግብር በመቃወም ህገወጥ ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ፡፡ በተለያየ መጥፎ ሥነ ምግባርና ድርጊት ከካቴድራሉ ሰንበት ትምህርት ቤት የተባረሩ ሁለት አባላትን ይዘው በካቴድራሉ ሁለተኛ ሰንበት ትምህርት ቤት ለማቋቋም ከጉርድ ሾላ እና አካባቢ የሰበሰቧቸው ወጣቶች ስለ ሰንበት ትምህርት ቤት አመሰራረት ግንዛቤ የሌላቸው በመሆናቸው የአዲሱ ሰንበት ትምህርት ቤት ምስረታ አልተሳካም፡፡  ቀደም ሲል የሰንበቴ ማኅበራቱ ከሀገረ ስብከቱም ሆነ ከካቴድራሉ አስተዳደር እውቅና ውጪ የሚሸጡትንና በወር እስከ 300.000.00 (ሦስት መቶ ሺህ ብር) ገቢ የሚያገኙበት የቀብር ፉካ ሽያጭ እና የአዳራሽ ኪራይ ንግድ ወይ ለቤተክህነቱ ፈሰስ እንዲያደርጉ አልያም ንግድ ፈቃድ አውጥተው ለመንግሥት ግብር እንዲከፍሉ በሀገረ ስብከቱ የቀረበውን ሐሳብ አልተቀበሉትም፡፡ እናም በመስከረም ወር 2006 ዓ.ም ከጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጁ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ ፤ የቅዱ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ሉቃስ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ በተገኙበት ተመርጦ ሥራ የጀመረውን ሰበካ ጉባዔ አይመራንም፤ እነርሱ ባቀረቡት ጥቆማ መነሻነት ከመንግሥት እና ከገለልተኛ አካላት የተዋቀረው የኦዲት  ኮሚቴ እኛን (የሰንበቴ ማኅበራቱን እና እንደ አቶ ወልዴ የሺጥላ አይነት በሕንጻ አሰሪ ኮሚቴ ገንዘብ ጉድለት የተገኘባቸውንና በቤተክርስቲያኑ ግቢ በቤተልሔሙ ጎን 26 ፉካ በመስራት መናፍቅ ልጆቻቸውን ወራሽ በማድረግ ሕገ ወጥ ሰነድ ያዘጋጁትን) ኦዲት ሊያደርጉ አይገባም በሚል ነጻና ገለልተኛ ቤተክርስቲያን እንመሰርታለን የሚል ፖስተር በመያዝ  እሑድ የካቲት 2 ቀን ጠዋት በቅዳሴ ሰዓት የቅዳሴ ሥነ ሥርዓቱን ለማስተጓጎል ሞክረዋል፡፡
በዚህ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ የሴት ሰባኪ የሆነችውና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሕጋዊ ባሏን ጥላ   ወልዴ የሺጥላ የተባለውን የቀድሞ የህንጻ ኮሚቴ ሊቀ መንበር የወሸመችው እራሷን የዘመኑ የወንጌል አብሳሪ በመንፈስ ቅዱስ የተቀባሁ ጳውሎሳዊት ነኝ በማለት ጸሎተ ፍትሐት አያስፈልግም እኔ በፍትሀቱ ፋንታ ጸሎት አድጋለሁ አስተምራለሁ በማለት ምንፍቅና የምታስፋፋው  ቅድስት አሳልፍ ወደ ቤተክርስቲያኑ ድንጋይ እንዲወረውሩ ተሰብሳቢዎቹን ስታግባባ ነበር፡፡
ከካቴድራሉ ሰንበት ትምህርት ቤት ሴት አባላትን በመተናኮልና ወሲባዊ ጥቃት በማድረስ በሕግ ተከሶ የተቀጣውና ከሰንበት ትምህርት ቤት በዚህ ቅሌት የተባረረው ሰለሞን አጥሌ የተባለው የታክሲ ሾፌርና የሰንበት ትምህርት ቤቱን ገንዘብ በተለያየ ወቅት በመውሰድ በሌብነት ወንጀል ተከሶ ከሰንበት ትምህርት ቤት የተባረረውና ዲቃላ ልጁን ደብቆ ሁለተኛ ሚስት በተክሊል ያገባው የሰለሞን አጥሌ ወያላ የሆነው ሲሳይ አፈወርቅ የተባሉት ሁለት ግለሰቦች መናፍቃንን በማሰባሰብ ሁለተኛ ሰንበት ትምህርት ቤት ለማቋቋም ያደረጉት እንቅስቃሴ አልተሳካላቸውም፡፡
ከዚህ ቀደም በዋነኛነት የሰንበቴ ማኅበራቱንና በመንግሥት ላይ ያኮረፉትን እንደነ ታዋቂውና ጨካኙ የደርግ የምስራቅ  ጎጃም ክፍለ ሀገር አስተዳዳሪና የደርጉ አባል አንሙት ክንዴን አይነት ሰዎችን በማሰባሰብ የደርግ ሥርዓተ ማኅበርን በቤተክርስቲያን ለመመስረት የሚታገለው የደርግ የስለላ ሹም የመቶ አለቃ አባቡ ታከለው በአጣዳፊ ህመም ከሰልፉ ላይ ወጥቶ ወደ ሆስፒታል የተወሰደ ሲሆን ህመሙ ጊዜ የማይሰጥ በመሆኑ እለቱን ኦፕራሲዎን መደረጉንና እስካሁን ከሰመመን እንዳልነቃ ታውቋል፡፡
የካቴድራሉ አስተዳደር በሰንበቴ ማኅበር ስም ተደራጅተው የሚነግዱትን አንዳንድ የደርግ ጡረተኞችና የሰንበቴ አላማ ጠላ ማንቃረርና ቆሎ ማሸርደም የሚመስላቸው ሥራ ፈት አባወራዎችንና የሚገስጻቸው ያጡ ባሎቻቸው የዘነጓዋቸውን እንደነ ቅድስት አይነት መናፍቃንን በቅጡ በመቃወሙና በፍርድ ቤት በተወሰነ ቤተክርስቲያኒቱ  ባወጣችው ሕግ ሕገወጥ ንግድ እና የቦታ ወረራ በመቃወሙ በመረጃ ባልተረጋገጠ ሙስና እና ስም ማጥፋት ሆ ብለን በመጮህ  ከሰን እናስወግዳለን ከሚመጣውም ጋር በመደራደር የፉካ ንግዳችንን እንቀጥላለን በማለት  ለሀገረ ስብከቱ ቅሬታቸውን በሕጋዊ ሽፋን ቢያቀርቡም ሀገረ ስብከቱ በቦታው ያለውን ችግር በዘላቂ ሁኔታ ለመፍታት ከመንግሥትና ከገለልተኛ አካላት  የተመደበው አጣሪ ግን በተጨባጭ በደረሰው መረጃ  እና በተለያዩ ጊዜያት በሰንበቴ ማኅበራቱ በቤተክርስቲኗ የድንጋይ  መአድን ሽያጭ  ባገኙት ገንዘብ በገዟቸው የቢራ አክስዮኖች ባለቤትነት ጉዳይ እንዲሁም እነ ወልዴ የሺጥላ የህንጻ ኮሚቴ ሊቀመንበር መሆናቸውን ሽፋን በማድረግ በሌሎች አብበያተክርስቲያናት ባልተለመደ መልኩ በቤተክርስቲያኗ ግቢ መኖሪያ ቤት በመገንባት እና ለግላቸው 26 ፉካ በመገንባት ለፈጸሙት ምዝበራ ከ1994 ዓ.ም ጀምሮ ኦዲት ለማድረግ በማሰብ ያዘጋጀውን የጊዜ አጠቃቀም መመሪያ በመቃወም ሰልፉን አደራጅተዋል፡፡
 ቁጥራቸው 60 የሚደርሱት እነዚሁ ሰልፈኞች ከያዟቸው መፈክሮች መካከል መንግሥትን የሚተቹ እና አመጹን በማስፋፋት ልክ በእስልምና እምነት በመስኪዶች አካባቢ እንዳለው አይነት ውጥረት ለመፍጠር ቢያስቡም ፖሊስ ደርሶ ሰልፉ እንዲበተን አድርጓል፡፡ በቅርቡ ከአሜሪካ የመጣውና የደህንነት አባል ነኝ በማለት አመጹን የሚያስተባብረው አለማየሁ ከልል  ክሰ ቢመጣ አዘጋላችኋለሁ በማለት ቃል እንደገባላቸው የሰንበቴ ማኅበራቱ አመራሮች አስታውቀዋል፡፡ በዚህ ድርጊት ውስጥ የተሳተፉት ዋናዎቹ ግለሰቦች የተለያየ ችግር ያለባቸው ሲሆኑ አንዳንዶቹ በአጫሽነት ፤ ሰካራምነት ፤ በቃሚነት የሚታወቁ እና በአካባቢ ማኅበረሰብ የእንጨት ሽበት ተብለው የተናቁ ሽማግሌዎች ናቸው፡፡ ይህን አጋጣሚ እንደ መልካም የቆጠሩት አንዳድ ፖለቲካ ኃይሎች ሰልፉን ለማጠናከርና ወደ ውጪ በመውጣት ህዝብን ቀልብ ለመሳብ ቢያስቡም ፖሊስ ግን ይህንን ሊፈቅድ አልቻለም፡፡ ከትግራይ የተመረጠ ፓትርያርክ ቤተክርስቲያኗን ሊመራ አይችልም መንግሥት እጁን ከቤተክርስቲያናችን ላይ ያንሳ ትግሬ ተወላጅ ሰራተኞች ይውጡ በማለት በዋናነት መፈክር ሲያሰሙ የዋሉት አንሙት ክንዴ፤ አስማረ ዋሴ ፤ ባዬ ባዘዘው፤ወልሴ የሺጥላ፤ አበበ ደስታ ፤ መልአከ ኃይሌ ፤ ታደሰ  ፤ ቅድስት አሳልፍ፤ ደሳለኝ ፋንታቢል፤ ወልደኢየሱስ በሻህ ፤ሙሉ በለጠ ሲሆኑ ከወጣቶቹ ደግሞ ሴሰኛው ታክሲ ሾፌር  ሰለሞን አጥሌ እና ሌባው ሲሳይ አፈወርቅ ሲሆኑ እነዚህ የግል ጥቅም ያሳወራቸውና እምነትና ፖለቲካ የተቀላቀለባቸው ግለሰቦች በፖሊስ ክስ እንደተመሰረተባቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡
በሰአሊተ ምህረት ያለው የሰንበቴ አካሄድ ገና ከጅምሩ በ34ኛው አጠቃላይ መንፈሳዊ ሰበበካ ጉባዔ ታላቅ ተቃውሞ የገጠምውና ሲኖዶሱ እልባት እንዲሰጠው በተሰብሳቢዎቹ አቋም የተያዘበትቤተክርስቲያን የምትመዘበርበት መንገድ ነው፡፡ የሰንበቴ ማኅበራቱ ወደ እድርነትና እክስዮን ማኅበርነት በመለወጣቸው እና ከቀብር ፉካና ከአዳራሽ ኪራይ ያገኙትን ገቢ የቢራ አክስዮኖችን በመግዛት ከመንፈሳዊ ተግባት ውጪ የሚያውሉት ሲሆን ለረፈደበት የፖለቲካ ዓላማ ከፍተኛ ገንዘብ እንደሚያንቀሳቅሱ ማወቅ ተችሏል፡፡ የዚህ ድርጊት ዋነኛ መሪ ወልዴ የሺጥላ በኢትዮ ቴሌኮም ሲሰራ በጽዳት ሰራተኞች ላይ በፈጸመው የወሲብ ትንኮሳ በአስተዳደር ተከሶ ከቅርንጫፍሥ አስኪጅነት ወደ ሽያጭ ሰራተኛነት የወረደ ግለሰብ መሆኑ ስለርሱ የሚያውቁት ሁሉ ይመሰክራሉ፡፡
በካቴድራሉ ጉብኝት ያደረጉት ቅዱስ ፓትርያርኩ እና ብፁአን ሊቃነጳጳሳት በሰንበቴ ማኅበራ የተወረረውንና ለብዝኃኑ ጥቅም መስጠት ያለበትን ቦታ እና ግንባታ ተመልክተው ማዘናቸው ታውቋል፡፡ የደብረ ምጥማቅ ሰአሊተ ምህረት ቅድስት ማርያም ካቴድራል ሰፊ የልማት ቦታና በሰንበቴ የተወረረ የቀብር ስፍራ እንዲሁም በሰንበቴ ማኅበራ ቁጥጥር ሥር የሆነ በብዙ ሚሊዮን ብር የሚገመት የድንጋይ ማእድን ሐብት እና ከ100.000 በላይ አማንያን ያሉበት ሲሆን በሰንበቴ የጥቅም ሰንሰለት የተደራጁ ከ60 የማይበልጡ ግለሰቦች ምክንያት ሰላሙን አጥቶ የቆየ ደብር ነው፡፡

Wednesday, January 29, 2014

የሶርያ ክርስቲያኖች በአሸባሪዎች እየተገደሉ፤ እየተሰደዱ፤ ገዳማትና አድባራት እየወደሙ ናቸው!




በዴር አልዙር የሚገኘው የሶርያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፍርስራሽ
ክርስትና በደም ተመስርታ፤ በፈተና ወጀብና ማዕበል እየተገፋች እነሆ ዛሬ ላይ ደርሳለች። ዓለም አንድ መንደር ሆናለች፤ ህግና ህግ ብቻ ዓለምን ይመራታል በተባለበት በ21ኛው ክ/ዘመን ላይም ክርስትና ሞትና የእሳት አደጋ አልተለያትም። 

የሚገርመው ደግሞ ክርስትና በእጇ የሚገኘውን መጽሐፍ ቅዱስ ይዛ ከመጓዝ ባሻገር ለእምነቷ መስፋፋት ጦርና ሰይፍ የማትመዝ ቢሆንም ባላጋራዎቿ እንዳትመጣባቸው ለመከላከል ሲሉ ወይም ከመጣች በኋላ ለማጥፋት ሲሹ በተቃራኒው ሰይፍና ጦር እየመዘዙባት ዘመናትን ማስቆጠሯ ነው።
 ይህንን መከራ ካሳለፉት ጥንታውያን አብያተ ክርስቲያናት መካከል የሶርያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን( የአንጾኪያ) ወይም ያዕቆባዊት ቤተ ክርስቲያን  ግንባር ቀደሟ ቤተ ክርስቲያን ናት።  በሐዋርያት ሥራ 11፤26 ላይ እንደተመለከተው «ሐዋርያት በመጀመሪያ ክርስቲያን ተባሉ» የሚለውን ቃል የክርስትናቸው መነሻ አድርገው የሚቆጥሩት ሶርያውያን ክርስቲያኖች፤ በሮማውያን፤ በፋርሶችና፤ በቱርኮች ወረራ ብዙ ግፍና መከራ ያሳለፉ ሲሆን ሶርያ ወደእስላማዊ ግዛት በእስላም ወረራ ከተለወጠችበት ጊዜ ጀምሮ ስቃይና ፈተናው ተጠናክሮ እንደቀጠለ ታሪክ ይነግረናል። ሀገሪቱ በአላዋይት የእስልምና ጎሳ በምትመራበት ዘመን የተሻለ ሰላም የነበራት የሶርያ ቤተ ክርስቲያን ዐረባዊ ዐመጽ በዐረብ ሀገራት ከተቀጣጠለ ጊዜ አንስቶ ግን ሰላም ርቋት፤ ገዳማቷ ፈርሰው፤ መነኮሳትና መነኮሳይያቷ ተገድለው፤ ክርስቲያኖቿ ተሰደው፤ አድባራቷ ተቃጥለው ዛሬ ላይ ወደመጥፋት ከተቃረቡት ጥናታዊ አብያተ ክርስቲያናት መካከል አንዷ ወደመሆን ደርሳለች።
በሰሜን ሶሪያ ወናውን የቀረው ገዳም

በቁስይር የሚገኘው የሶርያ ቤተ ክርስቲያን
 እስካሁን በዓለም አቀፍ አኀዛዊ መረጃ መሠረት 400, 000 ክርስቲያኖች የተወለዱበትንና ያደጉበትን ቀዬ ለቀው እግራቸው ወደመራቸው ተሰደዋል። 60 ትላልቅ ጥናታውያን አድባራትና ገዳማት ተቃጥለዋል። ከዚህ ውስጥ ለአብነት የሚጠቀሰው የጦርነቱ ቀውስ በክርስቲያኖቹ ላይ ያደረሰው በደል በታህሳስ ወር መጨረሻ ገደማ ላይ 13 መነኮሳይያት ጦርነቱን ሸሽተው ከተሸሸጉበት ገዳም ውስጥ እጃቸው በጽንፈኞቹ ተይዞ እንደመደራደሪያ መሣሪያ መቆጠራቸው አይዘነጋም። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሱኒ/ወሀቢዝም ጽንፈኞች ባሉበት ቦታ ሁሉ ከሳዑዲ ጋር ከጀርባ የማትጠፋው ኳታር ከሊባኖስ መንግሥት ጋር ባደረገችው ሽምግልና አሸባሪዎቹ በመነኮሳይያቱ ላይ ምን ጉዳት እንዳያደርሱና እንደመያዣ መጠቀማቸውን አቁመው በነጻ እንዲለቋቸው በማግባባቷ መለቀቃቸውን የሊባኖሱ ዴይሊ ስታር መዘገቡ አይዘነጋም። ይህንኑ ዘገባ  የኳታሩ «አልጀዚራ ሙባሸር» ቴሌቪዥን መነኮሳይያቱን በምስል በማሳየትም ጭምር የኳታርን ትስስርና የማንነት አቅም መረዳት ችለናል።
በኳታሩ አልጀዚራ ሙባሸር ቲቪ ከቀረቡት የታፈኑ መነኮሳይያት በከፊል

    ይህ በዚህ እንዳለ ብዙ ሶርያውያን ክርስቲያኖች በዚያው ያሉ ሲሆን፤ የሚመጣውን ሞት ለመቀበል የተዘጋጁ መነኮሳይያትና መነኮሳት ከሶርያ ገዳማት እስካሁን አልወጡም። ከእነዚህ መካከል አንዱ የሆኑት ፋዘር ኢዮአቄም የተባሉት ካህን ለሚዲያ እንደገለጹት የሚመጣውን ሁሉ እዚሁ ሆኜ ከመቀበል በስተቀር የትም ለመሄድ አልተዘጋጀሁም። አያይዘው እንደተናገሩት «የሶርያ ክርስቲያኖች ስደትና እንግልት ግን ልቤን ያደማዋል፤ ይህ ሁሉ ለምን ሆነብን? እያልኩ አምላኬን እጠይቃለሁ» በማለት የተሰማቸውን መንፈሳዊ ስብራት ለጋዜጠኞች ገልጸዋል።

«ሞቴን እዚሁ እጠብቃለሁ» ፋዘር ኢዮአቄም ሶርያዊ መነኩሴ
የሶርያ ክርስቲያኖች እየደረሰባቸው ያለው እንግልትና መከራ ትኩረት አግኝቶ ዓለም አቀፍ ክርስቲያኖች ሁሉ ከጎናቸው በመቆም ለችግራቸው በአፋጣኝ እንዲደርሱ የሚያሳስብ ጉባዔ በአሜሪካ የተደረገ ሲሆን በተለይም ምሥራቃውያን ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ፕሮግራሙን በጸሎትና እየጠፉ ላሉት ክርስቲያኖች እንድረስላቸው የሚል ጥሪ በማስተጋባት ማሰማታቸው ታውቋል። ይህንንም ተከትሎ የአሜሪካ መንግሥት በጎረቤት ሀገሮች ላይ ጫና በማሳደር የበኩላቸውን ሚና እንዲጫወቱ የሚያሳስብ መልዕክት እንድታስተላልፍ ጥሪ የቀረበላት ሲሆን ሳዑዲና ኳታርም የበሽር አልአሳድን መንግሥት በመጣሉ ዘመቻ ላይ ባላቸው ድርሻ ተዋጊዎቹ በክርስቲያኖች ላይ የሚያደርሱትን ጥቃት እንዲያቆሙ ጥሪ ቀርቧል።
ወሀቢያዊና ሰላፊያዊ  የዐረብ ዐመጽ ከተነሳ ወዲህ በዐረብ ሀገራት የሚገኙ ክርስቲያኖች መከራ፤ስደትና ሞት ከመቼውም ጊዜ የከፋ ቢሆንም እስካሁን የተደረገው ድጋፍ እዚህ ግባ የሚባል አይደለም።
አሸባሪዎች በሶርያ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ


  ከዚህ በፊት የሶርያ፤  አሌፖ ከተማ ሊቀጳጳስ ፖል ይዚጊ በአሸባሪዎቹ ታፍነው ከተወሰዱ በኋላ በብዙ ድርድር ሲለቀቁ በሶርያ የፍራንሲስካን ቄስ የነበሩት  ፍራንሶይስ ሙራድ የተባሉት ደግሞ አቡ ባናት በተባለው የአሸባሪዎቹ አለቃ ሌሎች ሦስት ሰዎችን ጨምሮ በሰይፍ« አላሁ አክባር» እያለ እንዳረዳቸው መረጃዎች ያሳያሉ። በኢራቅም ከነበሩት ክርስቲያኖች ውስጥ በመቶ ሺዎች ሀገራቸውን ለቀው ተሰደዋል። በግብጽ፤ በቱኒዚያ ያሉት ክርስቲያኖችም ለመኖር የሚያበቃ መንግስታዊ ጥበቃ ስለሌላቸው እየተሰደዱ ይገኛሉ። 
ከቀኝ ወደግራ በሁለተኛው ረድፍ የሚገኘውና አቡ ባናት (የእስላም ሴቶች አባት) የተባለው የአሸባሪዎቹ አለቃ ቄስ ፍራንሶይስ ሙራድንና ሁለት ዲያቆናትን በሰይፍ ያረደ

 የምሥራቅ ኦርየንታል ቤተ ክርስቲያን አባል የሆነችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዓለም ላይ መከራና ሞት ለሚደርስባቸው ክርስቲያኖች በዘወትር ጸሎቷ እንደምታስባቸው ቢታወቅም በኦፊሴል የጸሎትና የዓለም ክርስቲያኖች ኅብረት ለተጎጂዎች በፍጥነት እንዲደርስ ማሳሰብ ብትችል መልካም ነበር። በተለይም በአሁኑ ሰዓት ገዳማትና አድባራቷ እየወደሙ፤ክርስቲያኖቿ እየተሰደዱ፤ እየታረዱ፤ ለምትገኘው ለሶርያ ያዕቆባዊት ቤተ ክርስቲያን፤  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እንደአኀት ቤተ ክርስቲያንነቷ አጋርነቷን አለማሳየቷ ያሳዝናል። 
የክርስትና ምልክት መስቀል አንገታቸው ላይ በመገኘቱ ብቻ ክርስቲያኖች በገፍ እያተረዱ ነው

ለሶርያ ቤተ ክርስቲያን ሀዘንና ድምጽን ማሰማት የፖለቲካው ክፍል ፈቃድ የሚያስፈልገው ሳይሆን የክርስቶስን አገልግሎት መፈጸም መሆኑ መታወቅ ይገባዋል። በሶርያ ቤተ ክርስቲያን ላይ የእጅ አዙር መንግሥታት ሰይፍና ጦር ሲልኩ ያላፈሩ እኛ በጸሎትና በድምጽ ክርስቲያን ወንድሞቻችንን ለማጽናናት የሚያስፈራን ነገር ሊኖር ባልተገባ ነበር። እዚያ ያለው እሳት ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳይመጣ ድምጻችን መሰማት ያለበት ዛሬ ነው።

Saturday, January 18, 2014

የማኅበረ ቅዱሳን የግል ጋዜጦች ዘመቻና የሐራ ተዋሕዶ ጭቃ ሹምነት የትም አያደርስም!!





ደጀ ሰላም የተባለችው የማኅበረ ቅዱሳን ብሎግ ከተዘጋች በኋላ የጭቃ ሹምነቱን ሥልጣን የተረከበችው «ሐራ ዘተዋሕዶ» ብሎግ አንድም ቀን ተሳስታ ነገረ ወንጌል ሳታስተምር በነገረ ወሬ ጫሪነቷ እነሆ አንድ ዓመቷን አከበረች። የሐራ ዘተዋሕዶ ብሎግ አገልግሎት በወሬ ነጋሪነት ላይ ጊዜዋን የማጥፋቷ ምክንያት በማኅበሩና በዙሪያው ስላሉት የመርሃ ስብከት መልእክት በሙሉ «በማኅበረ ቅዱሳን» ዋናው ድረ ገጽ ስለሚተላለፍ «ሐራ» ስለወንጌልና ስለማኅበሩ አዳዲስ ዜና መዘገብ አይጠበቅባትም። ይህ የሚያሳየው የማኅበሩ  አመራር ቁጭ ብሎ እንዴት መተላለፍ እንዳለበትና ምን መተላለፍ እንደሚገባው በደንብ የመከረበት መሆኑን ያሳያል።
 ሰሞኑን ደግሞ በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ላይ ለመቸከል ያዘጋጁትን የአፈና እቅዳቸው መግቢያ መንገድ ይሆን ዘንድ የነደፉት የጥናትና ስትራቴጂ መርሃ ግብር በሐራ ዘተዋሕዶ ላይ  ብቻ እየለቀለቁ ዜና መስራት ስላቃታቸው የግል በተባሉ ጋዜጦች ላይ የጥናት ጩኸታቸውን ማስተጋባት ከጀመሩ ሳምንት አልፏቸዋል። ሐራ ደግሞ በማኅበሩ አባላት በጋዜጦች ላይ የወጡትን ዜና ወዲያው እንደ አዲስ ዜና ተከትላ ትለጥፋች።

ማኅበሩ የጳጳሳት አባላት ብቻ ሳይሆን በህክምና ሆስፒታሎች፤ በፌዴራል ፖሊሶች፤ በፍርድ ቤቶች፤ በትምህርት ሚኒስቴር፤ በመንገድ ትራንስፖርትና በመሳሰሉት መንግሥታዊ ተቋማት ውስጥ በግልጽና በስውር የሚሰሩ ምልምል አባላት እንዳሉት እርግጥ ነው።በግል ጋዜጦች ላይ የሚሰሩ አባላቱም በስም ጭምር የሚታወቁ እንዳሉም የአደባባይ ምስጢር ነው። ስለሆነም በፈለገው ጊዜ የፈለገውን መረጃና ዜና በፈለገው ጋዜጣ ላይ ለማውጣት የሚቸገር ባለመሆኑ የመረጃ መረቡን በቂ ሽፋን መስጠት ያቃታትን «ሐራ ዘተዋሕዶ» ብሎግን ለማስተንፈስ በስመ ነጻ ሚዲያዎች ላይ ያቀረበውን ጥናት ለመተግበር እንዲቻልና  ተፅዕኖ ለማሳረፍ ሲል በስመ አባ እስጢፋኖስ፤ በስመ ሰንበት ተማሪ አለያም ማን እንደዘገበው ስም ሳይገለጽ ጋዜጣ ላይ እንዲለቀለቅ ለማድረግ ውጣ ውረድ የለበትም።


በእርግጥ በስመ ነጻ ሚዲያ የሚታተሙት የኢትዮጵያ ጋዜጦች አብዛኞቹ ይህንን ያህል ትኩስና የአንባቢን ቀልብ በሚስብ መረጃ በቂ ልምድና ብቃት ያላቸው ስላልሆኑ ከጊዜ ማሳለፊያ ዜናነት ባለፈ ለማኅበረ ቅዱሳን ጥረት ውጤታማ ጎን ያስገኛሉ ተብሎ አይጠበቅም። ግማሾቹ የፕሬስ ህጉን ስለሚፈሩ እንደዱሮው በሬ ወለደ ብለው በመጻፍ ጉድ፤ ድንቅ የሚያሰኝ ፈጠራ ላለማቅረብ ራሳቸውን በራሳቸው ሳንሱር በማድረግ የተቸገሩ ናቸው። ገሚሶቹም «አቶ እንትና ተከሰሰ፤ ወ/ሮ ብሪቱ ቲማቲም ሸጠው ትርፋማ ሆኑ፤ ዓለማየሁ አዲስ ሆቴል ከፈተ » በሚል የተለመደ ዜና የሚውተረተሩ ስለሆነ የማኅበረ ቅዱሳንን የጥናት ወረቀት ተቀብለው ዜና ቢሰሩ ለጊዜ ማሳለፊያነት ማንበብ ከሚቻል ውጪ በዚያ ንባብ ስለጥናቱ የድጋፍ ይሁን የተቃውሞ ሰልፍ የሚወጣ እንደሌለ በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል። ብዙዎቹም /tabloid /ወሬና ጭምጭምታ በመለቃቀም፤ የኮከብ ቆጠራና ታሮት በመተረክ፤ ስሜታዊ ፈጠራ ላይ የሚያተኩሩ ናቸው። society reporting/ ማኅበራዊ ዜና የሚሰሩ፤ ስለምግብ፤ ፋሽን፤ ስለቁንጅና የሚተርኩ ናቸው። comedic 
/ ዋዛና ፈዛዛ፤ ቀልድና ቧልት የሚዘግቡ ሲሆኑ በተወሰነ መልኩ gonzo journalism / የተሻለ ምልከታ አለው። ራሱ የመረጃው ምንጭ ሆኖ በመጀመሪያ ረድፍ የሚዘግብ ሲሆን በያዘው አሳማኝ ጭብጥ ለመረጃው ኃላፊነትን የሚወስድ ነው። አሉ፤ ሰማሁ፤ ሰዎች ነገሩኝ አይልም።  /Investigative journalism/ የምርመራ ጋዜጠኝነትን ባህል የተከተለ ጋዜጣ ኢትዮጵያ ውስጥ የለም ብቻ ሳይሆን አይታሰብም። ታዲያ ከዚህ አንጻር የማኅበሩ ስውር ጋዜጠኞች ጽሁፍ በደረጃ በየትኞቹ ጋዜጦች ላይ የሀ/ስብከቱን የጥናት አስፈላጊነት አከታትለው አወጡ ብለን ብንጠይቅ ግልጽ መልስ አናገኝም።  በቃ ዜና ሆኖ መውጣቱ ብቻ በቂያቸው ነበርና ለማውጣት ማውጣት በቻሉት ጋዜጣ ላይ ሁሉ ዜና ሆኖ እንዲወጣ ደክመዋል። ውጤቱ ድካም ሆኖ መቅረቱ ግን ያሳዝናል።

ምናልባት 50 ሚሊየን ተከታይ አለኝ የምትለዋን ቤተ ክርስቲያን የሚመሩት ሹመኞች «አንድ ለእናቱ» የሆነውና ያውም በየወሩ አንዴ ከሚታተመው «ከዜና ቤተ ክርስቲያን» ውጪ ለጋዜጦች ዜና ባይተዋር ስለሆኑ ዛሬ ምን ተባለ? አዲስ አድማስ ምን ይዞ ወጣ? በማለት እንደአዲስ የመረጃ ምንጭነት የጽሁፉ ስውር ባለቤት የሆነው  ማኅበሩ እንደአዲስ ግኝት ሲነግራቸው በመባነን ተደንቀው ከሚያነቡት በስተቀር ለማኅበሩ የዜና ስራ ድካም አንዳች ትርፍ ለማስገኘት የሚችል ተጨባጭ ነገር እንደሌለው እርግጥ ነው።
«ድከም ያለው ውሃ ይወቅጣል» እንዲሉ ማኅበሩ አንዴ በሐራ ተዋሕዶ፤ አንዳንዴ በግል ጋዜጦች፤ አንዴ በሰንበት ተማሪዎች፤ አንዴ በጥምቀት ተመላሾች፤ ሌላ ጊዜ በጳጳሳት በኩል የሚወጣ፤ የሚወርደው ለአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ተጨንቆ ሳይሆን የራሱን መዋቅር በሀ/ስብከቱ ችግር አስታኮ ለመዘርጋት ከማለም የመነጨ ስለሆነ እንደታወቀበት ስንነግረው ፈጽሞ አይገባውም። 


አሁን ደግሞ የያዘው አዲስ ስልት ፓትርያርኩን በውዳሴ ከንቱ ጠልፎ በአንድ ጀንበር የጥናቱን ተአምር ለማሳየት ተዘጋጅተዋል የምትል ዜና ደጋግሞ ማሰማት ጀምሯል። ወደኋላ ያፈገፍጉብኛል ብሎ ስለሰጋ ብርታት ሰጪ የምስጋና መርፌ እየወጋ መሆኑ ነው። ቤተ ክህነትን በማኅበሩ ያስወረራት የሚያዥጎደጉደው ውዳሴ ከንቱ፤ ጥቅማ ጥቅምና በስለላ የሚሰበስበው የግለሰቦች የነውር ፋይል ናቸው። ስለዚህ ፓትርያርክ ማትያስ ቤተ ክርስቲያኒቷ ያለማንም ጣልቃ ገብነት በራሷ ልጆች፤ በራሷ ሊቃውንት፤ ለራሷ የሚሆን ሕግ ማውጣት ትችላለችና ማኅበሩ በግል ጋዜጦች፤ በወጣቶችና በጳጳሳት በኩል ጫና ለማሳደር የሚያደርገውን ዘመቻ እንዳይፈሩ እናሳስባለን። የማኅበረ ቅዱሳን የጋዜጦች ላይ ዘመቻና የሐራ ዘተዋሕዶ የጭቃ ሹምነት የትም አያደርስም!!

Saturday, January 11, 2014

የእግዚአብሔር መንፈስ እንዲያድርባችሁ ሳር ጋጡ የተባሉ ደቡብ አፍሪካውያን ሳር ሲግጡ ዋሉ!!

የፍጻሜው ዘመን የተቃረበ ይመስላል። ጤናማ አእምሮና በማኅበራዊ ኑሮው ሰላማዊ የነበረ ሕዝብ እንደጋማ ከብት ሳር እንዲግጥ ሲታዘዝ  ሲበላ ዋለ ማለት እጅግ ያስገርማል። ነገሩ በእርግጥ ሆኗል። በደቡብ አፍሪካ ፤ ጋራኑካ በተባለች ከተማ ውስጥ  የተቋቋመችውና ከ1000 በላይ ተከታዮች ያሏት ማኅበር መሪ የሆነው ፓስተር ሌሴጎ ዳንኤል የስብከት መርሐ ግብሩን እንደፈጸመ መገለጥ መጥቶልኛልና ከአዳራሽ ወጥታችሁ የሜዳውን ሳር ጋጡና በመንፈሰ እግዚአብሔር ትሞላላችሁ ባላቸው መሰረት ትእዛዙን ተቀብለው ሳር ለመጋጥ መሰማራታቸውን «ክርስቲያን ፖስት» ጋዜጣና «ቺካጎ ዲፌንደር» ዘግበዋል።


   ግማሹ ሳሩን አጎንብሶ እንደከብት እየጋጠ፤ ገሚሱ ደግሞ እንደጭላዳ ዝንጀሮ እየነጨ ሳሩን ሲበላ የዋለ ሲሆን የሰው ጭላዳ ከሆኑት መካከል አንዷ የሆነችው የ21 ዓመቷ የህግ ተማሪ ሮዝመሪ ፔታ ለጋዜጠኞች እንደተናገረችው «ሳሩን በመጋጤ ለአንድ ዓመት ያህል ሲያሰቃየኝ ከነበረው ከጉሮሮ ቁስለት በሽታ ተፈውሻለሁ» በማለት ያገኘችውን አስደናቂ ተአምርና የሳር መጋጡን ጠቃሚነት የገለጸች ሲሆን የ27 ዓመቷ ዶሪን ጋትል የተባለችው ደግሞ እንዲህ ስትል ስለተደረገላት ተአምር ያገኘችውን ጥቅም ገልጻለች። «በነበረኝ የስትሮክ በሽታ እግሮቼን ላለፉት ሁለት ዓመታት ማንቀሳቀስ ተስኖኝ ነበር። ሳር ብትበሉ በመንፈስ ትሞላላችሁ፤ በማለት ስለሳር መብላት አስፈላጊነት ፓስተሬ ባዘዘኝ ጊዜ በመብላቴ ከበሽታዬ በፍጹም ድኜ እነሆ በሁለት እግሬ ለመሄድ በቅቻለሁ» በማለት ስለተደረገላት ተአምር ለሚዲያ ተናግራለች።

  ይሁን እንጂ የሁለቱንም ሴቶች አባባል የሰሙ ታዛቢዎች በአባባላቸው ስቀዋል። ጤንነታቸውንም ተጠራጥረዋል።  ይህ የማይታመን ቀልድና በእግዚአብሔር ስም ማላገጥ ነው። መንፈስ ቅዱስ እንዲያድርብን ሳር አጎንብሳችሁ ጋጡ ተብለናል የሚሉት ጉዳይ የግድ መቆም ያለበትና ለህብረተሰቡ በመጥፎ አርአያነቱ ካልሆነ በመልካምነቱ የሚታይ አይደለም በማለት የተመለከቱ ታዛቢዎች ተቃውሟቸውን ገልጸዋል ። የሰው ልጅ ሲፈጠር እንደእንስሳ ሳር ለመጋጥና ለመፍጨት የተዘጋጀ የሰውነት አወቃቀር ስለሌለው የተደረገው ነገር ሁሉ ከክርስትና ሃይማኖት ጋር የማይገኛኝና መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሰረት የሌለው በመሆኑ ድርጊቱን እንቃወማለን ሲሉ ስለሳር ጋጮቹ ተናግረዋል።

 ከዚሁ ጋር ተያይዞ ስለሳር መጋጡ ውሎ እንደተዘገበው፤ በመስኩ ላይ ተሰማርተው ሳር ሲግጡ ከዋሉት የሰው ጭላዳዎች መካከል አብዛኛዎቹ ሲያስመልሳቸውና ሲሰቃዩ የዋሉ ሲሆን ገሚሶቹ መብላት አቅቷቸው ሲያለቅሱ ታይተዋል። አንዳንዶቹም ሆዳቸውን ታመው ህክምና እስኪደርስላቸው ድረስ መታመማቸውም ታውቋል። ከዚህ በፊትም ፓስተር ሌሴጎ ዳንኤል በአዳራሹ ውስጥ የተገኙ ተከታዮቹን በጥፊ እንዲጠፋጠፉ ባዘዛቸው ጊዜ ትእዛዙን ተቀብለው፤  ጉንጫቸው ድልህ እስኪመስል በጥፊ መጠዛጠዛቸውም ተዘግቧል።

እንደሚታወቀው ሳር በመጋጥ እንደእንስሳ ይሆን ዘንድ ከእግዚአብሔር ትእዛዝ የወጣበትና ልቡ የተሰወረበት ናቡከደነጾር እንደነበረ መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል።  ናቡከደነፆርም ለዚህ የበቃው በትምክህቱና በትዕቢቱ እንጂ ለበጎ ተግባሩ የተሰጠው ልዩ ጸጋ አልነበረም። እና ታዲያ የዘመኑ ሰዎች እንደናቡከደነፆር ወደእንስሳነት ወርደው ሳር በመጋጣቸው የናቡከደነፆር ቤተሰቦች የማይሆኑበት ምክንያት ይኖር ይሆን?
«ልዑሉም በሰዎች መንግሥት ላይ እንዲሠለጥን፥ ለሚወድደውም እንዲሰጠው እስክታውቅ ድረስ ከሰዎች ተለይተህ ትሰደዳለህ፥ መኖሪያህም ከምድር አራዊት ጋር ይሆናል እንደ በሬም ሣር ትበላ ዘንድ ትገደዳለህ፥ ሰባት ዘመናትም ያልፉብሃል አለው» ዳን 4፤32

Sunday, January 5, 2014

የምስካየ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም ሰራተኞች አስተዳደሩን አማረሩ


 (የጽሁፍ ምንጭ፤ አዲስ አድማስ )
በገዳሙ እንክብካቤ እንጂ ጭቆናና እንግልት የለም /የገዳሙ አስተዳደር/
የምስካየ ህዙናን መድሀኒያለም ገዳም ሰራተኞች በቤተ - ክርስቲያኑ አስተዳደር ከፍተኛ ጭቆናና በደል እንደሚደርስባቸው ተናገሩ፡፡ የቤተክርስቲያኑ አስተዳዳሪ መላዕከ ገነት አባተክልማርያም አምኜ የገዳሙን ሰራተኛየ ሚያስተዳድሩት እንደመፈንሳዊ አባት ሳይሆን እንደ አምባገነን መሪ ነው ሲሉ ሰራተኞቹ አማረዋል የቤተክርስቲያኑ አስተዳዳሪ አባ ተ/ማርያም አምኜ በበኩላቸው በቤተክርስቲያኒቱ ሁሉም ስርዓትና ደንብን ተከትሎ እንጂ ያለ አግባብ የሚንገላታም የሚጨቆንም የለም ሲሉ መልሰዋል፡፡ “ቤተክርስቲያኑ የሚመራው በፓትሪያርኩ ነው” ያሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ የደሞዝ ማነስን ተከትሎ እንዲያነጋግሩን አባ ተክለ ማርያምን ለስብሰባ ጠርተን እግረ መንገዳችንን የገዳሙን የመልካም አስተዳደር ችግር፣ እርሳቸው ያለ አግባብ የሚሰሯቸውን ስራዎች፣ እና አጠቃላይ ያለውን ችግር አስረዳናቸው ይላሉ ቅሬታ አቅራቢዎቹ፡፡
ይሁን እንጂ ለምን አካሄደን ተቃወማችሁ በሚል በግል እየጠሩ ማስፈራሪያና ዛቻ ያቀርቡብናል ለአንዳንዶቻችን ያለ አግባብ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ተፅፎብናል ብዙዎችም ከስራ ተባረዋል ብለዋል የገዳሙ ሰራተኞች፡፡ አስተዳዳሪው ወደ ገዳሙ ተሹመው ከመጠ አንድ አመት ከስድስት ወር ቢሆናቸውም እስከዛሬ በቤተክርስቲያኑ አንድም ልማት እንዳላካሄዱ የገለፁት ቅሬታ አቅቢዎቹ ችግር አለ ይስተካከል በማለት ቅሬታ የሚያርበውን ሁሉ እንደጠላት በማየት ሊመደብ ወደማይገባው ቦታ ይመድባሉ፣ ከደረጃ ዝቅ ያደርጋሉም ብለዋል፡፡ ቤተክርስቲያኒቷ ያለ አግባብ እየተመራች ነው ሰራተኞቹ እየተንገላቱ ነው በሚል ቅሬታ ያቀረበውና የቤ/ክርስቲያኑ ጉዳይ አስፈፃሚ የነበረውን መምህር ሰለሞን ተስፋዬን ከስራው አንስተው ሙያው ወደማይፈቅደው የገዳሙ ክሊኒክ እንደመደቡትና በዚህም ለገዳሙ የቦርድ ሊቀመንበር አመልክቶ ጉዳዩ እየታየ ባለበት ከስራ እንዳባረሩት ቅሬታ አቅራቢዎቹ ተናግረዋል፡፡
የቤተክርስቲያኑ አስተዳዳሪ አባ ተክለማሪያም በጉዳዩ ዙሪያ ተጠይቀው ሲመልሱም ሰራተኞቹ የደሞዝ ጥያቄ ባነሱ ጊዜ ባለፈው ሀምሌ ጨምረናልም ምግብ መጠለያና ሁሉን አሟልተን ይዘናችሁ እንዴት አሁን የጭማሪ ጥያቄ ታነሳላችሁ ብለናቸዋል ይላሉ፡፡ የመምህር ሰለሞንንን ከስራ መባረር በተመለከተም “ወደ ክሊኒኩ ያዛወርነው በእድገትና በሁለት እርከን የደሞዝ ጭማሪ ነው” ያሉት አስተዳዳሪው ጉዳዩን አምኖበት ስራውን ከተረከበ በኋላ ማንም ሳያውቅ ዘግቶ በመጥፋቱ ሊሰናበት ችሏል ብለዋል፡፡ ማስጠንቀቂያውን በተመለከተ ለአንድ ሰራተኛ መስጠቱን አምነው “ቤተክርስቲያኗ ሲኦል ናት” በሚል ለተናገረው ንግግር ማስጠንቀቂያ መስጠታቸውን ተናግረዋል፡፡ የገዳሙ ክሊኒክ መካከለኛ ሆኖ ሳለ አልትራ ሳውንድ ይጠቀማሉ፡፡ ይህ ክልክል ነው በሚል ቅሬታ አቅራቢዎቹ የተናገሩ ሲሆን “በፊት እንጠቀም ነበር አሁን ተከልክለን አቁመናል” ብለዋል አባ ተክለማሪያም አምኜ፡፡ “የቤተክርስቲያኗን ስም ለማጥፋት የሚንቀሳቀሱ ሀይሎች እንዳሉ እናውቃለን” ያሉት አስተዳዳሪው በገዳሙ ያሉ እስረኞች በእንክብካቤ ተያዙ እንጂ በአንዳቸውም ላይ ጭቆናና እንግልት አላደረስንም ብለዋል፡፡

Friday, January 3, 2014

አዲዮስ ማኅበረ ቅዱሳን፤ አዲዮስ!!



ስጳኛውያን ደህና ሰንብት፤ ደህና ሁን! ብለው ሲሰናበቱ «አዲዮስ!» ማለት ልምዳቸው ነው። እኛም ይህንን ቃል ተውሰው ሲናገሩ እንደቆዩት አበው ዛሬም ለማኅበረ ቅዱሳን «አዲዮስ» ብለነዋል።
መነሻ ምክንያታችን ሁለት ነው።
1/ ማኅበሩ ራሱ እያደገ ከመጣበት የኢኮኖሚ አቅምና የመዋቅር ስፋት አንጻር በቤተ ክርስቲያኒቱ ስር ተጠልሎ ያለስጋት መዝለቅ እንደማይችል በመረዳቱ  ወደ «ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ድርጅት» ወይም ሼር ካምፓኒ የመዛወር ፍላጎት እንዳለው ውሰጥ አወቅ ምንጮች በመጠቆማቸው የተነሳ ይህ እውን ከሆነ ለዓላማው ስኬት የምንሰጠው ድጋፍ «ማኅበረ ቅዱሳን አዲዮስ» በማለት ነው። Good bye MK!!
2/ በ23/ 4/2006 ዓ/ም  በጠቅላይ ቤተ ክህነት አዳራሽ ከፓትርያርኩ ጋር ተገናኝተው በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ላይ ሊተገበር በተፈለገው የማኅበረ ቅዱሳን ድርጅታዊ ጥናት ላይ የቀረበው የአስተዳዳሪዎችና የማኅበረ ካህናቱ ተወካዮች የተቃውሞ ሃሳብ ማኅበረ ቅዱሳን ከቤተ ክርስቲያን ታዛ ተገፍትሮ የመውጣቱን የጅማሬ ያመላከተ በመሆኑ «አዲዮስ ማኅበረ ቅዱሳን» ብለነዋል።
3/  በማኅበረ ካህናቱ መካከል ካለን መረጃ አንጻር ከዚህ በፊት «የማኅበረ ቅዱሳን መግነንና ብቀላ መሳ ለመሳ ናቸው፤ እንደጠዋት ጤዛም ቀትር ላይ ይጠፋሉ!» በሚል ርዕስ ባወጣነው ጽሁፍ ላይ እንደዚህ የሚል ቃል ጠቅሰን ነበር።
« ምናልባትም የማኅበረ ቅዱሳን በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ውስጥ የማቡካት የመጋገር ጅማሮ የማኅበሩን ዕድሜ ቀጣይነት ወሳኝ ምዕራፍ ከፋች ሊሆን እንደሚችል ይገመታል። በሂደት የምናየውም ይሆናል» (የጥቅሱ መጨረሻ)
ይህንን ጽሁፋችንን ወደተግባር ስለመቀየሩ የሚያመላክቱ ክስተቶች በቤተ ክህነቱ ደጃፍ በተግባር እያስተዋልን ነው። ወደፊት ማኅበሩ ራሱን እንዴት ሊከላከል ይችላል? በመናጆ ጳጳሳቱ በኩል እስከየት ይራመዳል? የሚሉ ጥያቄዎቻችን እንዳሉ ሆነው አሁን ያለው የማኅበረ ካህናቱ ድምጽ የማኅበሩን ረጅም ጉዞ በትክክል ባለበት አቁሞታል ብቻ ሳይሆን ለወደፊቱም ከዚህ በላይ እንዳይሄድ አስሮታል ማለት ይቻላል።
 አሁን በተያዘው የአስተዳዳሪዎችና የማኅበረ ካህናቱ አጠቃላይ በማኅበረ ቅዱሳን ላይ ያለው ተቃውሞ ቀጣይነት የማኅበሩን እድሜ ቀጣይነት ወሳኝ ምዕራፍ ከፋች መሆኑን አሳይቶናል። ለዚህ የሚጠቀስ በማኅበሩ ላይ በስብከተ ወንጌል አዳራሽ የቀረበው ተቃውሞ በጣም ከፍተኛ ሆኖ መገኘቱ፤ ፓትርያርኩም የካህናቱን ጥያቄ ተፈጻሚ ለማድረግ ቃል መግባታቸው አረጋጋጭ መሆኑ ነው።
በአዳራሹ ውስጥ የተገኙትና በማኅበረ ቅዱሳን የስም ማጥፋት ዘመቻ የተከፈተባቸው፣ እንዲሁም በተገኙበት ቦታ በስውር እንዲገደሉ የተወሰነባቸው ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ እንዲህ ሲሉ ደስታቸውን መግለጽ እስኪሳናቸው ድረስ ለማኅበረ ካህናቱ መናገራቸው ታውቋል።
« ማኅበሩ አሉ ብፁዕነታቸው፤ ማኅበሩ እስከሞት ድረስ እንደሚፈልገኝ አውቃለሁ፤ እንድንስማማ ለማባበል ቢሞክር አለመቀበሌ ቢያበሳጨው ስም ማጥፋትና ልዩ ልዩ ዘመቻ እንደዘመተብኝም ለሁላችሁ የተሰወረ አይደለም። ስላልቻለ እንጂ እንደእቅዱ እስከዛሬ እኔ የለሁም። የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ አሟሟት ራሱ ምስጢር ነው። የብፁዕ አቡነ መርሐ ክርስቶስ አሟሟት ራሱ ስውር ነው። ማንም እግዚአብሔር ካዘጋጀለት የሞት እድሜ ባያልፍም አሟሟት ሁሉ አንድ አይደለም። ስለዚህ ይህ ስውር አሟሟት ከተዘጋጀላቸው ሰዎች አንዱ እኔ ነኝ። ድሮ ብቻዬን የሆንኩ ያህል ይሰማኝ ነበር። ለካስ አጠቃላይ ማኅበረ ካህናቱ በዚህ መሰሪ ማኅበር ላይ ያለው እውቀትና ምሬት እኔ ከምጠብቀው በላይ ነበር። ሳልሞት እንኳን ይሄንን ለማየት በቃሁ እንጂ ከእንግዲህ ለምን ነገ አልሞትም፤ የቤተ ክርስቲያን ትንሣዔ መድረሱን ዛሬ አየሁ! ሲሉ ከፍ ያለ ጭብጨባና እልልታ በአዳራሹ አስተጋባ። አስተዳዳሪዎቹም በመረጃና በማስረጃ ስለማኅበሩ ያለውን አመለካከት የገለጹ ሲሆን ለአብነትም «ማኅበረ ቅዱሳን በሚሊዮኖች ብር እንደሚያንቀሳቅስ እናውቃለን፤ ለቤተ ክርስቲያን ፐርሰንት አይከፍልም፤ ለመንግስት ታክስ፤ ቀረጥ አይከፍልም። ይነግዳል፤ ያስነግዳል። በየዐውደ ምህረቶቻችን ይሸጣል፤ ይለውጣል። የቤተ ክርስቲያኒቱን አባላት የራሱ ምልምል አድርጎ ያደራጃል፤ ይሰልላል። ወንጌል ሰባክያንን ይነቅፋል፤ ይወነጅላል፤ ያስፈራራል። ታዲያ እንዲህ ዓይነቱን በሕጋዊነት ሽፋን የማፊያ ስራ የሚሰራ ማኅበር የምንሸከመው እስከመቼ ነው? ሲሉ ይጠይቃሉ። እኛ ይፍረስ ወይም ይጥፋ አንልም። የቤተ ክርስቲያኒቱ አባል ነኝ ካለ ሀብትና ንብረቱን በቤተ ክርስቲያኒቱ ስም ያስመዝግብ፤ ገቢውን ያሳውቅ። እንደአንድ ማኅበር በሚፈቀድለት ልክ ይኑር። አልፈልግም ካለ ግን ራሱን ችሎ ቢሻው የእርዳታ ድርጅት፤ ቢሻው ኢንቨስተር ሆኖ በመንግስት አስፈቅዶ በሕግ ስር ይኑር። ዐመጻ ከፈለገ ደግሞ መንግስት እንዲያስታግስልን አቤታችንን እንቀጥላለን በማለት ተራ በተራ ለፓትርያርኩ አስረድተዋል።
ጉዞውን ጀመርን እንጂ አልጨረስንም፤ እስከ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮና  የተወካዮች ምክር ቤት ድረስ እንዲህ እንደዛሬው ተሰብስብን ጩኸታችንን እናሰማለን። ማኅበረ ቅዱሳንን እንዲያስታግስልን ሰላማዊ ሰልፍ እንወጣለን» በማለት ምሬታቸውን መግለጻቸውን ለመረዳት ተችሏል።  በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ላይ ስለተጀመረው የስራ ዋስትና የሚያሳጣው የማኅበሩና የጳጳሱን ጥናት በተመለከተም  አስተዳዳሪዎቹና ማኅበረ ካህናቱ በአንድ ድምጽ እንደተናገሩት « ቤተ ክርስቲያናችንን የሚጠቅም፤ የማኅበረ ካህናቱን ችግር የሚፈታ፤ ሙስናን፤ አድልዎን፤ መልካም ያልሆነ አስተዳደርንና በአጠቃላይ ያሉብንን ችግሮች መቅረፍ የሚችል ጥናትና እቅድ በምሁራን ልጆችዋ፤ በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፤ በሕግ አዋቂዎቿና ቅዱስ ሲኖዶስ በሚሰጠው መመሪያ የሚወጣ ማንኛውንም የማሻሻያውን ትግበራ የምንደግፍና ለአፈጻጸሙም የበኩላችንን ድርሻ  ለመወጣት ቃል የምንገባ መሆኑን እየገለጽን ማኅበር በተባለ ድርጅትና በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስ በኩል የመጣውን የማንቀበል መሆኑን አበክረን እናስገነዝባለን በማለት ለፓትርያርኩ በግልጽ ተነግሯል። በአዳራሹ ውስጥ የነበረው ተሰብሳቢ በድጋፍ ስሜቱን  ገልጿል።
ፓትርያርኩም በተፈጸመው ነገር ማዘናቸውን፤ ወደፊትም የቤተ ክርስቲያኒቱን አጠቃላይ ችግር በሚፈታ መልኩ ጥናት ሊደረግ እንደሚገባው፤ ካህናቱ ያልተቀበሉትንና ያልደገፉትን በካህናቱ ላይ በግድ መጫን እንደማይቻል፤ ሁላችንም ለቤተ ክርስቲያናችን ሰላምና እድገት የሚጠቅመውን ማዘጋጀት እንደሚገባን አምናለሁ በማለት ለተሰብሳቢዎቹ የተስፋ ቃል በመስጠት የካህናቱን ድምጽ በጥሞና ሰምተው ምላሻቸውን በጉባዔው ላይ አቅርበዋል። ማኅበረ ካህናቱ የአቡነ እስጢፋን ከቦታቸው መነሳት በትኩረት ያነሱት ጉዳይ ሲሆን እሳቸውን በተመለከተ በሲኖዶስ የሚታየውን ነገር በዚያ ጉባዔ ላይ ይህ ይሆናል ብሎ መናገር ለጊዜው እንደማይቻልና ችግሮችን ከግለሰቦች ጋር ማስተሳሰሩ  ወደፊት አያራምድም በማለት ፓትርያርኩ በወዳጃቸውና ለሹመታቸው በተዋደቁላቸው ሊቀ ጳጳስ ላይ ማተኮር እንደማይገባ ለመምከር ሞክረዋል። እሳቸው እንዲህ ይበሉ እንጂ ማኅበሩን በካህናቱ ጫንቃ ላይ ይዘል ዘንድ የፈቀዱት ሊቀ ጳጳሱ መሆናቸው መስተባበል የሌለበት ጉዳይ  እንደሆነ ለመግለጽ እንወዳለን።
ብዙ ሃሳቦች ተሰንዝረውና የማኅበረ ካህናቱም ጥያቄ ተቀባይነት አግኝቶ የውይይቱ ፍጻሜ ሲሆን የማኅበረ ቅዱሳን ጥናት ግን «አዲዮስ» ተብሏል።
ማሳሰቢያ፦ ለአስተዳዳሪዎችና ማኅበረ ካህናት !
አበው  «የነብር ጅራት አይዙም፤ ከያዙም አይለቁም» እንዲሉ ይህንን በነብር የተመሰለ ጥፍራም ማኅበር የበለጠ እንዳይቧጥጠን ጥፍሩን ከተቻለ መከርከም ወይም ተይዞ ሰው በማይጎዳበት ሁኔታ እንዲኖር ማድረግ እንጂ አንድ እርምጃ በመጓዝ ውጤት ተገኝቷል ብሎ መቀመጥ የበለጠ እንዲደራጅ እድል መስጠት ስለሆነ ማኅበሩ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ጥጉን እንዲይዝ በሚደረገው ርብርብ ውስጥ እንቅስቃሴያችሁ ቀጣይነት ያለው ይሁን ምክራችን ነው። « ማኅበረ ቅዱሳን» በቅዱሳን ስም የተሰየመ ነጋዴ ቡድን፤ አዲዮስ!!!

Saturday, December 28, 2013

የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የደብር ሃላፊዎችና ሠራተኞች አዲሱን መዋቅር ተቃወሙ


(ደጀብርሃን) ሁሉን ዐቀፍ ጥናት ያልተደረገበትና በአናቱ በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ላይ የለውጥ ሽፋን ሽብልቅ ሆኖ የገባው ማኅበረ ቅዱሳን ካህናቱንና የቤተ ክርስቲያኑን ላዕላይ አመራር ለሁለት እየሰነጠቀ ይገኛል። አባ ሉቃስን፤ አባ እስጢፋኖስንና ሌሎች የማኅበረ ቅዱሳን አገልጋይ ጳጳሳትን የያዘው ማኅበሩ ከጀርባ ሆኖ በቢሮው አርቅቆ ያመጣውንና በቤተ ክህነት መዋቅር ውስጥ የማንነት አሻራውን ለመትከል ታች ላይ እያለ የሚገኝ ሲሆን ቅዱስ ፓትርያርኩ ጉዳዩ እንዲጠናና ሁሉንም አሳታፊ እንዲሆን የነበራቸውን አቋም በማስለወጥ በጓሮ ያቀረበውን «የያብባል ገና» ፕሮጄክት በመደገፍ ላይ እንደሆኑ ውስጥ አዋቂ ምንጮቻችን መረጃውን አድርሰውናል። ሰሞኑን በፓትርያርኩ ቢሮ የከተመው ማኅበሩና አቀንቃኝ ጳጳሳቱ ለውጡን የሚቃወሙት ወገኖች በጣት እንደማይቆጠሩና ለዚያው ሌቦችና ዘራፊዎች ናቸው በማለት በማጠየም ላይ ተጠምዶ ሰንብቷል። ፓትርያርኩ ከዚህ በፊት የነበራቸው ሃሳብ ሁሉን አሳታፊ፤ አጠቃላይ የለውጥ እቅድ እንዲሆንና የቤተ ክርስቲያኒቱ አመራር የሚያወጣውና የሁሉንም ካህናት ሃሳብ ያካተተ ሊሆን እንደሚገባው የነበራቸውን አቋም ትተው ማኅበሩ እየተሯሯጠለት የሚገኘውን እቅድ እንዲደግፉ ሲወተውት ሰንብቶ ፓትርያርኩን የቀደመ ሃሳባቸውን አስጥሎ የራሱን እቅድ እንዳስጨበጠ መረጃችን አክሎ ገልጿል። ጉዳዩ እስከየት ይሄዳል? የሚለውን ወደፊት የምናየው ሆኖ አሁን ባለው ሁኔታ አለቆችን ለብቻ የነጠለ በሚመስል ስልት እየታከከ፤ የካህናቱን የስራ ዋስትና በመንጠቅ የራሱን አዲስ መዋቅር እየተከለ የሚገኘውን እንቅስቃሴ ማኅበረ ካህናቱ በዝምታ የሚያልፈው ከሆነ አሉታዊ ውጤቱ ለቤተ ክርስቲያኒቱም፤ ለሀገርም የሚተርፍ ይሆናል።
ይህንን በመቃወም የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት አስተዳዳሪዎችና ሠራተኞች እያቀረቡ ያለውን አቤቱታ አዲስ አድማስ ጋዜጣ ዛሬ እንዲህ ዘግቦታል።
ዲግሪ ያላቸው በየአስተዳደሩ እንዲገቡ መደረጉ አግባብ አይደለምበኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት፣ ካለፈው ህዳር ወር ጀምሮ እያካሄደ ያለውን አዲስ የመተዳደሪያ ደንብ የማፅደቅ ሂደት እና መዋቅራዊ ለውጥ አጥብቀው እንደሚቃወሙ የሃገረ ስብከቱ የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎችና ሠራተኞች ለቅዱስ ፓትሪያርኩና ለጠቅላይ ሚኒስትር /ቤት አስታወቁ፡፡ ቅሬታ አቅራቢዎቹ ለፅ/ቤቶቹ ባስገቡት ደብዳቤ፤ የሃገረ ስብከቱ አዲስ መተዳደሪያ ደንብ ሁሉም የቤተክርስቲያኒቱ ሊቃውንት ሳይሳተፉበት በጥቂት አመራሮች ብቻ የተቀረፀና በውይይት ያልዳበረ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ መተዳደሪያ ደንቡ ከነባሩ ህገ ቤተ ክርስቲያንና ከቃለ-አዋዲ ደንብ ጋር የሚጋጭና የሚጣረስ ነው ያሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፤ደንቡ፤ ነባሩን የቤተክርስቲያኒቱን ሠራተኛ በማፈናቀል በምትኩ ስለቤተ ክርስቲያን ትምህርት ምንም እውቀት የሌላቸውን ግለሠቦች በስመ ድግሪና ዲፕሎማ በመሠግሠግ የቤተክርስቲያኗን ሙሉ አስተዳደራዊ መዋቅር ለመቆጣጠር ያለመ ነውሲሉ ተቃውመዋል፡፡

አዲሱን መዋቅር ያዘጋጁት አካላት ማንነታቸው በግልፅ እንደማይታወቅ በደብዳቤያቸው የጠቀሡት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፤ የቤተክርስቲያኗ የመጨረሻ ስልጣን ያለውን ቅዱስ ፓትርያርክ ስልጣንን በመገደብ፣ ቤተክርስቲያኗ የእነዚህ አካላት ሠለባ እንዳትሆን ስጋት አለን ብለዋል፡፡ የቤተክርስቲያኒቱን ቃለ አዋዲ ያልጠበቀ ነው ያሉትን አዲሱን መተዳደሪያ ደንብ እንደማይቀበሉትም አስተዳዳሪዎቹ ገልፀዋል፡፡ ለቅሬታው መነሻ የሆነው ደንብ፣ ህግ በማርቀቅና በማዘጋጀት ከፍተኛ ልምድና እውቀት ባላቸው ገለልተኛ ምሁራንና የቤተክርስቲያኗ ሊቀ ሊቃውንት እንዲሰናዳ የጠየቁት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፤ ህጉን አርቅቋል የተባለውን ማንነቱ ማህበር ፓትሪያርኩ እንዲያጣሩ ተጠይቀዋል፡፡አዲሱ ደንብ የካህናት ቅነሣ መርሃ ግብርም እንዳካተተ በግልፅ ተረድተናልያሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፤ድርጊቱ መንግስት ስራ አጥን ለመቀነስ የሚያደርገውን ጥረት የሚፃረር ነውሲሉ ያጣላሉት ሲሆን ብዙ ሊቃውንትን ከስራ በማፈናቀል ለችግር እና ለእንግልት የሚዳረግ በመሆኑ ህጉ መፅደቅ እንደሌለበት አሳስበዋል፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ ማብራሪያ የጠየቅናቸው የፓትርያርኩ ልዩ /ቤት ሃላፊ አቶ ታምሩ አበራ የቅሬታ አቅራቢዎቹ ደብዳቤ ወደ /ቤት ሳይገባ በቀጥታ ለፓትርያሪኩ የደረሰ በመሆኑ በጉዳዩ ላይ ምላሽም ሆነ አስተያየት ለመስጠት እንደሚቸግራቸው ተናግረዋል፡፡ ቅሬታ አለን የሚሉ ወገኖች በተናጥል ከሚቀርቡ፣ ለቤተክርስቲያኗ ይጠቅማል የሚሉትን ኮሚቴ መርጠው ሃሣባቸውን በማደራጀት ቢያቀርቡ እንደሚሻል የጠቆሙት ሃላፊው፤ የእነሡ ሃሣብ ተቀባይነት ባያገኝም እንኳ በውይይት ለመተማመን ዝግጁ መሆን እንዳለባቸው ገልፀዋል፡፡