Friday, January 31, 2014

እንደ እነዚህ ያሉ ሰዎች የክርስቶስን ሐዋርያት እንዲመስሉ ራሳቸውን እየለወጡ፥ ውሸተኞች ሐዋርያትና ተንኮለኞች ሠራተኞች ናቸውና! 2ኛ ቆሮ 11፤13-14

 

«የእግዚአብሔር መንፈስ እንዲያድርባችሁ ሳር ጋጡ የተባሉ ደቡብ አፍሪካውያን ሳር ሲግጡ ዋሉ!!» በሚል ርዕስ ከዚህ በፊት በጽሁፍ ያስነበብናችሁ መሆኑ አይዘነጋም። የሣር መጋጡን መርሐ ግብር ተንቀሳቃሽ ምስል እነሆ አቀረብናላችሁ። ፓስተር ሌሴጎ ዳንኤልና ተከታዮቹ በአዳራሽ ተቀምጠው የቀጥታ ስርጭቱን በማየት ይዝናናሉ። ፓስተሩ በመጀመሪያ ረጋገጣቸው፤ በጫማ ጠቀጠቃቸው ከዚያም ልቡናቸውን ሰውሮ እንደከብት ሳር እንዲግጡ አደረጋቸው።

«ነገር ግን ሐሰተኞች ነቢያት ደግሞ በሕዝቡ መካከል ነበሩ እንዲሁም በመካከላችሁ ደግሞ ሐሰተኞች አስተማሪዎች ይሆናሉ፤ እነርሱም የዋጃቸውን ጌታ እንኳ ክደው የሚፈጥንን ጥፋት በራሳቸው ላይ እየሳቡ የሚያጠፋ ኑፋቄን አሹልከው ያገባሉ፤ብዙዎችም በመዳራታቸው ይከተሉአቸዋል በእነርሱም ጠንቅ የእውነት መንገድ ይሰደባል» 2ኛ ጴጥ 2፤2