Wednesday, January 15, 2014

ትግርኛ ተናጋሪ ጎንደሬው ሊቀ ጳጳስ እስጢፋኖስ ከጎንደሬዎች ጋር እየመከሩ ነው!!


( ከብሶቴ ተሰማ አዲስ አበባ )
ዘር ለእህል ነው። የእህል ዘር ግንዱ አንድ አይደለም። ዘሩ በየመልኩ ልዩ ልዩ ነው። የሰው ልጅ ግን እንደዚያ አይደለም። መልኩ ቢለያይም ግንዱ አንድ አዳምና ሔዋን ናቸው። ከዚያም በላይ ሁላችንም በክርስቶስ ሞትና ትንሣዔ  አንድ ሆነናል። ይሁን እንጂ ክርስትናን ከስምና ከሹመት በስተቀር የማያውቁ አንዳንዶች ዛሬም  የሰውን ልጅ ከእህል የዘር ዓይነት ቆጠራ ራቅ ብለው ለማየት እንዳልቻሉ እርግጥ ነው።
ከእነዚህም አንዱ አባ እስጢፋኖስ በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የማኅበረ ቅዱሳን ሊቀጳጳስ ናቸው። ቤተ ክርስቲያን አንዲት ብትሆንም በአስተዳደር ይዞታዋ የተለያየ በመሆኑ ሊቀ ጳጳሱ በጅማ ሀ/ስብከት ሳሉ ገመናቸው ተሸፍኖ፤ በሰው መሳይ ሸንጎ ተከልለው በሰላም ይኖሩ ነበር።  ኅሊናቸውን አሳርፈው መኖር የሚችሉበትን ሀ/ስብከት ይዘው አርፈው እንደመቀመጥ ከወታደሮች ማኅበር ጋር አብረው በመቆም የእድሜ ልክ መጽሐፋቸው ይነበብ ዘንድ በየቦታው አለሁ ማለታቸው ያሳዝናል።  ደርሶ መንፈሳዊ መስሎ ለመታየት የአበው አጥንት ይወቅሰናል፤ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ይፋረደናል በሚል በአስመሳይ ተቆርቋሪነት የማኅበሩን ዓላማ ለማስፈጸም ደፋ ቀና ማለታቸው ለእርሳቸው የትጉህ ሰራተኛ ትግል ቢመስላቸውም እውነቱን ለሚያዩ ግን ያለቦታቸው በአጉል ሰዓት የተገኙ  ሰው ናቸው። ከአባ ገብርኤል ጋር ከአስመራ ጀምሮ በድሬዳዋ ዞረው፤ አዲስ አበባን አካለው ኮተቤ 02 እስካሳነጹት የመኖሪያ ህንጻ ድረስ ብዙ ጉድ መኖሩን የምናውቅ እናውቀዋለን።
በእርግጥ ሊቀጳጳሱ( ከተባሉ) ዓይናቸውን በጨው የታጠቡ ስለሆነ ስለበደልና ጥፋት ትንሽ ስሜት አይሰጣቸውም። የኅሊና ጸጸትም ፈጽሞ አይነካካቸውም። ከድፍረቱ ጋር የደነደነ ልብ ስለታጠቁ የተባለው ቢባል፤ የተወራው ቢወራ ደንታ የላቸውም። ለዚህም ነው ከበደል ጋር ዕረፍት በሌለው ወዳጅነት እስከ ህይወታቸው ህቅታ ድረስ ቃል በመግባት ዛሬም የአንድ ተራ ማኅበር ጉዳይ አስፈጻሚ ሆነው የመገኘታቸው ነገር  አረጋጋጭ ነው። በመሰረቱ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከትን ለማስተዳደር ራሱ ከሙስናና ከአስነዋሪ ስነ ምግባር የጸዳ መሆን ይገባው ነበር። አፉን ሞልቶ ለመናገር፤ ሌባና ብልሹ አስተዳደር ለማስተካከል የሚችለው ከዚህ የጸዳ ቢሆንም አባ እስጢፋኖስ ግን ለአባ ማትያስ በዋሉላቸው ውለታ የተነሳ በስራ አስኪያጅነት ዘመናቸው በጉቦ የጋጡትን ሀ/ስብከት  በፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስነት ስም ተመልሰው ባልያዙም ነበር። በዚህ ዘመን ከሰጪም፤ ከተቀባይም ኅሊና የሚባል ነገር ስለጠፋ እያየነው ያለው ሊሆን ግድ ሆነ።
በአዲስ አባ ሀስብከት ውስጥ መልካም አስተዳደር እንዲመጣ ካስፈለገ ያለው አማራጭ የአባ እስጢፋኖስ ከቦታው ማስነሳት ብቻ ነው። የተባለውም መዋቅር ጥናት እንደአዲስ ከሚታይ በስተቀር በእሳቸው አስፈጻሚነትና በማኅበሩ ገፊነት ችግሮችን ያባብሳል እንጂ ፈቺ ሊሆን አይችልም። /ሊሰመርበት የሚገባው ጉዳይ/ ችግሮችን ያባብሳል እንጂ ፈቺ ሊሆን አይችልም።
አባ እስጢፋኖስ የጎንደር ተወላጅ የቤተክርስቲያን አስተዳዳሪዎችንና የሰበካ ጉባዔ ምክትል ሊቃነ መናብርትን በደጋፊነት በማሰለፍ በማቅ የተዘጋጀውን የመዋቅራዊ ለውጥ በተግባር ላይ ለማዋልና ከጀርባቸው ያለውን አሳፋሪ ታሪክ ለመደበቅ ጥረታቸውን ቀጥለዋል፡፡
አቡነ እስጢፋኖስ የአዲስ አበባ ሥራ አስኪያጅ በነበሩበት በ1990ዎቹ መጀመሪያ ዓመታት በእሳቸው ድጋፍ የድራፍት ቡድን በማቋቋም አዲስ አበባን ሲያውኳት እንደነበር ቀደምት ታሪካቸው ያስረዳል፡፡ ያን ጊዜ ስያሜውን ያገኘው የድራፍት ቡድን አባ እስጢፋኖስን ቤተክርስቲያን ወንበር ላይ በስራ አስኪያጅነት አስቀምጦ በከተማዋ በሚገኙ ዝነኛ ሆቴሎች በመቀመጥ ቅጥር ዝውውርና እድገት በመስተት መላውን የቤተክርስቲያኒቱ ሰራተኞች ሲያበጣብጥ በወቅቱ በጉዳዩ መንግሥት እጁን አስገብቶ እሳቸውንም ከኃላፊነታቸው ድራፍት ቡድኑንም ከጣልቃ ገብነቱ በመግታት በወቅቱ ሰላም ተገኝቶ ቆይቷል፡፡ ታሪክ እራሱን ይደግማል እንደሚባለው ዛሬም ሳይገባቸው ያገኙትን አስኬማ ለዚሁ ሰላም አደፍራሽ ለሆነ ተልእኮ በመጠቀም በመላው አዲስ አበባ በመንግሥት ላይ ካኮረፈው የማቅ ቡድን ጋር በመሆን  ዛሬም ቤተክርስቲያኒቱን እያወኩ ይገኛሉ፡፡
በቅርቡ በማቅ ቡድን ራዕይ መሠረት ቤተክርስቲያኗን ለመቆጣጠር  በተዘረጋው ወጥመድ መዋቅራዊ ለውጥ በሚል የተዘረጋው ስውር እስትራቴጂ በግልጽ የቤተክርስቲያኗ ችግር መሆኑ ከተረጋገጠ በኋላ ቅዱስ ፓትርያርኩ በማቅ የተዘጋጀው የመዋቅራዊ ጥናት ውድቅ ሁኖ በቤተክርስቲያኗ ሊቃውንት ሁሉን ያማከለ ሕግ እና መመሪያ እንዲወጣ የማቅን የሽብር ሴራ ቀድመው ለተገነዘቡ አገልጋዮች ቃል ገብተው ነበር፡፡ አቡነ እስጢፋኖስ ከቤተክርስቲያኗ ሕግ ውጪ የወለዷቸውንና በየአብያተ ክርስቲያናቱ በቁጥጥር እና ሒሳብ ሹም የቀጠሯቸው ልጆቻቸው ጉዳይ እንዲጣራም ሐሳብ ቀርቦ ነበር፡፡ ታድያ ይህ አካሄድ ያሰጋቸው አቡነ እስጢፋኖስ በፖለቲካ ምክንያት የተገለሉና አካላቸው ኢትዮጵያ ሆኖ ልባቸው  የሰሜን አሜሪካው ሲኖዶስ  ጋር የሆኑ የጎንደር ተወላጅ አለቆችን በመሰብሰብ ይኸው የልጆቻቸው ጉዳይ ተዳፍኖ እንዲቆይና መዋቅራዊ ጥናቱ በተገባር ላይ እንዲውል የእሳቸው ሥላጣን ቆይታን የሚያረጋግጥ ውሳኔ በቅዱስ ሲኖዶስ እንዲያስወስኑ አደራ በማለት አሰማርተዋቸዋል፡፡ በየትኛውም ወገን አዲሱ መተዳደሪያ ሕግ ተግባራዊ ቢሆን  በሚፈጠረው አለመግባባት ሐገር ሲታመስ ከዚሁ ብጥብጥ ፖለቲካዊ ጥቅም ለማግኘትና የሰሜን አሜሪካው ሲኖዶስ ከብጥብጡ መልካም አጋጣሚ እንዲያገኝ ጥረታቸውን በመቀጠል ፓትርያርኩ ድረስ ዘልቀው የአደራ መልእክታቸውን አሰምተዋል፡፡
የአቡነ እስጢፋኖስ የሀገር ልጅና የጥቅም ተሳታፊ የሆነው የአፍሪካ ኅብረቱ ዋና ጸሐፊ አቶ አብርሃም አቧሀይ የእነዚህ የጎንደር ኃይሎች ዋና አደራጅና መሪ ሲሆን እራሳቸውንም የአርበኞች ግንባር ብለው ሰይመው ፓትርያርኩ ዘንድ በመቅረብ የተሰጣቸውን ተልእኮ ለመፈጸም ሞክረዋል፡፡ የጳሳሳት ልብስ ሰፊው ወርቁ አየለ ፤ የየረር ዑራኤል አለቃ ዘማርያም ሙጬ፤ የጃቲ ኪዳነምሕረት አስተዳዳሪ፤ የደብረሲና እግዚአብሔር አብ ምክትል ሊቀ መንበር፤   እና የሰሚት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ አባ ገብረ ስላሴ ከጎንደር ተወላጅ ሊቃነ መናብርቶቻቸው ጋር በመሆን ብዙ ባሉበት ስብሰባ  የአቡነ እስጢፋኖስ ሥልጣን እንዲራዘም ልመናቸውን ለፓትርያርኩ አቅርበዋል፡፡
ከአቡነ እስጢፋኖስ ተቃዋሚዎች ይቅርታ ጠይቀዋል በማለት  አዲስ ፕሮፓጋንዳ በማናፈስ ሌሎች ተቃዋሚዎችን ለማስበርገግ ጥረታቸውን ቀጥለዋል፡፡ እንደ ሌሊት ወፍ ከዚህኛውም ከዚያኛውም ቡድን አለሁ በማለት በመሀል ሰፋሪነት አንዴ ተቃዋሚ ሌላ ጊዜ ደጋፊ አሁን ደግሞ አስታራቂ የሆነውና የቦሌ መድኃኔዓለምን ጸሐፊነት ላለመነጠቅ በሚባዝነው በቀሲስ ሰሎሞን በቀለ አስታራቂነት ይቅርታ የጠየቁት የሲኤምሲ ሚካኤል አለቃ መ/ር ዘካርያስ ሲሆኑ እሳቸውም ይቅርታ የጠየቁት አዲስ በሚሰራው  ካቴድራል ስም የሚገባ ሲሚንቶ  ከንብረት ክፍል ኃላፊዋ ወ/ሮ ሰርክ አዲስ እና ከምክትል ጸሐፊው ፋንታሁን ከሙጨ ወንድም ጋር በመሆን መሸጣቸውን የሚያረጋግጥ መረጃ በአቡነ እስጢፋኖስ ሰዎች በመያዙ ይህንን እንደመደራደሪያ በመጠቀም አንተም ተው እኔም እተዋለሁ በሚል በአቡነ እስጢፋኖስ የተደረሰ ድራማ መሆኑን ታውቋል፡፡
ለቤተክርስቲያን ለውጥ የሚያስፈልጋት ቢሆንም ለውጡ ሁሉን አቀፍ የሆነና ከቤተክርስቲያኒቱ ሌሎች ሕጎች ጋር የማይጣረስ አዘገጃጀቱም ሁሉን ያሳተፈ እንዲሆን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አስተዳዳሪዎችና ሌሎች ሰራተኞች በግልጽ መጠየቃቸው አይዘነጋም፡፡
ጥያቄው መቼም አይቆምም!!