Friday, November 18, 2011

ቅዱሳን መላእክት ትእዛዝ ይጠብቃሉ!


መልአክ የሚለውን ለማየት የግስ ዘሮቹን መመልከት ይጠቅማል። ይህንን በተመለከተ ዓይናማው የቤተክርስቲያን ሊቅ የነበሩት አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ(በማቅ ተሃድሶ ተብለዋል) «መጽሐፈ፡ሰዋስው፡ወግስ፡ወመዝገበ፡ቃላት፡ሐዲስ» በተሰኘው መጽሐፋቸው ገጽ 549 ላይ እንዲህ ሲሉ አትተዋል። ልኢክ፤ ልኢኮት(ለአከ፤ይልእክ) መላክ፤መስደድ ማለት ሲሆን ባለቤቱን ሲያመልክት ለአኪ ማለት ላኪ፤ ሰዳጅ ማለት ነው። መልአክ ማለት በቁሙ ሹመኛ፣ አለቃ ሲሆን በረቂቃን ፍጥረታት አጠራር ደግሞ በእለተ እሁድ ተፈጥረዋል የሚባሉትን የእግዚአብሔር መላእክቶችን ስም ይወክላል። ከዚህ የትርጉም ጽንሰ ሃሳብ የምንረዳው መላእክት ማለት የሚላኩ፣ የሚታዘዙ ፍጥረታት ሲሆኑ ላኪያቸው ወይም ሰዳጃቸው የፈጠራቸው እግዚአብሔር ነው ማለት ነው። በእለተ እሁድ ተፈጥረዋል የተባሉት መላእክት ማለት እንግዲህ የወደቁትንም መላእክት ጨምሮ ነው። የወደቁት መላእክት ላኪያቸውንና ሰዳጃቸውን ለመታዘዝ ባለመፈለጋቸው ከእግዚአብሔር ቅዱሳን የመባል ሀገር ወጥተው በጭለማ ሀገርና አሰራር ወዲያና ወዲህ እያሉ የሚኖሩ መላእክት ሆነዋል። ቅዱሳኑ መላእክት ግን ትእዛዝ ሲደርሳቸው በጌታ ሲላኩ እናያለን። «ጴጥሮስም ወደ ልቡ ተመልሶ፦ ጌታ መልአኩን ልኮ ከሄሮድስ እጅና የአይሁድ ሕዝብ ይጠብቁት ከነበረው ሁሉ እንደ አዳነኝ አሁን በእውነት አወቅሁ አለ» የሐዋ 12፣11 ጴጥሮስን ሄዶ እንዲያድን የላከው ጌታ ነው። መልአኩ የተላከውም ጴጥሮስን እንዲያድን ነው። ቅዱሳን መላእክት እንደስማቸው ለሚገዙለት ጌታ ይላካሉ። አድኑ የተባሉትን ያድናሉ። እንዲሁም በመጨረሻው ዘመንም ቅዱሳኑ መላእክት ይላካሉ። «በዚያን ጊዜም መላእክትን ይልካል ከአራቱ ነፋሳትም ከምድር ዳርቻ እስከ ሰማይ ዳርቻ የተመረጡትን ይሰበስባቸዋል» ማር13፣27 በሌላ ስፍራም እንዲህ የሚል አለ፤ «በመንገድ ይጠብቅህ ዘንድ ወዳዘጋጀሁትም ስፍራ ያገባህ ዘንድ፥ እነሆ፥ እኔ መልአክን በፊትህ እሰድዳለሁ»ዘጸ23፣20
እንግዲህ ቅዱሳኑ መላእክት ከምስጋና ከተማቸው፤ ሊታዘዙና ሊገዙለት ከወደዱበት የአምላካቸው ቃል (ልኢክ፣ልኢኮት) ሲደርሳቸው ብቻ ይወጣሉ እንጂ እንደወደቁት መላእክት በገዛ ፈቃዳቸው ወዲያና ወዲህ አይዞሩም፤አይሄዱም።
የወደቁት መላእክት ግን የሚከሱትንና የሚወነጅሉትን ሲፈልጉ፣ ሲያሳስቱ በገዛ ፈቃዳቸው ሲዞሩ ይኖራሉ። ሲዞሩ ነበር፣ ማሸነፍ ያልቻሉትን የእግዚአብሔር ሰው ኢዮብን መልካም ስራ አይተው የቀኑበትና ክስ ያቀረቡበት። «እግዚአብሔርም ሰይጣንን፦ ከወዴት መጣህ? አለው። ሰይጣንም። ምድርን ሁሉ ዞርሁአት፥ በእርስዋም ተመላለስሁ ብሎ ለእግዚአብሔር መለሰ»ኢዮብ 1፣7 እንግዲህ ራሱ ሰይጣን እንደተናገረው ዟሪና ምድርን ለክፋት ስራው የሚያስሳት፣ በራሱ ፈቃድ የሚመላለስ ሲሆን ቅዱሳኑ መላእክት ግን ስራቸው ፈጣሪያቸውን ማመስገን«...ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ ቅዱስ፥ የነበረውና ያለ የሚመጣውም ሁሉንም የሚገዛ ጌታ አምላክ እያሉ ቀንና ሌሊት አያርፉም» ራእይ4፣8 እንዳለው ምስጋና መስጠት ነው። መልእክት ሲደርሳቸው ደግሞ በመላእክት አለቃ ሚካኤል በኩል (1ኛ ተሰ4፣16 እና በይሁዳ መልእክት 1፣9) እንደተመለከተው ትእዛዙ ተፈጻሚ ይሆናል።
እንግዲህ ይህ ያለው መጽሐፍ ቅዱሳዊ እውነታ ነው። ቅዱሳኑ ከእግዚአብሔር የተሰጠ ትእዛዝ ሲኖር ሰዎችን ያድናሉ፤ይረዳሉ፤ይታደጋሉ፤ይነግራሉ፤ ያስተምራሉ፣ በቅዱሳንና ንስሃ በሚገቡ ሰዎችም ይደሰታሉ። ያለእግዚአብሔር ትእዛዝ ግን የትም አይሄዱም፤ አይዞሩም። ይህንን የሚያደርግ ሰይጣን ብቻ ነው። ራሱ ምድርን አሰስኳት፣ዞርኩባት እንዳለው በኢዮብ 1፣7 ላይ። ምክንያቱም ከአገዛዙ ውጭ ለመሆን ባይችልም ከአገልግሎቱ ቁጥጥር ውጭ ያለው እሱ ስለሆነ ነው። በዚህ ዓለም እንኳን ከቤተሰብ ቁጥጥር ውጭ በመጥፎ ስነምግባሩ የተባረረ ልጅ ውሎና አደሩ እንደልቡ ሲሆን በስርዓት ያደገው ግን ቤተሰቡ ከሚያሰማራውና ከፈቀደለት ወይም ከሚገባው ቦታ ውጭ አይዞርም።
በመጨረሻም ሊሰመርበት የሚገባው ነገር እኛ የሰው ልጆች የትኛውንም መልዓክ ስለጠራነው ወይም ስለጨቀጨቅነው በምንፈልግበት ቦታ ሁሉ ስሙ ስለተጠራ አይመጣም። ለተልእኮ የተፋጠኑ ተላኪዎች እንጂ ከቁጥጥር ውጭ የወጡ ዟሪዎች አይደሉምና ነው። ምናልባት ዟሪውና ምድርን የሚያስሰው የክፉ መልአክ «የብርሃንን መልአክ እንዲመስል ራሱን ይለውጣልና»2ኛ ቆሮ 11፣14 እንዳለው እኔ ሚካኤል ነኝ፤ እኔ ገብርኤል ነኝ ብሎ ሊመጣ ይችላል። ቅዱሳኑ መላእክት ግን ለሰዎች የሚደርሱት ጸሎታችን ወይም ጥያቄያችን ወይም ለቅሶአችንና ሀዘናችን በእግዚአብሔር ዘንድ ሲሰማና ምላሽ የሚሰጠን ሲሆንና ሲላኩ ይመጣሉ። ጸሎታችንና መልካም ስራችን በእግዚአብሔር ዘንድ ሲወደድ እንኳን ቅዱሳን መላእክት ቅዱሳን ሰዎችም ሊላኩልን ይችላሉ። ልክ ለቆርኔሌዎስ ጴጥሮስ እንደተላከለት ማለት ነው። «ቆርኔሌዎስ ሆይ፥ በእግዚአብሔር ፊት ጸሎትህ ተሰማ ምጽዋትህም ታሰበ»የሐዋ10፣31 እንዳለውና ጴጥሮስ እንደተላከለት ማለት ነው።
ከዚህ ውጭ ቅዱሳን መላእክትን ስንጠራ ከተፍ ይላሉ ማለት ስለቅዱሳን መላእክት ተፈጥሮና ተግባር ያለማወቅ ብቻ ሳይሆን ከተፍ የሚለው ብርሃንን የሚመስለውን ከተፎ ዟሪ ማንነት ያለመረዳትም ጭምር መሆኑ ያሳዝናል። ቅዱሳን መላእክት እኛ ለእግዚአብሔር በምናቀርበው ጸሎትና ልመና ከእግዚአብሔር ቃል በሚወጣ ትእዛዝ ብቻ ለዚያውም እኛ ይህኛው ጠንካራ ነው፤ ያኛው ሰይፍ አለው፤ያኛው ደግሞ ቁጡ ነው፣ይህኛው ርኅሩኅ ነው ብለን ስለመረጥን ሳይሆን እኛ የማናውቃቸው ከእልፍ አእላፍ መላእክቱ መካከል ለተልእኰ የተዘጋጁትን እሱ የፈቀደውን ይልካል። ያኔም ይራዱናል፤ያግዙናል፤ የታዘዙትን ሁሉ ለእኛ በደስታ ይፈጽሙልናል። ከዚህ ውጭ ግን ቁጡ ወይም ርኅሩኅ ወይም ዓለምን በእጁ ሊገለብጣት ነበር፤ የወረወረው ጦር እስከምጽዓት ይወርዳል ወዘተ የሚሉ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ያልሆኑ ድምጾች ቅዱሳን መላእክትን ከሚያውቁ ሰዎች የሚወጡ ድምጾች አይደሉም። ይልቁኑም ከዚያ ከተፍ ከሚልና የብርሃንን መልአክ ሊመስል ራሱን ከሚለውጠው ዟሪ የሚወጣ መሆን አለበት። ምክንያቱም ስማቸው ስለተጠራ የሚመጡ ወይም ስላልተጠራ የሚቀሩ ቅዱሳን መላእክት የሉምና ነው። እነሱ እንደሰይጣን ያለትእዛዝ ወዲያና ወዲህ አይዞሩም። የቅዱሳን መላእክትን ተልእኰና ተግባር የሚያውቅ ልቡናን ከላይ ይስጠን።አሜን።(በዚህ ርእስ ላይ በሰፊው እንመለስበታለን)

Wednesday, November 16, 2011

በትዳር መካከል ያለውን ችግር መፍታት



ባልና ሚስት ፍጹማን ባለመሆናቸው በዚህ ምድር ባሉበት ጊዜ በግልም ይሁን በጋራ ስህተት ሊፈጽሙ እንደሚችሉ ማሰብ አያዳግትም።ባለትዳሮች ሁሉ በሆነ ወቅትና ሁኔታ ውስጥ ይሳሳታሉ። መጠኑና ዓይነቱ ይለያይ እንጂ ስህተት የማይሰሩ ባልና ሚስት የሉም። የአንዳንዶች በሰዎች ዘንድ ሲታወቅ የአንዳንዶች ደግሞ ሳይገለጥ ሊቀር ይጥላል።የአንዳንዶች ብዙ ኪሳራ የማያስከትል ሲሆን የአንዳንዶች ደግሞ ከእነርሱም አልፎ ትውልድን የሚጎዳ አሉታዊ ውጤት ያለው ይሆናል። ይህ ጽሑፍም መጽሐፍ ቅዱስን ዋቢ አድርጎ ይመለከታልና መልካም ንባብ ለባለትዳሮችና ትዳር ለመያዝ ላሰቡ ሁሉ!!

ሙሉውን ጽሑፍ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

Wednesday, November 9, 2011

ክብር ለሚገባው ክብር ስጡ!



ሮሜ 13፣7 «ለሁሉ የሚገባውን አስረክቡ፤ ግብር ለሚገባው ግብርን፥ ቀረጥ ለሚገባው ቀረጥን፥ መፈራት ለሚገባው መፈራትን፥ ክብር ለሚገባው ክብርን ስጡ»

ክብር ለአንድ ነገር ዋጋ መስጠትን ይመለክታል። ዋጋው ደግሞ በዓይነት፣በገንዘብ፣በጉልበትና
በሃሳብ ወይም በመንፈስ ሊገለጥ ይችላል። የሰው ልጅ በሕይወቱ ዘመን ይህንን ዋጋ ሲከፍል ኖሯል፤ ይኖራልም። ሰው ለፈጣሪውና ለሚያመልከው፤ ለሚበልጠው፤ ለሚወደው፤ ለሚፈራው፤ ለሚመራው ክብርን ይሰጣል። ምናልባት የሚሰጥበት መንገድና የሚሰጥበት ምክንያት ይለያይ እንደሆነ እንጂ ክብርን ስለመስጠት ሃሳብ ጥያቄን የሚያስነሳ ጉዳይ እንዳልሆነ እንስማማለን።

ሰው ፈጣሪው ስላደረገለትና ስለሚያደርግለት ነገር ሁሉ ክብርንና ምሥጋናን ይሰጣል። ክብርን የሚሰጠው ስለተደረገለት ብቻ ሳይሆን ፈጣሪ በመሆኑ ክብር ስለሚገባውም ጭምር ነው።

ነቢዩ ሙሴና ሕዝቡ እግዚአብሔር ከጠላት እንዳዳናቸው ደስታቸውን በዝማሬ ገልጠው ክብር ሰጥተውታል።

«በዚያም ጊዜ ሙሴና የእስራኤል ልጆች ይህንን መዝሙር ለእግዚአብሔር ዘመሩ፥ እንዲህም ብለው ተናገሩ። በክብር ከፍ ከፍ ብሎአልና ለእግዚአብሔር እዘምራለሁ ፈረሱንና ፈረሰኛውን በባሕር ጣለ» ዘጸ ፲፭፣፩

ክብሩ ከፍ ከፍ ያለ፣ ኃይልና ሥልጣን በእጁ የሚገኝ፣ ማድረግ የሚፈልገውን ከማድረግ የሚከለክለው ለሌለ ምስጋና ይገባዋል ሲሉ ተገቢውን ክብር ሲሰጡ እናያለን። ስለተደረገላቸው ብቻ ሳይሆን ክብሩ ፍጹማዊ በመሆኑ ለመለኰታዊነቱ ተገቢ ክብር እንደሆነም ሌላ ሥፍራም እንደዚሁ ምሥጋና ሲሰጡ እናገኛቸዋለን።

«በተራራው ራስ ላይ በእስራኤል ልጆች ፊት የእግዚአብሔር ክብር መታየት እንደሚያቃጥል እሳት ነበረ» ዘጸ ፳፬፣፲፯

ክብሩ ታላቅና ሰው ሊቀርበው የማይችል መለኮታዊ እሳት ስለሆነ ክብርና ምስጋና የተገባው ነበረ። የእግዚአብሔር ክብር በቦታና በሥፍራ አይወሰንም፣ መለኮታዊ አገዛዙ ሁሉን የመላ ስለሆነም ጭምር ክብር ይገባዋል። ሁሉን በሙላት መሸፈን የሚችል ያለእሱ ማንም የለምና።

Sunday, November 6, 2011

እኔ በእግዚአብሔር የምታወቅበት ማንነት!


በዚህ ምድር ሳለን እውቀታችን ያች ትንሿ ጭንቅላታችን በሚመጥናት መልኩ የያዘችውን ያህል ብቻ ታውቃለች። ከዚያ በላይ ልሁን ብትልም መስፋት ከምትችለው በላይ አትወጣም። ዓለም ባላት እውቀት የምታውቀው ማወቅ የቻለችውን ያህል ብቻ ነው። የሰው አእምሮ ከምታውቀው በላይ ለመሆን ብትሞክር የእውቀት መቋጠሪያዋ ይበጠስና የያዘችው ማፍሰስ ሲጀምር ሰው ለመባል ያበቃትን ማንነት ትስትና አጠቃላይ እኛነታችንን ወደ ሌላ ምዕራፍ ታሸጋግራለች። ወደ እብደት ወይም ወደ እንስሳት ጠባይዓት ማለት ነው።
አንደኛው የዓለም ጦርነትም ይሁን ሁለተኛው የዓለም ጦርነት መነሻቸው ሰው ካለው እውቀት በላይ ለማምጣት በተመኘ እውቀት የተከሰተ ነው። ምናልባትም ሶስተኛው የዓለም ጦርነት ሊመጣ የሚችለውና የከፋ የሚያደርገውም የሰው እውቀት ከማወቅ ጣሪያ በላይ ለመውጣት በሚያደርገው ጥረት ወዳለማወቅ ተሻግሮ የሚጎትተው እብደትና የእንስሳነት ጠባይ መገለጫ ሊሆን ይችላል።
ይህንንም ጥንታውያን አበው«እጅግም ስለት፤ ይቀዳል አፎት»ይላሉ። መጽሐፍ ቅዱስም የእግዚአብሔር ቁጣ እንዲርቅና የተመዘዘው ሰይፍ እንዲመለስ ሲያመለክት እንዲህ ሲል ይነግረናል። «አንተ የእግዚአብሔር ሰይፍ ሆይ፥ ዝም የማትለው እስከ መቼ ነው? ወደ ሰገባህ ግባ ጸጥ ብለህም ዕረፍ » ኤር 47፤6
በምድራችን ላይ የሚታየው የጦርነት፤ የእልቂት፤የእርስ በእርስ መበላላት፤ የበሽታና የረሃብ ክስተቶች ሁሉ የሰው እውቀት ያመጣው ጣጣ እንጂ የፈጣሪ ፈቃድ አይደለም። ምክንያቱም የያዝነው የዘመኑ እውቀት ስለቱ ለመኖርያ የተሰጠውን አፎት ዓለምን እየቀደደ በመገኘቱ ሰው ሰውኛነቱን ወደመካድ እብደትና እንስሳነት እውቀት እየተሸጋገረ በመገኘቱ የተነሳ ነው። እንዲሁም ይህ ሰይፍ ወደሰገባው (አፎቱ) የማይመለሰው የሰው ልጅ ያለው እውቀት እግዚአብሔር እሱን (የሰው ልጅን) እንዴት እንደሚያውቀው ለማወቅ ከመፈለግ ውጪ ስለሆነ ነው። በአጭር አገላለጽ ሰው ስለእግዚአብሔር ያለው እውቀት እሱ ማወቅ የሚችለውንና ለማወቅ የሚፈልገውን ያህል ሲሆን በአንጻሩ እግዚአብሔር ሰውን እንዴት እያወቀው እንደሆነ ለማወቅ አልቻለም ማለት ነው።

Thursday, November 3, 2011

እርግማንና ረጋሚዎች!



ኢትዮጵያ ቀደም ሲል በኦሪቱ በኋላም በወንጌል የበራላትንና ከእግዚአብሔርም የተሰጣት ከአፍሪካ እስከ በመካከለኛው ምስራቅ ገናና ታሪክ እስከ የመንም ድረስ የነበራትን የግዛት እንዲሁም የጸጋ፤የበረከት፤ መሬቷ ወርቅ፤ ወንዞቿ ወይን፤ ደኖቿ ኤደን፤ ሕዝቦቿ ታታሪ ሆነው የኖሩበትን ዘመን የቀየረውና የገለበጠው ምንኩስና የሚባለው የሰነፎችና «የአጸድቃለሁ፤ እኔም በስራዬ እጸድቃለሁ» የሚለው ማኅበር ከተንሰራፋ በኋላና ወንጌልን አሽቀንጥሮ ቤተመቅደሱን የሞላው ገድል የሚሉት የእግዚአብሔርን ክብር በመጋረድ ቅዱሳን ለተባሉት ክብርና መንቀጥቀጥን እንዲሰጥ የሚያስገድደው መጽሐፍ ቦታውን ከያዘና ተአምር የሚባል የዘርዓ ያዕቆብ የግዝት መጽሐፍ ብዙ ደም አፋስሶ፤ አፍንጫና ጆሮ አስቆርጦ፤ በሕይወት ሳሉ ከጉድጓድ አስቀብሮ የደም መሬት ኢትዮጵያ ላይ ከነገሰ በኋላ ነው። በኦርቶዶክስ ቤ/ክ መጽሐፍ ቅዱስን በደንብ ማንበብ የተጀመረው የፕሮቴስታንት እምነት መጽሐፍ ቅዱስን ይዞ ስለሚሰብክ እሱን ለመቋቋም ተብሎ እንጂ ከእቃ ግምጃ ቤት ወጥቶ አያውቅም። በትግራይ እስከቅርብ ጊዜ ድረስ መጽሐፍ ቅዱስን ይዞ የታየ ጴንጤ ወይም ካቶሊክ ያሰኝ እንደነበር አይዘነጋም። ድርሳነ ሚካኤልን ወይም የሆነ ተአምርን ከተሸከመ እሱ የወንጌል ሰው ሳይሆን ኦርቶዶክሳዊ እንደሆነ ይቆጠራል።
ሌላው ቀርቶ« ኦርቶዶክሳዊ ሆኖ «ኢየሱስ ጌታ ነው»ብሎ መናገር እንደጴንጤ ያስቆጥራል። ማር 12፤29...ጌታ አምላካችን አንድ ጌታ ነው» የሚለውን መመስከር ወንጀል ሆኖ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሌለው 78 ሰው ቅርጥፍ አድርጎ በላ የሚባለውን የተረት ታሪክ መናገር እንደክርስቲያን የሚያስቆጥረው በምን ስሌት ነው?

Monday, October 31, 2011

እውነቱን ብንናገር ምን ይለናል?


በዚህች ምድር ላይ ከተስፋፋውና በሰዎች ልቡና ላይ ከተማውን ከመሠረተው አስፈሪ ኃጢአት መካከል እውነትን ለመናገር የሚችል ሰው እየጠፋ መምጣቱ ቀዳሚውን ይዟል። ዓይኑ ያየውን፤ ጆሮው የሰማውን ሽምጥጥ አድርጎ በመካድ ልቡ ያመነጨውን እውነት አድርጎ ማውራትና ማስወራት፤ ይህንንም እንደእውነተኛ ምስክርነት መቁጠር ባህል እየሆነ መጥቷል። ሰዎች ከሥልጣን ኮርቻ ለመፈናጠጥም ሆነ ከሥልጣን ኮርቻ አስፈንጥሮ ለመጣል እውነቱን በሃሰት ቀይሮ እንደዘመናዊ የውጊያ ስልት መሳሪያ አድርጎ ሲጠቀምበትም መታየቱ የአደባባይ ምስጢር ነው። የሀሰት ምስክር ቀርቦበት ሞት የተፈረደበትን፤ ከርቸሌ የወረደውን፤ የተደበደበውን፤ የተንገላታውን፤ መልካም ስሙ የጎደፈውን፤ከማኅበራዊ ኑሮ የተገለለውን፤ ከማእረግ፤ ከሽልማት የታገደውን፤ ረዳት አጥቶ አልቅሶ የቀረውን ሰው ቤቱ ይቁጠረው! በማለት ብቻ ምንም እንዳልተፈጠረ የራሳችንም ሆነ የአካባቢያችንን ሁኔታ ላለመልከት የኅሊናችንን በር መዝጋት እንዴት ይቻለናል? ይልቅስ ለመናገር እንድፈር።
በዚህች ምድር ላይ የሀሰት መንገስ ጉዳይ በሥጋውያን ሰዎች ዘንድ አሳዛኝ መሆኑ ባይካድም አስተሳሰባቸው በሥጋዊ ደማዊ ኅሊና ላይ የሚመሠረት በመሆኑ ሀሰትን እንደመሳሪያ መጠቀማቸው ላይደንቅ ይችላል። አሳፋሪውና አሸማቃቂው ነገር እግዚአብሔርን እናውቃለን፤ የጽድቅ ልጆች ነን በማለት ዘወትር ስለቃሉ በመናገር ላይ ያለነው የእምነት ሰዎች ዘንድ እውነትን በሀሰት ተክተን እንደዘወትር ጸሎት በልባችን ላይ ጽፈን መያዛችንና ጠቃሚ መስሎ በታየን ጊዜና ቦታ ለዓላማችን ማስፈጸሚያ አገልግሎት ላይ ማዋላችን ነው። የሚዋሹ የሃይማኖት ሰዎች ብዙ ጊዜ እውነትን እውነት በምትመስልና ወደእውነት በተጠጋጋች ውበት የሚፈጽሟት ስለሆነ የዋሹ መስሎ አይሰማቸውም ወይም ውሸት መስሎ በተሰማቸው ጊዜ የኅሊናቸውን ቆሻሻ ለማጠብ ትንሽ ናት በምትል ምላሽ ውስጣቸውን አረጋግተው ከመንፈሳዊ ሰውነታቸው ምንም እንዳልጎደለ ራሳቸውን በራሳቸው አሳምነው ያንኑ መደበኛ ውሸታቸውን በተለመደው ጥበብ ይቀጥላሉ።
አንዳንዶቹም መዋሸታቸውን ቢያውቁም ምንም አዲስ ነገር እንዳልተፈጠረና ነባራዊ ክስተት አድርገው በመቁጠር ባገኙት ቦታ ሁሉ የአዞ እንባ እያነቡ፤ ለሃይማኖታቸው የሚውል እስከሆነ ድረስ ይህንኑ በዘመናዊ ውሸት አንዳንዴም ባስ ሲል ዘመነኞቹ «ቀደዳ »የሚሉትን ዓይነት ውሸት የዕለት ሕይወታቸው አድርገው ይዘውት ይታያሉ። ለምሳሌ«ኬንያ ውስጥ አንድ ግለሰብ ባንድ ጊዜ አንድ በርሜል ውሃ ጭልጥ አደረገ የሚልና ጃፓን ከምድር እስከሰማይ የሚደርስ እስክሪብቶ ገበያ ላይ አዋለች» የሚል የውሸትና የቀደዳ ንጽጽሮች ናቸው። እንደዚሁ ሁሉ የሃይማኖት ሰዎች የሚባሉት ይህንኑ የንጽጽር ተግባር ዘወትር ሲፈጽሙት ይታያሉ። ግን ሰዎች እውነትን እንዳይናገሩና ውሸትን ሥራቸው እንዲያደርጉ ያስገደደ ማነው?
ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ

Saturday, October 29, 2011

«ደመና ተበትኖ እንደሚጠፋ እንዲሁ ሲኦል የሚወርድ ዳግመኛ አይወጣም»ኢዮ7፤9



የትኛውም ሃይማኖት በንድፈ ሃሳብ ደረጃ (theoretically) ከሚያመልከው አምላክ ሕግና ትእዛዝ ከወጣ ቁጣና ቅጣት እንደሚጠብቀው የወል የእምነት ስምምነት አለ። ይህንኑ ቅጣት አስቀድሞ ለመከላከል በሕይወታቸው ሳሉ ያደርጉ ዘንድ የሰጣቸውን መመሪያ በሚችሉት አቅም ሁሉ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ተግባራዊ ለማድረግ ደፋ ቀና ማለታቸውም አይቀሬ ይሆናል። እንደዚያም ሆኖ ከሞተ በኋላ መልካሙ ሥራው መልካም ዋጋው ሆኖ ስለመከፈሉ ወይም ቁጣን ስለመቀበሉ ማረጋገጥ አይችሉምና ከአጠገባቸው ለተለየው ሟች በመሪር ልቅሶና በልዩ ልዩ ዓይነት የሥርዓት አቀባበር ሰውዬውን በመንከባከብ እንዲሁም በማሰማመር የልባቸውን ስሜት በጥሩ መንፈስ ለመሙላት ይጥራሉ። ምግብና መጠጥ፤ ማብሰያ ቁሳቁስና አልባሳትን ጭምር እዚያ በጉድጓዱ ከተማ እንዳይቸገር አብረው በመቅበር የችግሩ ልባዊ ተካፋዮች ለመሆን ሁሉን ያደርጉለታል። ጉድጓዱን ጥልቅ በማድረግ፤ ወደ ጎን ልዩ የኪስ ጉድጓድ በማዘጋጀት፤ የሬሳውን የማረፊያ አቅጣጫ ወደምሥራቅ፣ ወደምዕራብ ወይም በቁመት በመቅበርም ዘላለማዊ እረፍት ያገኝ ዘንድም ይደክሙለታል። አንዳንዶችም ሬሳውን ዛፍ ላይ በመስቀል ወይም በእሳት በማቃጠል ከአምላኩ እንዲታረቅ ይጥሩለታል። ይህንና ይህንን የመሳሰለውን ሁሉ ማድረጋቸው ሰውየው ዘላለማዊ እረፍትን እንዲያገኝ ከሚያመለከው አምላክ እንዲታረቅና ማድረግ ያለባቸውን ባለማድረጋቸው የሟች ነፍስ እንዳትከሳቸው ከመፍራት የተነሳ ነውጽሁፉን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ

Thursday, October 27, 2011

ማኅበረ ቅዱሳን ....




ይህ ማኅበረ ቅዱሳን የሚባለው ድርጅት ከብዙዎች ጋር እየተላተመ ነው። ይህንን መላተም ሚዲያዎች ሁሉ እያራገቡት ይገኛሉ። ነገሩ ምን ይሆን? እንዲያው ባጋጣሚ እየሆነ ያለ አይመስልም። «ከመምህሩ ደቀመዝሙሩ» እንዲሉ የማይገባበትና ቤተክርስቲያኗን ከጥቃት ለመከላከል በዚህ ዘመን ከሰማይ የወረድኩ እኔ ነኝ እያለ ነው ብለው ያሙታል። ጳጳሳቱ ተኝተዋል፤ ሰባክያኑም ጰንጥጠዋል፤ ተሃዳስያኑም በርክተዋል እያለም ይናገራል ሲሉ ብዙዎቹ ያወሩበታል። ጳጳሳቱ ከተኙ መንፈስ ቅዱስ እየመራቸው አይደለም ማለት ይሆን? ሰባክያኑ ከጰንጤቆስጤ ጎራ ከተቀላቀሉ እሱ ከየትኛው መንፈስ ጋር መሆኑ ነው? መታደስን የሕይወታቸው መመሪያ የሚደርጉ ከበዙ ታዲያ እሱ(ማኅበረ ቅዱሳን) ከምኑ ላይ ነው የቆመው? ለማንኛውም እንዲወገዙና እንዲረገሙ የጠየቀበትን አቤቱታ ለማወቅ እስኪ ይህንን ጽሑፍ ያንብቡለት።
(ጽሁፉን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)

Tuesday, October 18, 2011

የሕይወት ውሃ የት ይገኛል?



በዚህች ሰማርያ በሚባል ከተማ የምትኖር አንዲት ሴት ነበረች። በጥቂቱ በተገለጠው ታሪኳ ፭ ባሎች ነበሯት፤ ስድስተኛውም አብሯት ይኖራል። የምትኖረው በሲካር ከተማ ነው። ሲካርና ሴኬም ጎረቤታሞች ናቸውና የአምልኰ ስግደት የሚፈጽሙበት ገሪዛን የሚባል ተራራ በቅርቧ ይገኛል። ይህ ተራራ የበረከት ተራራ እንደሆነ ተነግሮ ስለነበረ ይኸው በረከት ከእርሱ እንደሚወርድ ከማሰብ ሰማርያውኑ ይሰግዱበታል። በዘዳግም ፲፩፤ ፳፱ ላይ እንዲህ የሚል ተጽፎ ይገኛልና። «....በረከቱን በገሪዛን ተራራ፤ መርገሙንም በጌባል ተራራ ታኖራለህ የሚል ቃል ስላለ በረከት ሲሹ ገሪዛን፤ መርገም ለማውረድ ጌባል ላይ ሲጸልዩ ኖረዋል። ኢዮአታምም በገሪዛን ተራራ ላይ ወጥቶ «የሴኬም ሰዎች ሆይ እግዚአብሔር እንዲሰማችሁ ስሙኝ» ሲል የተናገረውንም ይዘው እግዚአብሔር እንዲሰማቸው እነርሱም እዚሁ ተራራ ላይ ወደእግዚአብሔር ሲጮሁ ዘመናትን አልፈዋል።።( መሳ ፱፤፯) ይህች ውሃ ልትቀዳ ወደያዕቆብ የጉድጓድ ውሃ የወረደችው ሰማርያዊት ሴትም «አባቶቻችን በዚህ ተራራ ሰገዱ» ስትል ምስክርነቷን ሰጥታለች። አሁን እዚያ ለስግደት አልወረደችም፤ ይልቁንም ከአባቶቻቸው የውሃ ጉድጓድ አንዱ በሆነው ከያዕቆብ ጉድጓድ ውሃ ልትቀዳ ባዶ እንስራዋን ይዛ ነው የተጓዘችው። እዚያ የውሃ ጉድጓድ አጠገብ ደግሞ ከቀኑ ስድስት ሰዓት አካባቢ አንድ የደከመው ሰው ለእረፍት ተቀምጧል።(ዮሐ፬፤፮) ውሃ ሊቀዳ አይደለም። ስራውንም ጨርሶ እረፍት ይሻ ዘንድ የተቀመጠ እንዳልነበር እረፍት የሌለው ሥራው ማረጋገጫችን ነው። ይልቁንም ለተጠሙ የሕይወት ውሃ ቃሉን እያጠጣ እርካታንና እረፍትን ማግኘት ላይችሉ በገሪዛን ተራራና በጌባል ላይ ሲንከራተቱ ለኖሩት እርካታን ሊሰጣቸው እንጂ! ዛሬም ውሃ እየተጠሙ የሚፈልጉ፤ ጠጥተው ያልረኩ፤ በየጓሮአቸው የሚቆፍሩ፤ ኩሬውን ለማጣራት የሚባክኑ፤ ብዙ ደረቅ ወንዝ የተሻገሩ ሰዎች አሉ። የሕይወት ውሃ የት እንዳለ ቢሰሙም እንዴት እንደሚገኝ፤ አግኝተውትም እንዴት እንደሚጠጡት የማያውቁም ቁጥራቸው የትየለሌ ነው። አስፈሪው ነገር መፈለጋቸው ሳይሆን በብዙ ፍለጋ ሲባክኑ፤ በአይናቸው ሥር ያለውን የሕይወት ውሃ ተሰውሮባቸው ሳያገኙትና ጠጥተው ሳይረኩበት ሞት ባህረ ኤርትራ እንዳያሰጥማቸው ነው። የእርካታው ውኃ ከሰማይ መጥቶ ሳይጠጡትና ሳይረኩበት ሞት ማዕበል የኑሮ መርከባቸውን ሰባብሮ እስወዲያኛው ይዟቸው እንዳይሄድ ነው የሚያስጨንቀው። እስኪ ከዚህ ዓይነቱ አስፈሪ ጥማትና የሕይወት ውሃን ከማጣት ችግር የተላቀቀችውን የአንዲት ሰማርያዊት ሴት ታሪክ እንመልከትና እንደእሷው የሕይወት ወሃ ፍለጋ አቅጣጫችንን እናስተካክል።
(ሙሉውን ጽሑፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)

Thursday, October 13, 2011

ምን እናድርግ?








የብዙዎቻችን ምርጫ አንድ ዓይነት አይደለም። እንደየመልካችን ይለያያል። በሥጋዊ አስተሳሰብ ልዩነት ውበት ነው ሊባል ይችላል። ይሁን እንጂ ሥጋ ያለነፍስ ምውት እንደሆነ ሁሉ ለነፍሳችን የምንሰጠው የልዩነት ውበት ነው አባባል ዋጋ የለሽ ይሆናል። በነፍስ ዘላለማዊነት ውስጥ ልዩነት ውበት ነው የሚባል ታሪክ የለም። በዚህ ምርጫ ላይ ዘላለማዊ ውበትን ለማግኘት የግድ ምርጫችን አንድ ዓይነት ብቻ መሆን አለበት። የምንጊዜም ምርጫችን በሥጋ ዓለም እስካለን በክርስቶስ ላይ ካልተመሠረተ በነፍስ ዘላለማዊነት ላይ ልዩነት ውበት ነው የሚባል ሥጋዊ አባባል ዋጋ የለውም። ፍላጎታችንን የሚከተል ምርጫ የህይወታችን መሠረት ላይሆን ይችላል። እምነታችንን የሚከተለው ምርጫ ግን ለዘላለማዊ ኑሮ ወሳኝ ነው። ስለሆነም ምን እናድርግ?
ማንም ሰው የእግዚአብሔርን የፍቅርና የምህረት እንዲሁም የደህንነትን ጥሪ ከተቀበለ፣ ለመዳንና ኃጢአቱ እንዲሰረይለት የሚከተሉትን እንዲያደርግ መጽሕፍ ቅዱስ ያስተምረናል::

1ኛ ንስሐ መግባት:- "ይህንም በሰሙ ጊዜ ልባቸው ተነካ፣ ጴጥሮስንና ሌሎችንም ሐዋርያት:- ወንድሞች ሆይ፣ ምን እናድርግ? አሉአቸው:: ጴጥሮስም:- ንስሐ ግቡ...አላቸው::" ሐዋ 2፣37-38

"እንግዲህ እግዚአብሔር ያለማወቅን ወራት አሳልፎ፣ አሁን በየቦታቸው ንስሐ ይገቡ ዘንድ ሰውን ሁሉ ያዛል..." ሐዋ 17፣30

"ኃጢአታቸሁ ይደመሰስ ዘንድ ንስሐ ግቡ ተመለሱም::" ሐዋ 3፣20


ንስሐ መግባት ማለት በመጀመሪያ ኃጢአተኝነታችንና ፍርድ እንደሚጠብቀን አውቀን፣ ከእግዚአብሔር ዘንድ ኃጢአታችን ሁሉ በኢየሱስ ክርስቶስ ደም እንዲታጠብ መለመንና ከአሁን ጀምሮም በአዲስ ሕይወት እንጂ በድሮ በአጸያፊና ከእግዚአብሔር በተለየ ኑሮ ላለመኖር መቁረጥ ወይም መወሰን ነው:: ከእግዚአብሔር ጋር ታርቀን አዲስ ሕይወትን ለመጀመር የእኛ ውሳኔ አስፈላጊ ነው::

2ኛ በኢየሱስ ክርስቶስ ማመን:- ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነና ለሰው ልጆችም ብቸኛ የመዳን መንገድ እንደሆነ፣ ለኃጢአታችንም ሲል በመስቀል ላይ ደሙን እንዳፈሰሰና እንደ ሞተ እንዲሁም በሶስተኛው ቀን እግዚአብሔር ከሙታን እንዳስነሣውና በቀኙ እንዳስቀመጠው ከልብ ማመን:: በዚህ ምድር ላይ ቢሆን ወይም ከሞት በኋላ የነፍሳችን ጌታና ጠባቂ ኢየሱስ ብቻ እንደሆነ፣ እርሱም ከዘላለም ፍርድ ነፍሳችንን ሊያድን የሚችል ብቸኛ አዳኝ እንደሆነ ማመን::


Wednesday, October 12, 2011

ለስዕልና ለምስል ስግደትና በእነርሱ ፊት መጸለይ ይገባል?





ጥቅስ፤
   ኦሪት ዘሌዋውያን 26፥1 እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ነኝና ለእናንተ ጣዖት አታድርጉ፥ የተቀረጸም ምስል ወይም ሐውልት አታቁሙ ትሰግዱለትም ዘንድ በምድራችሁ ላይ የተቀረጸ ድንጋይ አታኑሩ። ኦሪት ዘዳግም 4 15 እግዚአብሔር በኮሬብ በእሳት ውስጥ ሆኖ በተናገራችሁ ጊዜ መልክ ከቶ አላያችሁምና እጅግ ተጠንቀቁ 16 እንዳትረክሱ፥ የተቀረጸውን ምስል የማናቸውንም ነገር ምሳሌ፥ በወንድ ወይም በሴት መልክ የተሠራውን፥ 17 በምድር ላይ ያለውን የእንስሳን ሁሉ ምሳሌ፥ በሰማይም በታች የሚበርረውን የወፍን ሁሉ ምሳሌ፥ 18 በምድርም ላይ የሚሽከረከረውን ሁሉ ምሳሌ፥ ከምድርም በታች በውኃ ውስጥ የሚኖረውን የዓሣን ሁሉ ምሳሌ እንዳታደርጉ፥ 19 ዓይኖችህን ወደ ሰማይ አንሥተህ አምላክህ እግዚአብሔር ከሰማይ ሁሉ በታች ላሉት አሕዛብ ሁሉ የሰጣቸውን ፀሐይንና ጨረቃን ከዋክብትንና የሰማይን ሠራዊት ሁሉ ባየህ ጊዜ፥ ሰግደህላቸው አምልከሃቸውም እንዳትስት ተጠንቀቅ። 

 ጥቅስ፤
   ኦሪት ዘጸአት 20፥4 በላይ በሰማይ ካለው፥ በታችም በምድር ካለው፥ ከምድርም በታች በውኃ ካለው ነገር የማናቸውንም ምሳሌ፥ የተቀረጸውንም ምስል ለአንተ አታድርግ። እግዚአብሔር እስራኤላውያንን ከግብጽ ካወጣ በኋላ አንዱ የሰጣቸው ትልቁ ትእዛዝ ቢኖር ምንም አይነት ምስል ወይም የተቀረጸ ነገር በፍጹም እንዳያደርጉ ነው። የሰውም ይሁን የእንስሳ ወይም የፀሐይና ጨረቃ ወዘተ ማናቸውንም ምስል ወይም ምሳሌ ማድረግ ክልክል ነው። ስለዚህም አይሁዶች እስከ ዛሬም ድረስ በምኩራባቸው የሰውም ይሁን የሌላ ነገር ስእልና ሃውልት ወዘተ አያደርጉም። ምክንያቱም በቃሉ እጅግ የተከለከለ እና ጣኦትን እንደማምለክ የሚቆጠር ስለሆነ ነው።

Sunday, October 9, 2011

የደም መስዋእት






እግዚአብሔር ለሰው ልጆች ሊያደርግላቸው ከሚፈልገው ነገሮች ሁሉ ዋናውና ትልቁ ነገር ኃጢአትን ማስወገድ ነው:: ኃጢአት የሰዎች የችግራቸውና የመከራቸው ዋነኛ ሥርና ምክንያት ነውና:: የሕይወትና የበረከት ምንጭ ከሆነው ከአምላካቸው ከእግዚአብሔር ያለያያቸውና ያጣላቸው ዋናው ነገር ኃጢአት ነው:: ኃጢአት በሰዎች ታሪክ ሁሉ የሰው ልጆች የሞትና የመከራ፣ የሃዘንና የለቅሶ ምንጭ ነው:: የሰዎችን ከእግዚአብሔር መራቅ ስለዚህም ደግሞ የሕይወት እርካታ አለማግኘታቸውና የመቅበዝበዛቸው፣ እርስ በርስ ፍቅር የማጣታቸው፣ በመጨረሻም ለዘላለም ፍርድና ስቃይ ለሲኦልም የሚያበቃቸው ዋነኛ ክፉ የሰዎች ጠላት ኃጢአት ነው::            ( የቀረውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)

Wednesday, October 5, 2011

መላእክት የሚወጡበትና የሚወርዱበት የሰማይ መሰላል
















"አሁንም የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል:-


ልባችሁን በመንገዳችሁ ላይ አድርጉ::" ሐጌ 1፣5


የእግዚአብሔር ቃል ልባችንን በመንገዳችን ላይ እንድናደርግ ይመክረናል:: በምን አይነት መንገድ ላይ እየተጓዝን እንዳለን ልንመረምር ይገባናል:: ከሁሉም በላይ መንገዱ ወዴት እንደሚወስድና እንደሚያመራ በትክክል ማወቅ አለብን:: በምድር ላይ ብዙ መንገዶች አሉ፣ ሁሉም ግን ያሰብነው ስፍራ አያደርሱንም:: ስለዚህ ትክክለኛውን መንገድ መምረጥና መጓዝ ከዚያም ልባችንን በመንገዳችን ላይ አድርገን መመርመር ይገባናል::

ዛሬ ብዙ ሰዎች በመኪናቸው ወዴት እንደሚሄዱ ያውቃሉ፣ የተሳፈሩትም አውቶቡስ የት እንደሚያደርሳቸው ጠንቅቀው ያውቃሉ፣ እንዲያውም አንዳንድ ሰዎች እጅግ የሚያስገርም የመንገድ እውቀት አላቸው:: ነገር ግን ብዙዎቹ የሕይወታቸው ጉዞ ወዴት እንደሚያደርሳቸው አያውቁም:: የመረጡት ሕይወት መጨረሻው ምን እንደሆነ እርግጠኞች አይደሉም:: የተሳሳተ መንገድ ላይ ይሁኑ አይሁኑ የሕይወታቸውን መንገድ የማይመረምሩ ጥቂቶች አይደሉም::

ወገኔ ሆይ፣ ወዴት እየሄድክ ነው? ይህ አኗኗርህ ወዴት ያደርስሃል? ትክክል ነው ብለህ የምትከተለው ሕይወትህና ሃይማኖትህ መጨረሻው ምንድነው? የተሳፈርክበት የሕይወትህ አውቶቡስ ወዴት እንደሚወስድህ በእርግጥ ታውቅ ይሆን? ወይስ ወዴት እየሄድክ እንደሆነ ቆም ብለህ አትመረምር ይሆን? ምናልባትም የትኛውንም መንገድ ብመርጥ ግድ የለም ትል ይሆናል:: የእግዚአብሔር ቃል ግን እንዲህ ሲል ይመክረናል:-
"ልባችሁን በመንገዳችሁ ላይ አድርጉ"!

Tuesday, October 4, 2011

መጥተህ እይ


አንድ ጊዜ ኢየሱስን ሊሰሙትና ከእርሱ ሊማሩ፣ ከበሽታቸውና ካለባቸው ስቃይ ሁሉ ነፃ ሊወጡ ወደ እርሱ ብዙ ሕዝብ ይቀርቡ ነበር:: ከእነዚህም ውስጥ የታወቁ ኃጢአተኞች ይገኙበት ነበር:: ጌታም እነዚህን ሲቀበላቸው፣ ከእነርሱም ጋር ሲበላና ሲጠጣ የዚያን ዘመን የሃይማኖት ሰዎች አይተው እርስ በርሳቸው አንገራገሩ "ይህስ ኃጢአተኞችን ይቀበላል፣ ከእነርሱም ጋር ይበላል" አሉ:: ሉቃ 15፣1-2 እስከ ዛሬ ድረስም የተለያዩ የሃይማኖት ተከታዮችን ወይም ሃይማኖተኞችን ግራ የሚያጋባቸውና የሚገርማቸው አንዱ ነገር ይሄ ነው:: እንዴት ታላቅ ነብይ በኃጢአተኞች መካከል ይቀመጣል? እንዴት የእግዚአብሔር ልጅ በተናቁ መካከል ያስተምራል? እንዴት ጻድቅ የሆነው ኢየሱስ ከኃጢአተኞች ጋር ይበላል? እንዴትስ ከእነርሱ ጋር ይጠጣል? ይሄ ነው እንግዲህ በመጽሐፍ ቅዱስ የተገለጸውን አምላክ ከሌሎች አማልክቶች የሚለየው:: ለሰው አዕምሮ ከባድ የሆነውና ሊቀበለው የሚያስቸግረው፣ ዮሐንስም ደግሞ ሊገልጽልን የሚፈልገው ትልቅ ቁም ነገር ይህ ነው::
"ቃልም ሥጋ ሆነ ጸጋንና እውነትንም ተሞልቶ በእኛ አደረ፣ አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነውን ክብሩን
 አየን::" ዮሐ 1፣14

እጅግ የሚገርመው ነገር ቃል ከሁሉ በፊት ከእግዚአብሔር ጋር መኖሩና ሁሉ ነገር በእርሱ መፈጠሩ ብቻ አይደለም:: በጣም የሚያስደንቀው፣ ለብዙ የሃይማኖት ሰዎችም ግራ የሚያጋባውና ለመረዳት የሚከብደው፣ ይህ ራሱ አምላክ የሆነው ቃል (ኢየሱስ ክርስቶስ) ሥጋ መሆኑ ነው:: አምላክ እንዴት ሰው ይሆናል? እንዴት ሥጋ ይሆናል? እንዴትስ በኃጢአተኞች መካከል ይመላለሳል? የእግዚአብሔርን ፍቅር የተለየና ከመታወቅም በላይ የሚያደርገው አንዱ ነገር እንግዲህ ይህ ነው::



«ሲያያት በሕይወት ይኖራል»








ወገኔ ሆይ፣ አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ:- ታምመህ ታውቃለህ? በእርግጥ የበሽታን ምንነት በሕይወትህ ቀምሰህ ይሆን? መልስህ አዎን እንደሚሆን እገምታለሁ:: በሽታን የማታውቅ ከሆንክ ደግሞ እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን:: በሽታ መልካም አይደለምና:: የሰውን ሙሉ ጤንነት እያናጋ፣ ሰዎች እንደሚገባው እንዳይኖሩና እንዳይሠሩ የሚያደርግ ትልቅ እንቅፋት ነው:: ብርታትን ወደ ድካም፣ ውፍረትን ወደ ክሳት፣ ደስታንም ወደ ሃዘን የሚለውጥ በመጨረሻም ለሞት የሚያበቃ ክፉ የሰዎች ጠላት ነውና::

በአሁኑ ዘመን ግን ለብዙ በሽታዎች መድኃኒት ስላለ እግዚአብሔር ይመስገን:: ያለ መድኃኒት እንዴት እንሆን ነበር? ያለ መድኃኒትና ያለ እርዳታ እናቶች የልጆቻቸውን በሽታና ስቃይ እየተመለከቱ እንዴት ይሆኑ ነበር? የምንወዳቸው ወገኖቻችን በትንሹም በትልቁም በሽታ ሲሰቃዩና ሲረግፉ ማየት እንዴት ያሰቅቃል:: ዛሬም መድኃኒትና ሕክምና በሌለባቸው ቦታዎች፣ ሕጻናት ገና በለጋ እድሜያቸው በበሽታ ይቀጫሉ:: ሕክምናና መድኃኒት ባለማግኘት ሕይወታቸው የሚያልፈው የወጣቶችና የጎልማሶች ቁጥር ጥቂት አይደለም::


ሕክምና ባለበት አካባቢ ግን የሰዎች እድሜ የረዘመና ሽማግሌዎችና አዛውንት የበዙበት ይሆናል:: ሕጻናት በጤንነት ሲጫወቱና ሲቦርቁ ማየት እንዴት ደስ ይላል:: ሰዎች ያለ ስቃይ ሲወጡና ሲገቡ በደስታም ሲመላለሱ ማየት እንዴት መልካም ነገር ነው::

Wednesday, September 28, 2011

የልባችሁን መንገድ ጥረጉ









የእግዚአብሔርን መንገድ አዘጋጁ
ብዙ ዘመናት አስቀድሞ ኢሳያስ መሢሕ መድኃኒት ከመምጣቱ በፊት መልእክተኛ እንደሚመጣ ትንቢት ተናግሮ ነበር፡፡ ትንቢቱ እንዲፈጸም ክርስቶስ ያ ደኀንነት ከመጀመሩ በፊት የቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ አባት ዘካርያስ በትንቢት ተናግሮ እንደነበር እግዚአብሔር ለእስራኤል ልጆች ኢየሱስን መድኃኒታቸውን እንደቀበሉ ሰበከላቸው፡፡ የእግዚአብሔር መንግስት ቀርቦአልና ስንሐ ግቡ እያለ በበረሃ የሚጮህ የአዋጅ ቃል ለእግዚአብሔር የሚሆን መንገድ አዘጋጁ፣ መንገዶቹ አቅኑ፣ ጉድጓዶች ይሞሉ፣ ተራራና ኮረብታ ሁሉ ዝቅ ይበል፣ ዳገትና ቁልቁለቱ ሜዳ ይሁን፣ ወጣገባው መሬት ይደልደል፣ የእግዚአብሔር ክብር ሊገለጥ ነውና፡፡
ከእግዚአብሔር የሚመጣ ሁሉ በነፍስ ወከፍ ደኅንነት ያገኛል፡፡ ምክንያቱም እግዚአብሔር ተናግሮአል በማለት የኢሳይያስን ትንቢት እየጠቀሰ ለአይሁዳውያን የኢየሱስን መምጣት አስታወቃቸው፡፡ ሊያድናችሁ ከሰማይ የሚመጣውን መሢሕ በልባቸው አምነው እንዲቀበሉ መከራቸው፡፡ ከዓመት ዓመት ከዘመን ዘመን ቤተክርስቲያን ለእኛም የእግዚአብሔርን መንገድ አሰናዱ ጥረጉ የሚለውን የመጥምቁ ዮሐንስን አዋጅ አድጋሚ ትነግረናለች፡፡ እንዴት አድርገን ነው የምናዘጋጀው? ቅዱስ ዮሐንስ “ንስሐ ግቡ” እንዳለን ንስሐ ገብተን የእግዚአብሔርን መንገድ እናዘጋጅ፡፡
ሕፃኑ ኢየሱስ ወደ እኛ የሚመጣበትን መንገድ ልናዘጋጅ እርሱ የሚጠላውን የሚከለክለውን የኃጢአትን መንገድ ትተን የሚወደውንና ተደስቶ ወደ እኛ እንደመጣ የሚያደርገውን የጽድቅ መንገድ እንድንይዘ ያስፈልገናል፡፡ ወደ እኛ እንዳይመጣ የሚከለክል የኃጢአት ተራራ ጥል፣ ቅንዓት፣ ሁከት፣ ዝሙት፣ ቂም በንስሐ መደምሰስ አለብን፡፡ በውስጣችን የሚገኝ የመንፈስ ቅዝቃዜ የመንፈሳዊነት ጉድለት በጸሎት በተጋድሎ በበጐ ሥራ በትሕትና በፍቅር በየዋሕነት በምሕረት በትዕግስት በሃይማኖት በእምነት እንድንሞላው ያስፈልገናል፡፡ ጠመዝማዛ አሰተሳሰብና አረማመድ እንዲቀና ንግግራችንና ሥራችን የታረመ እንዲሆን ሕይወታችን በሙሉ ከእግዚአብሔር ፈቃድ ጋር እንዲስማማ አድርገን መዘጋጀት አለብን፡፡

እንደዚህ ያለ መንገድ ከጠረግን ሕፃን ኢየሱስ ተደስቶ ወደ እኛ በመምጣት ወደ ልባችን ይገባል፡፡ መለኮታዊውን ሕፃን በመንፈስ ንጹሐን ሆነን ተዘጋጅተን ከአገኘነው በኋላ በመንፈስ እንደገና እንደምንወለድ የልደቱን ጸጋ ያድለናል፡፡
ልደት ለነፍሳችን እንጂ ሥጋችንን እንዲጠቅም የተዘጋጀ አይደለም፡፡ ልደት በሥጋ የምንደሰትበት የምንጠጣበት የምንለብስበት በነፍስ ግን ተርበን ተጠምተን በጸጋ ራቁታችን የምንወጣበት የምንውልበትና ነፍሳችን የምትጐዳበት የምታዝንበት ቀን ሊሆን አይገባም፡፡ ልደት የነፍስ በዓል ነው፡፡ ስለዚህ በዚህ ቀን ነፍሳችን በጸጋና በመንፈሳዊ ደስታ መሞላት አለበት፡፡ ይህን እንድናገኝ ደግሞ አስቀድመን በሚገባ ልንዘጋጅ ያስፈልጋል፡