Saturday, October 29, 2011

«ደመና ተበትኖ እንደሚጠፋ እንዲሁ ሲኦል የሚወርድ ዳግመኛ አይወጣም»ኢዮ7፤9



የትኛውም ሃይማኖት በንድፈ ሃሳብ ደረጃ (theoretically) ከሚያመልከው አምላክ ሕግና ትእዛዝ ከወጣ ቁጣና ቅጣት እንደሚጠብቀው የወል የእምነት ስምምነት አለ። ይህንኑ ቅጣት አስቀድሞ ለመከላከል በሕይወታቸው ሳሉ ያደርጉ ዘንድ የሰጣቸውን መመሪያ በሚችሉት አቅም ሁሉ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ተግባራዊ ለማድረግ ደፋ ቀና ማለታቸውም አይቀሬ ይሆናል። እንደዚያም ሆኖ ከሞተ በኋላ መልካሙ ሥራው መልካም ዋጋው ሆኖ ስለመከፈሉ ወይም ቁጣን ስለመቀበሉ ማረጋገጥ አይችሉምና ከአጠገባቸው ለተለየው ሟች በመሪር ልቅሶና በልዩ ልዩ ዓይነት የሥርዓት አቀባበር ሰውዬውን በመንከባከብ እንዲሁም በማሰማመር የልባቸውን ስሜት በጥሩ መንፈስ ለመሙላት ይጥራሉ። ምግብና መጠጥ፤ ማብሰያ ቁሳቁስና አልባሳትን ጭምር እዚያ በጉድጓዱ ከተማ እንዳይቸገር አብረው በመቅበር የችግሩ ልባዊ ተካፋዮች ለመሆን ሁሉን ያደርጉለታል። ጉድጓዱን ጥልቅ በማድረግ፤ ወደ ጎን ልዩ የኪስ ጉድጓድ በማዘጋጀት፤ የሬሳውን የማረፊያ አቅጣጫ ወደምሥራቅ፣ ወደምዕራብ ወይም በቁመት በመቅበርም ዘላለማዊ እረፍት ያገኝ ዘንድም ይደክሙለታል። አንዳንዶችም ሬሳውን ዛፍ ላይ በመስቀል ወይም በእሳት በማቃጠል ከአምላኩ እንዲታረቅ ይጥሩለታል። ይህንና ይህንን የመሳሰለውን ሁሉ ማድረጋቸው ሰውየው ዘላለማዊ እረፍትን እንዲያገኝ ከሚያመለከው አምላክ እንዲታረቅና ማድረግ ያለባቸውን ባለማድረጋቸው የሟች ነፍስ እንዳትከሳቸው ከመፍራት የተነሳ ነውጽሁፉን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ