Thursday, October 27, 2011

ማኅበረ ቅዱሳን ....




ይህ ማኅበረ ቅዱሳን የሚባለው ድርጅት ከብዙዎች ጋር እየተላተመ ነው። ይህንን መላተም ሚዲያዎች ሁሉ እያራገቡት ይገኛሉ። ነገሩ ምን ይሆን? እንዲያው ባጋጣሚ እየሆነ ያለ አይመስልም። «ከመምህሩ ደቀመዝሙሩ» እንዲሉ የማይገባበትና ቤተክርስቲያኗን ከጥቃት ለመከላከል በዚህ ዘመን ከሰማይ የወረድኩ እኔ ነኝ እያለ ነው ብለው ያሙታል። ጳጳሳቱ ተኝተዋል፤ ሰባክያኑም ጰንጥጠዋል፤ ተሃዳስያኑም በርክተዋል እያለም ይናገራል ሲሉ ብዙዎቹ ያወሩበታል። ጳጳሳቱ ከተኙ መንፈስ ቅዱስ እየመራቸው አይደለም ማለት ይሆን? ሰባክያኑ ከጰንጤቆስጤ ጎራ ከተቀላቀሉ እሱ ከየትኛው መንፈስ ጋር መሆኑ ነው? መታደስን የሕይወታቸው መመሪያ የሚደርጉ ከበዙ ታዲያ እሱ(ማኅበረ ቅዱሳን) ከምኑ ላይ ነው የቆመው? ለማንኛውም እንዲወገዙና እንዲረገሙ የጠየቀበትን አቤቱታ ለማወቅ እስኪ ይህንን ጽሑፍ ያንብቡለት።
(ጽሁፉን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)