Showing posts with label ዜና. Show all posts
Showing posts with label ዜና. Show all posts

Saturday, December 28, 2013

በከፊቾ ዞን የጽላት ዝርፊያና ቀበኞቹ "


ባለሃብቶች በእድሳት ስም ቤተ መቅደስ ዘልቀው ጽላት ይቀይራሉ" (የጽሁፍ ምንጭ፤ ጎልጉል የድረ ገጽ ጋዜጣ )
በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ክልል በከፊቾ ዞን በጥንታዊ አድባራት ጽላት መዘረፉን እናውቃለን ያሉ ለጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ ገለጹ። የዜናው ምንጮች የዞኑ አገረ ስብከት በዞኑ በሚገኙ አድባራት ላይ ምርመራ እንዲያካሂድ ጠይቀዋል። ዝርፊያውን የሚያካሂዱት “ባለሃብቶች” መቀመጫቸውን አዲስ አበባና ጅማ ከተማ ያደረጉ የክልሉ ተወላጆች መሆናቸውን አስታውቀዋል። ነዋሪነታቸው ቦንጋና ጊምቦ እንደሆነ የሚገልጹት የዜናው ምንጮች “ቀበኞች” በማለት የሚጠሯቸውን የጽላት ዘራፊዎች የዝርፊያ ስልት ተናግረዋል። በመጀመሪያ እድሜ ጠገብ የሆኑትን አድባራት ይለያሉ። በቃፊሮቻቸው አማካይነት መረባቸውን ዘርግተው ሰዎችን ያጠምዳሉ። ህዝበ ክርስቲያን በሚሰበሰብበት ወቅትና ዓመታዊ የበዓላትን ቀን መርጠው በርዳታና በእድሳት ስም ውዳሴ ይቀበላሉ።
በዞኑ የሚገኙት አቢያተ ክርስቲያናት እድሜ ጠገብ በመሆናቸው በርካታ ጥንታዊ ቅርስም እንዳላቸው የሚጠቁሙት ክፍሎች “ያረጁትን አድባራት እናድሳለን በማለት ጥቁር ለምዳቸውን ለብሰው መቅደስ ውስጥ ይዘልቃሉ” በማለት የዝርፊያው ድራማ እንዴት እንደሚከናወን ያስረዳሉ።
ለሃይማኖታቸው የቀኑና የታመኑ የቤተ መቅደስ ጠባቂዎችና አገልጋዮች ሲያጋጥሟቸው መቅደስ ውስጥ ተመላልሰው በሚሰበስቡት መረጃ መሰረት አብረቅራቂ ሃሰተኛ ጽላት በመተካት ዝርፊያ እንደሚካሂዱ፣ ለዝርፊያ የሚመችና ስብናው የወደቀ አገልጋይ ሲያገኙም በግልጽ ያሻቸውን አድርገው ስርቆቱን እንደሚፈጽሙ የዜናው ሰዎች ያስረዳሉ። ድርጊቱ የቆየና ሰዎቹም የሚታወቁ እንደሆኑ የሚጠቁሙት እነዚሁ ክፍሎች፣ “ቀበኞቹ” ካላቸው የገንዘብ አቅም አንጻር እጃቸው ከወቅቱ ጉልበተኞችና የቤተ ክህነት ከፍተኛ አመራሮች ጋርም የጠበቀ ግንኙነት ሊኖራቸው እንደሚችል ከግምት በላይ አመላክተዋል። በዚህ ተነሳ “እንፈራለን፤ ፊት ለፊት ለመግጠምም እንቸገራለን” በማለት ለጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ ምስጢራቸው እንዲጠበቅ አስጠንቅቀው መረጃውን ለመስጠት ችለዋል።
“ይህንን ዜና ጥቅማቸው የሚነካና ችግር ያለባቸው አካላት ዙሪያ ያሉ ጥቅመኞች ሊያስተባብሉት ይችሉ ይሆናል” ሲሉ ዜናው የሚያስደነግጣቸው ክፍሎች የሚወስዱትን የመጀመሪያ ርምጃ ያመላከቱት ተቆርቋሪዎች፣ “የእኛ ጥያቄ ግን ማጣራትና ምርመራ ተደርጎ ውጤቱ ከታወቀ በኋላ እውነታው እንዲረጋገጥ ነው” ብለዋል።
የዞኑ አገረ ስብከት ዛሬ ነገ ሳይል በተቀደሱ የማምለኪያ አድባራት ላይ የተፈጸመውንና እየተፈጸመ ያለውን ዝርፊያ የማጣራት ሃላፊነት እንዳለበት ያሳሰቡት ክፍሎች፣ ቀበኞቹ በርዳታ ስም እድሳት ባካሄዱባቸው አድባራት ላይ የሙከራ ምርመራ ቢደረግ ጥቆማው ምላሽ እንደሚያገኝም በርግጠኛነት ተናግረዋል።
በእድሳትና በርዳታ ስም መቅደስ በመዝለቅ ከሚከናወነው ዝርፊያ በተለየ በድርድር የሚካሄዱም ዝርፊያዎች ስለመኖራቸው ያመለከቱት ክፍሎች “ጉዳዩ እጅግ ጥንቃቄ የሚፈልግ በመሆኑ ስምና ቦታን ለይተን ለመጠቆም እንቸገራለን” ብለዋል። “መልዕክቱ ለቀበኞቹ፣ ለተባባሪዎቻቸውና የሚሰማ ተቆጣጣሪ አካል ካለ ለነሱ ነው” ሲሉም አክለዋል። በዞኑ ያሉ የህዝብ ወኪል እንደራሴዎችም በዚህ ጉዳይ ላይ ጥንቃቄ ወስደው እንዲሰሩ ጠይቀዋል።
“የቃል ኪዳን ጽላት ዘርፎ ከማነከስና ሰልሎ ከመሞት ውጪ ሌላ ዕድል የለም” ሲሉ ማስጠንቀቂያ ያስተላለፉት ተቆርቋሪ አዛውንቶች በ2005 መገባደጃ ላይ ዋሻ ውስጥ ተገኘ የተባለ ጽላት የት እንደገባ እንደማይታወቅ አመልክተዋል። ዜናው የመገናኛ ሰዎች ዘንድ ሁሉ ደርሶ እንደነበር፣ ነገር ግን በማይታወቅ ሁኔታ ተዳፍኖ መቅረቱ ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ አካላትን እስካሁን እንደሚከነክናቸው አመልክተዋል።

Saturday, December 21, 2013

(ሰበር ዜና) የአዲስ አበባ አድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች፤ ፀሐፊዎችና አጠቃላይ ማኅበረ ካህናቱ ለብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ አቤቱታቸውን አቀረቡ!


     ስድስት ገጽ የያዘው የማኅበረ ካህናቱ አቤቱታ በግልባጭ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤት፤ ለፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን፤ ለፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስትርና ለሚመለከታቸው ክፍሎች ሁሉ ገቢ መደረጉን ለማወቅ ተችሏል!
         (ደብዳቤውን ከታች አቅርበንላችኋል)
        ማኅበረ ቅዱሳን የቤተ ክርስቲያኒቱ ሲኖዶስ አይደለም በማለት ያሳሰቡ ሲሆን ይህ ተረፈ ደርግና በቤተ ክርስቲያን ታዛ የተጠለለ ነጋዴ ድርጅት የመጨረሻ እልባት ሊሰጠው የሚገባው ወቅት አሁን ነው በማለት ጠየቁ!
        ማኅበረ ቅዱሳንና ታማኝ አገልጋዮቻቸው ሊቃነ ጳጳሳት በሚፈጥሩት ሁከት ቤተ ክርስቲያናችን እየታመሰች መቀጠሏ ማቆም አለበት በማለት ድምጻቸውን ሲያሰሙ ውለዋል!
        የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ችግር ከአጠቃላይ የቤተ ክርስቲያኒቱ ችግር ጋር በሲኖዶስ የሚታይና የአስተዳደር ለውጥ ለማድረግም ሲኖዶሱ በሚሰጠው መመሪያ በምሁራን ልጆችዋ፤ በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፤ በሕግ አዋቂዎች፤ በአስተዳደርና በማኔጅመንት እውቀትና ልምድ ባላቸው አባላት ሰፊ ጊዜ ተሰጥቶት በሚቀርብ የማሻሻያ ረቂቅ ደንብ እንጂ ቤተ ክርስቲያኒቱ ሀብትና ንብረቴን መቆጣጠር አትችልም ባለ ዐመጸኛ ቡድን መሆን ስለማይገባው ቅዱስ ፓትርያርኩ አስቸኳይ መፍትሄ ይስጡን በማለት ተጠይቀዋል!
        21 ዓመት የተሸከምነውን ይህን ማኅበር ከእንግዲህ ተሸክመን በዚህ ዓይነት መልኩ ለመዝለቅ ስለማንችል መንግሥት አንድ እልባት እንዲሰጠን እንጮሃለን ብለዋል! በቃ የሚባልበት ወቅት ቢኖር አሁን ነው ያሉት ተሰብሰባዎቹ ወደፊት በዚህ ማኅበር ምክንያት ለሚመጣው ጉዳት ኃላፊነቱን አንወስድም ሲሉ ያላቸውን ፍርሃትም አሳስበዋል!
        ቅዱስ ፓትርያርኩም ጉዳዩን በቀላሉ እንደማይመለከቱትና መፍትሄም እንደሚሰጡ ቃል የገቡላቸው ሲሆን ማኅበረ ካህናቱ ያላቸውን ችግር ለመፍታትና ለመነጋገር የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ አዳራሽ ክፍት ሆኖ እንደሚያገለግላቸው ገልጸውላቸዋል!
     ከታች የቀረበው ጽሁፍና ማመልከቻ ለቅዱስ ፓትርያርኩ በጠቅላይ ቤተክህነቱ አዳራሽ የቀረበ የማኅበረ ካህናቱ ፊርማና አቤቱታ ነው።
                       ዐቢይ ዜና

ማኅበረ ቅዱሳን በአዲሱ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት መዋቅራዊ ለውጥ ምክንያት እየደረሰበት ያለው ተቋሞ ተጋግሎ ቀጥሏል፡፡ በየሆቴሉ በድብቅ ይሰበሰባሉ ሲባሉ የቆዩት የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት አለቆች በገሀድ በጠቅላይ ቤተክህነት አዳራሽ ተሰብስበው ፓትርያርኩንና አንዳድ የማኅበሩን ደጋፊ ሊቃነ ጳጳሳት አስጠነቀቁ፡፡ ጥያቄዎቻችን ምላሽ የማያገኙ ከሆነ የቤተክርስቲያኒቱ አስተዳደር በጥቁር ራስ (መነኮሳት ባልሆኑ) ሰዎች እንዲካሄድ በሕጋዊ መልኩ እንደሚጠይቁ አስረድተዋል፡፡
የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት ሰራተኞች ቤተክርስቲያኒቱ የአሰራር ለውጥ እንደሚያስፈልጋት አምነው ለውጡ ሁለንተናዊና መላውን የቤተክህነቱ ክፍል ሊያቅፍ እንደሚገባ ሕጉም ከዋናው ከሕገ ቤተክርስቲያን መጀመር እንዳለበትና በየደረጃው ደንቦችና መመሪያዎች ሊወጡ እንደሚገባው አስረድተው ይህንን የሚሰራው አካልም ከቅዱስ ሲኖዶስ፣ ከሊቃውንት ጉባዔ፣ በየደረጃው ከሚገኙ የቤተክርስቲያኒቱ መዋቅር ሰራተኞች ፣ ከገለልተኛ ባለሙያዎች ምእመናንና የሰንበት ት/ቤት ተወካዮች በተወጣጣ ኮሚቴ መሰራት እንደሚገባው አስምረውበታል፡፡
ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ጥያቄያችሁ በቀላሉ የሚታይ አይደለም ትኩረት ይፈልጋል  በማለት ኮሚቴ እንዲቋቋም ፈቅደዋል በቤተክህነቱ አዳራሽ መሰብሰብ እንደሚችሉ አረጋግጠውላቸዋል፡፡ስብሰባው ያበሳጫቸው አቡነ እስጢፋኖስ ግለቱ ከብዷቸው ወደ አሜሪካ እንደሚሄዱ ተናግረዋል፡፡
ጥናቱ ግልጽነት የጎደለውና ቤተክርስቲያኗን ለአንድ ማኅበር ድብቅ ዓላማ እና ፍላጎት አጋልጦ የሰጠ በመሆኑ፣ የካህናት ቅነሳ በሚል አገልጋዮችን የሚበትን ፣ ቤተክርስቲያኒቱ ያሏትን ሊቃውንት ያላካተተ በመሆኑ፣ የሰንበት ትምህርት ቤትን በማዳከም በአጥቢያ ቤተክርስቲያናት ብዙ ማኅበር እንዲደራጅና ሕጋዊ እንዲሆን በማድረግ በወጣቱ ዘንድ መከፋፈል የሚፈጥር በመሆኑ እንደማይቀበሉት  አስታውቀዋል፡፡    ማኅበረ ቅዱሳን  በጥቅምቱ የሰበካ ጉባዔ ምልአተ ስብሰባ በተወሰነው መሠረት  የ55 ሚሊዮን የቤተክርስቲያኗ ምእመናን ካህናትና የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች በወሰኑትባ በአቋም መግለጫ ባጸኑት ውሳኔ  መሠረት  ሀብትና ንብረቱን እንዲያሳውቅና በቤተክርስቲያኗ አሰራር መሠረት በሕጋዊ ሞዴሎች እንዲጠቀም ለቅዱስ ሲኖዶስ አባላትና ለቅዱስ ፓትርያርኩ በ 5000 ሰራተኞች ፊርማ በቀረበውና ለመንግሥት አካላት ግልባጭ በተደረገው ደብዳቤ ተጠይቋል፡፡
በማኅበረ ቅዱሳን በተዘጋጀውና ለአዲስ አበባ ሀገረ ሰብከት ብቻ እንዲተገበር በታለመው የመዋቅራዊ ጥናት ምክንያት  በሀገረ ስብከቱ ሥር በሚገኙ አድባራትና ገዳማት ሠራተኞችና በማኅበረ ቅዱሳን መካከል ያለው አለመግባባት ቀጥሏል፡፡ መዋቅራዊ ጥናቱን ይቃወማሉ የሚባሉት የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የአድባራት ሰራተኞች ባሳለፍነው ሳምንት ረቡዕ ወደ ጠቅላይ ቤተክህነት በማምራት ቅዱስ ፓትርያርኩንና ብፁአን ሊቃነ ጳጳሳትን አነጋግረዋል፡፡ የአቋም መግለጫቸውንም ለፓትርያርኩ ሰጥተዋል፡፡ በመድረኩ ማኅበረ ቅዱሳን አንድ የቤተክርስቲያን አካል ሆኖ እያለ ለመላዋ ቤተክርስቲያን መመሪያ አውጪ መሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስ ሥልጣን ወዴት ነው ያለው እንዳስባላቸው ተሰብሳቢዎቹ ለፓትርያርኩ አስረድተዋል፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን እራሱ ለቃለ አዋዲውና ለሕገ ቤተክርስቲያን ሳይገዛ እንዴት ሕግ አውጪ ሊሆን ቻለ? የሚል ጥያቄ አንስተዋል፡፡ መመሪያ የሚያስፈልግ በመሆኑ ከሕገ ቤተክርስቲያን ጀምሮ በየደረጃው መመሪያና ደንብ እንዲወጣና ይህንንም አንድ ማኅበር ሳይሆን የቤተክርስቲያኒቱ መዋቅር ውስጥ ያሉ እና ገለልተኛ አካላት ሊያዘጋጁት ይገባል ብለዋል፡፡ ተሰብሳቢዎቹ ማኅበሩ መዋቅራዊ ጥናቱን ለምን በድብቅ መስራት አስፈለገው፣ ሊቃውንት ለምን እንዲሳተፉ አልተፈለገም የሚሉ ጥያቄዎች ተነስተዋል፡፡ ለጥያቄዎቹ መልስ በሚሰጥበት ወቅት ብፁዕ አቡነ ሉቃስ የማኅበሩ የኢዲቶሪያል ኮሚቴ አባል ስለ መዋቅሩ አስፈላጊነት ለመግለጽ የሞከሩ ሲሆን አቡነ እስጢፋኖስ ግን ስለ ጥናቱ ብዙም መረጃ እንደሌላቸውና አንዳንዱንም ከተሰብሳቢው ወገን እንደሰሙ በመግለጽ እርስ በእርሱ የተምተታ መልስ ሰጥተዋል፡፡ መመሪያውና ጥናቱን ወድቆ ብናገኘውስ ምን ችግር አለው ሲሉ ምንጩን ለመደበቅ ሞክረዋል፡፡ ተሰብሳቢዎቹ ቅዱስ ሲኖዶስ ጥያቄያቸውን ማይመልስ ከሆነ የቤተክርስቲያኒቱ አስተዳደር በጥቁር ራስ (መነኮሳት ባልሆኑ) ሰዎች እንዲካሄድ በሕጋዊ መልኩ እንደሚጠይቁ አስረድተዋል፡፡ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ የተሰብሳቢዎቹ ጥያቄ አግባብ የሆነና በትኩረት መታየት እንዳለበት አስረድተው ከተሰብሳቢዎቹ ጉዳዩን የሚከታተል 15 ዐቢይ ኮሚቴ እና 20 ንዑሳን ኮሚቴዎች አስመርጠው በጠቅላይ ቤተክህነት አዳራሽ በመሰብሰብ ጉዳዩን በይበልጥ በትኩረት እንዲያጠኑ መመሪያ ሰጥተዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ለጊዜው እንዲቋረጥ ብፁአን አባቶች ሀሳብ የሰጡበት የመዋቅራዊ ጥናት ስብሰባ በአቡ እስጢፋኖስ ትእዛዝ እንደቀጠለ ሲሆን የሥልጠናው መሪ ማኅበረ ቅዱሳኑ አቶ ታደሰ ፍስሐ በሥልጠናው ተሳታፊዎች እናንተ እነማን ናችሁ? ከሊቃውንትስ ማንን ይዛችሁ ነው የምትሰሩት በሚል ለተነሳላቸው ጥያቁ በደፈናው የቤተክርስቲያን ልጆች ነን ከሊቃውንትም ታላቁን ሊቅ አቡነ እስጢፋኖስን ይዘን ነው የምንሰራው በማለት ምላሽ ሲሰጡ አዳራሹ በስላቅ ሳቅ ደምቋል፡፡
ማኅበረ ቅዱሳን የጠቅላይ ቤተ ክህነቱን ሠራተኛ አቶ ደስታን በሥልጠናው ሥፍራ በወሬ አቀባይነት መድቦ በሬኒ ካፊና ሬስቶራንት የምሳ እና የሻይ እየተከፈለው አንዳንድ መረጃዎችን ለማኅበሩ ሥውር ብሎጎች እንዲያቀብል መድቦታል፡፡ የአዲሱ ሚካኤል ሰንበት ትምህርት ቤት አባል የነበረውና ወደ ቤተክህነት እቃ ሊያደርስ ተልኮ በድንገት ሠራተኛ የሆነው አሁንም በጠ/ቤተ ክህነቱ ገዳማት አስተዳደር ተጧሪ ሆኖ ደመወዝ የሚበላውን ይህንን ጨዋ የአድባራት እና ገዳማት አለቆችንንና ሰራተኞችን ስም በማጥፋት ተግባሩ ማኅበሩ አንቱታን ቸሮታል፡፡ በተጨማሪ እነ ጳውሎስ መልክአ ሥላሴም በዚሁ ተግባር በመሳተፍ ከቤተክህነቱ አደባባይ መዋል ከጀመሩ ሰነባብተዋል፡፡ 



































Tuesday, December 10, 2013

ራሺያ የአሸባሪዎች መመሪያ ብላ የሰየመችው «ቁርአንን» በሀገሯ ቋንቋ ተተርጉሞ እንዳይገባ አገደች።


 
አዣንስ ፍራንስ ፕሬስ እንደዘገበው፤ የራሺያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የአሸባሪዎች የሽብር መመሪያ ነው ያለውን ቁርአን ወደሀገሩ እንዳይገባ የእግድ ውሳኔ አሳለፈ። ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ በውሳኔው ላይ እንዳመለከተው ፤ አንድ መጽሐፍ ወደራሺያ ከመግባቱ በፊት ማኅበራዊ ኑሮን፤ የራሺያን ባህልና ወግ የማይጻረር መሆኑ ሳይመረመር በፊት መግባት ስለማይችል፤ ቁርአን የተባለው መጽሐፍ በሳዑዲ ዐረቢያ ውስጥ በራሺያው ዜጋ ኤልሚር ኩልየቭ በኩል ተተርጉሞ በነጻ ከታተመ በኋላ  ኮፒውን መርምረናል ያለው ፍርድ ቤቱ፤ ይህ መጽሐፍ እንደማንኛውም ሌሎች መጽሐፍ ውስጡ ተመርምሮ የተደረሰበት ጭብጥ እንደሚያስረዳው ትርጉሙ ወደራሺያ ምድር ቢገባ ሽብርን በማበረታታት፤ ጥላቻን በመዝራትና ባህልና ወጋችንን በማደፍረስ ሰላምና መረጋጋት እንዲጠፋ በማድረግ በኩል አሉታዊ ጎኑ የበረታ በመሆኑ እንዳይገባ የእግድ ውሳኔ አሳልፈንበታል ሲል በውሳኔው ላይ ፍርድ ቤቱ ገልጿል።
  በኤልሚር ኩልየቭ በኩል የተተረጎመው ይህ በስም «ቁርአን» የተባለው መጽሐፍ በፍርድ ቤቱ የታየው በየትኛውም የሃይማኖት መጽሐፍነቱ ሳይሆን እንደአንድ ተራ መጽሐፍ ሲሆን የተመረመረውም ይኸው መጽሐፍ ሊሰጥ እንደሚችለው ሀገራዊ ጠቀሜታ አንጻር መሆኑንም ፍርድ ቤቱ ሳይገልጽ አላለፈም።

 ስለሆነም መጽሐፉ ለሀገራቸው ከሚሰጠው ጥቅም ይልቅ ውስጡ ሲመረመር ከጥቅሙ ጉዳቱ ስለሚያመዝን ትርጉሙ ወደሀገር ውስጥ እንዳይገባ ያገደ ሲሆን ይህንን የፍርድ ቤት እግድ ተላልፎ የተገኘ ማንም ዜጋ ሽብርተኝነትን በማበረታታትና በማስፋፋት በሚያስጠይቀው የሀገሪቱ ሕግ መሠረት ተጠያቂ እንደሚሆንም ተገልጿል።
  ይህ «ቁርአን» የተባለው መጽሐፍ የዐረቢኛው ትርጉም በራሺያውያን ሙስሊሞች እጅ የሚገኝ ቢሆንም ከራሺያ ቋንቋ ውጭ ስላሉ ትርጉሞች የተባለ ነገር የለም።

የራሺያው ቋንቋ የቁርአን ትርጉም  በወደሀገሪቱ እንዳይገባ መታገዱን በመቃወም የራሺያው የሙስሊሞች ሙፍቲ ራቪል ጋይኑትዲን ለራሺያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በጻፉት ደብዳቤ እንዳመለከቱት «ይህ እውቀት የጎደለውና ጸብ አጫሪ ውሳኔ እንደገና መታየት አለበት»  በማለት በኃይለ ቃል መግለጻቸውን «ኸፍ ፖስት» ጋዜጣ ዘግቧል።
  ጠቅላይ ሙፍቲው እንዳሳሰቡት « በጥቁር ባህር ወደብ ላይ ወደራሺያ ሊገባ የተዘጋጀው ይህ የቁርአን ትርጉም በአስቸኳይ መፍትሄ ካልተሰጠው፤ የእስላሞች መጽሐፍ ላይ የተወሰደ ውሳኔ አድርገን እንቆጥራለን» ሲሉ መናገራቸውም ተሰምቷል። አንድ ራሺያዊ ዜጋ ስለጉዳዩ በሰጠው አስተያየት እንደተናገረው « ራሺያ እስልምና ለሚፈልገው ማንኛውም ጉዳይ እንደውሻ ጭራዋን እየቆላች ለማስተናገድ የምትገደድበት ምክንያት የለም፤ እስልምና እዚያው ተፈጠርኩበት ካለው በሳዑዲ ምድር አርፎ ይቀመጥ፤ እንግድነት ከፈለገም እኛ ዜጎቹ በምንፈቅድለት መጠንና መንገድ ብቻ ሊስተናገድ ይገባዋል ሲል የገለጸ ሲሆን ምሬቱን በማከልም « ሳዑዲ ዐረቢያ ቁርአንን አሳትማ ወደራሺያ ስትልክ እንድንቀበልላት እንደምትፈልገው ሁሉ መጽሐፍ ቅዱስን በዐረብኛ ተርጉመን ወደሀገሯ እንድናስገባ በኦፊሴል ትፈቅድልናለች ወይ? ሲል ጠይቋል።

የራሺያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን የፍርድ ቤቱን ውሳኔ በተመለከተ ለሙፍቲው የሰጡት መልስ ምን እንደሆነ አልተዘገበም።

Saturday, December 7, 2013

መነኩሴው በግብረሰዶም ወንጀል በእስራት ተቀጡ



በአሸናፊ ደምሴ /ሰንደቅ ጋዜጣ፤ ህዳር 25 እትም/

ዐቃቤ ሕግ ለአካለ መጠን ባልደረሰ ታዳጊ ላይ የግብረ ሰዶም ጥቃት ፈፅመዋል ሲል ክስ የመሰረተባቸው የ33 ዓመቱ ተከሳሽ አባ ገብረፃዲቅ ወልደሩፋኤል በቀረበባቸው ማስረጃ ጥፋተኛ ሆነው በመገኘታቸው የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 7ኛ ወንጀል ችሎት ህዳር 19 ቀን 2006 ዓ.ም ውሎ በ4 ዓመት ፅኑ እስራት የቅጣት ውሳኔ ሰጠ።
የፌዴራሉ ዐቃቤ ህግ የክስ መዝገብ እንደሚያስረዳው፤ ተከሳሽ ከእርሱ ጋር ተመሳሳይ ፆታ ካለውና ዕድሜው ለአካለ መጠን ባልደረሰው ልጅ ላይ የግብረ ሰዶም ጥቃት ለመፈፀም አስበው ነሐሴ 22 ቀን 2005 ዓ.ም በግምት ከቀኑ 8፡00 ሲሆን፤ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 13/15 አካባቢ ልዩ ቦታው ዳንኤል ሆቴል ውስጥ ዕድሜው 15 ዓመት ከሆነው የግል ተበዳይ ጋር ግንኙነት ለማድረግ በመስማማት በሆቴሉ ሽንት ቤት ውስጥ ተከሳሽ አባ ገብረፃዲቅ ወልደሩፋኤል የግል ተበዳይን ካስገቡት በኋላ የግብረ ሰዶም ግንኙነት ሊፈፅሙ ሲል ሌሎች ግለሰቦች እየተከታተሏቸው መሆኑን ሲያውቁ ሱሪያቸውን አጥልቀው መሸሻቸውን ድርጊቱም በጅምር የተቋረጠ መሆኑን ያትታል። በመሆኑም ዐቃቤ ሕግ ተከሳሹ ለፈፀመው ለአካለ መጠን ባልደረሰ ልጅ ላይ የሚፈፀም የግብረ ሰዶም ጥቃት ለሥነ-ምግባር ተቃራኒ በሆነ ሌላ ድርጊት ሙከራ ወንጀል ክስ መስርቶባቸዋል።  
የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት 7ኛ ወንጀል ችሎትም የጉዳዩን ግራና ቀኝ ሲመረምር ከቆየ በኋላ ተከሳሹ የዐቃቤ ሕግን ማስረጃዎች በሚገባ ማስተባበል ባለመቻሉ ጥፋተኛ ነው ሲል ብይን ሰጥቷል። ይህም በመሆኑ ባሳለፍነው ሐሙስ ህዳር 19 ቀን 2006 ዓ.ም በዋው ችሎት ተከሳሹ ጥፋተኛ ሆነው በተገኙበት ወንጀል በአራት አመት ፅኑ እስራትና ለአራት አመታት በሚዘልቅ የመምረጥ መመረጥ እና ከማንኛውም ህዝባዊ መብቱ እንደታገድ ቅጣት ተጥሎበታል።

Wednesday, November 27, 2013

አንጎላ በሀገሯ የእስልምናን እንቅስቃሴ አገደች ተባለ!

 

 
 በትላንትናው ዕለት የግብጹ የሃይማኖት ሙፍቲ ሻውቂ ዓለም አንጎላ እስልምናን ከሀገሯ እንደሃይማኖት ተቋም ማገዷ በ 1ነጥብ 5 ቢሊዮን ሙስሊም ላይ የተወሰደ እርምጃ መሆኑን ልታውቅ ይገባታል ሲሉ አስጠነቀቁ። ይህም ትልቅ ዋጋ ያስከፍላታል ሲሉ ማስፈራሪያቸውንም አክለዋል።
 ይሁን እንጂ 83% የክርስትና እምነት ተከታይ ያለባት አንጎላ በሃይማኖት ጉዳዮች ዳይሬክቶሬቷ በኩል በሰጠችው መግለጫ በቁጥር ከአንድ ሚሊዮን በታች የሆነው የሙስሊም ቁጥር በነጻነት እየኖረ መገኘቱን በመግለጽ የሚታዩት አንዳንድ የእስልምና እንቅስቃሴዎችን ግን በትኩረት እየተከታተሉ እንደሚገኙ አስረድተዋል። በየቦታው እየሄዱ መስጊድ መገንባት፤ የሃይማኖት ትምህርት ቤት መስራትና እስልምናን ለማስፋፋት የሚደረጉ የእጅ አዙር እንቅስቃሴዎችን ግን መንግሥታቸው በፍጹም እንደማይቀበልና እንደማይታገስ ሳይገልጹ አላለፉም። አንጎላ ከየትኛውም የእስላም ሀገራት ጋር የትብብር ስምምነት ስለሌላት በውስጥ ጉዳያቸው የትኛውም የእስላም ሀገር እጁን እንዳያስገባ አሳስበዋል።
 እስልምና በተስፋፋባቸው የአፍሪካ ሀገራት ሁከት፤ ብጥብጥና ግድያ እየተስፋፋ እያየን ቁጥሩ ምንም ትንሽ ቢሆን በሌላው ያየነው ሁኔታ በሀገራችን እንዲታይ በምንም መልኩ እድል አንሰጥም ያሉት የአንጎላው  የሃይማኖት ጉዳዮች ዳይሬክተር ያለንን ሰላም ለማስጠበቅ የምንወስዳቸው እርምጃዎች ከሃይማኖት ዲሞክራሲ ጋር በፍጹም አይያያዝም ሲሉ የሃይማኖት ነጻነትን ትጋፋለች በማለት ለሚጮሁ ክፍሎች አስረድተዋል።

ንግግራቸውን በማያያዝም እንደተናገሩት፤ ማንም አንጎላዊ በእምነቱ ሳቢያ በግሉ አይጠየቅም፤ አድልዎም አይደረግበትም።  ነገር ግን ገንዘብና ነጻነት አለኝ ብሎ የትም እየዞረ መስጊድ ለመትከልና ከራሱ አልፎ በሌላው አካባቢ ላይ የማስፋፋት መብት የለውም። በቂ የአምልኮ ስፍራና የእምነቱ መግለጫ ስፍራ እያለው ተጨማሪ የመስፋፋት እንቅስቃሴ ሲደረግ በማግኘታችን አንድ ያልተፈቀደ መስጊድ ዘግተናል፤ አፍረሰናል፤ ይህንንም ቁጥጥር አጥብቀን እንገፋበታለን ሲሉ ጨምረው ገልጸዋል።

  በአንጎላውያኑ ዘንድ እስልምና እንደሁከትና የብጥብጥ መሳሪያ የሚታይ በመሆኑ 90% የሆነው ሕዝብ የመንግሥትን አቋም ይደግፋል። አንጎላ በነዳጅ ሀብት የበለጸገችና በእድገት ጎዳና ላይ እየገሰገሰች የምትገኝ ሰላማዊ ሀገር ሆና እንድትቀጥል ለማድረግ በ21ኛው ክ/ዘመን የመስፋፋትና ሁሉን እስላማዊ ግዛት የማድረግ ዐረባዊ ዘመቻ በፍጹም እንደማትቀበል እየተናገረች የምትገኘው አንጎላ በእውነት እድለኛ ሀገር ናት።
ያለምንም ማጋነንና ጥላቻ እስልምና ባለበት በየትኛውም ሀገር ሁከት አለ። የመቻቻል  ዜማ ጊዜ እስኪወጣልህ በሚል ብልጠት ስር የሚዘመር ሲሆን አጋጣሚ ሲገኝ የሃይማኖቱ መሠረት ሁከትንና ብጥብጥን ስለሚያበረታታ፤ ከእኔ በቀር ሌላውን «አላህ» አይፈልገውም በሚል ጭፍንነት ስለሚራገብ፤  ያንን ለማስፈጸም እስልምና የሚጓዝበት መንገድ ሁሉ ዐመጽና ኃይል የተቀላቀለበት  እንቅስቃሴ መሆኑ ግልጽ ነው። አንጎላ በሀገሯ የጀመረችው የእስልምናን  መስፋፋት የመገደብ ጉዳይ ከእምነት ነጻነት ጋር የሚያያዝ ሳይሆን በነጻነትና በዲሞክራሲ ሽፋን በገንዘብና በዘመቻ  የሚደረግ የሃይማኖት ወረራን መከላከል በመሆኑ አንጎላ በርቺ እንላለን።

Saturday, November 9, 2013

«እነ ጀማነሽ ድብደባ እየተፈፀመብን ነው አሉ!»


(አዲስ አድማስ ጋዜጣ)ፕ/ር ይስማውና ሌሎች አባላት ክስ ተመስርቶባቸዋል።

“የማኅበረ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ” ማኅበር አባላት፤ በተናጠል እና በጋራ በምናራምደው እምነት ምክንያት ሕገመንግስቱ የሰጠን መብት ተጥሶ ድብደባ፣ ወከባና እንግልት እየተፈፀመብን ነው፤በአባላቶቻችን ላይም ክስ እየተመሠረተ ነው ሲሉ አማረሩ፡፡ አርቲስት ጀማነሽ ሠለሞን አባል የሆነችበት ማህበረ ስላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ “ኤልያስ መጥቷል፣ ሰንበት ቅዳሜ ነው፣ አርማችን ቀስተደመና ነው” የሚሉና መሠል ሃይማኖታዊ ሃሳቦችን የሚያራምድ ሲሆን አባላቱ ሃይማኖታዊ አስተምህሮአቸውን በተለያዩ መንገዶች ለሰዎች ለማስተማር ሲሞክሩ ለሕይወታቸው አስጊ የሆኑ ጥቃቶች እየተፈፀሙባቸው እንደሆነና በአቃቤ ህግ ክስ እንደቀረበባቸው ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡ ከአዲስ አበባ 65 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው አሌልቱ ከተማ አቡነ ተክለሃይማኖት ፅላልሽ ገዳም አጥቢያ ነዋሪና የገዳሙ አገልጋይ እንደሆኑ የገለፁት ወ/ሮ ቀለመወርቅ ጀማነህ፤ የማኅበረ ሥላሴ አባልና አገልጋይ በመሆናቸው ብቻ በቤተሰቦቻቸው ላይ ውክቢያ፣ እንግልትና ድብደባ እንደተፈፀመባቸው ተናግረዋል፡፡
ግለሰቧ እንደሚሉት መስከረም 24 ቀን 2006 ዓ.ም የገዳሙ የሃይማኖት አባቶች፤ ቤተሰቦቻቸውን ሰብስበው “ልጃችሁ ሃይማኖታችንን እያጠፋች ነው” በሚል እንዳነጋገሯቸውና ከዚህ ድርጊት እንድትታቀብ አድርጉ የሚል ማሳሰቢያ እንደተሰጠ ገልፀዋል፡፡ የማህበረ ስላሴ አባላትን ወደ ገዳሙ ለበረከት ሐምሌ 30ቀን 2005 መጋበዛቸውን የሚገልፁት ወ/ሮ ቀለመወርቅ፤ ይህን በመፈፀማቸው “ሃይማኖታችንን የሚያጠፋ ተግባር ፈጽመሻል” ማለት፣ እንደበድብሻለን የሚል ዛቻ እንደደረሰባቸው አስታውሰው፤ ጥቅምት 17 ቀን 2006 ዓ.ም ዛቻው በቤተሰባቸው አባላት ላይ እንደተፈፀመ ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡
በዕለቱ በወላጅ እናታቸው ቤት በተዘጋጀ የመታሰቢያ ዝክር ላይ ተከፍለው ወደመጡበት ሲመለሱ መንገድ ላይ ድብደባ የተፈፀመባቸው የቤተሰባቸው አባላት፤ በአካባቢው ማኅበረሰብ እርዳታ እና በፖሊስ ትብብር ወደ ፖሊስ ጣቢያ በመሄድ ክስ ማቅረባቸውንና ጉዳዩም በህግ እየታየ መሆኑን ወ/ሮ ቀለመወርቅ ገልፀዋል፡፡ ከድብደባው ጋር በተያያዘም በድርጊቱ ተሣትፈዋል ተብለው የተጠረጠሩ የሃይማኖት አባቶችም ታስረው መለቀቃቸውን እኚሁ ቅሬታ አቅራቢ አክለው ተናግረዋል፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ የገዳሙን የስራ ሃላፊዎች በስልክ ለማነጋገር ያደረግነው ተደጋጋሚ ሙከራ ባይሳካም ጉዳዩን የያዙት የወረዳው ፖሊስ ባልደረባ አቶ ገዙ ወርቁ፤ የተፈፀመው ድርጊት ገና በምርመራ ሂደት ላይ መሆኑን ገልፀውልናል፡፡ የማህበሩ አመራር አባላት ለዝግጅት ክፍላችን ባቀረቡዋቸው የክስ ዝርዝር ሰነዶች እንደተመለከተው፤ ከማህበሩ አመራሮች አንዱ የሆኑት ፕሮፌሰር ይስማቸው አለሙን ጨምሮ በባህርዳር እና በደብረ ብርሃን የሚገኙ አባላቶች አስተምህሮውን በመስበካቸው የወንጀል አንቀጽ ተጠቅሶባቸው ክስ እንደተመሠረተባቸው ተመልክቷል፡፡
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር በሆኑት ፕ/ር ይስማው ላይ የተመሠረተባቸው ክስ እንደሚያስረዳው፤ ተከሳሹ በ28/07/2005 ዓ.ም ከሌሊቱ 10.00 ሰዓት በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 ክልል፤ ልዩ ቦታው ቦሌ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ውስጥ የቅዳሴ ስነ ሥርዓት እየተካሄደ እያለ ወደ ቤተመቅደስ በመግባት “ኤልያስ መጥቷል የተዋህዶን ነገር በደንብ መናገር አለብኝ፤ እናንተ በከንቱ ነው የምትደክሙት፤ ኦርቶዶክስ ትክክለኛ ሃይማኖት አይደለም፤ በውስጡ ቅባትና ዘጠኝ መለኮት የሚገለጽበት ነው፡፡
እውነተኛ እና ትክክለኛ ሃይማኖት ተዋሕዶ ብቻ ነው፤ ይሄንን እውነታ ለሕብረተሰቡ አስተምራለሁ እሰብካለሁ” በማለት ሃይማኖታዊ ስነሥርዓቱ እንዲታወክ እና ረብሻ እንዲፈጠር ያደረገ በመሆኑ፤ በፈፀመው ሃይማኖታዊ ሠላምና ስሜት መንካት ወንጀል ተከሷል ይላል፡፡ በባህርዳር ዙሪያ ወረዳ ጽ/ቤት በአቃቤ ህግ ክስ የተመሠረተባቸው አቶ ጌጤ ሣህሉ ንጋት የተባሉ የማኅበሩ አባል በቤተክርስቲያን ላይ የንግግር ወንጀል ፈጽመዋል የሚል ክስ የቀረበባቸው ሲሆን በደብረ ብርሃን ለባሶና ወራና ወረዳ ፍ/ቤትም አቶ አበበ ነጋሽ የተባሉ ግለሰብ፤ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖትን በማሽሟጠጥና በማራከስ እንዲሁም የተለያዩ በራሪ ወረቀቶችን በመበተን ፈፀሙ በተባሉት ሃይማኖታዊ ሠላምና ስሜት መንካት ወንጀል መከሰሳቸው ታውቋል፡፡

Sunday, October 6, 2013

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ አረፉ!



በቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ባሉ የኢትዮጵያ ገዳማት ውስጥ ላለፉት 43 ዓመታት ያህል የኖሩትና በምንኩስና ስማቸው አባ ላዕከ ማርያም በመባል ሲጠሩ ቆይተው በ1985 ዓ/ም  በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ አንብሮተ እድ  ኤጲስቆጶስ ሆነው የተሾሙት ብጹዕ አቡነ ሕርያቆስ ባደረባቸው ሕመም በሕክምና ሲታገዙ ቆይተው መስከረም 25/ 2005 ዓ/ም ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን የደረሰን ዜና ያስረዳል።
እግዚአብሔር አምላክ የብፁዕነታቸውን ነፍስ በአፀደ ቅዱሳን ያሳርፍልን!!

Tuesday, October 1, 2013

“መስቀል የሚያቃጥል አይደለም”

ከሠማይ ወረደ ስለተባለው መስቀል ሲኖዶሱ ውሣኔ ይሰጣል - አቡነ እስጢፋኖስ

(ከደጀ ብርሃን ) ከሰማይ ወረደ ስለተባለው ሰሞነኛ ወሬ ብዙ ብዙ ተብሏል። እንደዚህ ዓይነት ደብተራዊ ቁመራ የተለመደ ሆኖ መታየቱ ለክፉና አመንዝራ ትውልድ ምልክት ፈላጊነት ጥሩ አጋጣሚ ሆኖ ቀጥሏል። ከሰማይ ለወረደውና ወደሰማይ ለወጣው ለአብ አንድያ ልጅ ለኢየሱስ ክርስቶስ በእምነት ልብን አሳልፎ ከመስጠት ይልቅ ከሰማይ ወረደ ለተባለው ቁራጭ ብረት መንጋጋት አሳፋሪም አሳዛኝም ነው።  በእርግጥ ይህ ትውልድ በክርስቶስ አምኖ ልቡን ከማሳረፍ ይልቅ ምልክት እንደሚሻ ዕለት ዕለት እናያለን። ለኃጢአት ሥርየት የተሰነጠቀ ድንጋይ ሲሾልክ፤ የማያየውን የተቀበረ መስቀል ፍለጋ ከወሎ ተራራ ሲንከራተት፤ ይቅርታን ለማግኘት ፍርፋሪና ዳቦ ለመብላት ሲሻማ ማየቱ በክርስቶስ ደም ሥርየትን፤ ንስሐ በመግባት ብቻ ይቅርታን በማግኘት ማረፍ እንዳልቻለ ያሳያል። እረፍት ፍለጋ ምልክት መከተል መፍትሄ አይደለም። በእውነታው  ሰዎቹ እንደሚሉት እግዚአብሔር የተመሳቀለ እንጨትም፤ ብረትም ከሰማይ እርሻ ማሳ ውስጥ በመወርወር ከሰው ልጆች ጋር ይጫወታል ማለት ባህርይውን አለማወቅ ነው። ድንጋይ በመሹለክም፤ ፍርፋሪ በመብላትም፣ ተራራ በመውጣትም፤ ደረትን በመድቃትም ሆነ ጸጉርን በመንጨትም ኃጢአት አይደመሰስም። ሥርየትም አይገኝም። «በውድ ልጁም፥ እንደ ጸጋው ባለ ጠግነት መጠን፥ በደሙ የተደረገ ቤዛነታችንን አገኘን እርሱም የበደላችን ስርየት» እንደሆነ ወንጌል ቢናገርም (ኤፌ 1፤7) ይህንን ወደጎን ገፍቶ በሰንጥቅ ድንጋይ ለመሹለክ መሽቀዳደም ምልክት ፈላጊዎችን ከማብዛቱም በላይ ወንጌል ከስሙና ከንባቡ በስተቀር ለመታወቅ ብዙ እንደሚቀረው ነው።  ከዚህ ዓይነቱ እርባና የለሽ ሰሞነኛ ወሬዎች ውስጥ አንዱ በአዲስ አበባ ከተማ እርሻ ማሳ ውስጥ ወድቆ ተገኘ ስለተባለው መስቀል ብዙ መወራቱ እንዳለ ሆኖ አንስተው፤ ወደመቅደስ አስገብተውታል የሚባሉት የሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ ስለእውነታው በሲኖዶስ ውሳኔ ይሰጥበታል የሚል ዜና ስናነብ እጅጉን ገረመን። ምክንያቱም የነደብተራ ገለፈት ፈጠራ እንደቁም ነገር ሊቆጠር አይገባውም። እንዲያውም እንደዚህ ዓይነቶቹን ጸረ ወንጌል አጭበርባሪዎች ማስወገድ ይገባ ነበር።  ለማንኛውም የአቡኑን የአዲስ አድማስ ዘገባ እንዲያነቡት እነሆ ብለናል።
 
በአቃቂ ቃሊቲ ገላን ጉራ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ባለፈው ነሐሴ ወር መጨረሻ ላይ ከሠማይ ወረደ ስለተባለው መስቀል ቅዱስ ሲኖዶስ ውሣኔ እስኪያስተላልፍ ህዝቡ በትዕግስት እንዲጠባበቅ የአዲስ አበባና የጅማ ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ አሣሠቡ፡፡ “መስቀል ከሠማይ ወርዷል አልወረደም? ትክክለኛ ነው አይደለም?” የሚለውን ለመመለስ የግድ ቅዱስ ሲኖዶሡ ጉዳዩን መርምሮ ውሣኔ ሊያስተላልፍበት ይገባል ያሉት ብፁዕነታቸው፤ ይህን ለማድረግም ጉዳዩን ለቅዱስ ሲኖዶሱ ቋሚ አባላት እንዳሣወቁ ተናግረዋል፡፡ መስቀሉ እንደተባለው ከሠማይ የወረደ አለመሆኑ ከተረጋገጠም የቤተክርስቲያኒቱ ሃላፊዎች ይጠየቁበታል ብለዋል ብፁዕነታቸው፡፡
መስቀሉ ከሠማይ ወረደ በተባለ በ4ኛው ቀን ነሐሴ 27 ቀን 2005 ከሠአት በኋላ ወደ ስፍራው በማቅናት ተገቢውን የፀሎት ስርአት ከካህናቱና ከቤተክርስቲያኒቱ አገልጋዮች ጋር ካደረሡ በኋላ መስቀሉን ከወደቀበት መሬት አንስተው ወደ ቤተመቅደሡ እንዲገባ ማድረጋቸውን የገለፁት ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ፤ መስቀሉ ከሠማይ ስለመውረዱ በአይናችን አይተናል ካሉት የቤተክርስቲያኒቱ አገልጋዮች እንደማንኛውም ሠው መስማታቸውን ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡
መስቀሉን ከወደቀበት መሬት ያነሱት ብፁዕነታቸው፤ “መስቀሉ ያቃጥላል፤ ብርሃናማ ነፀብራቅ አለው” የሚባለውን አለማስተዋላቸውን ጠቁመው፤ “መስቀል የሚያቃጥል ሣይሆን የድህነት ሃይል ነው ያለው፣ የሚያቃጥል ቢሆን ኖሮ ከመሬት ላይ ማንሣት ባልተቻለ ነበር” ብለዋል፡፡ ወረደ የተባለውን መስቀል ለመመልከት ወደ ስፍራው የሚያቀኑ ምዕመናን ለምን እንዳይመለከቱት ተከለከለ የሚል ጥያቄ ያነሣንላቸው ብፁዕነታቸው፤ ጉዳዩ በቅዱስ ሲኖዶሡ ተጣርቶ ውሣኔ እስኪያገኝ ድረስ ህዝበ ክርስቲያኑ ጉዳዩን በጥሞና እንዲያጤነው በማሠብ ነው” ብለዋል፡፡ (ምንጭ: አዲስ አድማስ)

 

Thursday, August 15, 2013

ለአቡነ ገብርኤል ጥሪ የሀዋሳ ምእመናንና የሰ/ት/ቤት ወጣቶች ምላሽ ሰጡ!

«እስከ ጥቁር ዉሃ ሄዶ የተቀበለ  ሕዝብ እስከ ጥቁር ውሃ ተሰደደ» (ደጀ ብርሃን)

 /ምንጭ፦dejeselaam-dejeselaam.blogspot.com/
 በሀዋሳ በግፍ የተሰደዱት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ምዕመናንና የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች ብፁዕ አቡነ ገብርኤል "ኑ ልጆቼ ወደ ቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ ተመለሱ" ሲሉ ላደረጉት ጥሪ ምላሽ መስጠታቸውን ከስፍራው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ ምዕመናኑ ለአቡነ ገብርኤል በአድራሻ፣ ለ17 የቤተክርስቲያንና መንግሥታዊ ተቋማት ደግሞ በግልባጭ ያሠራጩትን ደብዳቤ በብሎጋችን ፖስት እንድናደርግላቸው ለዝግጅት ክፍላችን በኢሜይል ልከውልናል፡፡ የደብዳቤው ሙሉ ይዘት የሚከተለውን ይመስላል፡፡
ነሐሴ 7 ቀን 2005 ዓ.ም
ለብፁዕ አቡነ ገብርኤል
የሲዳማ፣ ጌዴኦ፣ አማሮና ቡርጂ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ሀገረስብከት ሊቀጳጳስ
ሀዋሳ፣
ጉዳዩ: ̶  "ወደ ቤተክርስቲያን እንድትመለሱ" በማለት ለተጻፈልን ደብዳቤ ምላሽ ስለመስጠት
በቀን 25/1/171/2005 (ቀኑን ከደብዳቤው ላይ ማየት እንደሚቻለው) በቁጥር 1459/171/2005 የተጻፈ ደብዳቤ ሐምሌ 25 ቀን 2005 ዓ.ም ከምሽቱ 1፡30 ሰዓት በሁለት ፖሊሶች እጅ ተልኮልን ወንጌል ከምንማርበት ሥፍራ ተጠርተን መተማመኛ ፈርመን በመቀበል በአንክሮ ተመልክተነዋል፡፡ ቀጥሎም ለምዕመናን ተነቦ ውይይት ከተደረገበት በኋላ የጋራ አቋም የተወሰደበት ሲሆን፣ ጥሪ ማድረግዎን በስምንቱም አጥቢያ ቤተክርስቲያናት ዐውደ ምሕረቶች እንዲነበብ እንዳደረጉት ሁሉ ይህንን የምላሽ ደብዳቤያችንንም  ለሰፊው ምዕመን በተመሳሳይ ሁኔታ እንዲያስነብቡልን አደራ እንላለን፡፡ የሰጠነውም ምላሽ የሚከተለው ነው፡፡ 
አንደኛ፣ ደብዳቤውን እንደ ወንጀል ክስ መጥሪያ በፖሊስ እጅ መላኩ እና ከመደበኛ የሥራ ሰዓት ውጪ ከምሽቱ 1፡30 ከሆነ በኋላ መምጣቱ፣ እንዲሁም መተማመኛ ፈርመን እንድንቀበል መደረጉ ከሕግ አንፃር ተገቢ ካለመሆኑም በላይ የጥሪው አካሄድ የፍቅር እንዳልሆነ ተገንዝበናል፡፡ በተጨማሪም ደብዳቤው ቅንነትና እውነት ያለበት ሳይሆን ማስመሰልና ውሸት የተሞላበት ከመሆኑም በላይ እርቅ፣ ሠላምና አንድነትን ከማምጣት ይልቅ ራስን ከሕዝብ (ከታሪክ) ፍርድ ለመከላከልና ለገጽታ ግንባታ (ፕሮፖጋንዳ ፍጆታ) ሲባል ብቻ የተዘጋጀ መሆኑን ተረድተናል፡፡
በደብዳቤው ውስጥ "የተወደዳችሁ ልጆቻችን ምዕመናንና ወጣቶች" የሚል ሐረግ ተደጋግሞ ይታያል፡፡ ልጆቻችሁ እንደሆንን ሲነግሩን ከእርስዎ ሳይሆን ከሌላ አካል የሰማነው ያህል መስሎ ነው የተሰማን፡፡ ምክንያቱም እኛ ልጆችዎ እንደሆንን ባንክድም ከእርስዎ ዘንድ ግን የአባትነት ወግ ፈጽሞ አይተን ስለማናውቅ ነው፡፡ ከዚህ አንፃር የደብዳቤውን ይዘት ስንመረምረው የተረዳነው ነገር ቢኖር ̶ አንዳንዴ በግልጽ፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ በስውር በሀገረ ስብከታችን የሚካሄዱትን ሕገወጥ ሥራዎች ለመሸፋፈንና "ለምን አሳደዳችኋቸው? ለምን አትመልሷቸውም"? ብሎ ለሚጠይቃችሁ አካል "ይኸው፣ በደብዳቤ ጠርተናቸውም እምቢ ብለውናል" በማለት በብልጣብልጥ አካሄድ ሪከርድ ለማስያዝ እና ወደፊት ለምታደርጉት የተለመደ እንቅስቃሴ ምክንያት ለማመቻቸት መሆኑን ለማወቅ ልዩ ጥበብ አያስፈልገውም፡፡
ጥሪዎ ቅንነት ቢኖረው ኖሮና እኛን "ልጆቻችን" እንዳሉን ሁሉ እርስዎም አባትነትዎን አምነውበት ቢሆን በአባትና በልጅ መካከል አለመግባባት ተፈጥሮ ልጅ ቤቱን ለቆ ቢኮበልልና አባትም በበኩሉ የኮበለለው ልጅ ወደ ቤቱ እንዲመለስ ቢፈልግ ደብዳቤ ጽፎ በፖሊስ በኩል መላክ ትክክለኛው መንገድ አለመሆኑን ለእርስዎ መንገር ለእናት ምጥ እንደማስተማር ይቆጠራል፡፡
በተጨማሪም፣ ከቤተክርስቲያን ቅጥር ግቢ ተባርረን ከወጣን ሁለት ዓመታት እስኪቆጠሩ ድረስ ከሀገረ ስብከቱ ውጪ ያሉ ካህናትና አገልጋዮች መጥተው ሲባርኩንና ሲያፅናኑን እርስዎና ከእርስዎ ሥር ያሉ አባቶች ግን የጠፉትን በጎች ፍለጋ ሳትወጡ ኖራችሁ፣ ዛሬ ከረፈደና ከመሸ፣ ጉዳዩም ከእጃችሁ ወጥቶ በጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤትና በቅዱስ ሲኖዶስ ከተያዘ በኋላ ድንገት ይህንን ኦፊሴላዊ ጥሪ ለማድረግ የተገደዳችሁበትን ሚስጥር ስናሸተው ጠረኑ የሚነግረን ሌላ ጉዳይ መሆኑን ነው፡፡ ደብዳቤው ሆን ተብሎ እውነታውን ለማዛባት የተደረጉ ጥረቶች እንዳሉበት ከማሳየቱም በላይ "እንዳያማህ ጥራው፤ እንዳይበላ ግፋው" እንደሚባለው ለይተበሀል ያህል ብቻ የተጻፈ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡
ሁለተኛ፣ በደብዳቤው የመጀመሪያ መሥመር ላይ፣ "ከቤተክርስቲያን ተባረናል በሚል . . .  እየተሰባሰባችሁ የምትገኙ ልጆቻችን ምዕመናንና ወጣቶች . . . " የሚል ሐረግ ሰፍሯል፡፡ ይህ የሚያሳየን እኛ ተባረናል እንላለን እንጂ እናንተ ማባረራችሁን አምናችሁ ለመቀበል እንደማትፈልጉና ዛሬም እንኳን ፀፀት እንዳልተሰማችሁ ያመለክታል፡፡  ታዲያ ከእናት ቤተክርስቲያናችን ውጪ ለመገኘታችን ምክንያቱ እርስዎ፣ የእርስዎ አስተዳደር እና እርስዎ ያደራጁት ማኅበር ካልሆነ፣ ቤተክርስቲያንና ቅጥሯ አስጠልቶን አካባቢ ለመለወጥና ለሽርሽር የሄድን መስሎዎት ይሆንን? ይሁን እንጂ እንዳባረራችሁን መላው የሀዋሳ ምዕመናን ምሥክር ናቸው፡፡

Sunday, July 7, 2013

እነ አርቲስት ጀማነሽ “የቅዱስ ኤልያስ”ን መልዕክት ለፓትሪያሪኩ እንዳናደርስ ተከለከልን አሉ


(አዲስ አድማስ )“የማህበረ ስላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ” አባላት፤ ከቅዱሳን አባቶች የተላክነውን የቅዱስ ኤልያስን መልዕክት ለአዲሱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክርስቲያን ፓትሪያሪክ አቡነ ማቲያስ እንዳናደርስ ተከለከልን አሉ፡፡ አርቲስት ጀማነሽ ሰለሞን የተካተተችበት መልዕክት አድራሽ ቡድን፤ ባለፈው ማክሰኞ ረፋዱ ላይ መልዕክታቸውን ጋዜጠኞች ባሉበት ለፓትርያርኩ ለማቅረብ ፓትሪያሪኩ ጽ/ቤት በር ላይ ተገኝተው የነበረ ቢሆንም የጥበቃ አባላት “ለማነጋገር ፍቃድ የላችሁም” ብለው መልሰዋቸዋል፡፡ ከማህበሩ አባላት መካከል አርቲስት ጀማነሽ ሰለሞን እና መ/ር ወልደመስቀል ፍቅረማርያም ለአዲስ አድማስ እንደገለፁት፤ ለሁለት ጊዜያት ያህል 4 ኪሎ በሚገኘው መንበረ ፓትሪያሪክ ጽ/ቤት በመሄድ ከአባቶች የተላኩትን መልዕክት ለማድረስ ቢሞክሩም ከጽ/ቤቱ የጥበቃ ሃላፊዎች ማለፍ አልቻሉም።
“በመጀመሪያው ቀን ከማህበረ ስላሴ መልዕክት ይዘን መምጣታችንን ለጥበቃዎች በመንገር ወደ ውስጥ እንድንገባ ከተፈቀደልን በኋላ ሌሎች በግቢ ውስጥ የነበሩ ጥበቃዎች በድጋሚ አስቁመውን ከስላሴ ካቴድራል ማኅበር የመጣችሁ መስሎን ነው እንጂ እናንተ መግባት አትችሉም በማለት ፓትሪያሪኩን እንዳናገኝ ተደርገናል” የሚሉት መ/ር ወልደመስቀል፤ በተለይ አንዲት ሴት የጥበቃ አባል ከአግባብ ውጭ ጀማነሽን እየገፈታተረች እንድትወጣ ማድረጓን ገልፀዋል፡፡ በሚዲያ ሳይቀር ቅዱስ ፓትሪያሪኩ ማንም ሰው ያለከልካይ በአካል መጥቶ ሊያነጋግረኝ ይችላል ያሉትን መነሻ አድርገን በመጀመሪያ ቀን ያለቀጠሮ የሄድን ቢሆንም ለሁለተኛ ጊዜ ቀጠሮ ለማስያዝ ብንፈልግም የሚያስተናግደን አካል በማጣታችን ለመመለስ ተገደናል የሚሉት መ/ር ወልደመስቀል፤ ጥበቃዎቹ የሄድንበትን ጉዳይ ጠይቀውን ከተረዱ በኋላ ፈጽሞ መግባት አትችሉም፤ ቀጠሮ ማስያዝ ከፈለጋችሁ አንድ እማሆይ አሉ፤ እሣቸውን አነጋግሩ ተባልን፤ የተባሉት ግለሰብ ግን ፍቃድ ወጥተዋል የሚል ምላሽ አገኘን ብለዋል፡፡ “አሁንም ለሶስተኛ ጊዜ ስንሄድ ጥበቃዎቹ ፈጽሞ መግባት አትችሉም፡፡ አካባቢውን ለቃችሁ ሂዱ አሉን” ብለዋል - የማህበሩ አባላት፡፡
ባለፈው ማክሰኞ 10 የሚደርሱ ሴቶችና ወንዶች የማህበሩ መገለጫ የሆነውን ነጭ ባለቀስተ ደመና ጥለት ልብስ ለብሰው ፓትሪያርኩ ጽ/ቤት በሩ ላይ ቆመው ነበር፡፡ የነብዩ ኤልያስ መልዕክት ምንድነው ብለን የጠየቅናት አርቲስት ጀማነሽ ሠለሞን “መልዕክቱ ለፓትሪያሪኩ ስለሆነ እሳቸው ከሰሙ በኋላ ለህዝብ እንድታደርሱ ይነገራችኋል” ብላለች፡፡ የመንበረ ፓትሪያሪክ ልዩ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ታምሩ አበራ ከአዲስ አድማስ ስለ ጉዳዩ ማብራሪያ ተጠይቀው “እስካሁን ጥያቄ ያቀረበልን የለም፤ ቤተክርስቲያኒቷ የራሷ የቅሬታ አቀራረብ ሥርዓት አላት፡፡ ለቅሬታም ሆነ ለቡራኬ የሚመጡትን በቀጠሮ እናስተናግዳለን፡፡ እስከ ሀምሌ 21 ቅዱስ ፓትሪያሪኩን በስልክ ለማነጋገር የተያዙ ቀጠሮዎች አሉ” ብለዋል፡፡ ከነብዩ ኤልያስ መልዕክት አለን ያሉት ግለሰቦች “ኦርቶዶክስ” የሚለው ስያሜ “ለተንኮል” የገባ ስለሆነ የቤተክርስቲያኒቱ ስያሜ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መባሉ ቀርቶ “የኢትዮጵያ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን” መባል አለበት በሚል አላማ እንደሚንቀሳቀሱ ይታወቃል፡፡

Friday, May 31, 2013

የግብጽ ኮፕቲክ ፓትርያርክ ታዋድሮስ 2ኛ በዓባይ ግድብ ጉዳይ ላይ ቤተክርስቲያናቸው የሽምግልና ሚና እንድትጫወት በመሐመድ ሞርሲ አልተጠየኩም አሉ»

 የኮፕቲክ ቤተክርስቲያን ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጋር የነበራትን የብዙ ዘመናት የበላይነትና የጠነከረ ቅርርብ መሠረት አድርገው በፖፕ ታዋድሮስ 2ኛ በኩል የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ላይ ግፊት ለማድረግና የግጭት መነሻ እንዳይሆን ጫና እንዲያሳድሩ በመሐመድ ሙርሲ በኩል ጥያቄ ቀርቦላቸዋል የሚል ሰፊ ዘገባ ይዘው የወጡትን የግብጽ ጋዜጦች መነሻ በማድረግ የፓትርያርኩ ጽ/ቤት መግለጫ ሰጥቷል። አናዶሉ የተባለው የዜና ወኪልም በቀጥታ ፖፕ ታዋድሮስ ጉዳዩን ያውቁት እንደሆነ በስልክ አነጋግሮአቸው በሰጡት ምላሽ  እንደገለጹት «የግብጽ ጋዜጦች ይህንን ዜና ከየት እንዳገኙት አላውቅም፤ ለእኔ በግሌ ከፕሬዚዳንት ሞርሲ በኩል  የኢትዮጵያን ግድብ በተመለከተ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ጋር የሽምግልና ድርድር እንዳደርግ የጠየቁኝ ምንም ዓይነት ነገር የለም» በማለት ምላሻቸውን ሰጥተዋል።

  የፓትርያርኩ ጽ/ቤት ለዜና ወኪሉ በተጨማሪ እንደገለጸው ጥያቄው ቢቀርብላቸው የኮፕት ቤተ ክርስቲያን በጉዳዩ ላይ ለመሥራት ምንም ቅሬታ የሌላት ቢሆንም መታወቅ ያለበት ነገር ግን፤  የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን በሀገሪቱ መንግሥት የውሳኔ ሰጪነት ሥልጣን ውስጥ ምንም ድርሻ የሌላት መሆኑን መረዳት እንደሚያስፈልግ በመግለጫው ተመልክቷል። ለግብጽና ለኢትዮጵያ ሕዝቦች የጋራ ጥቅምና ሰላም በሚበጅ ጉዳይ ላይ ለመነጋገር ዝግጁ ነን፤ ይህንን በተመለከተም የኢትዮጵያው ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ሐምሌ 19/2013 ግብጽ በሚመጡበት ወቅት ስለግድቡ ጉዳይ እናነሳላቸዋለን በማለት ጽ/ቤቱ ያለውን ሃሳብ በተጨማሪ አስረድቷል። የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ቀድሞ በነበራት ተደማጭነት በመንግሥት ላይ የምታሳድረው ተጽእኖ ባለመኖሩ በግድቡ ጉዳይ ላይ የጎላ ሚና ይኖራታል ተብሎ አይጠበቅም ሲል በዜና ዘገባው ላይ «አናዶሉ» የዜና ወኪል ያገኘውን ማብራሪያ መነሻ አድርጎ የራሱን ትንታኔ በመስጠት ስለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን የወቅቱ አቅም እስከየት ድረስ እንደሆነ በግልጽ አስቀምጧል።
     ከዚሁ ጋር ተያይዞ የደርግን የውድቀት ቀን ተጠግቶ ግንቦት 20 የመፍሰሻ አቅጣጫው መለወጡ ስለተነገረው ታላቁ ኅዳሴ ግድብ የግብጽ ሚዲያዎች የጩኸትና የጦርነት ዜማ በማቅረብ ላይ ይገኛሉ። የጃማአ አል ኢስላሚያ ሙፍቲ የሆኑት ሼክ አብደል አክሄር ሐማድ ለተከታዮቻቸው ባሰሙት ንግግር እንደተጠቆሙት «ኢትዮጵያ የዓባይን ወንዝ አቅጣጫ መቀየሯ በግብጽ ሕዝብ ላይ ጦርነት እንዳወጀች ያህል ይቆጠራል» በማለት ጠጣር መልዕክት አስተላልፈዋል። «አል አረቢያ» ለተሰኘው ቴሌቪዥን ጣቢያም በቀጥታ ስርጭት ባደረጉት ንግግር «የኢትዮጵያን ድርጊት የግብጽ መንግሥት በትዕግስትና በዝምታ ሊመለከተው አይገባም፤ የኢትዮጵያ ድርጊት በግብጽ ላይ የተፈጸመ የጦርነት አዋጅ ነው፤ ይህንን ድርጊት በፍጹም አንታገስም፤ በሽምግልና  ብቻ የሚፈታ ጉዳይ ስላልሆነ መብታችንን በኃይል እስከማስከበር መሄዳችን የግድ ወደሚል ሁኔታ ውስጥ እየገባን ነው» በማለት አቋማቸውን ለአድማጭ፤ ተመልካቹ በግልጽ ተናግረዋል። ግብጾች የሚጠብቀንን ግዴታ ሳንዘነጋ የዲፕሎማሲውን ጉዳይ ጎን ለጎን በማካሄድ ትኩረት መስጠት ይገባናል ማለታቸውም ተወስቷል።
    በሌላ በኩልም በመካከለኛው ምሥራቅ ጦርነት ወቅት የግብጽ ጦር አዛዥ የነበሩት ጀነራል ሞሐመድ አሊ ቢላል እንዳስገነዘቡት ግብጽ በዓባይ ግድብ ላይ የጥቃት እርምጃ ብትወሰድ  ቀጣናውን ወዳልተፈለገ አቅጣጫ የሚቀይረው ሲሆን በኢትዮጵያ ውስጥ ሰፊ የጋራ ጥቅም ያላት ቻይናና የግብጽ ባላንጣ የሆነችው እስራኤልን ወደጉዳዩ እንዲገቡ ሊያደርጋቸው ስለሚችል ግብጽ በምትወስደው  የጥቃት እርምጃ ምንም ትርፍ አታገኝም ሲሉ ለአል አረቢያ ሳተላይት ቴሌቪዥን ጣቢያ የረቡዕ 30/ 5/2013 ዕለት ስርጭት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
      የሰሞኑ የግብጽ ሚዲያዎች እያራገቡ የሚገኙበትን ዘገባ ስንቃኝ  ጦር፤ ጦር የሚሸት መንፈስን ባዘለ መልኩ መሆኑ  ምናልባትም አንዳንዶቹ ለኢትዮጵያ ባላቸው ዝቅተኛ ግምትና  ለራሳቸው ጥቅም አብልጦ የማሰብ ራስ ወዳድነት ሲሆን አንዳንዶቹም በከፍተኛ ፖለቲከኞች በኩል ሆን ተብሎ በማስፈራሪያ ሰበብ  የሚሰራጭና የግብጽ እርምጃ የት ድረስ ሊሄድ እንደሚችል ለኢትዮጵያ መንግሥት መልዕክት ለማስተላለፍ ተፈልጎ ሊሆን እንደሚችል ይገመታል። 
በዚህም ተባለ በዚያ «አስቀድሞ ነበር መጥኖ መደቆስ፤ አሁን ምን ያደርጋል ድስትን ጥዶ ማልቀስ» እንዳይሆን  አንዴ የገቡበትን ሥራ ቀድሞ ባልጀመርነው ኖሮ ከማለት የኢትዮጵያ መንግሥት ከዲፕሎማሲው ጎን ለጎን ራሱን ማዘጋጀት ይገባዋል እንላለን። መንግሥት ልቡን ሰፊና እጁን ረጅም አድርጎ በፖለቲካ ያኮረፉትን በመጥራት በሀገር የጋራ ጉዳይ ላይ ማግባባት ወደሚችል የግል ሁኔታ ለመግባት የመድብለ ፓርቲውን ሥርዓት በር ከፈት ማድረግ አለበት።  እንደኢትዮጵያ ባለና ውጥንቅጡ በወጣ አመለካከት ውስጥ ልማት ብቻውን ሀገር አይገነባም። አሸባሪ የተባለ ማንም ተነስቶ የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው ቢል አያስገርምም። ባራቅነውና በረገምነው ቁጥር መራቁ ባህሪያዊ ነውና። አሁን በኢትዮጵያ የሚታየው ሕገ መንግሥታዊ መብቶችን በልማት ዜማ የማዳፈን ጉዳይ አኩራፊ ማበራከቱና ለጠላት በር መክፈቱ አይቀሬ ይሆናል። ግብጾች ራሳቸው መሥራት ያልቻሉትን የውጪ ሥራ በሌሎች እጅ ከማሰራት ይመለሳሉ ማለት የዋህነት ነው። 
ዓለማችን በአየር ለውጥ የተነሳ ሙቀቷ እየጨመረና በረሃማነትም እየተስፋፋ እንደመሄዱ መጠን አንድ ዓባይን ብቻ በተስፋ የምትጠብቅ ግብጽ በሆነ አጋጣሚ አንድ ክረምት ዝናብ በበቂ ባይጥልና ወንዙ ጎድሎ በትነት መጠኑን ከቀድሞው ቢቀንስባት ወደአጥፍቶ መጥፋት አትገባም ማለት አይቻልም። ረጅም እሳቤ ያለው እቅድ ለዓባይ የዛሬው ግድብ አስፈላጊው ነው እንላለን። 
እንዲያውም ስለዓባይ የተነገረው  የግብጽ ሸክም የሚራገፍበት ዘመን ደርሶም ይሆን? የሚል የትንቢት ጥያቄም እናነሳለን።
«ግብጻውያንንም በጨካኝ ጌታ እጅ አሳልፌ እሰጣለሁ ጨካኝ ንጉሥም ይገዛቸዋል ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፦ ውኆችም ከባሕር ይደርቃሉ፥ ወንዙም ያንሳል ደረቅም ይሆናል። ወንዞቹም ይገማሉ፥ የግብጽም መስኖች ያንሳሉ ይደርቃሉም ደንገልና ቄጤማ ይጠወልጋሉ።  በዓባይ ወንዝ ዳር ያለው መስክ በዓባይም ወንዝ አጠገብ የተዘራ እርሻ ሁሉ ይደርቃል፥ ይበተንማል፥ አይገኝምም። ዓሣ አጥማጆቹ ያዝናሉ፥ በዓባይም ወንዝ መቃጥን የሚጥሉት ሁሉ ያለቅሳሉ፥ በውኆችም ላይ መረብ የሚዘረጉት ይዝላሉ» 
ኢሳ 19፤ 4-8

Thursday, May 16, 2013

የማኅበረ ቅዱሳን ተላላኪና ሙሰኛው አባ ኅሩይ ወንድይፍራው ከሥራ አስኪያጅነታቸው ታገዱ።

አባ ኅሩይ ወንድይፍራው የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ኃላፊነቱን ከአባ ሠረቀ ብርሃን ወ/ሳሙኤል እጅ ተረክበው ማኅበረ ቅዱሳን በሚሰጣቸው መመሪያና ምክር መሠረት ለቤተ ክህነቱ ሸክም፤ ለማኅበሩ ግን ታማኝ አገልጋይ ሆነው መቆየታቸው ይታወሳል። በሥራው ላይ እያሉም በአንድ ወቅት አምነው የፈረሙበትን ደብዳቤ በጨለማ ተታልዬ ነው፤ አሳስተውኝ ነው፤ መዝገብ ቤቷ አሞኝታኝ ነው…………. ወዘተ፤ በሚል ማጭበርበሪያ ምክንያት የፈረሙትን ደብዳቤ መልሰው በመካድ የሰውዬው አቋመ ቢስና እምነት የማይጣልባቸው፤ እንደተልባ ስፍር የሚንሸራተቱ መሆናቸውን አይተን ከዚህ በፊት መዘገባችንም አይዘነጋም። ሰውዬው ማኅበረ ቅዱሳንን የሚያገለግሉት ስለሚወዱት ሳይሆን ስለሚፈሩት እንደሆነ በቅርብ የሚያውቋቸው ሰዎች ሲናገሩ ተሰምተዋል። ለምን እንደሚፈሩት የሚያውቁት እሳቸውና የኃጢአት መዝገብ ጸሐፊው ማኅበር ብቻ ናቸው። እንደክርስቲያን መፍራት የሚገባቸው የፈጠራቸውን እግዚአብሔርን ብቻ መሆን እንደሚገባው  ብናምንም እንደሥጋዊ ሰው ድካማቸውን አይተን ማኅበሩ እዳ በደላቸውን አደባባይ እንዳያውለው ቢፈሩ በእርግጥም ሊታዘንላቸው ይገባል እንላለን።
ይሁን እንጂ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት አራት ቦታ ተበታትኖ ልዩ ልዩ ያልጠረቁ ጅቦችን ለማዳረስ ቅርጫው በሲኖዶስ በተወሰነ ጊዜ አባ ኅሩይም አንዱ እግር ደርሷቸው በምዕራብ ክፍለ ከተማ ሀ/ስብከት ሥራ አስኪያጅነት ተመድበው ነበር። አባ ኅሩይ ብዙዎች ከሚያዝኑባቸውና ከሚያማርሩባቸው ምክንያቶች ዋናውና ግንባር ቀደሙ ጉዳይ ፈርሃ እግዚአብሔር የተለየው ጉቦኝነታቸው ሲሆን እስከዛሬም ብዙዎች እንባቸውን እንደራሔል ወደሰማይ የረጩባቸው ርኅራኄ የለሽ መሆናቸው ነው። አባ ኅሩይ እንኳን ሥራ አስኪያጅ የመሆን ብቃት ምንም የሌላቸው ይሁኑ እንጂ  ጉቦ / ዘረፋ/ በተባለው በሽታ ግን ፈጣንና ጥሩ የገፈፋ ልምድ ያካበቱ እንደሆኑ ገንዘባቸውን የገበሩ ሰዎች በምሬት ሲናገሩ ይደመጣሉ። እሰራልሃለሁ ብለው ሳይሰሩላቸው ያጉላሏቸውና አቤቱታ አቅርበው ከተባባሪ ሌባ አስተዳዳሪዎች ጋር ውስጥ ለውስጥ እየተገናኙ ባለጉዳዩን ያለሥራ ያንሳፈፈፉ፤ ማስጠንቀቂያ እንዲጻፍበት ያስደረጉ፤ የቤተ ክህነቱ ሸክምና የካህናቱ የልቅሶ ምንጭ መሆናቸው ሲነገር የቆየ ጉዳይ ነው።
ይህ ግፍና መከራው የበዛባቸውና ሸክሙ የከበዳቸው ካህናት በአንድ ድምጽ ሆ ብለው ጩኸት በማሰማታቸው፤ ጉዳዩ እስከ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ድረስ ቀርቦ ማስረጃዎች በመገኘታቸው የመጨረሻ ውሳኔ እስኪሰጥባቸው ድረስ የማኅበረ ቅዱሳኑ ተላላኪና የሙሰኞች አባት አባ ኅሩይ ወንድይፍራው በሊቀጳጳሱ ደብዳቤ ከሥራቸው ታግደዋል።
ከዚህ በፊት «ደጀሰላም» ብሎግ እኒህን ሙሰኛ መነኩሴ ሲያንቆለጳጵሳቸውና ከማኅበረ ቅዱሳን ጋር ተስማምተው ለመስራት ተነሳሽነቱ ያላቸው እያለ ለመካብ የሞከረ ቢሆንም በወቅቱ እንደዘገብነው ጊዜውን ጠብቆ ማንነታቸው ገሃድ ወጥቶ እነሆ በሙስና ተግባራቸው ከስራቸው እስከመታገድ ደርሰው የተሸፈነው ሲገለጥ ለማየት ችለናል። ጊዜው ቢረዝምም «ጉድና ጅራት ከወደኋላ ነው» እንዲሉ ከብዙ ጥፋት በኋላ ስራቸው  ማንነታቸውን ገልጦ ሰዓቱ ሲደርስ በመናገሩ፤ ማኅበረ ቅዱሳንን ሲሸማቀቅባቸው፤ እውነታውን ሲለፈልፉ ያልተሰሙት ደግሞ ተግባሩ ራሱ ምስክርነቱን ሰጥቶላቸዋል።  እነማን የማኅበሩ አባላት እንደሆኑ እንደአንድ ማሳያ  ሆኖም ይቆጠራል።
በሌላ መልኩ በእነአሉላ ጥላሁን፤  በእነ መረዋ ዱከሌ በዘመናዊ ስሙ/ ጳውሎስ መልክአ ሥላሴ/ እና በመሰሎቹ የሚዘወረው ከደጀ ሰላም ብሎግ ሞት በኋላ አዲስ የመጣው የማኅበሩ አገልጋይና የደብረ ብርሃን ወታደር የሆነው/ ሐራ ዘተዋሕዶ/ ብሎግ በአዲሱ ፓትርያርክ ምርጫ ወቅት የምርጫው ሂደት ፍትሃዊ አይደለም ሲል እንዳልቆየ ሁሉ የፈለገው አለመሳካቱን ሲያረጋግጥ ፓትርያርኩ ከሰማይ የወረዱ መልአክ ናቸው ወደሚል ውዳሴ መሸጋገሩ ፍቅር ስለጸናበት ሳይሆን »ጅብን ሲወጉ……» እንዲሉ ሆኖ በፓትርያርኩ ሙገሳ ተተግኖ «የማኅበሩ መንገድ ይጠረግ፤ ስርጓጉጡም ይቅና» ለማለት ካልሆነ በስተቀር የንግድ ማኅበሩን ነጋዴነትና የሙሰኞች ወዳጅነቱን ሊሸፍነው አይችልም። ለቤተ ክርስቲያን ከማሰብ የመነጨ እንዳይደለም አሳምረን እናውቃለን። ሌላው ጉዳይ ደግሞ የሙስና አለቃና የቤተክህነቱ ሸክም እንደሆነ የሚነገርለት ንቡረ እድ ኤልያስ አብርሃና  በዙሪያው ያሉ ሙሰኞች የስራ መሰናክል መሆናቸው ባይካድም ማኅበሩ ደግሞ ይህንን ግልጥ ጉድለት በሐራ ተዋሕዶ በኩል ፓትርያርኩን ተጠግቶ እየጮኸ፤  መንገዱን በመዝጋት ማኅበሩ ሰርጎ እንዳይገባ እንቅፋት የሆነባቸውን ሰው በስመ ሙስና አስወግደው  የራሳቸውን የቀን ጅቦች በቦታው ለመተካት ብሎጉ ሲዳክር ይታያል። ነገሩ «ከዝንጀሮ ቆንጆ ማን ይመራርጡ» ስለሆነ የእነ ንቡረ እድ ኤልያስ ቡድንም ይሁን የደብረ ብርሃኑ ወታደር ቡድን ሁላቸውም በቤተክህነቱ ውስጥ የራሳቸውን ጥቅም ለማስጠበቅ የሚደክሙና የፍትህና ርትዕ ዜማ እየጮሁ ቀበሮነታቸውን ለመሸፈን የሚጥሩ አስመሳይ በላተኞች እንጂ ቤተክህነት የምትሄድበትን የቁልቁሊት መንገድ ለማቃናት ተፈጥሮም ዓላማም የላቸውም። ምክንያቱም  እነንቡረ እድ የሚታሙበትን ሙሰኝነት በተቃራኒው በማኅበሩ አባልና ደጋፊ በአባ ኅሩይም በኩልም እየተገለጸ ይገኛልና። ሁሉም ሙሰኞችና ነጋዴዎች ስለሆኑ ከቤተክህነት ዐውድ መገኘታቸው አንዱ አንዱን ለመጣል በሚደረገው የባለሥልጣናት ጥገኛ የመሆን አባዜ ውስጥ ቤተ ክህነቱን የመንፈሳዊነት ሳይሆን የጥቅም ጦር ዐውድማ አድርገዋታል።
ለፓትርያርኩ የምናሳስበውና የምንጠይቀው ዐብይ ነጥብ ማንም የቤተ ክህነቱ አዛኝ መስሎ የሚጮኸውን ሁሉ በግ ብለው እንዳይቆጥሩና እንዳይታለሉ ሲሆን የመዋቅር ለውጥ፤ የአስተዳደር ሪፎርም፤ የሥራና ሠራተኛ ግንኙነትን ማሻሻል፤ ሕግና ደንብ ገዢ ማዕከል እንዲሆን በማስቻል አዲስ የሥራ መንፈስን በመፍጠር እንጂ በጥገናዊ ለውጥ አንዱን በማቅረብ ሌላውን በማራቅ ላይ አይጠመዱ ድምጻችን ነው። የአባ ኅሩይን የእግድ ደብዳቤ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

Sunday, May 12, 2013

አዲስ ሃይማኖት አልመሰረትንም

(አዲስ አድማስ)!
 ከቤተክርስቲያን ጋር ፀብ የለንም፤ ለአመፃ አልመጣንም” (“የማህበረ ዘደቂቅ ኤሊያስ” መሪዎች)
“በማህራችን እኔ ኤልያስ ነኝ የሚል አላጋጠመኝም. ነብዩ ኤልያስ በነገረን መንገድ የጥንቷን ሃይማኖት እያስተካከልን ነው -ቅዱስ ኤልያስ በኢትዮጵያ ሚሊኒየም ወደ ምድር ወርዶ በእሳት ሰረገላ እየተዘዋወረ ነው”
ነብዩ ኤልያስ ለፍርድ ወደ ምድር ወርዶ በእሳት ሰረገላ እየታየ ነው ከሚለው እምነታቸው ጋር በተያያዘ ድንጋይ ተወርውሮባቸው በተፈጠረ ሁካታ ለሰባት ቀናት ታስረው የነበሩት አባ ዮሴፍ ብርሃነ፣ አርቲስት ጀማነሽ ሰለሞን፣ መምህር ወልደመስቀል ፍቅረማሪያም እንዲሁም ፕሮፌሰር ይስማማው አለሙ፤ ሃይማኖታችን ተዋህዶ ነው፤ ኦርቶዶክስ የሚለው ቃል አላግባብ የተጨመረ ነው ይላሉ፡፡ “ማህበረ ዘደቂቀ ኤልያስ” በሚል ስያሜ ራሳቸውን የሚጠሩት የማህበሩ መሪዎች፤ አዲስ ሃይማኖት እንዳልፈጠሩ ሲያስረዱ፣ የጥንቷን እውነተኛ ሃይማኖት ወደ ትክክለኛ ቦታዋ እንድትመለስ እያደረግን ነው ብለዋል፡፡ ይህን የምንሰራው ነብዩ ኤልያስ በነገረን መንገድ እንጂ እኛ በመሰለን መንገድ አይደለም የሚሉት የማህበሩ መሪዎች፤ በማህበሩ ውስጥ ኤልያስ ነኝ የሚል ሰው የለም ብለዋል፡፡
ከማህበሩ መሪዎች መካከል አንዱ የሆኑት አባ ዮሴፍ ብርሃነ “ኤልያስ ወደ ምድር መጥቷል” በሚለው እምነታቸው ዙሪያ ተጠይቀው፤ ከ2000 ዓ.ም ጀምሮ አለምን ለመፋረድ ከገነት ወደ ምድር ወርዶ በእሳት ሰረገላ እየተዘዋወረ ነው ብለዋል፡፡ ኤልያስ መጥቷል ስላልን አይመጣም፡፡ እኛ ኤልያስ አልመጣም ስላልን አይቀርም ያሉት አባ ዮሴፍ፤ ኤልያስ እንደሚመጣ በመፅሃፍ ቅዱስ በግልፅ የተነገረ ስለሆነ ብቻ ሳይሆን የሚመጣበት ጊዜም ስለተጠቀሰ ጊዜውን አስልቶ ማወቅ ይቻላል ብለዋል፡፡ ከአንዳንድ ሰዎች ዘንድ ተቃውሞ እንደተሰነዘረባቸው ያመኑት አባ ዮሴፍ፤ እስካሁን ጉዳዩ በሲኖዶስ ቀርቦ እንዳልተወገዘና ሲኖዶሱ ጉዳዩን ቢመረምረው እንደሚወዱ ገልፀዋል። ማህበሩን ከተቀላቀለች አንድ አመት ከ7ወር እንደሆናት የገለፀችው አርቲስት ጀማነሽ፤ አንዳንድ ሰዎች ጀማነሽ የመሠረተችው አዲስ ሃይማኖት መጥቷል በሚል ህብረተሰቡን እያደናገሩ ነው ካለች በኋላ፣ እኔ የመሠረትኩት አዲስ ሃይማኖት የለም ብላለች፡፡ “ተዋህዶ” የሚለው ስም ከጥንት የኖረ የሃይማኖታችን መገለጫ እንጂ እኔ የፈጠርኩት አይደለም ያለችው አርቲስቷ፤ “እውነትን እየተናገረ በሚኖር ሰው ላይ ክፉ ስም እየለጠፉ ለማሳደድና እውነትን ለመደበቅ ከመሞከር እውነቱን መመርመር ይሻላል” ብላለች፡፡
ኦርቶዶክስ የሚለው ቃል አላግባብ የተጨመረ መሆኑን የሚያምኑት የማህበሩ መሪዎች፤ የጥንቷ እውነተኛ ሃይማኖት መገለጫዋ ተዋህዶ የሚለው ስያሜ ነው ብለዋል፡፡ “ኤልያስ መጥቷል ትላላችሁ፤ ኤልያስ በማህበራችሁ ውስጥ አለ ወይ?” በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ፤ “ኤልያስ መጥቷል አልመጣም የሚለው መልዕክት ሊያከራክር ቢችልም፣ እስካሁን በማህበራችን እኔ ኤልያስ ነኝ የሚል አላጋጠመኝም” ብላለች፡፡ መ/ር ወልደመስቀልም በበኩላቸው፤ በበረሃ ያሉ፤ በፆምና በፀሎት የተጉ አባቶቻችን ኤልያስ ተገልጦላቸዋል፣ ዳሷቸዋል፣ አነጋግሯቸዋል” ብለዋል፡፡ በፖሊስ የታሰሩበትን ምክንያት ተጠይቀው ሲመልሱ፣ በሚያዝያ 16 ቀን የኪዳነምህረትን ዝክር ለመዘከር 4 ኪሎ ቅድስት ስላሴ ቤተክርስቲያን አካባቢ ወደ ምትገኝ የማህበሩ መሰብሰቢያ ቤት ፀበል ፃዲቅ ይዘው በሚሄዱ አባላት ላይ አንዳንድ የሠፈሩ ወጣቶች ድንጋይ በመወርወራቸው በተፈጠረ አለመግባባት መሆኑን አስረድተዋል፡፡ በወጣቶቹ ድርጊት አንዲት ታዳጊ መፈንከቷን የገለፁት የማህበሩ መሪዎች፤ በእለቱ በከሣሽነት ወደ ፖሊስ ጣቢያ ሄደው የከሳሽነት ፎርም ሞልተው ቃላቸውን ከሰጡ በኋላ፣ በጣቢያው አዛዥ ውሳኔ የከሳሽነት ቃላቸው ተቀይሮ በተከሳሽነት ቃላቸውን እንዲሰጡ መደረጋቸውን ተናግረዋል፡፡
ከከሳሽነት ወደተከሳሽነት እንዲቀየሩ የተደረገው ቀደም ሲል የአካባቢው ሰው ለፖሊስ ጣቢያው ተደጋጋሚ አቤቱታ በማቅረቡ መሆኑን መምህር ወልደመስቀል ተናግረዋል፡፡ ማህበሩ መርሃ ግብሮችን ሲያከናውን ድምጽ ይረብሸናል የሚሉ አቤቱታዎች እንደቀረቡብን ተረድተናል፣ ነገር ግን በፍርድ ቤት ሲቀርቡ በደፈናው ሁከት ፈጠራችሁ የሚል ክስ ነው የተመሰረተብን ብለዋል የማህበሩ መሪዎች፡፡ በመጀመሪያ የፍርድ ቤት ውሎ የዋስ መብታቸውን ቢጠይቁም፤ መርማሪው የአካባቢው ህብረተሰብ ቦታውን ለቀው እንዲወጡ የሚል አቤቱታ እያቀረበ ስለሆነ ጉዳዩ እስኪጣራ የዋስ መብታቸውን እቃወማለሁ በማለቱ ለ7 ቀናት በእስር መቆየታቸውን የገለፁት የማህበሩ መሪዎች፤ በመጨረሻ ግን ስትፈለጉ ትቀርባላችሁ ተብለው እያንዳንዳቸው በ500 ብር ዋስ እንደተለቀቁ ተናግረዋል፡፡

Friday, May 10, 2013

«ጠንቋዩ ግርማ ወንድሙ በእስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን ሲያደርግ ከነበረው የጥንቆላ ሥራው ታገደ»



ግርማ ወንድሙ የተባለው አጥማቂ ነኝ ባይ ግለሰብ ከሚያዚያ 28/2005 ዓ/ም ጀምሮ ከአጥማቂነት ሥራው መታገዱንና ሰው ማንጋጋቱን እንዲያቆም የታዘዘ መሆኑን አያይዞ ባወጣው የእግድ ደብዳቤ ላይ ዝርዝር ምክንያቱን ተጠቅሶ ተጽፎለታል።
እንደሚታወቀው ጠንቅ ዋይ ግርማ ወንድሙ  በመንግሥት ባልተመዘገበና ከአነስተኛና ጥቃቅን የሥራ መስኮች ውስጥ አንዱ ባልሆነው ልዩ የሥራ ፈጠራ ላይ ተሰማርቶ ጥንቆላውን በሱዳንና በሺናሻ ዕጽ እየታገዘ ጤናማውን ሁሉ እያሳበደና እያስጮኸ ሲያጭበረብር መቆየቱ ይታወቃል። ቤተ ክህነት ይህንን ማጭበርበሩን በጸጋ መንፈስ ቅዱስ የሚያደርግ ያህል ቆጥራ ዝምታን በመመምረጧ ልጆቼ ናቸው የምትላቸው ተከታዮቿን ገንዘባቸውን እየመዘበረ፤ አእምሮአቸውን እያቃወሰ፤ የተረጋጋና ሰላማዊ ኑሮ እንዳይኖሩ ብኩን እያደረገ፤ ለሰይጣን ግዛት እያመቻቸ ሲሸኛቸው እስካሁን ዝም ከማለቷ ባሻገር አቡነ እስጢፋኖስን የመሳሰሉ ጳጳሳት ደግሞ ለግርማ ወንድሙ ጥንቆላ እውቅና በመስጠት ይባስ ብለው ሀገረ ስብከታቸው ድረስ ወስደው ሕዝቡን እያሳበደ ገንዘብ እንዲሰበስብላቸው እስከማድረግ መድረሳቸውን አይተን አፍረናል።
ግርማ ወንድሙ የሥራ ፈጠራውን ተደናቂ የሚያደርገው በቤተክርስቲያን ከለላ ስሟን እየጠራና ግቢዋን ተተግኖ መሆኑ እንጂ በግብር ከታምራት ገለታ የሚለይ አይደለም። ከዚያ ባሻገር በስመ አጥማቂና ባህታዊ በቤተ ክርስቲያን ተጠግተው ሕዝብ በማስጮህ ገንዘብ የመሰብሰቢያ ስልት እንጂ ግርማ ወንድሙ መንፈስ ቅዱስ ስላደረበት አይደለም። ቅዱሳን በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ሙት ሲያስነሱም ሆነ ድውይ ሲፈውሱ ውሃ ውስጥ በመዝፈቅ ወይም በመቁጠሪያ በመደብደብ ሳይሆን ስመ እግዚአብሔርን በመጥራት ብቻ ነው።
«ጴጥሮስ ግን። ብርና ወርቅ የለኝም፤ ይህን ያለኝን ግን እሰጥሃለሁ፤ በናዝሬቱ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተነሣና ተመላለስ አለው።በቀኝ እጁም ይዞ አስነሣው፤ በዚያን ጊዜም እግሩና ቍርጭምጭምቱ ጸና» የሐዋ 3፤6-7
መንፈስ ቅዱስ ባደረባቸው አባቶች እንኳን ቃል ተናግረው ይቅርና ጥላቸው ሲያርፍባቸው ሙታን ይነሱ፤ ድውያን ይፈወሱ ነበር። ጠንቅ ዋዩ ግርማ ወንድሙ ግን በእጁ ላይ የሚያንጠለጥላትን መቁጠሪያ ካልያዘ ማዳን ሳይሆን ማሳበድ የማይችል አስማተኛ ነው። የቅርብ ወዳጁ የሆነ አንድ ሰው መረጃ እንዳካፈለን ግርማ ወንድሙ ገንዘብን የአምላኩ ያህል እንደሚወድና እስካሁንም ባግበሰበሰው ብር እንዳልረካ ነገር ግን ወደአሜሪካ መሄድ የሚችልበትን መንገድ ወይም ከሰዎች ጋር እንዲያገናኘው ብዙ ጊዜ እንደጠየቀው የገለጸልን ሲሆን ይህንን ለገንዘብ ያለውን ፍቅር በመመልከት ቀድሞ በሱ ላይ የነበረውን የማጥመቅ ችሎታ እንደተጠራጠረው ተናግሯል። አሜሪካ የመሄዱ ጉዳይ ለጊዜው ባይሳካለትም ሰሞኑን ወደእስራኤል በአበሾች ላይ  እብደት በማስፋፋት ገንዘብ ለመሰብሰብ ማቅናቱ ይነገራል። የግርማን ከሀገር መውጣት ተከትሎ የእስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ በሌለበት የእግድ ደብዳቤ ጽፈውበታል። ቀጣዩ ጉዞው ምናልባትም አሜሪካ ይሆንና የሚበቃውን ዘርፎ የሚመኘውን ያህል ካገኘ አንዷን ቆንጆ አግብቶ ባለትልቅ ኢንቨስትመንት ባለቤት የመሆን ሕልሙን ያሳካል ማለት ነው። የሰው ሃሳብ እንደዚያ ቢሆንም የእግዚአብሔር የተለየ ስለሆነ ግርማ ወንድሙ ሥጋዊ ሩጫህን በጥንቆላ ከምትጨርስ ንስሐ በመግባት ራስህን አድን ምክራችን ነው።
 የእግዱን ደብዳቤ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ

Wednesday, May 8, 2013

አርቲስት ጀማነሽ ሰሎሞን ከፋንታሁን ንጉሤ ጋር ያደረገችው ቃለ መጠይቅ


ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአርቲስት ጀማነሽ ሰሎሞን ላይ የማኅበረ ቅዱሳን ብሎጎች፤ የሀገር ቤት ተወካይ መጽሔቶችና ተላላኪዎች የስም ማጥፋት ዘመቻ ከመክፈት በዘለለ ወደኃይል መጠቀም መሸጋገራቸውን ለማወቅ ችለናል። እምነት የግል ነጻነት መሆኑ ያልገባቸው እነዚህ የእስልምና ሰለፊ የግብር ወንድሞች ጀማነሽ ሰሎሞን እንኳን በነብዩ አልያስ ዳግም መምጣት ማመን ቀርቶ ነብያት ሁሉ ተመልሰው መምጣታቸውን በማወጅ የሚቀበላት ካገኘች ለማሳመን መብቷ መሆኑን ባለማወቃቸው ብዙ ብዙ ብለዋል። መካነ ጦማራችን ስለነብዩ ኤልያስ መምጣት ትረካ የማታምንበት ቢሆንም እንኳን የጀማነሽ ሰሎሞን ነብዩ ኤልያስ በመምጣቱ የማመኗን መብት ግን ከመቀበል ባሻገር ይህንን ለመደፍጠጥ የሚፈልጉትን አትደግፍም። ያለንበት የመጨረሻው ዘመን ላይ ስለሆነ ገና ከዚህ የባሰ ልንሰማ ስለምንችል ራስን ጠበቅ አድርጎ እውነቱን በመናገር እንጂ በዚህ መጣ፤ በዚያ ወጣ እያሉ በማጣደፍ ነገሮችን ሁሉ በኃይል ለመፍታት ዘመቻ መክፈት ትክክል አይደለም። ጠማማ ልብና ክፉ ምላስ ቢዘገይ እንጂ መውደቁ እርግጥ ነው። «ጠማማ ልብ ያለው መልካምን አያገኝም፥ ምላሱንም የሚገለብጥ በክፉ ላይ ይወድቃል» ምሳሌ 17፤20 ሌላውን ጠማማ እያሉ ራስን ማጣመም ትክክል አይደለም እንላለን። ነብዩ አልያስ መጥቷል የሚሉትን ለመቃወም የት እንዳለ አሳዩን ማለቱ አይቀልም ነበር? ሐዋርያው እንዳለው «አሁንም እላችኋለሁ። ከእነዚህ ሰዎች ተለዩ ተዉአቸውም፤ ይህ አሳብ ወይም ይህ ሥራ ከሰው እንደ ሆነ ይጠፋልና» የሐዋ 5፤38 ለማንኛውም አርቲስቷ ከእስር ከተፈታች በኋላ ያደረገችውን ቃለ ምልልስ አቅርበንላችኋል።

Tuesday, May 7, 2013

I shall (persevere)! Eskinder Negga from Kaliti ( may history will judge!!)



 So that I may do the deed
That my soul has to itself decreed.

- Keates

Individuals can be penalized, made to suffer [oh, how I miss my child] and even killed. But, democracy is a destiny of humanity which cannot be averted. It can be delayed but not defeated.

No less significant, absent trials and tribulations, democracy would be devoid of the soul that endows it with character and vitality. I accept my fate, even embrace it as serendipitous. I sleep in peace, even if only in the company of lice, behind bars. The same could not be said of my incarcerator though they sleep in warm beds, next to their wives, in their home

The government has been able to lie in a court of law effortlessly as a function of the moral paucity of our politics. All the great crimes of history, lest we forget, have their genesis in the moral wilderness of their times.

The mundane details of the case offer nothing substantive but what Christopher Hitchens once described as “a vortex of irrationality and nastiness.” Suffice to say, that this is Ethiopia’s Dryfus affair. Only this time, the despondency of withering tyranny, not smutty bigotry, is at play.

Martin Amis wrote, quoting Alexander Solzhenitsyn, that Stalinism [in the 30s] tortured you not to force you to reveal a secret, but to collude you in a fiction. This is also the basic rational of the unfolding human rights crisis in Ethiopia. And the same 30s bravado that show-trials can somehow vindicate banal injustice pervades official thinking. Wont to unlearn from history, we aptly repeat even its most brazen mistakes.

Why should the rest of the world care? Horace said it best: “mutato nomine de te fabula naratur.” “Change only the name and this story is also about you.” Whenever justice suffers our common humanity suffers, too.

I will live to see the light at the end of the tunnel. It may or may not be a long wait. Whichever way events may go, I shall persevere!

liberté, egalité, fraternité.

History shall absolve democracy!

Monday, May 6, 2013

ፓትርያርኩ የህዳሴው ግድብ ያለጥርጥር እንደሚሳካ ተናገሩ


(Reporter) መጋቢት 24 ቀን 2003 .. የተጀመረውና በአሁኑ ጊዜ ስምንት ከመቶ ማደጉ የተነገረለት የህዳሴውን ግድብ ጨምሮ፣ ሁሉም የተጀመሩ ትላልቅ ሥራዎችን ያለምንም ጥርጥር ማሳካት እንደሚቻል፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ አስታወቁ፡፡
ፓትርያርኩ የተናገሩት ሚያዝያ 27 ቀን 2005 .. የሚከበረውን የፋሲካ በዓል አስመልክተው ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች ባስተላለፉት የቡራኬ ቃል ላይ ነው፡፡

‹‹የእውነትና የሕይወት መንገድ አድሶልናልና የሚለውን የፋሲካ ትምህርተ ሃይማኖት፣ የህዳሴውን ልማት በማፋጠንና በማሳካት ልንገልጸው ይገባል፤›› ያሉት ፓርትያርኩ፣ በታላቁ የሕዳሴ ግድብ እንደሚታየው፣ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሃያ አራት ሰዓታት በትጋት ከሠራ፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሌሎች የበለፀጉ አገሮች ከደረሰቡት የዕድገት ደረጃ የማይደረስበት ምክንያት እንደሌለ ገልጸዋል፡፡
ከክርስትና ሃይማኖት አስተምህሮ በሚመነጨው መርህ መሠረት በሥራ መትጋትና በፍፁም ፍቅር መኖር፣ ሕይወትን ይበልጥ ማሳደግ እንደሚገባና ከሁሉም በፊት ሰው የተፈጠረው ለሥራና ለክብር መሆኑን መዘንጋት እንደማይገባ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ አስረድተዋል፡፡ ‹‹ወደ መጣህበት መሬት እስከምትመለስ ድረስ ጥረህ፣ ግረህና ላብህን አንጠፍጥፈህ ብላ፤›› የሚለውን የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ በማስታወስ፣ ሰው ለአንዲት ደቂቃ እንኳ እጅ እግሩን አጣጥፎ ያለሥራ እንዲቀመጥ እግዚአብሔርም እንደማይፈቅድ ተናግረዋል፡፡ ሁሉም ኢትዮጵያዊያን በኅብረት፣ በአንድነት፣ በስምምነት፣ በመተማመንና በመቻቻል ለሥራና ለሥራ ብቻ መነሳት እንደሚገባቸው ተናግረዋል፡፡

የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች በዓሉን ሲያከብሩ፣ ለሰው ልጆች ብሎ በሰው ልጆች ፈንታ መስዋዕት በመሆን የዘለዓለም ሕይወትን ካጐናፀፈው ጌታ ጋር ማክበር እንዳለባቸው፣ የተራቡትን በመመገብ፣ የተጠሙትን በማጠጣት፣ የታረዙትን በማልበስ፣ የታመሙትንና የታሰሩትን በመጠየቅ፣ እንግዶችን በመቀበልና በማስተናገድ መሆን እንዳለበት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ አሳስበዋል፡፡