Tuesday, December 10, 2013

ራሺያ የአሸባሪዎች መመሪያ ብላ የሰየመችው «ቁርአንን» በሀገሯ ቋንቋ ተተርጉሞ እንዳይገባ አገደች።


 
አዣንስ ፍራንስ ፕሬስ እንደዘገበው፤ የራሺያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የአሸባሪዎች የሽብር መመሪያ ነው ያለውን ቁርአን ወደሀገሩ እንዳይገባ የእግድ ውሳኔ አሳለፈ። ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ በውሳኔው ላይ እንዳመለከተው ፤ አንድ መጽሐፍ ወደራሺያ ከመግባቱ በፊት ማኅበራዊ ኑሮን፤ የራሺያን ባህልና ወግ የማይጻረር መሆኑ ሳይመረመር በፊት መግባት ስለማይችል፤ ቁርአን የተባለው መጽሐፍ በሳዑዲ ዐረቢያ ውስጥ በራሺያው ዜጋ ኤልሚር ኩልየቭ በኩል ተተርጉሞ በነጻ ከታተመ በኋላ  ኮፒውን መርምረናል ያለው ፍርድ ቤቱ፤ ይህ መጽሐፍ እንደማንኛውም ሌሎች መጽሐፍ ውስጡ ተመርምሮ የተደረሰበት ጭብጥ እንደሚያስረዳው ትርጉሙ ወደራሺያ ምድር ቢገባ ሽብርን በማበረታታት፤ ጥላቻን በመዝራትና ባህልና ወጋችንን በማደፍረስ ሰላምና መረጋጋት እንዲጠፋ በማድረግ በኩል አሉታዊ ጎኑ የበረታ በመሆኑ እንዳይገባ የእግድ ውሳኔ አሳልፈንበታል ሲል በውሳኔው ላይ ፍርድ ቤቱ ገልጿል።
  በኤልሚር ኩልየቭ በኩል የተተረጎመው ይህ በስም «ቁርአን» የተባለው መጽሐፍ በፍርድ ቤቱ የታየው በየትኛውም የሃይማኖት መጽሐፍነቱ ሳይሆን እንደአንድ ተራ መጽሐፍ ሲሆን የተመረመረውም ይኸው መጽሐፍ ሊሰጥ እንደሚችለው ሀገራዊ ጠቀሜታ አንጻር መሆኑንም ፍርድ ቤቱ ሳይገልጽ አላለፈም።

 ስለሆነም መጽሐፉ ለሀገራቸው ከሚሰጠው ጥቅም ይልቅ ውስጡ ሲመረመር ከጥቅሙ ጉዳቱ ስለሚያመዝን ትርጉሙ ወደሀገር ውስጥ እንዳይገባ ያገደ ሲሆን ይህንን የፍርድ ቤት እግድ ተላልፎ የተገኘ ማንም ዜጋ ሽብርተኝነትን በማበረታታትና በማስፋፋት በሚያስጠይቀው የሀገሪቱ ሕግ መሠረት ተጠያቂ እንደሚሆንም ተገልጿል።
  ይህ «ቁርአን» የተባለው መጽሐፍ የዐረቢኛው ትርጉም በራሺያውያን ሙስሊሞች እጅ የሚገኝ ቢሆንም ከራሺያ ቋንቋ ውጭ ስላሉ ትርጉሞች የተባለ ነገር የለም።

የራሺያው ቋንቋ የቁርአን ትርጉም  በወደሀገሪቱ እንዳይገባ መታገዱን በመቃወም የራሺያው የሙስሊሞች ሙፍቲ ራቪል ጋይኑትዲን ለራሺያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በጻፉት ደብዳቤ እንዳመለከቱት «ይህ እውቀት የጎደለውና ጸብ አጫሪ ውሳኔ እንደገና መታየት አለበት»  በማለት በኃይለ ቃል መግለጻቸውን «ኸፍ ፖስት» ጋዜጣ ዘግቧል።
  ጠቅላይ ሙፍቲው እንዳሳሰቡት « በጥቁር ባህር ወደብ ላይ ወደራሺያ ሊገባ የተዘጋጀው ይህ የቁርአን ትርጉም በአስቸኳይ መፍትሄ ካልተሰጠው፤ የእስላሞች መጽሐፍ ላይ የተወሰደ ውሳኔ አድርገን እንቆጥራለን» ሲሉ መናገራቸውም ተሰምቷል። አንድ ራሺያዊ ዜጋ ስለጉዳዩ በሰጠው አስተያየት እንደተናገረው « ራሺያ እስልምና ለሚፈልገው ማንኛውም ጉዳይ እንደውሻ ጭራዋን እየቆላች ለማስተናገድ የምትገደድበት ምክንያት የለም፤ እስልምና እዚያው ተፈጠርኩበት ካለው በሳዑዲ ምድር አርፎ ይቀመጥ፤ እንግድነት ከፈለገም እኛ ዜጎቹ በምንፈቅድለት መጠንና መንገድ ብቻ ሊስተናገድ ይገባዋል ሲል የገለጸ ሲሆን ምሬቱን በማከልም « ሳዑዲ ዐረቢያ ቁርአንን አሳትማ ወደራሺያ ስትልክ እንድንቀበልላት እንደምትፈልገው ሁሉ መጽሐፍ ቅዱስን በዐረብኛ ተርጉመን ወደሀገሯ እንድናስገባ በኦፊሴል ትፈቅድልናለች ወይ? ሲል ጠይቋል።

የራሺያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን የፍርድ ቤቱን ውሳኔ በተመለከተ ለሙፍቲው የሰጡት መልስ ምን እንደሆነ አልተዘገበም።