Monday, December 2, 2013

የአፍሪካ ኅብረት ቅ/ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን የገንዘብ ምዝበራ ተጋለጠ!

ለውድ ደጀ ብርሃን  ብሎግ በቤተክርስቲያናችን ያሉ ሕገ ወጥ አሰራሮችን በመቃወም የምታደርጉትን እንቅስቃሴ የምንደግፍ ሲሆን የቤተክርስቲያን አገልጋዮች በእውነት የሚታመኑ መሆን እንዳለባቸው እናምናለን እኛ የአፍሪካ ኅብረት ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ሰንበት ተማሪዎች ከእኛው አብራክ የወጡ ቤተክርስቲናችንን ይጠብቁልናል ባልናቸው ወንድምና እህቶቻችን ቤተክርስቲያን እየተመዘበረች ነው፡፡ ስለዚህ ሁሉም ይህንን እውነት ተረድቶ በስመ ታማኝነት ከሌቦች ጋር የተሰለፉ ሰንበተማሪዎችን እንዲጠብቅና እንዲያጋልጥ በቅርቡ የተፈጸመውን ምዝበራ በብሎጋችሁ እንድታወጡልን እንጠይቃለን፡፡

የአፍሪካ ኅብረት ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን በህዳር 12 ከተሰበሰበ ገንዘብ 200.000.00 (ሁለት መቶ ሺህ ብር ) በላይ ገንዘብ ተመዘበረ፡፡ የደብሩ አስተዳዳሪ የዓመት ፍቃድ በመሆናቸው በእለቱ ቆጠራ አልተገኙም ይህንንም እንደ መልካም አጋጣሚ በመቁጠርና የሰበካ ጉባዔ ምክትል ሊቀ መንበር ስልክ ተደውሎላቸው ቆጠራውን አቋርጠው በመውጣታቸው የደብሩ ዋና ጸሐፊ መ/ስ አብርሃም አቧይ  የወረዳው ስራ አስኪያጅ የአባ አእምሮ የቅርብ ዘመድ ከወረዳ የተወከሉት ወ/ሮ አባይ እና የሀገረ ስብከቱ ጸሐፊ ወ/ሮ አዲስ ዓለም እንዲሁም በአዲስ አበባ ሙስናና ዘረፋን በማበረታታት እነ የካ ሚካኤልን እንዳያገግሙ አድርጎ በዘረፋ ባዶ ያስቀራቸው በአዲስ አበባ ከተማ ለተለያዩ የውጪ ሀገር ኗሪዎች 7 ፎቅ ቤቶችን በተለያዩ አካባቢዎች  ሰርቶ የሚያከራየው ቀድሞ አለቃ የአደራው ንጉሤ ሴት ልጅ  ወ/ት እጸገነት አደራው በገንዘብ ያዥነት እንዲሁም በካቴድራሉ መልካም ሰው በመምሰል ለሁሉ ወዳጅ የሆነው አቶ ፋንታሁን ምረቴ እና ሊቀ ቀትጉሃን ኃ/ጊዮርጊስ በጋራ ዘረፋውን ማከናወናቸው ታውቋል፡፡የአፍሪካ ኅብረት ቅ/ሚካኤል በህዳር 12 ቀን ከምእመናን የተሰበሰበውን ገንዘብ ግማሹን በመቀነስ 280 ሺህ ብር ብቻ ወደ ደብሩ ባንክ እንዲገባ ሲደረግ ሌላውን ግን በቆጠራው የተገኙት ስማቸው የተዘረዘሩት ግለሰቦች ተካፍለውለታል፡፡ የደብሩ ጸሐፊ አብርሃም አቧይ ለአቡነ እስጢፋኖስ ቀራቢ ነኝ በማለት ደብሩን እየበጠበጠ ሲሆን፤ በትዳሩ ላይ በመወስለት እና ከሙስሊም ሳይቀር ዲቃላ በመውለድ ቤተክርስቲኒቱን ያሰደበ ተግባር መፈጸሙንና በአባ እስጢፋኖስ ዘንድ አለኝ በሚለው ተሰሚነት ሰራተኛውን እያስፈራራና እያሸበረ እንደሚገኝ ለማወቅ ተእሏል፡፡ በደብሩ ሰንበት ት/ቤት ተማሪ የነበሩና በኋላ በግል ጥቅም ታውረው የምዷየ ምጽዋት ገንዘብ የጣማቸውና ወደ ሰራተኛነት ያደጉት ዲ/ን ዳዊት ወርቁ ከሰበካ ጉባዔ አባልነት በተጨማሪ የደብሩ የእለት ገንዘብ ሰብሳቢ ተደርጎ የተመደበ ሲሆን ሌላዋ ሰንበት ተማሪ የመ/ር እንቁ ባሕርይ ቅምጥ የደብሩ ምክትል ሒሳብ ሹም በመሆን ስትሰራ የነበረቸው ወ/ት ምንጭቱ ከሒሳብ ሹሙ ጋር  ባለት የፍቅር ግንኙነት ቤተክርስቲኑ ውስጥ ያልተገባ ተግባር በመፈጸሟ ወደ ሌላ ቤተክርስቲያን መዛወሯን ለማወቅ ተችሏል፡፡
የገንዘብ ምዝበራውን ለማን አቤት ይባላል? ባለቤት የሌላት ቤተ ክርስቲያንን ከታች እስከላይ ወሮበሎች ወረዋታልና።