Showing posts with label ስብከት. Show all posts
Showing posts with label ስብከት. Show all posts

Thursday, July 18, 2013

የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ለምን ተሐድሶ ያስፈልጋታል? ክፍል ሁለት፡-

      
              (www.tehadeso.com)
ላደግንባት፣ ቃሉን ላወቅንባት እና አሁንም እያገለገልንባት ላለችው ለዚህች ቤተ ክርስቲያን ለዘመናት ሁሉ ዐዲስ የሆነውን የእግዚአብሔርን ቃል በመደገፍ እንደ ቃሉ የሆነ እና የሰላም አለቃ የሚሰለጥንበት ተሐድሶ እንደሚያስፈልጋት፣ በሙሉ ልባችን እናምናለን፡፡ ቤተ ክርስቲያን ተዘፍቃበት ካለው ሁሉን አቀፍ ችግር ለመውጣት የሚያግዛት በመንፈስ ቅዱስ መሪነት የሚከናወን ተሐድሶ አስፈላጊ ነው፡፡
“…እንደ ምሕረቱ መጠን ለዐዲስ ልደት በሚሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ አዳነን..”  የሚለው ዐረፍተ ነገር፣ ተሐድሶ በእግዚአብሔር መንግሥት አስፈላጊው እና ፍሬያማው እውነት እንደሆነ ያሳያል፡፡ የእግዚአብሔር ምሕረት ከፍተኛነት በመንግሥቱ ውስጥ ለሚኖረን ቦታ የሚያበቃን፣ በመንፈስ ቅዱስ በኩል የሆነው መታደስ ነው፡፡ ይህ እውነት ለግለሰብም ለቤተ ክርስቲያንም በእኩልነት ይሠራል፡፡ አንድ ሰው ከጠፋው ማንነቱ ተመልሶ ለእግዚአብሔር መንግሥት ዜጋ እንዲሆን ከመንፈስ ቅዱስ የሆነው ተሐድሶ እንደሚያስፈልገው ሁሉ ቤተክርስቲያንም የቀበረችውን እውነት ቆፍራ እንድታወጣ እና ለእግዚአብሔር ሐሳብ እሺ በጄ ብላ እንድትታዘዝ ከመንፈስ ቅዱስ የሆነው ተሐድሶ ያስፈልጋታል፡፡

ባለፈው በክፍል አንድ ጽሑፋችን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ለምን ተሐድሶ አንደሚያስፈልጋት ሦስት መሠረታዊ ምክንያቶችን አንሥተን ማቅረባችን ይታወሳል፡፡  ዛሬ ደግሞ ቀጣይ ሐሳቦችን እናቀርባለን፡፡

•    የሥጋዊ  አሠራር ሥር መስደድ፡-


በቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ ሰውና መንፈሳዊ አሠራር ከጠፋ ሰነባብቷል፡፡ ቤተ ክርስቲያን፣ ነገሮች ሁሉ በጸሎት የእግዚአብሔርን ምሪት በመፈለግ ሳይሆን የሚሠራባት፣ የሰውን ፊት በማየት የሚከናወኑባት የዓለማውያን ሸንጎ ሆናለች፡፡ ከሞላ ጎደል በማንኛውም ጉዳይ ለማለት ይቻላል ቤተ ክርስቲያኗ የእግዚአብሔርን ምሪት ጠይቃ አገልጋዮችዋንና ምእመናኗን አስተባብራ በአንድነት በጸሎት በፊቱ ወድቃ የምትከውናቸው ነገሮች የሏትም፡፡ ይልቁንም በአሠራርዋ ከእሷ የተሻለ እንቅስቃሴ ካለው ከመንግሥት ፖሊሲዎች እና ወቅታዊ አጀንዳዎች በመነሣት እነዚያን አጀንዳዎች በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ለማስፈጸም ከመሯሯጥ ያለፈ ሥራ ተሠርቶ አይታወቅም፡፡ መንግሥት “አቅም ግንባታ” ሲል ቤተ ክህነትም አቅም ግንባታ፣ መንግሥት “ደን ልማት” ሲል ቤተ ክርስቲያንም ደን ልማት፣ መንግሥት የፀረ ሙስና ርምጃ ሲወስድ ቤተ ክርስቲያንም ያውም ላትተገብረው ስለ ሙስና ማውራትን እንደ ትልቅ ቁም ነገር ወስዳ መጽሐፍ ቅዱሳዊ የሆነ የአሠራርም ሆነ የአመለካከት ለውጥ ለማምጣት ምንም  ዝግጅትና ርምጃ ሳታደርግ የሰሞኑ ነጠላ ዜማዋ አድርገዋለች፡፡
እውነተኛው ባለ ራእይና የምሪት አለቃ እግዚአብሔር ተረስቶ፣ ትልቁ ሕገ መንግሥት መጽሐፍ ቅዱስ ተዘንግቶ “ምን ተባለ” እያሉ ሥራ ለመሥራት መሞከር በእስካሁን እንቀስቃሴዋ እንደታየው የተሻለ ለውጥ አላመጣላትም፡፡ መንግሥት የሚያወጣቸው ሕጎችና አፈጻጸሞች የተሳሳቱ ናቸው ባንልም፣ ቤተ ክርስቲያን ግን በእግዚአብሔር መንግሥት አሠራር ውስጥ የዓለማዊውን መንግሥት አሠራር ሙሉ በሙሉ ያውም ምን እንደሆነ እንኳ ሐሳቡ ሳይገባት ለመፈጸም ከሞከረች የሥጋዊነት መገለጫዋ ነው፡፡
በሌሎችም በቤተ ክርስቲያን በሚሠሩ ሥራዎች፣ የእግዚአብሔርን ቤት እንደ መንደር እድር በዘፈቀደ የመምራት እንቅስቃሴዎች ስለምታደርግ፣ ይበልጥ ከእግዘአብሔር ሐሳብ ሲያርቃት እንጂ ወደ ዘላለማዊ አምላኳ ሲያስጠጋት አላየንም፡፡ የሚደረጉት ማንኛቸውም ነገሮች ሥጋ ሥጋ ከመሽተት ያለፈ አንዳች መንፈሳዊነት አይታዩባቸውም፡፡ ከነጭራሹም መጽሐፍ ቅዱስ ተነብቦ የማይታወቅ እስኪመስል ድረስ ከመንፈስ ቅዱስ የሆነ አሠራር ጠፍቷል፡፡ መንፈስ ቅዱስ በሲኖዶስ ጉባኤ እንደሚገኝ ለማሳየት  በጉባኤው አንድ ባዶ ወንበር ቢቀመጥም፣ መንፈስ ቅዱስ ከሲኖዶስና ከቤተ ክርስቲያን ሥፍራ ካጣ ዘመናት ተቆጥረዋል፡፡ የማናውቃቸውን ብዙ “ቅዱሳትና ቅዱሳን” እንድንቀበል አድርጋ በስማቸው ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ስታስገነባላቸው ለመንፈስ ቅዱስ ግን ሥፍራ አልተገኘለትም፤ በርግጥ በሚያምኑበት ልብ ውስጥ ያድራል እንጂ የሰው እጅ በሚሠራው ሕንፃ አይኖርም፡፡
ይህ የቤተ ክርስቲያናችን ሥጋዊነትም፣ ሕዝቡን ከእግዚአብሔር ቤት ገፍቶ ሲያስወጣው እንጂ ወደ ንጉሥ ክርስቶስ ቤት ሲመልሰው አልታየም፡፡ ያደጉባትን ቤተክርስቲያንንም፣ በዚህ ሥጋዊነትዋ ምክንያት “አይንሽን ለአፈር” እያሉ ጥለዋት የሚሄዱ ምእመናን ቁጥር ቀላል አይደለም፡፡ ስለዚህም ቤተ ክርስቲያን ሥጋዊነትዋን ጥላ በመንፈስ ቅዱስ እየተመራች ለብዙዎች ፈውስ ትሆን ዘንድ ተሐድሶ ያስፈልጋታልና “መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን ጆሮ ያለው ይስማ” እንላለን ፡፡


•    አስተዳደራዊ ብልሽቷ አገልጋዮቿንና ሕዝቧን ስላስጨነቀ


ስለ ኦርቶዶክሳዊቷ ቤተ ክርስቲያናችን ሲነሣ፣ አብሮ ሳይነሣ የማይታለፍ ነገር አስተዳደራዊ ብልሽቷ ነው፡፡ ይህ ርእስ፣ ቤተ ክርስቲያናችን በመንፈስ ቅዱስና በእግዚአብሔር ቃል የተመሠረተ ሁለንተናዊ ተሐድሶ አግኝታ ወደ ጥንተ ቅድስናዋና ክብሯ መመለስ ይገባታል የምንለውን እኛን እና ቤተ ክርስቲያን ከቶውንም ለውጥ አያስፈልጋትም “ስንዱ እመቤት ናት” የሚሉትን ወገኖች ያስማማናል፡፡ አስተዳደራዊ ብልሽቱን ሰዎች የሚያነሡበት መንገድ ይለያይ እንጂ  “የቤተ ክርስቲያኗ ህልውና ያሳስበኛል” የሚል ወገን ሁሉ ያለ ልዩነት የሚያነሣው ርእስ ነው፡፡
ቤተ ክርስቲያንዋ ከተቋማዊ እንቅስቃሴ ይልቅ የግለሰቦች ጠንካራ እና ደካማ ጎን ተገዢ መሆኗ በርግጥ ያሳስባል፡፡ ባለፈው ዓመት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ካረፉ በኋላ በጠቅላይ ቤተ ክህነት አካባቢ የነበረው የአሠራር ዝርክርክነት ከእሳቸው ጋር ጠቅላይ ቤተክህነቱም የሞተ አስመስሎት እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትዝታችን ነው፡፡ በሰው ላይ የተደገፈ አስተዳደራዊ ሥርዓት ፍጻሜው ይሄ ነው ለማለት፣ የብፁዕነታቸውን እንደ ምሣሌ አነሣን እንጂ፣ ከእሳቸው በፊት የነበሩትም አሁንም ያሉት ፓትርያርኮች አሠራር ተመሳሳይ ነው፡፡ በዙርያቸው የሚሰበሰቡ ሰዎችም እነርሱ የሚፈልጉት እስከተሳካ ድረስ ለሌላ ነገር ግድ የሚላቸው አይደሉም፡፡
የደብር አስተደደር ሹመት እንኳ በጥንት ዘመን ከነበረው አውቀት ተኮር ሹመት፣ አሁን ወደ ዝምድና እና ጉቦ ተኮር ወደ መሆን ተሸጋግሯል፡፡ እንዲህ ያለው ሹመት፣ አንድን የደብር አስተዳዳሪ፣ በደብሩ ውስጥ ከሚገኙት በእውቀት ሻል ካሉ አገልጋዮች ይቅርና ከአንድ ዲያቆን ጋር እንኳ የሚስተካከል  ክብር ስለማያሰጠው መናናቁና ጥላቸው፣ ቡድናዊነቱና ወገንተኝነቱ ሥር የሰደደ ነው፡፡ በእውነትና በእውቀት ማስተዳደር ስላልተቻለ፣ ሊቃውንቱ ተገፍተው ጨዋና ወሬ አመላላሹ ተከብሮ እና ተፈርቶ ይገኛል፡፡  የሥራ ድርሻውን የሚያውቅና ሥራውን በአግባቡ የሚሠራ ሰውም ስለጠፋ ምእመኑ የክርስትና ካርድ እንኳ ለማውጣት ጉቦ እየተጠየቀ ይገኛል፡፡ የአገልጋዮች ቅጥር፣ ዝውውር እና የደመወዝ ጭማሪን በተመለከተ ወጥ የሆነ ሕግ ስለሌለ በአስተዳዳሪው እና በሀገረ ስብከት ሹመኞች ይሁንታና ተጠቃሚነት፣ ነገሮች እንደፈለጉ የሚደረጉበት ደብር እጅግ ብዙ ነው፡፡ በብዙ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት፣ መሪጌቶች ከዲያቆን ያነሰ ደመወዝ ስለሚከፈላቸው፣ ተስፋ የሚቆርጡበት ሁኔታ የተለመደ ነው፡፡ ከተማ አቀፍ የደመወዝ አከፋፈል እስኬል ስለሌለ የተሻለ ደመወዝ የሚከፍል ደብር ለመቀጠር እና ለመዘዋወር ያለው ሹክቻና የሚጠየቀው መደለያ ገንዘብ ቀላል አይደለም፡፡ ይህ የአስተዳደር ችግር ውጤት ነው፡፡
በአስተዳደር ችግር ውስጥ እንደገና ሊታይ የሚገባው ቤተ ክርስቲያንዋ የፋይናንስ አያያዝ ነው፡፡ ከገንዘብ አሰባሰቡ ጀምሮ በዐፄ ምኒልክ ጊዜ ከነበረው የገንዘብ አስተዳደር የተሻለ ነገር ምንም  የላትም፡፡ በገንዘብ አቆጣጠር ላይ ያለውን አካሄድ ስንመለከተው፣ ለአታላይ በጣም የተመቸ ነው፡፡ ምንም ዐይነት ዘመናዊ የሂሳብ አያያዝ መንገድ የማይታይበት፣ ዘመናዊውን የሂሳብ አያያዝ ዘዴ የተማረ ሰው የማይቀጠርበት፣ የደመ ነፍስ መድረክ ሆናለች፡፡ ሌላው የሂሳብ አያያዙ ከፍተኛው ድክመቷ፣ የቤተ ክርስቲያን አንድነት ተረስቶ  “ወነአምን በአሀቲ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን” የሚለው የአባቶች ትምህርት ተዘንገቶ፣ ደብሮች  እንደ ፌደራል መንግሥት፣ ለጠቅላይ ቤተ ክህነት የሚፈለግባቸውን ብር ከሰጡ በኋላ፣  ገንዘቡን በገዛ ፈቃዳቸው የፈለጉትን ማድረግ የሚችሉበት መሆኑ ነው፡፡ ገጠር ያሉ አብያተ ክርስቲያናት በደመወዝና በንዋየ ቅዱሳት እጦት እየተዘጉ በአዲስ አበባ ግን ሰባ እና ሰማንያ ሚሊየን ብር በዝግ አካውንት የሚያስቀምጡ ደብሮች መኖራቸው የተለመደ ነገር ሆኗል፡፡
ቤተ ክርስቲያን አንድ እንደሆነች ከንግግር ባለፈ በቃሉ የሚታመን ከሆነ፣ የኑሮ ድካም ትከሻቸውን አጉቡጧቸው ወደ ከተማ የሚሰደዱትን የገጠር አብያተ ክርስቲያናት አገልጋዮችን ለመታደግና ባሉበት ቦታ በቂ ገንዘብ ከፍሎ ለማኖር ይቻል ነበር፡፡ ምእመኑ ከቤተ ክርስቲያን የሚፈልገውን አገልግሎት ለማግኘት ሲመጣ ቀድሞ የሚታየው ኪሱ እንጂ ልቡ አይደለም፡፡ ቤተ ክርስቲያን የድሆች መጠጊያ መሆንዋ ከቀረ ሰንብቷል፡፡ እንደ መንግሥት ቢሮ  ገንዘብ ያለው ከፍሎ የሚስተናገድባት የሌለው ተገፍቶ የሚወጣባት ቤት መሆንዋ ለብዙዎች የልብ ስብራት ምንጭ አድርጓታል፡፡
እንደዚህም በእጅጉ የሚያሳዝነው የአስተዳደር ብልሹነት መገለጫ በገጠር ያሉ እና ሊዘጉ የተቃረቡ አብያተ ክርስቲያናትን ለሀገረ ስብከት የተመደበባችሁን ብር አልላካችሁም በመባል የሚደርስባቸው ማስፈራራት እና “ቤተክርስቲያኑን እንዘጋዋለን” ቁጣ ነው፡፡ ለእነዚህ የገጠር ካህናት፣ በነጻ የሚያገለግሏት ቤተ ክርስቲያን የበላይ ኃላፊዎች የአባትነት ፍቅርና ምስጋና ማቅረብ ቢያቅታቸው እንኳ የኑሯቸውን ሁኔታ እያወቁ ማስጨነቅ ባልተገባቸው ነበር፡፡ ዲታዎቹን የአዲስ አበባ አብያተ ክርስቲያናትን፣ የእስፖንሰር ገንዘብ እየጠየቁ ለቅንጦት ነገሮች ከማዋል፣ በጭንቅ በሬ ሸጠው ዓመታዊ መዋጯቸውን እንዲከፍሉ የሚገደዱትን የገጠር አብያተ ክርስቲያናት አባቶች መታደግ ይገባ ነበር፡፡
ይህንን የአስተዳደር ብልሹነት በቤተክህነት ሥር የሰደደውን ሙስና ባለፈው ሰኔ 29/2005 ዓ. ም.  ቅዱስ ፓትርያርኩ በተገኙበት፣ የቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪዎች ምረቃ ላይ መምህር ልዑል የተባሉ ሰው በዘይእሴ ቅኔ እንዲህ ሲሉ ገልጠውታል፡፡
ቤታችን ሆኗል ቤተ ወንበዴ፣ እጅግ ያሣዝናል በእውነት የሚፈጸመው ግፍ ተግባሩ፡፡
ሊቃነ ጳጳሳት ፍቀዱና፣  ቢ. ፒ. አር. ወፀረ- ሙስና ገብተው ይመርምሩ፡፡
ብዙዎች ስላሉ በግል መዝብረው የከበሩ፡፡
ዘረፉኝ እያለች በቀን ምንም ሳይፈሩ፡፡
ሙዳየ ምፅዋት ምስኪን ትጮኻለችና በበሩ
ዘረፉኝ እያለች በቀን ምንም ሳይፈሩ፡፡

እንዲህ ያለውን የውስጥ ብሶት በአደባባይ ሲቀርብ ሰምቶ ከማጨብጨብ እና ይበል ብለናል ከማለት ያለፈ የተደረገ ነገር የለም፡፡
ባለፉት ብዙ ወራት ሊፈታ ያልቻለውና ይልቁንም እየተባባሰ ያለው፣ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ተማሪዎች ጉዳይ ሌላው በቤተክርስቲያን የተንሰራፋውን አስተዳደራዊ ችግር አጉልቶ የሚያሳይ ነው፡፡ ተማሪዎች ችግር አለብን ሲሉ ሰምቶ የሚያስተናግድ እና ችግሩን የሚፈታ አባት አልተገኘም፡፡ በየአቅጣጫው ከእውነታ ይልቅ ለሁኔታ እና ለቀረቤታ የሚያደሉ አሠራሮች ቤተክርስቲያኗን ይጎዳል እንጂ አይጠቅምም፡፡ ደቀመዛሙርቱን በግፍ ለማባረርና አስተዳደራዊ ጥያቄያቸውን ላለመመለስ፣ ፖለቲካዊ መልክ እንዳለው በማስመሰል ከመንግሥት ጋር ለማጋጨት በመሪዎች እየተወሰደ ያለው ርምጃ አስተዳደራዊ ብልሽቱን ከማጋለጡም በላይ ጉዳዩን በንቀት እየተመለከቱት መሆኑን ማሳያ ነው፡፡  
ሌላው የአስተዳደር ብልሹነቱ ገጽታ የሆነው በሐዋሳ፣ በክብረ መንግሥት፣ በዲላ፣ በሐረርና በሌሎችም የሀገሪቱ ክፍሎች የተፈጠሩት ችግሮች እና የምእመናን መንገላታት ነው፡፡  ለችግሮቹ “ይህ ነው” የሚባል መፍትሔ ሳይሰጠው አሁንም እንደ ቀጠለ መሆኑን ስናስብ በተለይ አሁንም ተስፋ ሳይቆርጥ፣ ሲኖዶሱን እየተማጠነ ላለው ሕዝብ በእጅጉ እናዝናለን፡፡ የዚህ ችግር ፈጣሪዎች ከሆኑት መካከል አንዳንዶቹም መንፈስ ቅዱስ ይመራዋል የሚባለው ሲኖዶስ አባላት የሆኑ ጳጳሳት መሆናቸውን ማሰብ ልብን ያደማል፡፡ የመፍትሔ አመንጪ መሆን የሚገባቸው አባቶች የችግሩ ፈጣሪዎችና አባባሾች መሆናቸው የሚያስገርም እውነት ነው፡፡
በቤተ ክርስቲያን ያለው የአስተዳደር በደል እና የሥራ ዝርክርክርነት ከመነገር በላይ ነው፡፡ አገልጋዩም ሆነ ሕዝቡ በቤተ ክርስቲያን ባለው አስተዳደራዊ በደል ተስፋ ቆርጦ እና አዝኖ ይገኛል፡፡ እንዲህ ያለው ችግር በቶሎ መስተካከል ካልቻለ እንደደነበረ በግ እየበረረ የሌሎችን በረት በመሙላት ላይ ያለውን የምእመናን ፍልሰት በእጅጉ ያባብሰዋል፡፡ ከዚህ እና ከሌች አስተዳደራዊ ችግሮች ለወውጣት ተሐድሶ አማራጭ የሌለው መንገድ ነውና ደግመን መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን ጆሮ ያለው ይስማ ልንል እንወዳለን፡፡
ይቀጥላል! …

Friday, May 17, 2013

ሰምና ወርቅ ! geezonline.com

 (The best ever Gold & Wax of the year ) dejebirhan
ጥጃዋ የሞተባትን ጥገት፤ አላቢዎች የቋንቋ ዕድርተኞች የጥጃውን ቆዳ ከጅራቱ እስከ አፉ ፈልቅቀው ሥጋውን አውጥተው በምትኩ 800 ቅርጫት ጭድ 500 ያኽሉን በጥጃው ቆዳ ጎስረው ጠቅጥቀው፤ የጥጃ ጎፍላ ወይም እንቡጣ (እንቦሣ) አስመስለው ሠርተው፤ ጸጕር ይብዛው እንጂ መንፈሰ ሕይወት በተለየው ቆዳ ገላው ላይ ጥቁር ጨው ነስንሰው፤ ለሷ ያንን እያላሱ፤ ለራሳቸው ወተቷን እያለቡ "ቴሌቫንጀሊዝም" እሚባል ቅላቸው ውስጥ ሲያንቆረቁሩባት፤ ላሚት እንዲህ አለች አሉ፦

ያለ እየመሰለኝ! ልጄ ሙቶ ሳለ
እንቦሣውን ባየው ልቤ ተታለለ!!

አላቢዎቹም ታዲያ እንዲህ ሲሉ መለሱላት ይባላል፦

ስንኳን አንቺ! ቤተ እስራኤል
ትታለል ነበረች በጥጃ ምስል!!

ሰሙ ጥጃዋ የሞተባትን ጊደር ኑሮ ለሚያውቅ ኹሉ ግልጥ ነው፤ ወርቁም ቢኾን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ዛሬ የምትገኝበትን ኹኔታ ለሚያውቅ የተሰወረ አይደለም። እንዲያውም ዕድሜ ለቴክኖሎጂ በዓይነ ኅሊና ብቻ ሳይኾን እነሆ በዓይነ ሥጋም ጭምር ወለል ብሎ ይታያል።
http://www.eotc.tv/?q=node/65 ( ሊንኩን ከግዕዝ ኦን ላይን ይመልከቱ )
አዬ ቤተ ተዋሕዶ፤ አንቺም እንዲህ በትንሣኤው ምድር ልብሽ ሙቶ አእምሮሽ ደንዝዞ የለየልሽ ሞኝ ተላላ ላም ኾነሽ ታርፊው!!! "ከመ ዘንቃሕ እምንዋም" ትንሣኤውን ያሳየን አምላክ ያንችንስ ትንሣኤ የሚያሳየን መቼ ይኾን?!

Thursday, May 2, 2013

ፋሲካችን ክርስቶስ ታርዶአል!





ዕብራውያን     פֶּסַח» ፔሳኽ» ይሉታል። ፋሲካ ማለት ነው።  በወርኀ ኒሳን በዐሥራ ዐምስተኛው ቀን ይከበራል። ሥርዓቱ የሚጀመረው በዐሥራ አራተኛው ቀን ዋዜማ ሲሆን በፋሲካው ሳምንት እርሾ የገባበት ምንም ዓይነት ምግብ መመገብ ክልክል ነው።ዕለቱን ተቦክቶ ወዲያው የሚጋገር እንጂ የኮመጠጠ ወይም የቦካና የዋለ፤ያደረ መመገብ በሕጉ እንደተቀመጠው ከእስራኤል አንድነት ያስወግዳል። ከማንኛውም እርድ ላይ ጥሬ መብላት ወይም ከበሉትም አስተርፎ ማሳደር አይፈቀድም። ለመስዋዕት የሚቀርበው የበግ ወይም የፍየል መስዋዕትም እድሜው ከአንድ ዓመት ያልበለጠ ጤናማና የተመረጠ መሆን ይገባዋል። በዐሥራ ዐራተኛው ቀን ምሽት መስዋዕቱ ይታረዳል።ሥጋውን ደግሞ ሌሊት  ከመራራ ቅጠል ጋር ቀላልቅለው ይበሉታል።  

Saturday, March 30, 2013

ንስሐ ለአብያተ ክርስቲያናት




የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ገጽ ዓርብ መጋቢት 20/2005 ዓ.ም.

ከዛሬ ሠላሣ ሁለት ዓመት በፊት በጎጃም ይኖሩ የነበሩ 40 ዓመት የዘጉ አንድ ባሕታዊ ከዘጉበት በኣት/ቤተ ጸሎት/ ወጥተው ለሕዝቡ ታዩ፡፡ ታይተው የማያውቁ እኚህ አባት ዛሬ መውጣታቸው ሕዝቡን አስደንግጦታል፡፡ ለሰንበት ቅዳሴ ለተሰበሰበው  ሕዝብ እንዲህ በማለት ተናገሩ፡- “በሕልሜ ቤበ- መኩ- እፍ- ጸጉ የሚሉ ቃላትን ያሳየኛል፡፡ ተጨንቄአለሁና እባካችሁ ፍቱልኝ” አሉ፡፡ ሕዝቡም፡- “አባታችን እኛ ምኑን እናውቀዋለን? ለእርስዎ እንዳሳየ ይፍታልዎ እንጂ” አሏቸው፡፡ እርሳቸውም ሕልሙን ሲተረጕሙ፡-
ቤበ  - ማለት ቤተ ክርስቲያን በረት ሆነች ማለት ነው፡፡
መኩ - መሥዋዕት ኩበት ሆነ ማለት ነው
እፍ -  ዕጣን ፍግ ሆነ ማለት ነው፡፡
ጸጉ - ጸሎት ጉባዔ/ ታይታ/ ሆነ ማለት ነው በማለት ተረጎሙ፡፡
ሕልምም ሆነ ትንቢት በፍጻሜው ይታወቃል፡፡ እኝህ አባት ያሳያቸው እውነት እንደሆነ ዛሬ እያየነው ነው፡፡ በረት ቆሻሻ የበዛበት፣ ንጽሕና የጎደለው፣ ሥነ ሥርዓት የሌለበት፣ የሕያው ነፍስ ሳይሆን የደመ ነፍስ /የእንስሳት/ መከማቻ፣ ነጻነት የማይሰጥ፣ በውስጡ የሚኖሩት የሕሊና፣ የሰብአዊና የመንፈሳዊ ሕግ የማያዛቸው፣ ዙሪያው የሚበርድ ክፍት የሆነ ስፍራ ነው፡፡ እኝህ አባት ቤተ ክርስቲያን በረት ሆነች ይለኛል አሉ፡፡ ንስሐን የመሰለ የሕይወት ውኃ የሚነገርባት ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮቿ  ያልታጠቡባት፣ ንስሐን ተሸክመው ንስሐ የሚቀበሉባት፣ በዓለም የሌለ ነውር በእርስዋ የሚሰማባት፣ ቅድስና የራቃት፣ ሁሉም በፊቱ ደስ ያለውን የሚያደርግባት፣ የደፈረ የሚኖርባት፣ እንኳን መንፈሳዊነት ሰብአዊነት የማይሰማቸው አገልጋዮች የተሰበሰቡባት፣ ትሩፋት የሚሠራ አይደለም የታዘዘውን የሚፈጽም የታጣባት፣ ለሚያያቸው ዕረፍት የማይሰጡ ያልተገሩ ሠራተኞች የሞሉባት፣ ለእግዚአብሔርና ለአገር ሕግ የማይገዙ የተከማቹባት፣ ሲያስቧቸው ብርድ ብርድ የሚሉ ሥርዓት አልበኞች የነገሡባት ስፍራ ሆናለች፡፡


Monday, March 18, 2013

«ቦኪሜ ነህ ኢየሱስ» ዘማሪት ምርትነሽ

«የእግዚአብሔርም መልአክ ከጌልገላ ወደ ቦኪም ወጥቶ እንዲህ አለ፦ እኔ ከግብፅ አውጥቻችኋለሁ፥ ለአባቶቻችሁም ወደ ማልሁላቸው ምድር አግብቻችኋለሁ እኔም። ከእናንተ ጋር ያደረግሁትን ቃል ኪዳን ለዘላለም አላፈርስም፤ እናንተም መሠዊያቸውን አፍርሱ እንጂ በዚህች ምድር ከሚኖሩ ሰዎች ጋር ቃል ኪዳን አታድርጉ አልሁ። እናንተ ግን ቃሌን አልሰማችሁም፤ ይህንስ ለምን አደረጋችሁ? ስለዚህም። ከፊታችሁ አላወጣቸውም፥ ነገር ግን ያስጨንቋችኋል፥ አማልክቶቻቸውም ወጥመድ ይሆኑባችኋል አልሁ። የእግዚአብሔርም መልአክ ይህን ቃል ለእስራኤል ልጆች ሁሉ በተናገረ ጊዜ ሕዝቡ ድምፃቸውን አንሥተው አለቀሱ። የዚያንም ስፍራ ስም ቦኪም ብለው ጠሩት በዚያም ለእግዚአብሔር ሠዉ»መሣ 2፤1-5



Thursday, April 5, 2012

ጌታ ኢየሱስ የመገበው ስንት ሰው ነው? 4ሺ ወይስ 5ሺ ሰዎችን?

የማቴዎስ ወንጌል
14፥21
ከሴቶችና ከልጆችም በቀር የበሉት አምስት ሺህ ወንዶች ያህሉ ነበር።
የማቴ ወንጌል 15፥38
የበሉትም ከሴቶችና ከልጆች በቀር አራት ሺህ ወንዶች ነበሩ።
በማርቆስ ወንጌል ላይም እንደዚህ የሚል ተጠቅሷል።

የማርቆስ ወንጌል
6፥44
እንጀራውንም የበሉት ወንዶቹ አምስት ሺህ ነበሩ።
8፥9
የበሉትም አራት ሺህ ያህል ነበሩ።
8፥19
አምስቱን እንጀራ ለአምስት ሺህ በቈረስሁ ጊዜ፥ ቍርስራሹ የሞላ ስንት መሶብ አነሣችሁ? እርሱም፦ አሥራ ሁለት አሉት።
8፥20
ሰባቱን እንጀራስ ለአራት ሺህ በቈረስሁ ጊዜ፥ ቍርስራሹ የሞላ ስንት ቅርጫት አነሣችሁ? እርሱም፦ ሰባት አሉት።
ታዲያ የተመገቡት ትክክለኛው የሰዎች ቁጥርና የተነሳው የቁርስራሽ ቁጥር ስንት ነው? ወንጌላውያኑስ ለምን ቁጥሮቹን አበላልጠው ዘገቡ? አልገባኝምና መልስ እሻለሁ
መልስ
(ከደጀብርሃን)
ጥቅሶቹን አበዛሃቸው እንጂ ጥያቄህ በማቴ 14፤21 እና በማቴ 15፣38 ላይ የተመገቡት ሰዎች ቁጥርና የተነሳው ቁርስራሽ መጠን የተለያየው ለምንድነው? የሚል ይመስለኛል።
ከዚህ አንጻር በአጭሩ ስመልስልህ አዎ፤ 4 ሺህ ሰዎችና 5 ሺህ ሰዎች መግቦ አንዴ 7 ቅርጫት፣ አንድ ጊዜ ደግሞ 12 ቅርጫት አትረፍርፏል። ይህንንም በአጭሩ ላብራራ።
1/ በማቴ 14፣20-21 ላይ የተመለከተው 5 ሺህ ሰዎችና 12 ቅርጫት ቁርስራሽን በተመለከተ፣
ነገሩን ለመረዳት እንድንችል ከማቴዎስ ምእራፍ 13 እንጀምር። ማቴዎስ 13 የምሳሌዎች ምዕራፍ ተብሎ በነገረ መለኰት ምሁራን ይጠራል። ምክንያቱም የዘሪው ምሳሌ ማቴ 13፣3 ፣ የሰናፍጭ ምሳሌ ማቴ 13፣31 የእንቁ ምሳሌ ማቴ 13፣44፤ የመረብ ምሳሌ ማቴ 13፣47 ፤ የተነገረበት ምዕራፍ ነው። እዚህ ላይ የምሳሌዎችን ምዕራፍ ማንሳት ያስፈለገበት ምክንያት ምሳሌዎችን ለመተንተን ሳይሆን ምሳሌዎቹ የተነገረበት ቦታና ሁኔታ በነገረ ጭብጥነት እንድንይዝ በማስፈለጉ ነው። በዚሁ መሰረት ይህ የምሳሌ ምዕራፍ ታሪክ በኢየሱስ የተነገረው ከቤቱ ወጥቶ በባህር ዳሩ አጠገብ መሆኑን ነው።
«በዚያን ቀን ኢየሱስ ከቤት ወጥቶ በባሕር አጠገብ ተቀመጠ፤እርሱም በታንኳ ገብቶ እስኪቀመጥ ድረስ ብዙ ሰዎች ወደ እርሱ ተሰበሰቡ፥ ሕዝቡም ሁሉ በወደቡ ቆመው ነበር» ማቴ 13፣1-2
ይህም ከቤቱ ሲል ከናዝሬት (ሉቃ 4፣16) ሲሆን የባህሩ ዳር ደግሞ ገሊላ (ማር 1፣16) መሆኑን ጥቅሶቹ ያረጋግጡልናል። ያም ማለት ከናዝሬት ወደ ገሊላ ሄዶ «የምሳሌዎቹን ታሪክ» ከባህሩ ዳር አስተማረ ማለት ነው። ከዚያስ በኋላ ወደየት ሄደ? የሚለውን ስንከተል ደግሞ ይህንን እናገኛለን። ማቴ 13፣53 ላይ ተቀምጦልናል።


Saturday, March 3, 2012

«እኔ የመረጥኩት ጾም»

እኔስ የመረጥሁት ጾም ይህ አይደለምን? (ክፍል ፩)

የያዝነው አርባ ጾም ዐቢይ (ታላቅ) ጾም እንደመሆኑ መጠን በመጽሐፍ ቅዱሳችን በምዕራፉ ሙሉ ስለጾም የሚናገረውን ትንቢተ ኢሳይያስ ም. ፶፰ ከሕይወታችን ጋር በማያያዝ መጽሐፍ ቅዱስ የሚያስተምረንን እናያለን።
ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕራፍ ፶፰፡-
ቁ .፩  በኃይልህ ጩኽ፥ አትቈጥብ፥ ድምፅህን እንደ መለከት አንሣ፥ ለሕዝቤ መተላለፋቸውን ለያዕቆብ ቤትም ኃጢአታቸውን ንገር።
ኃጢአት ሰዎችን ከእግዚአብሔርን የሚለይ ሲሆን ንስሐ ወደ እግዚአብሔር እንዲመለሱ የሚያደርግ ተግባር ነው። ሰዎች ወደ እግዚአብሔር እንዲመለሱ ኃጢአታቸው ሊነገራቸው፡ እነርሱም ኃጢአታቸውን በመናገር ንስሐ ሊገቡ ይገባል። በዚህ ክፍል እግዚአብሔር ነቢዩ ኢሳይያስን ለአይሁድ ኃጢአታቸውን እንዲነግራቸው ያዘዋል። አይሁድ እግዚአብሔርን የሚያውቁና የሚያምኑ ሕዝቦች ቢሆኑም ጥፋታቸው ሊነገራቸው ይገባ ነበርና ነቢዩን ላከላቸው።
ዛሬ እግዚአብሔርን የሚያውቁና፡ በቤቱ ስለሚኖሩ ክርስቲያኖች ጥፋት ምን እያደረግን ነው? ጥፋታቸው ለራሳቸው ተነግሮአቸው ንስሐ እንዲገቡ ወይስ ለሌላው ተነግሮባቸው እንዲበረግጉ?  ወንድሞቻችን ምንም ዓይነት ጥፋት ያጥፉ ቁም ነገሩ ለምን አጠፉ? ሳይሆን እንዴት ይመለሱ? መሆን አለበት። አንድ ወንድም «ከጥፋቴ በፊት መጥፋቴ ያሳስባችሁ» ብሎአል። ብዙ ጊዜ ስለ ጥፋታቸው እንጂ ስለመጥፋታቸው አናስብም። እግዚአብሔር ግን ሁሉም በጥፋታቸው ተጸጽተው በንስሐ ይመለሱ ዘንድ ጥሪ እንድናደርግ በኃይልህ ጩኽ፥  ዝም እንዳንልም አትቈጥብ  ይለናል። በአንድምታውም ጩኽህ አስተምር፡ ማስተማሩን ቸል አትበል ይላል።

Friday, February 10, 2012

«ኢያሱ ወልደ ነዌ በአባቶች እግር»



«ኢያሱ ወልደ ነዌ በአባቶች እግር»

ምድራችን አንዱን በአንዱ እየተካች እዚህ ዘመን ላይ ደርሳለች። ቀድሞ የነበረው ዛሬ የለም። ዛሬ ያለው ደግሞ ነገ ላይኖር ይችላል። በለውጥ ሂደት ውስጥ እንዳለን እንገነዘባለን። ዓለም እንኳን እየተለወጠች ነው። ድሮ የሌለ እምነት ዛሬ ተፈልስፏል። የነበረውም ቢሆን ገሚሱ ረስቶታል ወይም ከልሶታል አለያም ጥሩ አድርጎ አክርሮታል። ዝናባማው ዘመን በፀሐይ ተተክቷል። የሙቀት ጨምሯል ጩኸት፣ የዕለት ከዕለት ዜና ከሆነ ውሎ አድሯል። ሉላዊነት(Globalization) የሚሉት ስልጥንና በመንፈሳዊ ሀብት የሚታይ አብሮነትና አንድነት ባይኖረውም የሳይንስ ቁስ ዓለምን አቀራርቧል። ዓለምን ለመቃኘት ማጄላንን ወይም ኢብን ባቱታን መምሰል አይጠበቅብንም። ቁርስ አዲስ አበባ፣ ምሳ አቴንስ ለመመገብ ተችሏል። ድምፀትን ለመቀበል ወይም ለመስጠት ዛሬ ሁሉ ነገር የዓይንና የጆሮ ያህል ቀርቧል። ሲሰየጥኑ ይሁን ሲሰለጥኑ «ገንዘብ ካለ በሰማይ መንገድ አለ» የሚለው ትረካ ዓለምን እየነዳት ይገኛል። ይህ እንግዲህ ዓለም ደርሼበታለሁ የምትለው ግኝቷ ሲሆን የተቆላለፈው ችግሯ ደግሞ የትየለሌ ሆኗል።
ኤድስ የሚሉቱ አይድኔ በሽታ ብዙዎችን ወደ መቃብር ሸኝቷል። ኢቦላና የአእዋፍ ጉንፋን(BIRD FLU) ስንቱን ፈጅቶ የታገሰ ቢመስልም ጨርሶ እንዳልጠፋ ይወቃል። ካንሰር፣ ወባ፣ ስኳር፤ ግፊትና ብዛት፣ ማነስና ድክመት ልዩ ልዩ ህመሞች በርክተዋል፣ ወይም ህመምተኞችን አበራክተዋል። ከቺሊ እስከጃፓን፣ ከግሪንላንድ እስከ አንታርክቲካ የመሬት መንቀጥቀጡና የበረዶ መደርመሱ፣ የመሬት መናዱና ጎርፉ ብዙዎችን አጥፍቷል።
ሀይቲ 230,000 ሰው ሲሞትባት፤ሱናሚ ከኢንዶኔዢያ እስከ ሶማሊያ ጠረፍ ከ280,000 በላይ ሰዎችን መጥረጉን ሰምተናል። ጃፓንም ሀገር አማን ባለችበት ሀብቷን ሳይጨምር10 ሺዎችን ዜጋ አጥታለች።
ጦርነቱ፣ ፍጅቱ፣ የስልጣን ሽኩቻው፣ የሃይማኖት ፉክክሩ፣ የአሸናፊና ተሸናፊ ግብግቡ አይሏል። ያም ሆኖ ዓለም አለሁ፣ ማለቷን አልተወችም። ያለፈውን እየረሳች፣ መጪውን ትኖር ዘንድ ትጥራለች። «ገንፎ እየሞተ፣ ይተነፍሳል» እንዲሉ መሆኑ ነው። አዎ ዓለማችን እየሞተች መተንፈሷን አላቋረጠችም። ባለውና በሚታየው ነገር ለመጽናናት ትሻለች። ቁም ነገሩ ባለውና በሚታየው ነገር ፍጹም መጽናናትን ማግኘት አለመቻሏን አለማወቋ ነው። የተነገረውን አልሰማችም ወይም አልሰምቶም ሆኖባታል።
ማቴ 243-8
እርሱም በደብረ ዘይት ተቀምጦ ሳለ፥ ደቀ መዛሙርቱ ለብቻቸው ወደ እርሱ ቀርበው። ንገረን፥ ይህ መቼ ይሆናል? የመምጣትህና የዓለም መጨረሻ ምልክቱስ ምንድር ነው? አሉት።
ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፦ ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ።
ብዙዎች። እኔ ክርስቶስ ነኝ እያሉ በስሜ ይመጣሉና፤ ብዙዎችንም ያስታሉ።
ጦርንም የጦርንም ወሬ ትሰሙ ዘንድ አላችሁ፤ ይህ ሊሆን ግድ ነውና ተጠበቁ፥ አትደንግጡ፤ ዳሩ ግን መጨረሻው ገና ነው።
ሕዝብ በሕዝብ ላይ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣልና፥ ራብም ቸነፈርም የምድርም መናወጥ በልዩ ልዩ ስፍራ ይሆናል፤
እነዚህም ሁሉ የምጥ ጣር መጀመሪያ ናቸው።
እናም ዓለም የምትወልደውን በምትወልድበት በመጨረሻው ወር ውስጥ ነው ያለችው። እንደነፍሰ ጡር ሴት በምትወልድበት በ9ኛው ወር ውስጥ እንዳለች ልትረዳና «ወልደ አብ፣ ኢየሱስ» 9ነኛው ሰዓት ያስተማራትን ጸሎት ልታሰማ ይገባታል። «
ማቴ2746
ዘጠኝ ሰዓትም ኢየሱስ፦ ኤሎሄ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ? ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ። ይህም። አምላኬ አምላኬ፥ ስለ ምን ተውኸኝ? ማለት ነው።

በዚህ ጽሁፍ ስለዓለም የዳሰስኩት ጽሁፌን በዚያ ላይ ለማንተራስ እንጂ ስለዓለም ለማስተማር ስላለሆነ ዋናው ነጥቤ ዓለም ያለችበትን ደረጃ በማሳየት የዓለም አንድ ክፍል የሆንን እያንዳንዳችን ከዚህ የዓለም ጣር ለመዳን ምን ማድረግ እንዳለብን «የኢያሱ ወልደ ነዌ»ን አብነታዊ መንገድ ለማሳየት ነው። ኢያሱ እንደልጅ ልጅ ሆኖ ኅሊናውን ሳያባክን፣ መንፈሳዊ ልቡናውን በጊዜው ከነበረው መሳሳቻ ጠብቆ የአባቶቹን እግር እንደተረከበ በማሳየት እኛም በዚያ መሠረትነት ላይ ቆመን ዛሬ ዓለምን ከሚንጣት ወጀብ በመዳን የኃጢአት ከተማ ኢያሪኰን አፍርሰን ርስታችንን ለመውረስ እንድንችል ለማስገንዘብ ነው። ፍየል በኃጢአተኛ የምትመሰልበት ዋናው ምክንያት፣ ግልገሎቿን አድፍጦ ወደበላባት የቀበሮ ጫካ ቅጠል ለመቀንጠስ ዳግመኛ የምትመለስ በመሆኗ ነው። እንዲሁ ሁሉ ከጎናችን ብዙዎች ንስሐ ሳይገቡ መሞታቸውን እያየን፣ በቅጽበታዊ አደጋ ዓለም ብዙዎችን እንደሸኘች እየተመለከትን፣ እኛ ዘንድ እንደማይደርስ አስበንና ለእነርሱ እያዘንን በመቆየት ሰንበትበት ሲል ሁሉን ነገር ረስተን እንደነበረው የምቀጥል መሆናችን ነው።

ይቀጥላል.............

Thursday, January 19, 2012

በጥምቀትም ከእርሱ ጋር ተቀበራችሁ!



(ከእንግሊዝኛ ማጣቀሻ ጋር)

ቆላስ ፪፥፲፪ (Colossians2:12) « በጥምቀትም ከእርሱ ጋር ተቀብራችሁ፥ በጥምቀት ደግሞ፥ ከሙታን ባስነሣው በእግዚአብሔር አሠራር በማመናችሁ፥ ከእርሱ ጋር ተነሣችሁ»
ኦሪቱ የአዲስ ኪዳኑን ጥምቀት በማንጻትሥርዓት ታከናውነዋለች። ከኃጢአት ማንጻት! ማንም ቅድስናንና ንጽሕናን ሲሻ ይህንን የማንጻት ልማድ መፈጸም ግዴታው ነው። እንደሕጉ የታዘዘውን መስዋዕት አቅርቦ የሥርዓቱ ማጠቃለያ በምንጭ ውሃ ሰውነቱ መታጠብ አለበት። የማንጻት ልማዱ የሚከናወነው ከሰፈር ውጭ ነው።
«ንጹሕም ሰው የጊደሪቱን አመድ ያከማቻል ከሰፈሩም ውጭ በንጹሕ ስፍራ ያኖረዋል ርኵሰትም ለሚያነጻ ውኃ ለእስራኤል ልጆች ማኅበር ይጠበቃል ከኃጢአት ለማንጻት የሚሆን ነው» ዘኁ ፲፱፣፱ (Numbers19:9)
ፈሳሽ ያለበት ይሁን ለምጽ የወጣበት ወይም ቆረቆር የታየበት ይሁን የመርገም ወራቷ የመጣባት ሴት ሁላቸውም እንደሕጉ የታዘዘውን የኃጢአት መስዋዕት አቅርበው ሲያበቁና ሥርዓቱ ከተከናወነ በኋላ ለመንጻት በምንጭ ውሃ መታጠብ የግድ ነው። ያኔ ነጽተው ወደሕዝቡ ይቀላቀላሉ። አለበለዚያ ከሕዝቡ ጋር ሕብረት አይኖቸውም።ፈሳሽ ነገር ያለበት ሰው ከፈሳሹ ነገር ሲነጻ ስለ መንጻቱ ሰባት ቀን ይቈጥራል ልብሱንም ያጥባል፥ ገላውንም በምንጭ ውኃ ይታጠባል፥ ንጹሕም ይሆናል» ዘሌ ፲፭፣፲፫ (Leviticus15:13)
«የሞተውን ወይም አውሬ የሰበረውን የሚበላ ሰው ሁሉ፥ የአገር ልጅ ወይም እንግዳ ቢሆን፥ ልብሱን ያጥባል፥ በውኃም ይታጠባል፥ እስከ ማታም ርኩስ ይሆናል ከዚያም በኋላ ንጹሕ ይሆናል። ልብሱንና ገላውን ባያጥብ ግን ኃጢአቱን ይሸከማል» ዘሌ ፲፯፣፲፭-፲፮ (Leviticus17:15-16) ያ ማለት ኦሪት የምታነጻውና መስዋዕቱን ፍጹም የምታደርገው በውሃ በመታጠብ ነው።
የዚህ የማንጻት ልማድ የድንጋይ ጋኖች አብነት ሆነው በዘመነ ሐዲስ ከአንድ ሰርግ ቤት ተቀምጠው እናገኛቸዋለን። ቦታው ቃና ዘገሊላ ነው። እነዚህ የድንጋይ ጋኖች በኦሪቱ ለማንጻት ሥርዓት የምንጭ ውሃ የሚጠራቀምባቸው ነበሩ። ወንጌሉ አገልግሎታቸውን ለይቶ አስቀምጦልናል።
«አይሁድም እንደሚያደርጉት የማንጻት ልማድ ስድስት የድንጋይ ጋኖች በዚያ ተቀምጠው ነበር፥ እያንዳንዳቸውም ሁለት ወይም ሦስት እንስራ ይይዙ ነበር» ዮሐ ፪፣፮ (John2:6)
እነዚህ የማንጻት ሥርዓት የድንጋይ ጋኖች የመጀመሪያውን የአዲስ ኪዳን ተአምርም አስተናግደዋል። የእውነተኛው የወይን ግንድ ደም ለዓለሙ ሁሉ እንደሚፈስ ምሳሌ ሆነዋል። ቅድስት ማርያም ወይን እንዳለቀባቸው ባሳሰበች ጊዜ ጌታም እውነተኛው ወይን ለዓለሙ ሁሉ የሚፈስበት ጊዜ ገና መሆኑን ሲያስረዳ «ኢየሱስም፦ አንቺ ሴት፥ ከአንቺ ጋር ምን አለኝ? ጊዜዬ ገና አልደረሰም አላት» ዮሐ ፪፣፬ (John2:4)እውነተኛ ወይን እስኪሰጥ የኦሪቱ የማንጻት ሥርዓት የድንጋይ ጋኖች ጊዜው እስኪደርስ ድረስ ተአምር አስተናግደዋል። እነሱ ሲፈጽሙ የቆዩበትን የማንጻት ሥርዓት አዲስ ኪዳን በማይደጋገምና አንዴ በሚፈጸም የኃጢአት ሥርየት ለውጣዋለች። እሱም «ጥምቀት» ነው። ኦሪት ከሰፈሩ ውጭ ሁልጊዜ በሚፈጸምና በሚፈሰው የደም መስዋዕት ማሳረጊያ የሚሆን የመንጻትን ሥርዓትን ታዛለች።
አዲስ ኪዳን ደግሞ ከሰፈሩ ውጭ በተሰቀለውና አንዴ በሞተው የበጉ መስዋዕት ምሳሌ የውሃ ጥምቀትን በመቀበሩ ጠልቀው፣ ከውሃው በመውጣት ትንሳዔውን መስክረው፣ አንዴ በፈጸሙት ሥርዓት የኃጢአት ስርየት ታስገኛለች።
ለዚህም ነው ሐዋርያው ጳውሎስ እንዲህ ያለው።
ቆላስ ፪፣፲፪ (Colossians2:12) «በጥምቀትም ከእርሱ ጋር ተቀብራችሁ፥ በጥምቀት ደግሞ፥ ከሙታን ባስነሣው በእግዚአብሔር አሠራር በማመናችሁ፥ ከእርሱ ጋር ተነሣችሁ»
ጥምቀት ከንስሐ በኋላ የምትፈጸም ስለመሆኗ መገንዘብ ያስፈልጋል። ንስሐ ደግሞ ስላለፈው ተጸጽቶ፣ በጥምቀት ስለሚገኘው ጸጋ አምኖ መቀበልን ይጠይቃል። መጥምቁ ዮሐንስ በዮርዳኖስ ዙሪያና በሄኖን ማጥመቂያው ሁሉ ሲናገር የነበረው የቅድሚያ አዋጅ «ንስሐ ግቡ» እያለ ይሰብክ እንደነበር እንያለን።
«ዮሐንስ በምድረ በዳ እያጠመቀ የንስሐንም ጥምቀት ለኃጢአት ስርየት እየሰበከ መጣ» ማር ፩፣፬ (Mark1:4)
«ከመምጣቱ በፊት ዮሐንስ አስቀድሞ ለእስራኤል ሕዝብ ሁሉ የንስሐን ጥምቀት ሰብኮ ነበር» የሐዋ ፲፫፣፳፬ (Acts13:24)
«እኔስ ለንስሐ በውኃ አጠምቃችኋለሁ፤ ጫማውን እሸከም ዘንድ የማይገባኝ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ግን ከእኔ ይልቅ ይበረታል፤ እርሱ በመንፈስ ቅዱስ በእሳትም ያጠምቃችኋል»ማቴ ፫፣፲፩ (Matthew 3:11)
ሐዋርያው ጴጥሮስም በበዓለ ሃምሳ ተሰብስበው ለነበሩት ነፍሳት ሁሉ አዲሱን የምስራች ከሰበከ በኋላ «ምን እናድርግ?» ብለው በጠየቁት ጊዜ የሰጣቸው መልስ ቅድሚያው ንስሐ ግቡ ነው። ቀጥሎም ኃጢአታችሁ ይሰረይ ዘንድ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ ነው። ከዚያም የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ ትቀበላላችሁ ነበር ያላቸው ንግግሩን በማያያዝ።
«ጴጥሮስም፦ ንስሐ ግቡ፥ ኃጢአታችሁም ይሰረይ ዘንድ እያንዳንዳችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ፤ የመንፈስ ቅዱስንም ስጦታ ትቀበላላችሁ» የሐዋ ፪፣፴፰ Acts2:38
«እምነት ከመስማት ነው፣ መስማትም ከእግዚአብሔር ቃል ነው» ሮሜ፲፣፯ Rome10:7 የሚለው ትምህርት በመጀመሪያ ገቢር ላይ ሲውል የተነገራቸውን ቃል አመኑ፣ ያመኑበትን ተቀበሉ፣ በተቀበሉት ተጠመቁ፣ ከዚያም ወደ መዳን ሕይወት ተጨመሩ ይለናል መጽሐፉ።
« በብዙ ሌላ ቃልም መሰከረና። ከዚህ ጠማማ ትውልድ ዳኑ ብሎ መከራቸው። ቃሉንም የተቀበሉ ተጠመቁ፥ በዚያም ቀን ሦስት ሺህ የሚያህል ነፍስ ተጨመሩ» የሐዋ ፪፣፵-፵፩ Acts40:41
ታዲያ እኛስ ምን ማድረግ ይጠበቅብናል?
፩/ « እነሆም፥ ድምፅ ከሰማያት መጥቶ። በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው አለ» እርሱን ስሙት ያለውን ብቻ ተቀብለን በማመን አንዲት ጥምቀት በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም መጠመቅ! ማቴ ፫፣፲፯,Matthew3:17 ኤፌ ፬፣፬, ማቴ ፳፰፣ ፲፱
፪/ ከተጠመቅን ደግሞ «ከእንግዲህስ ወዲያ ለኃጢአት እንዳንገዛ የኃጢአት ሥጋ ይሻር ዘንድ አሮጌው ሰዋችን ከእርሱ ጋር እንደ ተሰቀለ እናውቃለን፤ የሞተስ ከኃጢአቱ ጸድቋልና» ሮሜ ፮፣፮ እንዳለው ዳግም ወደኃጢአት አለመመለስ!
፫/ ያመነና የዳነ የክርስቶስ ፍሬ ይታይበት ዘንድ ግድ ነው። «በመልካም መሬት የተዘራውም ይህ ቃሉን ሰምቶ የሚያስተውል ነው፤ እርሱም ፍሬ ያፈራል አንዱም መቶ አንዱም ስድሳ አንዱም ሠላሳ ያደርጋል» ማቴ ፲፫፣፳፫ Matthew13:23
ከዚህ ከሦስቱ የወጣ ሁሉ ይህን ሆኗል ማለት ነው።
«አውቀዋት ከተሰጣቸው ከቅድስት ትእዛዝ ከሚመለሱ የጽድቅን መንገድ ባላወቋት በተሻላቸው ነበርና። ውሻ ወደ ትፋቱ ይመለሳል፥ ደግሞ። የታጠበች እርያ በጭቃ ለመንከባለል ትመለሳለች እንደሚባል እውነተኞች ምሳሌዎች ሆኖባቸዋል» ፪ኛ ጴጥ ፪፣፳፩-፳፪ 2 Peter2:21-22
ስለሆነም ጥምቀትን ከእውቀት ጋር ስለመዳናችን እንጂ ስለበዓል ጭፈራና የጭፈራ ስርዓት አከባበር እንዳይውል እንጠንቀቅ!
መልካም በዓለ ጥምቀት!!!!!!!!!




የጥምቀት በዓል መታሰቢያ ስዕሎች

Friday, January 13, 2012

የተስፋው ቃል!





«እኛ በመንፈስ ከእምነት የጽድቅን ተስፋ እንጠባበቃለንና» ገላ ፭፣፭
በተስፋ የሚጠብቅ ክርስቲያን ትክክለኛ እምነትን የያዘ ነው። ፍጹም የሆነ እምነት በሌለበት የጽድቅን ተስፋ መጠባበቅ የለም። ስለሚጠባበቁት ተስፋ ፍጻሜ እምነት ሊኖር የግድ ነው።
ወንድና ሴት ሊጋቡ ሲወስኑ በጋብቻ ውስጥ ሳሉ ስለሚሆነው ነገር ሁሉ አስቀድመው በተስፋ አምነው ይፈጽማሉ። በጋብቻቸው ልጆችን ይወልዱ ዘንድ ተስፋ አድርገው ያምናሉ እንጂ እየወለዱ አይጋቡም። ሴትም በጽንሷ መጨረሻ ወራት ልጇን ትወልድ ዘንድ በተስፋ ትጠብቃለች እንጂ የጽንስ ውጤት ምን እንደሆነ ሳታውቅ ጽንስን አትለማመድም። ስለሚሆነው ነገር ባለው ጽኑ እምነት የተነሳ ውጤቱን በተስፋ መጠበቅ የግድ ይሆናል ማለት ነው።
አንድ ሰው ቃል ከገባለት ሌላ ሰው የተገባለትን ቃል ፍጻሜ በተስፋ ይጠብቃል። የገባለት ቃል ፍጻሜው ምንም ይሁን ምንም የተስፋውን ቃል ያይ ዘንድ በልቡ አስቀምጦ ይጠብቃል።
እንደዚሁ ሁሉ የተበደለ እንደሆነ የሚያምን ማንም ቢኖር ወደፍርድ አደባባይ ቢሄድ የበደሉን ዋጋ መልካም ፍርድን በተስፋ ይጠብቃል። በተስፋ ስለሚጠብቀው ነገር የጸና እምነት ባይኖረው ወደፍርድ አደባባይ በደሉን ይዞ ሊሄድ አይችልም።
ኦርቶዶክስ ይሁን እስላም፣ ይሁዲ ይሁን ጄሆቫ ዊትነስ፣ ፕሮቴስታንት ይሁን ካልቪኒስት የሁሉም ሃይማኖት ተከታይ በሚያምነው ሃይማኖት ውስጥ የመጨረሻ ግቡን በተስፋ ይጠባበቃል። ውጤቱ ምንም ይሁን ምንም የሚጠባበቀውን ተስፋ በእምነት ሳይቀበል ሃይማኖታዊ ልምምዱን በኑሮው ሁሉ ሊተገብር አይችልም።
ተስፋውን የሚጠባበቀው ከማመን ነው። ማመን ደግሞ ከመስማት ነው። በተስፋው ነገር ላይ እምነት ሳይኖረው ተስፋ አያደርግም። የሚያምነው ደግሞ ስለሚጠባበቀው ተስፋ በደንብ በመስማት ነው። ሳይሰማ እንዴት ያምናል? መጽሐፉም «እምነት ከመስማት ነው» ያለውም ለዚህ አይደል!!

Wednesday, December 28, 2011

የኢየሱስ ክርስቶስ አስታራቂነትና አምላክነት

«ክርስቶስ ማለት በቁሙ ወደአማርኛ የተገለበጠው የግሪኩ(ጽርእ)ቃል «Χριστός»«ክሪስቶሽ ሲሆን ትርጉሙም «የተቀባ» ማለት ነው። መቀባት « χριστῷ» የሚለውን ብቻውን የሚያመለክተው ከሌላ መቀበልን ሲሆን «ክርስቶስ» የሚለው ቃል ግን የቅብእ ባለቤትነትንና የመቀባት ግብርን አያይዞ የሚጠራ ስም ነው። (ኢሳ 45፣1) ይመልከቱ። «ክርስቶስ» በእብራይስጡ «המשיח» ሀመሺያኽ ቅቡእ፣ የተቀባ ሲሆን ግእዙ «መሲህ» በሚለው ይተካዋል። የቤተክርስቲያን ሊቃውንትም «የክርስቶስን መቀባት ወይም ቅቡእ መሆን ለማመልከት ሲያስተምሩ «አብ ቀባኢ፣ ወልድ ተቀባኢ፣ መንፈስ ቅዱስ ቅብእ» በማለት ይገልጻሉ። በእርግጥ ይህ ትምሕርተ መለኰት ሰፊና ጥልቅ እንደመሆኑ መጠን በዚህ ዙሪያ የተነሱ ትምህርቶችና ክርክሮች ብዙ ሲያምሱ ቆይቷል፣ ዛሬም ቢሆን ጨርሶ የጠፋ ስለመሆኑ የሚታወቅ ነገር የለም። እኛም ያንን ላለመድገም እንደመንደርደሪያ ይህንን ያህል ካልን ወደተነሳንለት ዓላማ እናምራ!
«ክርስቶስ» የተቀባ ማለት ነው ብለናል። እንደዚሁ ሁሉ «ኢየሱስ» የሚለውን ስንመለከት የእብራይስጡ «ישוע» የሹአ ሲሆን ትርጉሙም «መድኃኒት» ማለት ነው። ግሪኩም «Ιησούς» መድኃኒት፣( ማዳን)፣ አዳኝ የሚለውን ትርጉም ይሰጣል። ከዚህ የተነሳ «ኢየሱስ ክርስቶስ» ማለት «የተቀባ፣ቅቡእ እና መድኃኒት፣ አዳኝ» የሆነ ማለት ነው። ይህንን የስም ትርጉም ካገኘን ለሚቀጥሉት ሃሳቦቻችን መረዳት መጠነኛ ግንዛቤ ጨብጠናል ማለት ነው።
የሚቀባው ማነው? የሚቀባውስ ለምንድነው?
እነዚህን ነገሮች አጥርቶ ማወቅ የብሉይ ኪዳን አስተምህሮዎችን መመርመር ግድ ይላል። ያንንም ማድረግ አስፈላጊ የሚሆነው «ስለመሲሁ» ክርስቶስነት ላይ በሚነሱ ልዩ ልዩ አመለካከቶች ከብዥታ የወጣ እይታ እንዲኖረን ይረዳናል።
ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ........>>>(እዚህ ላይ ይጫኑ

Thursday, December 8, 2011

መጽሐፈ ሰዓታት ምን ይላል?

                               መጽሐፈ ሰዓታት.............to read in PDF click here





«ሰዓሊ ለነ ሰንበተ ክርስቲያን ቅድስት፣
ለውሉደ ሰብእ መድኃኒት፣
ወእስከ ለዓለም ሰፋኒት» ትርጉም--ለሰው ልጆች መድኃኒትና እስከዘለዓለም ገዢ የሆንሽ፣ የክርስቲያን ሰንበት ሆይ ለምኝልን ማለት ነው።
ሰንበተ ክርስቲያን የተባለችው ዕለት ለሰው ልጆች መድኃኒት በመሆኗ እንዲሁም እስከዓለም ፍጻሜ የሰው ልጆች ገዢ ስለሆነች እንድታማልደን እንጠይቃት ማለቱን መጽሐፈ ሰዓታት ይጠቁመናል።
እዚህ ላይ ጥቂት ጥያቄዎችን እናንሳ።
1/ሰንበተ ክርስቲያን የምትባለው ምናልባትም ዕለተ እሁድ ናት። ሐዲስ ኪዳን ግእዙ «ወበእሁድ ሰንበት መጽአት ማርያም መግደላዊት ኀበ መቃብር»ዮሐ20፣1 «ማርያም መግደላዊት ወደመቃብር በሳምንቱ መጀመሪያ ቀን መጣች»ይላል። ምንም እንኳን የእብራይስጡም ሆነ የጽርዑ መጽሐፍ ቅዱስ እሁድ ሰንበት የሚል ቃል ባይዝም እሁድ ብለው ያስቀመጡትን የግእዝ ተርጓሚዎች ተከትለን ብንሄድ እሁድ የተባለችው ቀን---
ሀ/እንዴት ሆና ነው የሰው ሁሉ ገዢ የምትሆነው?
ለ/ እሁድ በምን አፏ ነው የምልጃ ቃልን የምታሰማው?
ሐ/ እሷስ ከማነው የምታማልደን?
ሐ/ከሳምንቱ እለታት የተለየች ናት ካልን የጌታ እለታት ያልሆኑት የትኞቹ ናቸው?
መ/ድርሳነ ሰንበት የተሰኘው መጽሐፍ «ሰንበት» ማለት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ይለናል። ታዲያ ሰንበት የተባለው መድኃኔዓለም ያማልደናል ማለታቸው ነው?
2/ አስታራቂና አማላጅ የሆነችው እለተ ሰንበት ስለመሆኗ የተቀመጠ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ ምንድነው?
ሐዋርያው ጳውሎስ ለገላትያ ሰዎች ወንጌልን ከሰበከላቸው በኋላ ወደቀደመው ከንቱ የሆነ አምልኰ ሲመለሱ ተመልክቶ እንዲህ ብሎ ነበር።
«ነገር ግን በዚያን ጊዜ እግዚአብሔርን ሳታውቁ በባሕርያቸው አማልክት ለማይሆኑ ባሪያዎች ሆናችሁ ተገዛችሁ» ገላ 4፣8
እንደዚሁ ሁሉ እለተ እሁድ እግዚአብሔር ከቀናት እንደአንዱ የሰራት መሆኗ ተረስቶ ልክ አማልክት ወደመሆን የተቀየረች ይመስል አስታርቂን፣አማልጂን ማለት ጳውሎስ በባህሪያቸው አማልክት ለማይሆኑ ባሪያዎች ሆናችሁ የተገዛችሁ ነበረ ያለውን ቃል እኛ ዛሬም እየፈጸምን መገኘታንን ያሳያል።

Sunday, November 27, 2011

ታቦት በአዲስ ኪዳን እንዴት?




ታቦት በአዲስ ኪዳን እንዴት?to read in PDF

ለዚህ ጽሑፍ መነሻ የሆነው በኢቢኤስ ቴሌቪዥን በዲያቆን ዓባይነህ ካሴ የተሰጠውና ስለጽላት የአዲስ ኪዳን ዘመን አስፈላጊነት ስብከቱ የተነሳ ነው። አባይነህ ካሴ ያልገለጻቸው፣ ያልመለሳቸውና ያላብራራቸው፣ ነገር ግን በምንም መልኩ ሊታለፉ የማይገባቸው ነጥቦች ስላሉ በዚህ ጽሁፍ ይዳሰሳሉ። ምክንያቱም ለክርስቲያኖች ከየትኛውም መረጃ በላይ የእምነታቸው መሠረት መጽሐፍ ቅዱስ ሲሆን እሱም ሳይሸፋፍን ለብሉይ ኪዳኑ ሥርዓትም ይሁን ለአዲስ ኪዳኑ ዘመን እምነት መመሪያን፣ትእዛዛቱንና መንገዶቹን በግልጽ አስቀምጦት ስለሚገኝ ነው።
ዓባይነህ ካሴ ስሜቶቹን ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር እያዛመደ በዚህ የጽላት ዓለም እምነት ላሉ፣ በዚያው እንዲጸኑ፣ ይህንን ለማይቀበሉት ደግሞ ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች መልስ በመስጠት የሁለት ወገን ስራውን ለመስራት ሞክሯል። ይሁን እንጂ መረጃውን በማብራሪያ ለማጠናከር ከመሞከር ባለፈ በተጨበጠ ማስረጃ ማስደገፍ ባለመቻሉ ግልጽ እውነቶችን እያነሳንሥነ አመክንዮ «Give reasons or cite evidence in support of an idea, action, or theory, typically with the aim of persuading others to share one's view» እንሰጥበታለን።
ታቦት ለእስራኤል ዘሥጋ ያስፈለገበት ዋናው ምክንያት
ነብዩ ሙሴ ከእግዚአብሔር ቃል እየተቀበለ ለሕዝቡ መልእክቱን ያደርስ ነበር።
ዘጸ 3፣15 እግዚአብሔርም ደግሞ ሙሴን አለው። ለእስራኤል ልጆች እንዲህ ትላለህ። የአባቶቻችሁ አምላክ፥ የአብርሃም አምላክ የይስሐቅም አምላክ የያዕቆብም አምላክ እግዚአብሔር ወደ እናንተ ላከኝ ይህ ለዘላለሙ ስሜ ነው፥ እስከ ልጅ ልጅ ድረስም መታሰቢያዬ ይህ ነው።

Friday, November 25, 2011

እሬት የተቀባ ጡት ማን ይጠባል?



 ሁላችንም ህጻን ልጅ ሆነን አድገን አሁን ካለንበት መድረሳችን እርግጥ ነው። ህጻናትን በተመለከተም ህጻናት ወንድሞችና እህቶችም ይኖሩን ይሆናል። ምናልባትም ህጻናት ልጆች ይኖረንም ይሆናል። ባይኖረን እንኳን ስለህጻናት ያለን እውቀት ትንሽ እንደማይሆን ተስፋ አደርጋለሁ። ስለህጻናት ማንሳት የወደድኩት «ምርጥ ምርጡን ለህጻናት» የሚል አስተምህሮ ለመስጠት አይደለም። አእምሮአችሁን ለአፍታ ስለህጻናት እንዲያስብና ላነሳ ስለፈለኩት ጉዳይ ግንዛቤ እንዲኖራችሁ ነው።
ጥያቄ ላቅርብላችሁ? ህጻናት ጡት የሚተዉት እንዴት ነው? ጡት የሚጠባ ህጻን ጡት ሲያጣ ወይም ጡት ሲከለክሉት እንዴት ያደርገዋል? መቼም እንደማይስቅና እንደማይፍለቀለቅ አናጣውም። ይነጫነጫል፣ያለቅሳል፤ በአቅሚቲ እናቱን ይቧጥጣል፣ጡት አምጪ ብሎ ይማታል ብንል እውነት ነው። ሲያገኝና ሲጠግብ ደግሞ ጤነኛ እስከሆነ ድረስ ይስቃል፣ይጫወታል። እንዲህ እንዲህ እያለ ሁለትና ሶስት ዓመት ሲሞላው ደግሞ ደግሞ ጡቱን ያስጥሉታል።አራትና አምስት ድረስ የሚጠባ ልጅ እንዳለ ሳይዘነጋ መሆኑን ልብ ይሏል? ጡት የምታስጥል የገጠር እናት ያንን የለመደውን ነገር ለማስጣል ከባድ ይሆንባታል። እንዲጠላው ለማድረግ እሬት ይቀቡታል። ይቆነጥጡታል። ሌላም ነገር እያደረጉ ይከለክሉታል። ይሁን እንጂ የህጻኑ ለቅሶ ሲበረታ ልምድ አደገኛ ነውና እንደገና ያጠቡታል። እንደዚያ እንደዚያ እያደረጉ ምግብ እያቀረቡ፣ጡት እየነፈጉ ከህጻንነት የጡት መጥባት ዓለም ያወጡታል።

Monday, November 21, 2011

የሚያድን ዕይታ


የዘመኑ መስታወት.......



by Dagnu Amde on Friday, November 18, 2011 at 7:11pm

አቤቱ÷ እኔን ለማዳን ተመልከት
አቤቱ÷ እኔን ለመርዳት ፍጠን
(መዝ.69÷ 1)::

በሕይወታችን ብዙ ነገሮችን ዐይተናል፡፡ ዐይተናቸው በውስጣችን የቀሩ፣ ዐይተናቸው የረሳናቸው፣ ዐይተናቸው ደግመን ለማየት ያልፈቀድናቸው፣ ዐይተን እንዳላየ ያለፍናቸው፣ ዐይተን የታዘብናቸው ብዙ ነገሮች አሉ፡፡ ጽጌረዳን ዐይተን እሾህን እናያለን፡፡ የተንሰራፉ አበቦች በአሜከላዎች ላይ ተጐዝጉዘው እናያለን፡፡ ዐይናችን ሁለቱንም ታያለች፡፡ ኅሊና ግን አጥርታና መርጣ ታያለች፡፡ በዐይናችን ብዙ መልካምና ክፉ ነገሮችን እናያለን፡፡ ላየነው ሁሉ ምላሽ መስጠት አያስፈልገንም፡፡ ምላሻችንን የሚፈልጉ ዕይታዎች ግን አሉ፡፡ ማየት ከመስማት በላይ ነው፡፡ ሰምቶ ምላሽ ያልሰጠ ሲያይ ግን ምላሽ ይሰጣል፡፡ ማየት የተግባር አዛዥ ናት፡፡

Saturday, November 19, 2011

የመላእክት ተፈጥሮና ተልእኰ



ቅዱሳን መላእክት ተፈጥሮአቸው ረቂቅ ነው። አይጨበጡም፣አይዳሰሱም። ዳዊትም በመዝሙሩ እንዲህ ሲል ገልጿቸዋል። መዝሙር 104መላእክቱን መንፈስ የሚያደርግ፥ አገልጋዮቹንም የእሳት ነበልባል»
ስለዚህ መላእክቱ መንፈስና እሳት ናቸው ማለት ነው። ስጋዊ ደማዊ አይደሉም። እርጅናና ሞት አይስማማቸውም። ምንም እንኳን መላእክት መንፈስና እሳት ቢሆኑ፣ እርጅናና የዚህ ዓለም ሞት ባይስማማቸው በራሳቸው ኃይል ምንም ሊደርጉ አይችሉም። ምክንያቱም እሳትና መንፈስ ያደረጋቸው ፈጣሪያቸው ገዢያቸውና ኃይላቸው እሱ ስለሆነ ነው። መላእክት ፍጡራን ስለሆኑ በቦታ ውሱን ናቸው። በሁሉም ስፍራ በአንድ ጊዜ የመገኘት ችሎታ የላቸውም። መላእክት ፍጡርና ውሱን ስለመሆናቸው መጽሐፍ ቅዱስ በብዙ ቦታ በቃሉ ይነግረናል። ለምሳሌ ያህል ያዕቆብ በፍኖተ ሎዛ ድንጋይ ተንተርሶ በተኛ ጊዜ ከምድር እስከሰማይ በተተከለ መሰላል ላይ መላእክት ሲወጡና ሲወርዱ በህልም አይቷል። «ሕልምም አለመ እነሆም መሰላል በምድር ላይ ተተክሎ፥ ራሱም ወደ ሰማይ ደርሶ፥ እነሆም የእግዚአብሔር መላእክት ይወጡበት ይወርዱበት ነበር» ዘፍ 2812 መላእክቱ ውሱን ፍጥረት ስለሆኑ በዚያ መሰላል ላይ ይወጣሉ፣ ይወርዳሉ። በሁሉም ስፍራ የመገኘት ብቃት የላቸውም። በራሳቸው ምንም ማድረግ የማይችሉ ስለሆነ ነው በዚያ መሰላል ላይ የሚወጡት የሚወርዱት። ያም መሰላል ኢየሱስ ክርስቶስ ነበረ።
«እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ሰማይ ሲከፈት የእግዚአብሔርም መላእክት በሰው ልጅ ላይ ሲወጡና ሲወርዱ ታያላችሁ አለው» ዮሐ 152 መላእክት የሚወጡበትና የሚወርዱበት ለመላእክት ሰማያዊ የኃይላቸው መሰላል ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ይህንን ራሱ ባለቤቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው የተናገረው!
አንዳንዶች ግን ያዕቆብ በፍኖተ ሎዛ መላእክት ሲወጡበትና ሲወርዱበት ያየውን መሰላል እመቤታችን ማርያም ናት ይላሉ። «አንቲ ውእቱ ስዋስዊሁ ለያዕቆብ» የያዕቆብ መሰላል አንቺ ነሽ። (ቅዳሴ ማርያም)ይህ በፍጹም ተቀባይነት የሌለው ነው። ቅድስት ማርያም በዘመነ ያዕቆብ አልተፈጠረችም። ማርያም ከሐናና ከኢያቄም በሥጋ ተወልዳለች ካልን ከዚያ ቀደም በመንፈስ ነበረች ማለት ክህደት ነው። ማርያም መንፈስ ሳትሆን የሰው ልጅ ናትና፣ ስጋ ሳትለብስ በዘመነ ያዕቆብ በሰማይ ወይም በምድር የነበረችና መላእክት ይወጡባት፤ይወርዱባት ነበር ማለት ክርስቶስ ከእሷ የለበሰውን ስጋ አለመቀበል ነው። ይህ ደግሞ አደገኛ ክህደት ነው። ደግሞም ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱ «እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ሰማይ ሲከፈት የእግዚአብሔርም መላእክት በሰው ልጅ ላይ ሲወጡና ሲወርዱ ታያላችሁ አለው»ያለውን ቃል በማርያም ስም መለወጥ ኃጢአት ነው። ቅድስት ማርያም አምላክን በስጋ ስለወለደች ወደአምላክነት አልተቀየረችም። ዘመን የማይቆጠርላት ረቂቅ መንፈስ አይደለችም። (ሎቱ ስብሐት እንላለን)
ወደ ተነሳንበት ርእስ ስንመጣ መላእክት ለመውጣትም ለመውረድም የክርስቶስ ኃይል የሚያስፈልጋቸው ፍጥረታት መሆናቸውን እንረዳለን።




በሌላ ቦታም መጽሐፍ ቅዱስ ስለመላእክት ውሱንነት በደንብ ይነግረናል። በትንቢተ ዳንኤል መጽሐፍ ላይ እንዲህ የሚል ተጽፎልናል። ዳንኤል በምድረ ፋርስ በሀዘን ላይ በጾምና በጸሎት ተወስኖ በነበረበት ወቅት ከእግዚአብሔር ዘንድ አንድ መልአክ ተልኮለት ወርዷል። ዳን 1011 «እርሱም፦ እጅግ የተወደድህ ሰው ዳንኤል ሆይ፥ እኔ ዛሬ ወደ አንተ ተልኬአለሁና የምነግርህን ቃል አስተውል፥ ቀጥ ብለህም ቁም አለኝ። ይህንም ቃል ባለኝ ጊዜ እየተንቀጠቀጥሁ ቆምሁ» ይላል። ይህ መልአክ ግን ዳንኤል ካለበት ዘንድ ከመድረሱ በፊት የፋርስ መንግሥት አለቃ ይለዋል( ንጉሱን የሚመራው የሰይጣን መንፈስ) ማለት ነው። የተላከውን መልአክ ከዳንኤል ዘንድ እንዳይደርስ 21 ቀን በአየር ላይ ተዋግቶታል። በኋላም የመላእክት አለቃ ሚካኤል መጥቶ ሲያግዘው እሱ ወደ ዳንኤል መምጣት ችሏል። «የፋርስ መንግሥት አለቃ ግን ሀያ አንድ ቀን ተቋቋመኝ እነሆም፥ ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ እኔም ከፋርስ ነገሥታት ጋር በዚያ ተውሁት» ዳን 1013
የዚህ ዓለም ገዢ(ዮሐ1430) የተባለው ሰይጣን የፋርስ መንግሥት ገዢ መንፈስ ሆኖ ለዳንኤል የተላከለትን መልአክ 21 ቀን እንደተቋቋመው መልአኩ ራሱ ለዳንኤል ሲነግረው እናነባለን። ያኔም የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ደርሶለታል። ሰይጣን ደግሞ በሌላ ጊዜም ከቅዱስ ሚካኤል ጋር ሲከራከር እንደነበር በይሁዳ መልእክት ላይ እናገኛለን። (ይሁዳ19)ሰይጣን ጳውሎስንም ከሚሄድበት መንገድ አዘግይቶታል።
«ወደ እናንተ ልንመጣ ወደን ነበርና፥ እኔ ጳውሎስም አንድና ሁለት ጊዜ፥ ሰይጣን ግን አዘገየን»1 ተሰ218
እንግዲህ ከላይ የምንረዳው የመላእክት ኃይል ውሱን መሆኑን፤ ከአንዱ መልአክ የአንዱ ሊበልጥ እንደሚችል፤የሚያዘገያቸው ነገር ሊያጋጥማቸው እንደሚችል፣ ሰይጣን የሚከራከራቸው መሆኑን፣ የሚያሸንፉትም የስድብን ቃል በመናገር ሳይሆን«እግዚአብሔር ይገስጽህ» በማለት ስመ እግዚአብሔርን መከታ በማድረግ ኃይል እንደሆነ ነው።

መላእክት የተፈጠሩበትን ቀን የሚያመለክት ቁልጭ ያለነገር ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አልተቀመጠም። ይሁን እንጂ መምህራን አባቶች በእለተ እሁድ(በመጀመሪያው ቀን) ስለመፈጠራቸው ያስተምሩናል። ሰይጣንም በዚሁ ቀን ብርሃን ከመገለጡ ቀደም ብሎ በትእቢቱና ስልጣንን በመሻቱ እንደወረደም ይነግሩናል። ይህንን የሚያጠናክር መረጃ ከትንቢተ ኢሳይያስ 1412-15« አንተ የንጋት ልጅ አጥቢያ ኮከብ ሆይ፥ እንዴት ከሰማይ ወደቅህ! አሕዛብንም ያዋረድህ አንተ ሆይ፥ እንዴት እስከ ምድር ድረስ ተቈረጥህ! አንተም በልብህ ወደ ሰማይ ዐርጋለሁ፥ ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ከፍ ከፍ አደርጋለሁ፥ በሰሜንም ዳርቻ በመሰብሰቢያ ተራራ ላይ እቀመጣለሁ። ከዳመናዎች ከፍታ በላይ ዐርጋለሁ፥ በልዑልም እመሰላለሁ አልህ፣ነገር ግን ወደ ሲኦል ወደ ጕድጓዱም ጥልቅ ትወርዳለህ» የሚለውን በማቅረብ ያስተምሩናል። አክሲማሮስ የተሰኘው የስነፍጥረት መጽሐፍንም በዋቢነት ያቀርባሉ። በጥቅሉ ግን ሰይጣን ከክብሩ የወደቀ መልአክ ነው።
ቅዱሳን መላእክት ግን ለእግዚአብሔር ተልእኮ ይፋጠናሉ። እግዚአብሔር ወደ ላካቸው ስፍራም ይሄዳሉ።«ያዕቆብም መንገዱን ሄደ፥ የእግዚአብሔር መላእክትም ተገናኙት።ያዕቆብም ባያቸው ጊዜ። እነዚህ የእግዚአብሔር ሠራዊት ናቸው አለ የዚያንም ስፍራ ስም መሃናይም ብሎ ጠራው» ዘፍ 321-2
ሎጥንም ቅዱሳን መላእክት ተልከው አድነውታል። «ጎህም በቀደደ ጊዜ መላእክት ሎጥን፦ ተነሣ፥ ሚስትህንና ከዚህ ያሉትን ሁለቱን ሴቶች ልጆችህን ውሰድ በከተማይቱ ኃጢአት እንዳትጠፋ እያሉ ያስቸኵሉት ነበር» ዘፍ 1915
መላእክት የምስራች ቃልን ያደርሳሉ። ለሶምሶን መወለድ ምስራች የተናገረው መልአኩ ነበር። «የእግዚአብሔርም መልአክ ለሴቲቱ ተገልጦ እንዲህ አላት፦ እነሆ፥ አንቺ መካን ነሽ፥ ልጅም አልወለድሽም ነገር ግን ትፀንሻለሽ፥ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ» መሳ 133
መላእክት የተላኩበትን ፈጽመው ስማቸውን ሳይነግሩን ሊሄዱ ይችላሉ። «ሴቲቱም ወደ ባልዋ መጥታ። አንድ የእግዚአብሔር ሰው ወደ እኔ መጣ፥ መልኩም እንደ እግዚአብሔር መልአክ እጅግ የሚያስደነግጥ ነበረ ከወዴትም እንደ መጣ አልጠየቅሁትም፥ እርሱም ስሙን አልነገረኝም» መሳ 136
መላእክት የተራበውን ለማብላት የተጠማውን ለማጠጣት ሊላኩ ይችላሉ። «በክትክታውም ዛፍ በታች ተጋደመ እንቅልፍም አንቀላፋ እነሆም፥ መልአክ ዳሰሰውና። ተነሥተህ ብላ አለው፣ሲመለከትም፥ እነሆ፥ በራሱ አጠገብ የተጋገረ እንጎቻና በማሰሮ ውኃ አገኘ። በላም ጠጣም፥ ተመልሶም ተኛ። 1 ነገ 195-6
መላእክት ሰዎችን ለተልእኰ ያፋጥናሉ። የሐዋ 826 «የጌታም መልአክ ፊልጶስን።፣ተነሥተህ በደቡብ በኩል ከኢየሩሳሌም ወደ ጋዛ ወደሚያወርደው ምድረ በዳ ወደ ሆነ መንገድ ሂድ አለው»
እግዚአብሔርን ለሚፈሩና ለሚታዘዙ መልአክ ይላክላቸዋል። « እርሱም ከቤተ ሰዎቹ ሁሉ ጋር እግዚአብሔርን የሚያመልክና የሚፈራ ለሕዝብም እጅግ ምጽዋት የሚያደርግ ወደ እግዚአብሔርም ሁልጊዜ የሚጸልይ ነበረ። ከቀኑም ዘጠኝ ሰዓት ያህል፣ ቆርኔሌዎስ ሆይ የሚለው የእግዚአብሔር መልአክ ወደ እርሱ ሲገባ በራእይ በግልጥ አየው» የሐዋ 102-3
የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱሳንን ለማበረታታት ይላካል።
የሐዋ 2723-25 «የእርሱ የምሆንና ደግሞ የማመልከው የእግዚአብሔር መልአክ በዚች ሌሊት በአጠገቤ ቆሞ ነበርና፥ እርሱም፦ ጳውሎስ ሆይ፥ አትፍራ፤ በቄሣር ፊት ልትቆም ይገባሃል፤ እነሆም፥ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር የሚሄዱትን ሁሉ ሰጥቶሃል አለኝ። ስለዚህ እናንተ ሰዎች ሆይ፥ አይዞአችሁ፤ እንደ ተናገረኝ እንዲሁ እንዲሆን እግዚአብሔርን አምናለሁና»
መላእክት የጌታ አገልጋዮች ናቸው።
«ያን ጊዜ ዲያብሎስ ተወው፥ እነሆም፥ መላእክት ቀርበው ያገለግሉት ነበር»ማቴ 411
የመጨረሻውን የዓለም መከር የሚያጭዱት መላእክት ናቸው። «እንክርዳዱም የክፉው ልጆች ናቸው፥ የዘራውም ጠላት ዲያብሎስ ነው፤ መከሩም የዓለም መጨረሻ ነው፥ አጫጆችም መላእክት ናቸው» ማቴ1339
መላእክት የእግዚአብሔርን የምስጢር ቀን አያውቁም። «ስለዚያች ቀንና ስለዚያች ሰዓት ግን ከአባት ብቻ በቀር የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ ልጅም ቢሆን የሚያውቅ የለም»ማቴ2436
በጌታ ትእዛዝና በመላእክት አለቃ ድምጽ በክርስቶስ ለሞቱት ትንሳዔ ይሆናል።
«ጌታ ራሱ በትእዛዝ በመላእክትም አለቃ ድምፅ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና፥ በክርስቶስም የሞቱ አስቀድመው ይነሣሉ» 1 ተሰሎ 416
ከላይ ያለተጨማሪ ማብራሪያ እያየነው የመጣነው በነጥብ የተቀመጡት ጥቅሶች ሲጠቃለሉ ቅዱሳን መላእክት ለማዳን፤ ለማስተማር፤ የምስራችን ቃል ለመንገር፤ ለማበርታት፤ ለማወጅ፣ ለማገልገልና ለማመስገን የተመረጡ መሆናቸውን ነው።
እነዚህ ቅዱሳን መላእክትን የተመለከተ ሲሆን የወደቁት መላእክትስ ምን ይሰራሉ? የሚለውን እንመልከት!
የወደቁ መላእክት
አለቃቸው ዲያብሎስ ነው፣


 ስራቸው

ዋና ዋና ስራዎቻቸው 5 መደብ ሊከፈል ይችላል።
1/የእግዚአብሔርን ዓላማ መቃወም። ለዳንኤል የተላከውን መልአክ 21 ቀን እንደተዋጉት ማለት ነው።
2/ የዚህ ዓለም ገዢ ሆኖ መንግሥታትን፣ ነገሥታትን አገልጋዩ ማድረግ (ዮሐ1231)(ራእ 1614)
3/ሰዎች አምነው እንዳይድኑ የወንጌልን ቃል ከሰው ልብ በመስረቅ። (ሉቃ 812)
4/ ኃጢአተኞችን በኃጢአታቸው፤ ቅዱሳንን በመልካም ስራቸው ዘወትር በመክሰስ። (ኢዮ17-8)
ዘካ 31-2 እርሱም ታላቁን ካህን ኢያሱን በእግዚአብሔር መልአክ ፊት ቆሞ አሳየኝ፥ ሰይጣንም ይከስሰው ዘንድ በስተ ቀኙ ቆሞ ነበር። እግዚአብሔርም ሰይጣንን፦ ሰይጣን ሆይ፥ እግዚአብሔር ይገሥጽህ ኢየሩሳሌምን የመረጠ እግዚአብሔር ይገሥጽህ በውኑ ይህ ከእሳት የተነጠቀ ትንታግ አይደለምን? አለው።
ራእ1210 ታላቅም ድምፅ በሰማይ ሰማሁ እንዲህ ሲል፦ አሁን የአምላካችን ማዳንና ኃይል መንግሥትም የክርስቶስም ሥልጣን ሆነ፥ ቀንና ሌሊትም በአምላካችን ፊት የሚከሳቸው የወንድሞቻችን ከሳሽ ተጥሎአልና።
5/ የእግዚአብሔርን ቃል በማጣመም። (የሐዋ 1310)(2 ጴጥ 316)(መዝ 565) ዘፍ 31 እባብም እግዚአብሔር አምላክ ከፈጠረው ከምድር አውሬ ሁሉ ይልቅ ተንኰለኛ ነበረ። ሴቲቱንም፦ በውኑ እግዚአብሔር ከገነት ዛፍ ሁሉ እንዳትበሉ አዝዞአልን? አላት። ብሎ እንደተናገረው ዛሬም እንዲሁ ይሰራል። ለሃይማኖቶች መበራከትና የየራሳቸውን ስም ይዘው ራሳቸው ብቻ ጻድቅ፣ ሌላው ግን የውሸት መሆኑን የሚያስተምሩት ባጣመመው ቃሉ የተነሳ ነው።
ሌላውን ዐመጻና ኃጢአት ሁሉ የሚሰራውና የሚያሰራው በእነዚህ ነጥቦች ላይ ተንተርሶ ነው።
ሰይጣን(ዲያብሎስ) አብረውት የወደቁ የአጋንንት ሰራዊት አሉት። እነሱን በማሰማራት ይዋጋል።
ከእግዚአብሔር ፈቃድ ሲያገኝ ሊፈትን ይችላል። ኢዮብን እንደፈተነው ማለት ነው። ከሰማይ እሳትን ሊወረውር፣ አውሎ ንፋስን አስነስቶ ሊያጠፋ፣ ጦረኞችን አስነስቶ እልቂት ሊያደርስ ይችላል። ከዚያም አልፎ ተርፎ ስጋን መግደልም ይችላል። ኢዮ 117 (ማቴ 1028)ሥጋንም የሚገድሉትን ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ፤ ይልቅስ ነፍስንም ሥጋንም በገሃነም ሊያጠፋ የሚቻለውን ፍሩ» እንዳለው።
ሰይጣን ይህን ማድረግ የመቻል ብቃት ቢኖረውም የወደቀ መልአክና በክርስቶስ መስቀል ከቅድስና መንገዳችን ላይ የተወገደ ነው። ቆላስ 214 የምናሸንፍበትን ኃይል አግኝተናል። ኤፌ 320 «እንግዲህ በእኛ እንደሚሠራው ኃይል መጠን ከምንለምነው ወይም ከምናስበው ሁሉ ይልቅ እጅግ አብልጦ ሊያደርግ ለሚቻለው»
«በእኛ ላይ የነበረውን የሚቃወመንንም በትእዛዛት የተጻፈውን የዕዳ ጽሕፈት ደመሰሰው። እርሱንም በመስቀል ጠርቆ ከመንገድ አስወግዶታል»

ማጠቃለያ፣

ቅዱሳን መላእክት በእግዚአብሔር አገዛዝና ሥልጣን ስር ያሉ፤ የሚታዘዙ፤ የሚላኩ፤ ፈቃዱን የሚፈጽሙና ዘወትር የሚያመሰግኑ ናቸው።
ውዱቃን መላእክት፤ ከእግዚአብሔር አገዛዝ ስር ያሉ ግን ከስልጣኑ ያፈነገጡ፤የማይታዘዙ፤ የማይላኩ ፈቃዱን የማይፈጽሙና የማያመሰግኑ ናቸው። በአገዛዙ ስር ስላሉ ያለፈቃዱና ያለእውቅናው አንዳች ማድረግ አይችሉም። ኤፌ 21 «አሁን ያሉት በአየር ላይ፣ በምድር ላይና በሲኦል ሲሆን በመጨረሻበበደላችሁና በኃጢአታችሁ ሙታን ነበራችሁ፤ በእነርሱም፥ በዚህ ዓለም እንዳለው ኑሮ፥ በማይታዘዙትም ልጆች ላይ አሁን ለሚሠራው መንፈስ አለቃ እንደ ሆነው በአየር ላይ ሥልጣን እንዳለው አለቃ ፈቃድ፥ በፊት ተመላለሳችሁባቸው።ም በገሀነም ይኖራሉ»
ሉቃ833 አጋንንትም ከሰውዬው ወጥተው ወደ እሪያዎች ገቡ፥ መንጋውም ከአፋፉ ወደ ባሕር ተጣደፉና ሰጠሙ»
የሰው ልጅ የእግዚአብሔር ቸርነትና ምሕረት የበዛለት በአርአያውና በአምሳሉ ስለፈጠረው ነው። ያም ጥልቅ በሆነው የእግዚአብሔር ፍቅር አማካይነት በአንድያ ልጁ እንዲድን አስችሎታል። «ፍቅር ሰሐቦ ለወልድ ኃያል እመንበሩ፣ ወአብጽሖ እስከለሞት» የተባለውም ለዚህ ነው።
አምላካዊ ጥበቃውንና ድጋፉን በቅዱሳን መላእክቱ በኩል ያደርግልናል። ቅዱሳን መላእክቱም እግዚአብሔር በላካቸው ስፍራና ቦታ ተገኝተው ትእዛዛቱን ይፈጽማሉ። ቅዱሳኑ መላእክት ግን ትእዛዝ ሳይደርሳቸው የትም አይንቀሳቀሱም። የሰው ልጅ በሰው ሰውኛነት የመረጠውን መልአክ ስለጠራ ወይም ስለለመነ መልአኩ ስሜ ስለተነሳ ልሂድ፤ልውረድ አይልም። እንኳን ተጠርቶ፣ ሳይጠራ ከተፍ የሚለው ሰይጣን ብቻ ነው። ከቅዱሳን መላእክት ከተማ ውጪ ያለው እሱና ሰራዊቱ ናቸው። በእዚህ ምድር ያለውን የሰው ልጆች የሚንከባከበን የሁሉ መገኛ የእግዚአብሔር ጥበቃና መግቦት ነው። ነቢዩ ዳንኤልን በጾም በጸሎቱ ወቅት ይጠብቀውና ያጸናው የነበረው የእግዚአብሔር ኃይል ነበረች። መልአኩንማ 21 ቀን እንዳይደርስ ጠላት ሲዋጋ አቁሞት ነበር።
ስለዚህ ቅዱሳን መላእክትን እናከብራቸዋለን፤ ይራዱናል፤ ያግዙናል ስንል እነርሱን በተለየ ስም በምናደርግላቸው ጥሪና ልመና ሳይሆን ለእግዚአብሔር በምናቀርበው ጸሎት ተቀባይነት የተነሳ እኛ የማናውቀው መልአክ ሊላክልን ሲችል ብቻ መሆኑን እንረዳ!!
በተጨማሪ ገብሩ ወልዱ የተባሉ ጸሐፊ በሰይጣን ባህሪይ ላይ የጻፉትን መጽሐፍ ቢያነቡት ብዙ እንደሚጠቀሙ አምናለሁ።
ለሁሉም ነገር እግዚአብሔር አእምሮውን ለብዎውን ያሳድርብን፣አሜን።