Friday, May 17, 2013

ሰምና ወርቅ ! geezonline.com

 (The best ever Gold & Wax of the year ) dejebirhan
ጥጃዋ የሞተባትን ጥገት፤ አላቢዎች የቋንቋ ዕድርተኞች የጥጃውን ቆዳ ከጅራቱ እስከ አፉ ፈልቅቀው ሥጋውን አውጥተው በምትኩ 800 ቅርጫት ጭድ 500 ያኽሉን በጥጃው ቆዳ ጎስረው ጠቅጥቀው፤ የጥጃ ጎፍላ ወይም እንቡጣ (እንቦሣ) አስመስለው ሠርተው፤ ጸጕር ይብዛው እንጂ መንፈሰ ሕይወት በተለየው ቆዳ ገላው ላይ ጥቁር ጨው ነስንሰው፤ ለሷ ያንን እያላሱ፤ ለራሳቸው ወተቷን እያለቡ "ቴሌቫንጀሊዝም" እሚባል ቅላቸው ውስጥ ሲያንቆረቁሩባት፤ ላሚት እንዲህ አለች አሉ፦

ያለ እየመሰለኝ! ልጄ ሙቶ ሳለ
እንቦሣውን ባየው ልቤ ተታለለ!!

አላቢዎቹም ታዲያ እንዲህ ሲሉ መለሱላት ይባላል፦

ስንኳን አንቺ! ቤተ እስራኤል
ትታለል ነበረች በጥጃ ምስል!!

ሰሙ ጥጃዋ የሞተባትን ጊደር ኑሮ ለሚያውቅ ኹሉ ግልጥ ነው፤ ወርቁም ቢኾን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ዛሬ የምትገኝበትን ኹኔታ ለሚያውቅ የተሰወረ አይደለም። እንዲያውም ዕድሜ ለቴክኖሎጂ በዓይነ ኅሊና ብቻ ሳይኾን እነሆ በዓይነ ሥጋም ጭምር ወለል ብሎ ይታያል።
http://www.eotc.tv/?q=node/65 ( ሊንኩን ከግዕዝ ኦን ላይን ይመልከቱ )
አዬ ቤተ ተዋሕዶ፤ አንቺም እንዲህ በትንሣኤው ምድር ልብሽ ሙቶ አእምሮሽ ደንዝዞ የለየልሽ ሞኝ ተላላ ላም ኾነሽ ታርፊው!!! "ከመ ዘንቃሕ እምንዋም" ትንሣኤውን ያሳየን አምላክ ያንችንስ ትንሣኤ የሚያሳየን መቼ ይኾን?!