Tuesday, August 21, 2012

ሰበር ዜና፤ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው ተገለጸ።




ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ አረፉ።
ሕወሀትን በመምራትና ኢህአዴግን በማዋቀር ትልቅ ሚና የነበራቸውና ከደርግ ውድቀት በኋላም የሀገሪቱ ርእስ መንግሥት ሆነው ላለፉት 21 ዓመት የቆዩት፤ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን ዛሬ ነሀሴ 15/2004 ዓ/ም በይፋ ለሕዝብ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ተነግሯል።
አቶ መለስ ዜናዊ እድሜአቸውን ሙሉ በትግል ያሳለፉ፤ በዚሁ ትግል ውስጥ እያሉ በሞት የተለዩ ትልቅ መሪ ነበሩ። በሞታቸው ሃዘናችንም ጥልቅ ነው።
እግዚአብሔር ለወዳጅ ኢትዮጵያውያን ሁሉ የሀዘን ጽናቱን ይስጥ!