Friday, May 4, 2012

አንዳንድ የማቅ አባላት የሲ. አይ. ኤ. ሰላዮች ሆነው ተገኙ

በዋናነት ቤተ ክህነት አካባቢ “የቀን መጋኛ” የሚባለው ባያብል ሙላቱ የሰጠውን መረጃ ዊኪሊክስ ይፋ አድርጓል።   በዲ/ን ሙሉጌታ ወ/ገብርኤል
 

በይበልጥም የኬብል ቁጥር 
ADDIS ABAB 00000451  002 OF 003  የሚለውን ይመልከቱ!!

 
በርካታ የማኅበረ ቅዱሳን አባላትና ሌሎች ወገኖች ማኅበረ ቅዱሳንን በተመለከተ ያላቸው አመለካከት የተለያየ ነው። ማኅበሩ እውነተኛ ማንነቱን ደብቆ በቅድሚያ ቤተክርስቲያንን ከዚያም የመንግስትን ሥልጣን ለመያዝ በግልጾቹም በስውሮቹም አመራሮች እየተደገፈ የሚያደርጋቸው እንቅስቃሴዎችን አባላቱ በቅጡ አልተረዱም። ቤተክርስቲያን እኛ ባንኖር ኖሮ ጠፍታ ነበር። ያለንላት እኛ ነን። ቤተክርስቲያን ሰው ስለሌላት አስራታችሁን ለማኅበረ ቅዱሳን አውጡ በማለት የሚያሰወራውን ወሬ  እና በአካፋ ተቀብሎ በማንኪያ የሚሰጠውን ስጦታ በማመን የተታለሉ ወገኖች ይገኛሉ። እውነቱን ከማህበሩ ጋር ለበርካታ አመታት በቅርብ የሰሩ ወገኖችና እንቅስቃሴውን በሙላት የተረዱ የቤተክርስቲያን ልጆች ያውቁታል።

Thursday, May 3, 2012

አዎ ኢትዮጵያ ውስጥ በትክክል አሸባሪነት አለ!

ሙስሊሞች ሁሉ አክራሪዎች ወይም ክርስቲያን የተባሉ ሁሉ ክርስቲያኖች ናቸው ብለን አናምን። ከሁለቱም ወገን ሃይማኖቱን ተጠግቶ የራሱን ገበያ የሚያደራና ስውር አጀንዳውን በሰው ላይ ለመጫን የሚፈልግ እንዳለ የአደባባይ እውነታ ነው።
በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት የፓርላማ መግለጫ ላይ በሁለት ወገን ስላሉት ሃይማኖታዊ ታዛውን የተጠለሉትን ኢትዮጵያውያን ችግር ፈጣሪዎችን ቀድሞውኑ ያወቅናቸው ቢሆንም የየግላችንን ጩኸት ከረፈደ በኋላም ቢሆን በግልጽ አውጀው ነግረውናል።
የሚገርመው ነገር ከእስላሞቹ አሸባሪዎች ወገን የጠቅላይ ሚኒስትሩን ድምጽ ከንቱ ስሞታ ለማለት ጊዜ ያልፈጀባቸው ሲሆን እውነታው ግን በኢትዮጵያ ውስጥ አሸባሪነት ስለመኖሩ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዲሞክራት ይሆኑ አምባ ገነን ከእሳቸው ሥርዓት ጋር ሊያያዝ የማይገባውን ነገር ለማያያዝ በመሞከር ግራና ቀኝ የተቃውሞ ጅራፍ ማስጮህ በምድሪቱ ላይ ያለውን እውነታ የሚለውጠው አይደለም። 

ይድረስ ለመልአከ ሰላም ቀሲስ ደጀኔ ሽፈራው



                                    a source from:www.abaselama.org   
                                       To read in PDF ( Click Here )
እርስዎ በብፁዕ አባታችን በአቡነ ጎርጎርዮስ ጥቂት ኦርቶዶክሳዊ እምነት ተምረው መልካም መንፈስ እንደነበረዎት ጓደኞችዎ ይመሰክራሉ፤ ለእግዚአብሔር ወንጌልም ቀናተኛ ደቀ መዝሙር ነበሩ። አሁን እያስተማሩት ያለው ትምህርት ግን በሰውም ሆነ በጌታ ዘንድ ያስጠይቀዎታልና በብሎግዎ ከጻፉት ላይ አንዳንድ ኦርቶዶካስዊ ያልሆኑ ትምህርቶችን እንዲያርሙ ልጠቁመዎት ወደድሁ። ከመንፈሳዊ ሰላምታ ጋር!
መልክአ ሚካኤል በሚለው ርእስ ከጻፉት ውስጥ፦
 «መልክዕ፦ ቅዱሳን የሚመሰገኑበት መንፈሳዊ ድርሰት ነው። ከራስ ጠጉራቸው ጀምሮ እስከ አግር ጥፍራቸው ድረስ ያለውን የአካላቸውን ክፍል እየዘረዘረ ያመሰግናቸዋል» ብለዋል።