Thursday, October 11, 2012

ቋሚ ሲኖዶስ ጀግኗል!

በቤተ ክርስቲያን ትልቁ ችግር ከአናቱ እስከ እግሩ ጥፍሩ ያለው መዋቅር በበሰበሰ አስተዳደር መተብተቡ ነው። 2 ሺህ ዘመናትን በመከራና በወጀብ ስትናጥ፤ የደም አበላ ግብሯን ጠያይም ልጆችዋን እየሰጠች፤ ከጉዲት እስከ ግራኝ፤ ከድርቡሽ እስከጣሊያን ድረስ ከልጆቿ እስከ ንብረቷ ስትገብር የቆየችና እዚህ 21ኛው ክ/ዘመን ላይ የደረሰች ቤተክርስቲያን ሉላዊ እውቀትና አስተዳደር በዘመነበት ዘመን ላይ ምን እንደነካት ሳይታወቅ የገዛ ልጆቿ የስልጣንና የሀብት ክምሯ ላይ ሰፍረው እንደ ዳልጋ ዝንጀሮ እየፈነጩ ሲንዷት ማየቱ ውሎ ያደረ ከመሆኑም በላይ ሁሉም እየተባበሩ በአንድ ድምጽ ውድቀቷን እናፋጥን የሚሉ እስኪመስል ድረስ በጥፋት እድምተኞች መሞላትዋ ግልጽ ነው።
ሙዳየ ምጽዋት የሚገለብጡ ይሁዳዎች፤ አፍኒንና ፊንሐስ አመንዝራዎች፤ በነጻ የተሰጣቸውን የሚሸጡና በእናጸድቃለን ካባ የመበለት ቤቶችን የሚመዘብሩ ግብረ በላዎች፤ ስመ ብጽእናን ለምግባረ ብልሹ ስራቸው የደረቱ አባዎች ሞልተው የጋራ ክንዳቸውን በዐመጽና በጥፋት «አንስእ ኃይለከ» ተባብለው የተማማሉ የግብረ እከይ ሰዎችን ማንነትና አድራጎት መመልከቱም እንግዳ ነገር አይደለም። ሆዳቸው ከሞላ የበሻሻ አቦ ምእመናን ሰይፍ በአንገታቸው ቢያልፍ አፋቸው በስብ የተዘጋ ይመስል የማይናገሩ አፈ ዲዳዎች መሪ በሞላባት ዘመን ላይ ቤተክርስቲያን መድረሷ አጥፊዎቿ የውጪ ጉዲት ሳይሆን የራሷ እሬቶዎች መሆኑንም ብዙ ታዝበናል። በአዲስ አበባ ከተማችን የ2000 ብር ደመወዝ እየበላ የሁለት መቶ ሺህ ብር መኪና የሚነዳ የመሪነት ስምን የተሸከመ ሙዳየ ምጽዋት ገልባጭ ማየት የተለመደ ሆኗል። የዘረፋ መዋቅር ዘርግተው የቤተክርስቲያኒቱን ጡት ያለርኅራኄ የሚመጠምጡ አይጠ መጎጦች ተንሰራፍተው ይገኛሉ። ገንዘብ የሚገኝበትን ቤተክርስቲያን ለመምራት ከላይ እስከታች በሚደረገው መቆላለፍ ጅቦቹ አፋቸውን ከፍተው ሲያሰፈስፉ መስማትም ዛሬ ዛሬ እንደተገቢ እየተቆጠረ ይገኛል። በአንድ ወቅት የወይብላ ማርያም ቤተክርስቲያን ከነበራት የ400,000 ብር ካዝና ውስጥ በወራት ልዩነት ወደ 20 ሺህ ደርሶ ለካህናት ደመወዝ መክፈል እስኪያቅት መደረሱን አይተን እነሆ እስከዛሬ በአስገራሚነቱ መዝግበነዋል። ከማኅደረ ስብሐት ልደታ ለማርያም እስከ ዑራኤል ቤተክርስቲያን፤ ከመርካቶ ሚካኤል እስከ ግቢ ገብርኤል የጅብ መንጋ ሲግጥ ማየት እንግዳ መሆኑ ቀርቷል።  በየደረጃው የእያንዳንዱን አብያተ ክርስቲያን ካዝና ገልብጠው ባዶ ካደረጉ በኋላ ወደተረኛው ቤተክርስቲያን የሚዛወሩ ወሮ በሎች በዚህ አጭር ጽሁፍ ዘርዝሮ የሚዘለቅ አይደለም።
 የሚያስደንቀው ደግሞ ቤተክርስቲያኒቱ ምን ዓይነት ቁጣ ወረደባት እስኪያሰኝ ድረስ ከሀገር ቤት አንስቶ እስከባህር ማዶ ድረስ የአበሻ ጅቦች የሰፈሩባት መሆኑ ያስገርማል። ከቦርድ እስከ ሰበካ ጉባዔ ከተገንጣይ እስከ ገለልተኛ፤ ከግለሰብ ቤተክርስቲያን እስከ ሁለ ገብ ድረስ እየተቧደኑ መዝረፍና ማስዘረፍ፤ የየሀገራቱን ፍርድ ቤቶች ፋይል እስከማጨናነቅ ያደረሰ የዘረፋ ስልጣኔ መንገሱም ፀሐይ የሞቀው፤ አገር ያወቀው ጉዳይ ነው።
የክህነቱና የመሪነቱ መስፈርት የማንነት ሚዛንስ ምኑ ተነግሮ? እንዲያው ተከድኖ ይብሰል! ይህ ሁሉ ሲሆን ቤተክርስቲያንን በመንፈስ ቅዱስ እመራለሁ የሚል ከፍተኛው የሥልጣን እርከን ሲኖዶስ ነበራት። ለመብላትና ለመናገር ካልሆነ ለመሥራት አቅሙና ፍላጎቱ የሌለው፤ ቤተክርስቲያን ብትሞት እንጂ ለእሷ ሞት ራሳቸውን ለማስቀደም የሚደፍሩ የመሪ ቁርጠኞች በሌለበት ሁኔታ ውስጥ መገኘቷ ችግሯ እንዲባባስና ከልካይ የሌለበት እንድትመስል አድርጓታል። ወጉ ደርሶ ማስቆም ባይችሉ ራሳቸውም አብረው ወራሪና አስወራሪ መሆናቸውን ቢያቆሙ እንኳን እሰየው ባልን ነበር! ነገሩ ግን የተገላቦጦሽ ነው። ሕዝቡ በG ማይነስ ቤት ውስጥ እየኖረ እነሱ በG ፕላስ ውስጥ መኖራቸው ነገሩን ሁሉ አስከፊ ያደርገዋል።

የሽጉጡ ጦስ ሁለት የአቡነ ገብርኤልን የቅርብ ረዳቶች ከሥራ አፈናቀለ


source: dejeselaam-dejeselaam.blogspot.com
የሲዳማ፣ ጌዴኦ፣ አማሮና ቡርጂ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የሆኑት አቡነ ገብርኤል ወደ ሀዋሳ በሥራ ተመድበው ከሄዱበት ጊዜ ጀምሮ አንድም ቀን ሠላምና ዕረፍት አግኝተው አያውቁም፡፡ ልባቸው ከሠላምና ከዕርቅ ርቋል፡፡ ከቤተክርስቲያን የተባረሩ በሺዎች የሚቆጠሩ ምዕመናንን ጥያቄ በመመለስ ፈንታ ሕልምና ሃሣባቸው ለጥቂት ጥገኛ ነጋዴዎችና ለ"ማኅበረ ቅዱሳን" አባላት እየተሸነፈ ማንኛውም ዕርቅ እንዳይደረግ ከማገድ ውጪ ምንም ነገር አይታያቸውም፡፡
በሺዎች ከሚቆጠሩ ምስኪን ምዕመናን ይልቅ ጥቅም ሊያገኙ የሚችሉት ከጥቂት ጥገኛ ነጋዴዎችና ከ"ማኅበረ ቅዱሳን" እንደሆነ ራሳቸውን አሳምነውታል፡፡ ስለዚህ በእነዚህ ሁለት አካላት አቀነባባሪነት በድሃዎቹ የሀዋሳ ምዕመናን ላይ ጥቃት ሲፈጸም፣ አይተው እንዳላየ፣ ሰምተው እንዳልሰማ በመሆን ፍትሕን ከሀገረ ስብከቱ የሰማይ ያህል አራቁት፡፡ የእግዚአብሔር መንግሥት ወንጌል እንዳይሰበክ ሲታፈን ነገሮችን ሁሉ በፊርማና በማኅተማቸው እያፀደቁ የድኆቹ የአምልኮ ነፃነት በጠራራ ፀሐይ ሲቀማ ምንም አልተሰማቸውም፡፡
ይሁንና በዚህ ሁኔታ የተማረሩት የሀዋሳ ምዕመናን ስለመልካም አስተዳደርና ስለ ፍትሕ ጮኹ፡፡ ቁጣቸውን በተለያዩ መንገዶች ገለጹ፡፡ ግጭቱ ተጋግሞ ሀገረ ስብከቱን አልፎ በመላው ሀገሪቱ በተለይም በጠቅላይ ቤተክህነት ውስጥ መነጋገሪያ ሆነ፡፡ ቋሚና ቅዱስ ሲኖዶሶች ተከታታይ ስብሰባዎችን በማድረግ ልዩ ልዩ ውሳኔዎችን አስተላለፉ፡፡ ይሁን እንጂ አቡነ ገብርኤል ያላወረዱትን ዕርቅ፣ ዕርቅ አውርጃለሁ፣ ያልመሠረቱትን ሠላም፣ ሠላም መሥርቻለሁ፣ ያላመጡትን አንድነት፣ አንድነት አምጥቻለሁ እያሉ ጠቅላይ ቤተክህነት አካባቢ ቢዋሹም ሐቁ ግን እየገዘፈ መጥቶ ለስድስት ወራት (ጥር/2003 -ሐምሌ/2003) ያህል ለሕይወታቸው በመስጋት ሸሽተው አዲስ አበባ ላይ መቀመጥ ግዴታ ሆነባቸው፡፡
ይሁን እንጂ፣ ከእትብቱ እንደተቆረጠ ጽንስ መተንፈስ የተሳናቸው ጥቂት ጥገኛ ነጋዴዎቹና የ"ማኅበረ ቅዱሳን" አባላት እንደምንም ተሟሙተው ሐምሌ 18 ቀን 2003 ዓ.ም ምሽት በአንዲት አሮጌ ሃይላክስ ፒክ አፕ መኪና በስውር ወደ ሀዋሳ መልሰው ወሰዷቸው፡፡
ከዚያም ዙሪያውን ጥበቃ ተጠናከረላቸው፡፡ ሲወጡም ሲገቡም በግል ሴኪዩሪቲ ማሠልጠኛ የሠለጠኑ ጠባቂዎችን በመመደብ፣ ብርሃን ቀርቶ አየር እንኳን እንዳያገኙ እፍንፍን አድርገው አጀቧቸው፡፡ ዐውደ ምሕረቱ በልዩ ልዩ መሰናክል ታጥሮ ምዕመናን በቅጡ ማስቀደስ ተሳናቸው፡፡
በዚህን ጊዜ ይላሉ ውስጥ ዐዋቂዎች፣ በዚህን ጊዜ የአቡነ ገብርኤልን መንፈስ ለማረጋጋት ሲባል፣ በአግባቡ የተመዘገበ ስለመሆኑ እንኳን በቅጡ የማይታወቅ ለራስ መጠበቂያ የሚሆን አንድ ሽጉጥ ከጥገኛ ነጋዴዎቹ በአንዱ በእጅ አዙር ተበርክቶላቸዋል፡፡ በዚህ ሁኔታ የተነቃቁት ሊቀጳጳስ ምስኪኖቹን የሀዋሳ ምዕመናንን ለግል የወሲብ መጽሔት በሰጡት ቃለ መጠይቅ "ቀበሮዎች ናቸው" ብለው እስከመሳደብ ደረሱ፡፡ በሠላም የሚመጣውን በእጅ መስቀላቸው፣ በኃይል የሚመጣባቸውን ደግሞ በተሰጠቻቸው ራስ መጠበቂያ ቀልጥመው ሊያሳርፉት ንቁ ሆነው መጠበቅ ያዙ፤ በሠለጠነ ዘመን ማን ይሞታል ታዲያ?
አቡነ ገብርኤል እንዲህ እንዲህ እያሉ፣ ልባቸው ዕርቅና አንድነትን እየተፀየፈች፣ ልታረቅ ቢሉ እንኳን ጥገኛ ነጋዴዎቹና የ"ማኅበረ ቅዱሳን" አባላት እንዳይታረቁ እያከላከሏቸው የሠላም መንፈስ አንድ ቀን እንኳን በውስጣቸው ሳትገባ፣ ሀዋሳ ላይ ሥራ ከጀመሩ ሁለት ዓመት ሊሞላቸው አንድ ሁለት ወራት ብቻ ቀራቸው፡፡ ታዲያ በአንድ ዕድለ ቢስ የነሐሴ 2004 ዓ.ም የተረገመች ቀን፣ ያቺ ለራስ መጠበቂያ የተሰጠቻቸው ሽጉጥ ጠፋችባቸው፡፡ ከሁኔታው መረዳት እንደተቻለው አቡነ ገብርኤል ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ሥርዓተ ቀብር አዲስ አበባ በተገኙበት ወቅት ሽጉጣቸውን መኝታ ክፍላቸው ውስጥ ረስተውም ይሁን አስቀምጠው ያገኘ ሰው እንደወሰደባቸው ተገምቷል፡፡
በዚህ ሁኔታ የተበሳጩትና የተቆጡት አቡነ ገብርኤል ከእነርሱ በስተቀር አንስቶ ሊወስድብኝ የሚችል የለም በማለት የጠረጠሯቸውን ፍጹምን (ተላላኪያቸው) እና ሊቀመዘምራን ልሳነወርቅን (ሾፌራቸው)፣ በቅርብ እንዲከታተሉላቸውና እንዲያጠኗቸው የጥገኛ ነጋዴዎችንና የ"ማኅበረ ቅዱሳን"ን ጥምር ኮሚቴ አይሉት ስብስብ ነገር ይመድቡባቸዋል፡፡ የሽጉጧ ነገር የውሃ ሽታ ሆነ ቀረ፡፡ ፍጹም ሲጠየቅ ከልሳነወርቅ በስተቀር ሊወስድባቸው የሚችል የለም እርሱን ጠይቁት ይላቸዋል፡፡ ልሳነወርቅ ደግሞ በበኩሉ "አብሯቸው የሚያድር ማን ሆነና ነው እኔን የምትጠይቁት? ለመሆኑ ለእርሳቸው ከፍጹም የቀረበ አለ እንዴ? ፍጹምን መርምሩት" ይላቸዋል፡፡
ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ያችን ውድ ዕቃ ሳያገኟት መስከረም ወር እንደዋዛ ሊጠናቀቅ ተቃረበ፡፡ እንደ እርሳቸው እምነት በእነዚህ ሁለት ሰዎች መጠቃታቸው ያንገበግባቸዋል፡፡ በተለይ የፍጹም እንዲህ መጨከን ሊገባቸው አልቻለም፡፡ ፍጹም እኮ ሁለ- ነገራቸው ነው፡፡ ቃል አቀባያቸው፣ ጠባቂያቸው፣ አስገቢና አስወጪ አጋፋሪያቸው፣ አንዳንዶች ደግሞ እንደሚሉት፣ የላመ የጣፈጠ ምግባቸውን ቀምሶ ለይቶ የሚያስቀርብላቸው ወጥ ቀማሽ እልፍኝ አስከልካያቸው፣ ኧረ ስንቱ . . . ? የፍትሕ ጥያቄ ለማቅረብ ወደ መንበረ ጵጵስናው የሚመጡትን የሀዋሳ ምዕመናንን "እርሳቸው የሉም"፤ "ተኝተዋል"፤ "ዕረፍት ላይ ናቸው"፤ "አሁን ሊያነጋግሯችሁ አይችሉም" እያለ የሚያባርርላቸው አለኝታቸው ነው፡፡ ሲያስፈልግም ከእርሳቸው ቀደም፣ ቀደም እያለ ምዕመናኑን ላቀረቡት ጥያቄ መልስ ሳያገኙ አፍ አፋቸውን እያለ ወደ መጡበት ይመልስላቸዋል፡፡ እርሱን እንደ እሳት መከላከያ አስቤስቶስ ነው የሚጠቀሙበት፡፡ እንደሻንጣቸው ሁልጊዜ የትም ነው ይዘውት የሚዞሩት፡፡ በተለይ ረፋድና አመሻሽ ላይ በፌስታልና በብብቱ ሥር በጋዜጣ የተጠቀለሉ የሚበሉና የሚጠጡ ፍሬሽ ፍሬሽ ነገሮችን ባሻው መንገድ በማቅረብ እርሱን የሚተካከለው አንጀት-አርስ የለም፡፡ ፍጹም እኮ በፍጹም ተተኪ የሌለው ረዳታቸው ነው፡፡
ሲያሻው ደግሞ "ተቀመጥ በወንበሬ፣ ተናገር በከንፈሬ" ብለው በሀገረ ስብከቱ ልዩ ልዩ ወረዳዎችና ከተማዎች እየወከሉት ልዩ ልዩ ካህናትን እየሰበሰበ ይገስጽላቸዋል፡፡ የተበላሹ አሠራሮችን ያስተካክልላቸዋል፡፡ እንደ እርሳቸው ሆኖ የሚገባቸውን ግብዣ ስለእርሳቸው ይጋበዝላቸዋል፡፡ ታዲያ "ፍጼን" ምን ነካው? ደግሞ እኮ እርሱን ላለማጣት ቃለ ዐዋዲን ሽረው በመዋቅር የሌለ የሥራ መደብ ፈጥረው "የጳጳሱ የመልዕክት ክፍል"     የሚል የሥራ መደብ መጠሪያ አውጥተው በወር ብር 930 ከአሮጊቶች መቀነት ከሚሰበሰብ ገቢ ወርሃዊ ደመወዝ እንዲከፈለው ቆርጠውለታል፡፡ ይህም ብቻም አይደለም፤ እርሱን ከመውደዳቸው የተነሳ ቅጥሩ ያለ ማስታወቂያና ያለ ነፃ ውድድር በመስከረም 2004 ዓ.ም ሆኖ፣ ደመወዙ ደግሞ ከቅጥሩ ቀን በፊት አንድ ወር ወደ ኋላ ተደርጎ ከነሐሴ 2003 ዓ.ም ነው የተደረገለት፡፡ እርሳቸው ይህንን ሁሉ ሕግን እየተላለፉለት፣ እየጣሱለት፣ እንዲህ ጉድ ያደርጋቸዋል? ወይኔ! ወይኔ! ወይኔ! ሰውየዉ . . . !!

Wednesday, October 10, 2012

‹‹ለእንጀራ ብዬ ›› . . . አይባልም!

በሰላማዊት አድማሱ Selam.admassu@yahoo.com

ሸዋንግዛው፣ በላይነህ፣ ጌታ ነህ፣ ግርማዊ፣ ልዑል፣ ኩራባቸው  . . . እነዚህን እና እነዚህን የመሳሰሉ ስልጣንን፣ ጌትነትን ፣ልዕልናን የሚገልፁ በርካታ ኢትዮጵያዊ ሰሞች አሉ፡፡ ስለ ስም ካነሳን ዘንድ ስያሜ ጠባይን፣ግብርንና ሁኔታን የሚገልጥ ሆኖ በእስራኤል ዘንድ ይሰየም እንደነበር የታወቀ ነው፡፡ ለምሳሌ ምናሴ፡- ‹‹ማስረሻ›› ዘፍ 41፡51 (የስም ሰጪውን ሁኔታ ሲገልጥ) ዮሴፍ ‹‹ይጨምር›› ዘፍ 30፡24 (የዮሴፍን ህይወት ያንጸባርቃል)፡፡ የእግዚአብሔር ስሞችም ባህሪውን ፤ስራውን እና አምላክነቱን ይገልጻሉ፡፡ የእኛዎቹ የኢትዮጵያውያን ስሞችስ ምን ያህሉ ይሆን እኛነታችንን የሚገልጹት? ወይንስ መግለጽ አይጠበቅባቸውም ይሆን?፡፡
    አንድ የቤተሰብ አባወራ ለልጁ የሚሰጠው ኩርማን እንጀራ፤የሚያወርሰው አንድ ክንድ መሬት ሳይኖረው ‹‹ ግዛቸው›› ብሎ ስም ያወጣለታል፡፡ ልጅዬውም ከእናቱ ጓዳ ዳቦውን እየገመጠ፤ ቆሎውን እየቆረጠመ አድጎ ለአቅመ አዳም ሲደርስ እርሱም ተራውን ለልጁ ‹‹በላይ ነህ›› ወይንም ‹‹ጌታ ነህ›› ብሎ ስም ያወጣለታል፡፡ እንዲህ እንዲህ እያለ እስከ አስር ትውልድ ቢቆጠርም አንድም ጊዜ ከቤተሰቡ መሃል ‹‹እንደ ስሙ›› የሆነ ላይገኝ ይችላል፡፡ ‹‹ግዛቸው›› ተብሎ በድህነቱ ሳቢያ ላለው የተገዛ፤ ‹‹በላይነህ›› ተብሎ ‹‹ በታች›› የሆነ እጅግ ብዙ ሰው አለ፡፡ እንዲያው ለመግቢያ ያህል ምን ያህል ሥራችን እንደስማችን ወይንም ስማችን እንደስራችን ይሆን?  ስል መጠየቅ ፈለኩ እንጂ በዋንኛነት ላወራስ የፈለኩት ስለ ሥራ ነው፡፡ እንደው የስሞቻችን ነገር በሥራ ባህላችን ላይ ያመጡት አሉታዊ ተጽዕኖ ይኖር ይሆን እንዴ? እናንተስ ምን ይመስላችኋል?
የሥራ ፈጣሪው ማን ነው?
   መቼም ሁሉም ነገር መነሻና ጅማሬ አለው ፡፡ ለመሆኑ ሥራን ማን ፈጠረው? ተፈጥሮ ወይንስ ፍጥረት? ሃጢያት ወይንስስተት?  . . ሁሉ የየራሱ መላ ምት ሊኖረው ይችላል፡፡ መጽሐፍ ቅዱሳችን ግን የሥራ ፈጣሪው ራሱ እግዚአብሔር እንደሆነ ይናገራል፡፡ ዘፍ 1፡28፡፡ ይህንን ሃሳብ መጋቢ ደሞዝ አበበ ሥራ-ሥራ በሚለው መጽሐፋቸው ላይ ‹‹ ሥራ የሰዎች ግኝት አይደለም፡፡ ከእግዚአብሔር የተገኘ አምላካዊ በረከት ነው፡፡ በመሆኑም በአምሳሉ ለፈጠረው ሰው ሥራን ሰጠው ፡፡ እርሱ ቦዘኔ ስላልሆነ ሰውም ቦዘኔ እንዲሆን አይፈልግም፡፡›› በማለት ገልጸውታል፡፡ ስለዚህ በቀላል እና በማያሻማ መንገድ የሥራ ፈጣሪው ራሱ እግዚአብሔር መሆኑ ተገልጾልናል፡፡
ሥራ ለምን? ለሆድ ወይንስ? . . .
    እግዚአብሔር አምላክ በዘፍጥረት መጽሐፍ ላይ ለአዳም ‹‹ሥራን›› የሰጠው ‹‹ለሆዱ›› ወይንም ለሚበላው አይደለም፡፡ ምናልባት እኛ ‹‹ለእንጀራ ብዬ ነው ስራ የምሰራው›› ብለን እንደምንለው አይነት አይደለም፡፡  ምክኒቱም ኤደን ገነት ‹‹ለእንጀራ›› የሚለፋባት አልነበረችም ዘፍ 2፡8፡፡ አንዳንድ መጽሐፍት ‹ገነት›› የሚለውን ቃል ሲተረጉሙት ሁለት ፍቺ ይሰጡታል፡፡ አንደኛው ‹‹ አትክልት ማለት ነው›› ሲሉ ሁለተኛው ‹‹ በቅጥር የተከለለ የአትክልት ስፍራ›› ማለት ነው ይላሉ፡፡ ስለሆነም የአዳም በገነት መቀመጥ እና ሥራን መስራት የተፈለገው የሚበላው ነገር ስለሌለው አልነበረም፡፡ ይልቁንም መልካሙን እና ክፉውን ከሚያሳውቀው ዛፍ በቀር በገነት ካለው ሁሉ እንዲበላ ተፈቅዶለታል፡፡ ታዲያ እግዚአብሔር አምላክ አዳም የሚበላው ነገር ሞልቶት ሳለ  ሰራተኛነቱን ለምን ፈለገ? ብለን ብንጠይቅ አዳም ከተፈጠረ በኋላ ምድርን የማበጀት እና የመጠበቅ ኃላፊነት ስለተሰጠው ነው፡፡ ‹ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር አምላክ ሰውን በኤደን የአትክልት ቦታ አኖረው ሰው የአትክልቱን ቦታ እንዲያለማና እንዲንከባከበው ነው፡፡› ዘፍ 2፡15