Thursday, May 24, 2012

በፍርድ ፈንታ ደም ማፍሰስ በጽድቅ ፈንታ ጩኸት(ኢሳ. 5÷7)


                      ምንጭ፦ቤተ ጳውሎስ ብሎግ  

አንዲት ሕጻን ልጅ ሞታ የጎጃሟ አልቃሽ፡-
                         ምን ዓይነት ቄስ ናቸው የማይጠብቁ ዕቃ
                      እበተስኪያን ጓሮ እጣኒቱ ወድቃ
በማለት የሀዘን ቅኔ (ሙሾ) አሰምታለች፡፡ የቄሱ አንዱ ሥራ ዕጣን መጠበቅ ሲሆን ዋነኛው ሥራቸው ግን ሕጻናትን መጠበቅ ወይም ማሳደግ ነው፡፡ ሕፃናት ከቤተ ክርስቲያን አደባባይ ሊቀመጡ አባቶቻቸውን እያዩ ሊማሩ ሲገባ ከቤተ ክርስቲያን ጓሮ ከመቃብር ውስጥ ሲወድቁ ማየት አሳዛኝ ነው፡፡ አልቃሿ በሕፃናት ማለቅ ቀሳውስቱ ለምን አይጸልዩም ማለቷ ሲሆን ከዚያ ባሻገር ግን ትውልድን ለምን ይቀጫሉ? ማለቷ ነው፡፡ አባቶች አደራቸውን ባለመወጣታቸው ትውልዳችን የሞት ልጅ ሆኗል፡፡ ራሱን በራሱ እየመራ የዘመን ምርኮኛ፣ የኃጢአት ግዞተኛ ሆኗል፡፡ ይልቁንም በአባቶች ፈንታ እንዲተኩ ከዐውደ ምሕረቱ ሊቀርቡ የሚገባቸው ወጣቶች እየተገፉ ወደ መቃብር ስፍራ መውረዳቸው ዛሬም ልብ ያለውን የሚያስለቅስ ነው፡፡
ነቢዩ ኢሳይያስም፡- “አሁን ስለ ወዳጄና ስለ ወይን ቦታው ለወዳጄ ቅኔ እቀኛለሁብሏል (ኢሳ. 5÷1)፡፡ ነቢዩ ኢሳይያስ ለእግዚአብሔር አዝኖ ወዳጅነቱን ለመግለጥ የሀዘን ሙሾ አሰምቷል፡፡ ስለ ወዳጅ ይለቀሳል፡፡ ወዳጅ በሞት ስለተለየ ብቻ ሳይሆን የጠበቀው እንዳልጠበቀው ሲሆንበት ይልቁንም ልጁን በሞት ሲያጣ ለወዳጅ ይለቀሳል፡፡ እግዚአብሔር ሕያው ወዳጅ ነው፤ ነቢዩ ኢሳይያስ ግን ያለቀሰው ሞትን ስለመረጡት ትውልዶች ነው፡፡ እግዚአብሔር መንግሥቱ የማይነካ ነው፤ ነቢዩ ኢሳይያስ ግን ያለቀሰው ከእግዚአብሔር ፍቅር ለተፈናቀሉት ነው፡፡ እግዚአብሔር የማይጎድልበት ነው፤ ነቢዩ ኢሳይያስ ግን ያለቀሰው ሰላማቸውን ስላላወቁ ሕዝቦች ነው፡፡ በእውነት ካጣ ሰው ይልቅ አግኝቶ ያላወቀበት እጅግ ሊለቀስለት ይገባል፡፡ እግዚአብሔርን ያህል ጌታ ለገፉ፣ ገነትን ታህል ቦታ ችላ ላሉ ልቅሶ ይገባል፡፡ ኢሳይያስ ግን ያለቀሰው ለሟቾቹ ሳይሆን ለወዳጁ ለእግዚአብሔር ነው፡፡ የሰው ልጆች እንዳፈቀራቸው አለመገኘታቸው፣ እንዳደረገላቸው አለማመስገናቸውን ባሰበ ጊዜ ለወዳጁ አለቀሰ፡፡

አፍ በእነሱም ዘንድ አለ!


ማቅ( ማቅ፤ ማለት ጥቁር የሀዘን ልብስ ማለት እንደሆነ ልብ ይሏል?) ማቅ  ቅድመ ሲኖዶስ ለማሳካት ካወጣችው እቅድ ውስጥ በተወሰነ ደረጃ ማሳካቷን ሰምተናል። እግረ መንገዱንም ሲኖዶስ በምን በምን ጉዳዮች ላይ ሊወያይ እንደተዘጋጀና ምን ምን ውሳኔዎችን እንደሚያሳልፍ ለማወቅ የፈለገ ካለ ከማቅ ማእከላዊ ቢሮ በቂ መረጃ ሊያገኝ እንደሚችል ከበቂ በላይ አረጋግጦ አልፏል።እነ ማንያዘዋል በታክሲው ውስጥ የቀደዳ ወጋቸው ሲኖዶሱ ገና ሳይሰበሰብ «ሁሉም ነገር በኛ እቅድና መንገድ እንዲፈጸም ተመቻችቷል፤ ምንም የሚያሳስብ ነገር የለም» ሲል ለኤፍሬም ካጽናናውና የድኅረ ሲኖዶስን  ውጤት ስንመለከት  በእርግጥም ሲኖዶሱ አስቀድሞ በተጠናቀቀ ውሳኔ ላይ መሰብሰቡን እና ማቅ ከማኅበርነት በላይ ሲኖዶሱን ለአስፈጻሚነት የሰየመችው ስብስብ እንደሆነም  ደረት የሚያስነፋ ንግግሩ አስረጂያችን ሆኗል ። በአጭር ቃል ስምዓ ጽድቅንና ሐመር መጽሔትን በማንበብ ወይም ቱባ የማቅ ሹመኛን በመጠጋት ብቻ ከእንግዲህ ወዲያ ባለው የሲኖዶስ ስብሰባ ላይ መወያያ የሚሆነውን አጀንዳ አስቀድሞ ማወቅ እንደሚቻል ተረድተናል። አባ ጳውሎስም አስቀድሞ የተዘጋጀላቸውን  ውሳኔዎችን ለማንበብ አሁን ከሚጠቀሙበት በተሻለ ደረጃ ፊደላትን የሚያጎላ መነጽር እንዲገዙ ብንመክራቸው የምናየው ነገር ሁሉ ለምክሩ አመላካች ነገር ነው። ፓትርያርክነቱን ፈንግሎ 7 ኰሚቴ በማዋቀር እሰጥ አገባ ውስጥ ከመግባት ፓትርያርኩን ባሉበት አስቀምጦ የ7 ቱን ኰሚቴዎች ውሳኔ እንዲያነቡ ማድረጉ አዲሱ የተዋጣለት የማቅ ስልት ነው። እኛም ይበል ብለናል! ግን እስከመቼ?
ማኅበሯ በተወሰነ ደረጃ የተሳካላት ነገር ያለ ቢመስልም በወሬ ሊደሰኰር ከሚችል ባለፈ  ምንም የሚጨበጥ ነገር አይታይም።
ለምሳሌ ብናነሳ፤ አባ ኅሩይን ከውድቀት ማዳን ወይም ወደነበሩበት ማስመለስ ብዙ ታግላለች። ይህም ማቅን ከኅሊና መላላጥ አውጥቶ ያሰበችውን ታዛዥ ሰው መታደግ ያስቻላት ሳይሆን ቀርቷል። ይህ ትልቁ ኪሳራዋ ነው። መፈንቅለ እንቍ ባህርይ ለማድረግ ያደረገችው ኩዴታም አልተሳካም። ይህም ኪሳራ ቁጥር ሁለት ነው።
 አባ ሠረቀ ብርሃን ወ/ሳሙኤልንና መ/ሐዲስ በጋሻው ደሳለኝን ለማስወገዝ ያልፈለቀለችው ድንጋይና ያልቆፈረችው ጥልቅ ጉድጓድ አልበረም። ማን እንደሚገባበት እግዚአብሔር ብቻ የሚያውቀው የማኅበሯ ጥልቅ ጉድጓድ አፉን እንደከፈተ ህልሟ  ለወዲያኛው ዓመት ተሸጋግሯል። ሁሉን ለማየት የዚያ ሰው ይበለንና ለጊዜው ማቅ በዚህ ጉዳይ ላይ ብዙ የደከመችበትና የለፋችበት የኃጢአትና የዐመጻ ስብስብ ጩኸቷ አልተሳካላትም። ይህም ሦስተኛው ኪሳራዋ ነው።
ተወግዘዋል ወይም ማእረገ ክህነታቸው ተገፎ «አቶ» ተብለዋል፤ በማለት የምታላዝነውን  ውሳኔ ስንመለከት፤ ከሚስተጋባ የገደል ማሚቱ ጩኸት በስተቀር የሚያዝ፤ የሚጨበጥ እውነተኛ ነገር አይታየንም። ምክንያቱም የወንጌሉ መምህር ጽጌ ስጦታውም ሆነ ወንጌልን በመተንተን ድንቅ ጽሁፎችን ያበረከተው ዲ/ን አግዛቸው ተፈራ ከቤተክርስቲያኒቱ በግፍ ከተባረሩ ዓመታትን አስቆጥረዋል። እንዲያውም መምህር ጽጌ ስጦታው ነፍስና ስጋውን ለመለየት በደረሰ ድብደባ ነበር የደህና ሰንብት አሸኛኘት የተደረገለት። አሁን ያንን ድብደባ ለመድገም ካልሆነና አግዛቸውንም ሳንደበድበው አመለጠን ለማለት ካልሆነ በስተቀር የሌሉትን ሰዎች ማእረገ ክህነታቸውን ገፈን አውግዘናል በማለት የምታገኘውን ጥቅም  የምታውቀው የሀዘን ሸማ የሆነችው ማቅና ተላላኪ ጳጳሶቿ ብቻ ናቸው። እኛ ግን የሚገባን ነገር ቢኖር የግለሰቦቹን እንደኢትዮጵያዊ የመኖር መብታቸውን ለመግፈፍና፤ «ባልሰብክ ወዮልኝ» ያለውን ቃል እንዳይናገሩ አፋቸውን በመዝጋት፤ የማስተማር ነጻነታቸው ለመቀማት የተደረገ ጩኸት መሆኑን ነው። ስለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ከሊቃውንቱና ከመጻሕፍቱ ውጪ ያስተማሩት ነገር ካለ ስህተቱን በመጻህፍትና በሊቃውንቱ ወግ መልስ መስጠት እንጂ ማቅ በነዳችው ስብሰባ ላይ የሌለ ክህነት ቀምተናል፤ በዚያ ላይ አውግዘናል ማለት ቤተክርስቲያኒቱ በአላዋቂዎች መከበቧን ያመላከተ ስለመሆኑም ያረጋገጠ ሆኗል። የተባረሩት ቀድሞ አይደለም እንዴ? የዛሬው ስለምን ይሆን? ማውገዝ ያስፈለገው ብለን እንጠይቃለን።
እነ መልዓከ ብርሃን አድማሱ ጀምበሬ በነበሩባት ቤተክርስቲያን ስለግብረ ሰዶም ከመጻፍ ያልዘለሉ ሰዎች ሞልተውባት ስናይ አውግዘናል የሚለው «እሪ በከንቱ » ጩኸት መታየቱ የግድ ነው። ሊቁ አባት ብጹእ አቡነ መርሐ ክርስቶስ ብንድራቸው ይሻላል ያሏቸው ሰዎች ከከበቧት ቤተክርስቲያን በእውቀት ላይ የተመሰረተ ውሳኔ መጠበቅ ያልዘሩትን ለማጨድ ከመሞከር የተለየ አይደለም።

የማኅበረ ቅዱሳን ተላላኪ ጳጳሳት ሕገ ቤተ ክርስቲያንን ባልተከተለ መንገድ መወገዝ የሌለባቸውን የቤተ ክርስቲያን ልጆች “አወገዝን” አሉ

                 ምንጭ፦ አባ ሰላማ ብሎግ
              ( ለፒዲኤፍ ንባብ እዚህ ይጫኑ )
ነውራችን ተሸፈነልን ብለውና ከማኅበሩ የሚከፈላቸውን ረብጣ ብር ከግምት በማስገባት፣ እንዲሁም ከማኅበረ ቅዱሳን ጎን ብንቆም ፓትርያርክነቱ ለእኛ ይሆናል በሚል ክፉ ምኞት ተይዘው ለአንድ ወንበር እርስ በርስ እየታገሉ፣ የቤተክርስቲያንን ሳይሆን የማኅበሩን አላማ ለማሳካት በግንቦቱ ሲኖዶስ ከመጠን በላይ ሲፋንኑ የነበሩት አባ አብርሃም፣ አባ ዲዮስቆሮስና አባ ሳሙኤል፣ እንዲሁም አባ ጢሞቴዎስ፣ “ምንም ቢሆን ማኅበረ ቅዱሳን የከሰሳቸውን ሰዎችና ማኅበራት ሁሉ ሳናወግዝ አንበተንም፤ ማኅበረ ቅዱሳን ያጠናው በቂ ነው፤ እነርሱን ጠርቶ ማነጋገር አያስፈልግም” በሚል የማኅበረ ቅዱሳንን ክስ ብቻ በመቀበልና ተከሳሾቹን ሳያነጋግሩ ፍትሀዊነት የጎደለውን ፍርድ በመፍረድ “አውግዘናል” ማለታቸው ተሰማ። እነዚህ በስም የተጠቀሱ የሰሙኑን የሲኖዶስ ስብሰባ ማኅበረ ቅዱሳን በአቡነ ጢሞቴዎስ ቤት ያገባላቸውን ግብር በምሳ ሰአት እየበሉ፣ የቀኑን ውሎ ለማኅበሩ አመራሮች ሪፖርት እያቀረቡና በቀጣዩ ስብሰባ ላይ ማድረግ ስለሚገባቸው መመሪያ ከማኅበሩ አመራሮች እየተቀበሉ ሲኖዶሱን ሲያውኩ መሰንበታቸው ይታወሳል።በተለይም አባ አብርሃም ከአሜሪካው ሀገረ ስብከት መነሳታቸው ጥቅማቸውን ስላስቀረባቸው በግላቸውም በማኅበረ ቅዱሳንም በኩል አልተወደደምና፣ ይህን ቂም ለመወጣት ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ “ክስ የቀረበባቸው ግለሰቦች ተጠርተው ሳይጠየቁ እንዴት ይወገዛሉ? ስለዚህ ተጠርተው ይጠየቁና ውሳኔ ይሰጥ” ሲሉ ያቀረቡትን ሐሳብ ለጊዜው ተቀብለው የነበረ ቢሆንም፣ በዚህ እጅግ የተከፋው ማኅበረ ቅዱሳን “ሰዎቹማ ካልተወገዙ ጤና አይሰጡንም። ስለዚህ ስብሰባው ከመዘጋቱ በፊት አውግዛችሁ መለያየት አለባችሁ ሲል ተላላኪ ጳጳሳቱን ባዘዘው መሰረት ተልእኮዋቸውን ተወጥተዋል። አንዳንዶቹ አረጋውያን ጳጳሳት ግን ውግዘት የተባለውን ህገወጥነት “ኧረ ተዉ ምንድነው ለውሳኔ መቸኮል? ተጠርተው ያልተጠየቁ ሁሉ ተጠርተው ይጠየቁ። አሊያ ይህ ለቤተክርስቲያን የሚጠቅም ውሳኔ አይደለም” ቢሉም ለቤተክርስቲያን ሳይሆን ለግል ምቾታቸውና ለሥልጣናቸው ብቻ የቆሙት አባ አብርሃም፣ አባ ሳሙኤል፣ አባ ዲዮስቆሮስና አባ ጢሞቴዎስ አሻፈረን በሚል ማውገዛቸውን አውጀዋል። እነዚህ በቀሚሳቸውና በቆባቸው ካልሆነ በቀር አንድም የጳጳስ ሰብእና የሌላቸውና ሊወገዙ የሚገባቸው “ጳጳሳት”፣ መጽሐፍ ቅዱስንም ሆነ ህገ ቤተክርስቲያንን እንደማያውቁ ካስተላለፉት ህገወጥ ውግዘት መረዳት ተችሏል። እንደክርስቶስ ትምህርት ቤተክርስቲያን ያጠፋውን ሰው ጠርታ መምከርና እንዲመለስ ማድረግ የመጀመሪያ ሥራዋ ነበር። ተመለስ የተባለው ሰው አልመለስ ብሎ ከጸና ግን ታወግዘዋለች። አሁን እነ አባ አብርሃም አስተላለፍን ያሉት ውግዘት ግን ይህን ስርአት ያልተከተለ፣ ከቤተክርስቲያን ፈጽሞ የማይጠበቅ፣ በእነርሱ መለኪያ የተሳሳተን ሰው ከስህተቱ ለመመለስ ሳይሆን በዚያው ጠፍቶ እንዲቀር ለማድረግ የተላለፈ የ“ጥፋ” አዋጅ ነው። በእውነተኛዪቱ ቤተክርስቲያንና በደጋጎቹ አባቶች አይን ሲታይ “ውግዘት ዘበከንቱ” ነው። መጽሐፍ ቅዱስም “እንደሚተላለፍ ድንቢጥ ወዲያና ወዲህም እንደሚበርር ጨረባ፥ እንዲሁ ከንቱ እርግማን በማንም ላይ አይደርስም።” (መጽሐፈ ምሳሌ 26፡2) ሲል የገለጸው አይነት ከንቱ መሆኑን ይናገራል።