Thursday, January 5, 2012

የአባታችሁን ምኞት ልታደርጉ ትወዳላችሁ!



ደጀሰላምና አንድ አድርገን የተባሉ ብሎጎችን እንጠይቃለን
 

                              ወንጌል ደግሞ«የአባታችሁን ምኞት ልታደርጉ ትወዳላችሁ» ይላችኋል።ዮሐ ፰፣፵፬

(by dejebirhan)ይህንን ቃል የተናገረው የዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ለፈሪሳውያን ካህናት ነበር። ጌታ የመጣው የታሰሩትን እንዲፈቱ፣ በሞት ጥላ ስር ያሉ ወደሕይወት እንዲመጡ ነበርና የመንግሥቱን ወንጌል በቃል እያስተማረ፣ ኃይሉንም በግብር እየገለጠ የመጣ የይቅርታና የምህረት ባለ ቤት መሆኑን አሳይቷል። ከዚህም ውስጥ አንዱ የሆነው ጉዳይ ፈሪሳውያን በዝሙት የተያዘችውን ሴት በክስ ወንበር አቁመዋት እንደሕጋቸው በድንጋይ ተወግራ የምትገደል መሆኑን ቢያውቁም ጌታችንን ሊፈትኑትና የሚከሱበትን ምክንያት ሲሹ ፈታኝ በሆነው መንፈስ እየተነዱ ዘማዊቷን ከፊቱ አቅርበው የሙሴ ሕግ ተወግራ ትገደል ይላል፣ አንተስ በሕግህ ምን ትላለህ? ብለው ሲጠይቁት «መላልሰው በጠየቁት ጊዜ ግን ቀና ብሎ። ከእናንተ ኃጢአት የሌለበት አስቀድሞ በድንጋይ ይውገራት አላቸው» ዮሐ ፰፣፯
ኃጢአት ያልሰራ ማንም ፈሪሳዊ ካህን አልነበረምና ውልቅ ፣ውልቅ እያሉ እሱና ሴትየዋ በመቅረታቸው ፣ ከሳሾችሽ ወዴት አሉ? ሲላት «አንድም» ብላ መለሰች፣ እሱም «ሂጂ፣ ከአሁን ጀምሮ ኃጢአት ደግመሽ አትስሪ» ብሎ በፈውስና በሰላም እንዳሰናበታት እናነባለን።
ጌታ ብርሃን በመሆኑ በጨለማ ላሉ ሊያበራ እንጂ በአንድም ስንኳ ሊፈርድ እንዳልመጣ፣ የሚፈርድበት በልጁ ባላመኑ ሁሉ ላይ አብ መሆኑን፣ ኢየሱስ ቢፈርድም እንኳን ፍርዱ እውነት እንጂ በዘማዊቷ ላይ ህግ ጠቅሰው ለመፍረድ እንደሚሹ ፈሪሳውያን እንዳይደለ፣ ለራሱ የሚመሰክር አባቱ መሆኑንና ራሱም ቢመሰክር ምስክሩ እውነት መሆኑን የሚገልጸው የወንጌል ቃል በሰፊው ተጽፎልን እናገኛለን።
ስለራስህ ራስህ እንዴት ትመሰክራለህ? እውነት አርነት ያወጣኋችል እንዴት ትለናለህ? አንተ አባቴ ብትል እኛስ አብርሃምን የሚያክል አባት አለን ብለው ሲሞግቱ በየዘመናቱ እንደተነሱት ፈሪሳውያን በዘመናችንም በተነገረው ዘላለማዊ ቃል ትንቢት ሆኖ የሚመሳሰሉበትን አንድነት  እንረዳለን። ይኸውም፣
1/ ስለኢየሱስ የሚመሰክረው አብ ነው። ራሱ ቢመሰክርም ምስክሩ እውነት ነው። ፈሪሳውያኑ ራሳቸው ህግ ጠቃሽ፣ ራሳቸው ፈራጅ፣ ራሳቸው ፈታኝ ሆነው ከሚታዩ በስተቀር አንድም የእውነት ምስክር የሌላቸው የኃጢአት ባሪያዎች ናቸው። ዮሐ ፰፣፴፬
2/ኢየሱስ በኃጢአት ላሉ መፈታትንና በሞት ጥላ ስር ላሉ መዳንን ሊሰጥ መጥቷል። ዘማዊቷን «ሂጂ፣ ደግመሽ ኃጢአት አትስሪ »ሲላትና በነጻ ከእስራት ሲያወጣት የያኔው ፈሪሳውያንም ይሁኑ የዘመኑ፣ በጨለማ የኃጢአት ዓለም ሳሉ አንድ ዘማዊ፣ ወይም በስጋ ድካም የሚሰራውን ብዙ ብዙ ኃጢአት እየጻፉ የሚከሱ፣ በድንጋይ ወግረው ለመግደል አደባባይ የሚቆሙ ናቸው። ምክንያቱም እነሱ «እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ የአባታችሁንም ምኞት ልታደርጉ ትወዳላችሁ። እርሱ ከመጀመሪያ ነፍሰ ገዳይ ነበረ፤ እውነትም በእርሱ ስለ ሌለ በእውነት አልቆመም። ሐሰትን ሲናገር ከራሱ ይናገራል፥ ሐሰተኛ የሐሰትም አባት ነውና» ዮሐ፰፣፵፬ በማለት ማንነታቸውን ገልጿል። ይባስ ብለውም ራሳቸው የሰይጣንን ስራ እየሰሩ ሳለ በተቃራኒው የራሳቸውን ግብር ለኢየሱስ ሰጥተው «አንተ ሳምራዊ እንደሆንክና ጋኔን እንዳለብህ እናያለን» ሲሉ ሰድበውታል። በእነሱ ዘንድ ሳምራዊ የሆነ ሰው ሁሉ ጋኔን አለበት፣ ከእነሱ ውጪ የተለየ ሃሳብም ያለው ጋኔን የያዘው ነው ማለት ነው። ዛሬም የዘር ውርስ ፈሪሳዊነትን የተረከቡት የሚጠሉትን አንተ ርኩስ ሳምራዊ ብለው ጎራ ይለዩበታል፣ ያለ የሌለ ኃይላቸውን ይዘው ይዘምቱበታል።
ከዚህ በላይ ያየነው የእግዚአብሔር ምርጦች ነን፣ የአብርሃም ልጆች ነን፣ የሙሴን ሕግ የምንጠብቅ ጥንቁቆች ነን እያሉ ነገር ግን እገሌ ተሃድሶ፣ እገሌ ሳምራዊ፣ እገሌ ሰዱቃዊ፣ እገሌ ደግሞ ኦርቶዶክሳዊ ነው በማለት እራሳቸው መርምረው፣ እራሳቸው መጽሐፍ ገልጠው፣ እራሳቸው በፍርድ ወንበር ተቀምጠው ከፈረዱ በኋላ አንደኛውን ወገን በድንጋይ ወግረው ለመግደል፣ የራሳችን የሚሉትን ወገን ደግሞ ከፍ ከፍ ሲያደርጉ ይታያሉ።
ያዕቆብ ፬፣፲፬«ሕግን የሚሰጥና የሚፈርድ አንድ ነው፤ እርሱም ሊያድን ሊያጠፋም የሚችል ነው፤ በሌላው ግን የምትፈርድ አንተ ማን ነህ? »የሚለው ቃል እነርሱ ዘንድ አይሰራም።
ዛሬም በዚህ ዘመን ክርስቶስ የሞተለትን አንድ ደካማ ወይም ኃጢአት ያሸነፈውን ወይም እነሱ ላቆሙት ህግ አልገዛም ያለውን ሰው ክስ መስርተውበት በሕጋቸው ወግረው ለመግደል፣ ራሳቸው ለኃጢአት ባሪያ ሆነው ሳሉ፣ ሌላውን ጋኔን አለብህ የሚሉ፣ የአብርሃምን ስራ ሳይሰሩ አብርሃም አባት አለን የሚሉ፣ የአባታቸውን የዲያብሎስን ስራ እየፈጸሙ በክስ አደባባይ የሚያቆሙ፣ ስም የሚያጠፉ፣ የሚደበድቡ፣ የሚወነጅሉ፣ የሀሰት አባት ልጆች መሆናቸውን የሚመሰክሩ ፈሪሳውያን በዚህ ዘመንም ሞልተዋል። ከእነዚህም ውስጥ ግንባር ቀደሞቹ ማኅበረ ቅዱሳን፣ እንደዚሁም ዓይንና ጆሮ ሆነውለት የሚሰሩ ደጀሰላምና አንድ አድርገን የተባሉ በስም ስለሰላምና አንድ መሆን የሚመስሉ፣ በግብር ግን ሰላምና አንድነት እንዳይመጣ ሌሊትና ቀን የሚደክሙት ተጠቃሾች ናቸው። ይህም በማስረጃ ይረጋገጣል።ውድ አንባቢያን አስተዋይ ልቦና ኖሮን እንደእግዚአብሔር ቃል እውነቱን በማወቅ ለወንጌሉ ምስክር ልንሆን እንደሚገባን በአጽንዖት አሳስባለሁ!!
ከታች ያለውን አስረጂዎች ይመልከቱ።

Thursday, December 29, 2011

እውነትም ፍቅር ትቀዘቅዛለች!


ሩቅ ሳንሄድ ኢትዮጵያ ውስጥ እስላሙ በክርስትያኑ ላይ «የአላሁአክባር» ዘመቻውን በደንብ እያስፋፋው ስለመገኘቱ ከታች ባለው ርእስ የተመለከተው የቪዲዮ ምስል ማሳያ ነው። እራሱ ክርስቲያን ነኝ የሚለው ኦርቶዶክሱ እርስ በእርሱ እየተባላ፣ እየተካሰሰ፣ የአሸናፊነት ከበሮ ለመደለቅ በአንድ ወገን ሲኖዶሱ እርስ በእርስ፣ በሌላ ወገን ማኅበረ ቅዱሳንና ደጋፊዎቹ በእነ በጋሻው ላይ የተያዘ የሞት ሽረት ትንቅንቅ፣ በእስልምናው በራሱ የሱኒና የሐነፊ ሽኩቻ በመጨረሻው ዘመን የተነገረው ትንቢት እየደረሰ ይሆን? ያስብላል። «ሕዝብ በሕዝብ ላይ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣልና፥ ራብም ቸነፈርም የምድርም መናወጥ በልዩ ልዩ ስፍራ ይሆናል» ማቴ 24፣7ከሁሉ የሚገርመውና ትንቢቱን በትክክል የሚያረጋግጥልን ነገር ክርስቶስ በተወለደበት ቤተልሔም መቅደስ የፈረንጆቹ ገና በሁለት ወገን ጦርነት ደምቆ መዋሉ ነው። ኳኳታና የሰው ግንባር ፍንዳታ በተሰማበት አዲስ ዜማ በቤተክርስቲያኑ ውስጥ ክርስቲያን ቀርቶ አረሚ የማያደርገውን ፈጽመው አክብረው ዋሉ። እውነትም «ከዓመፃም ብዛት የተነሣ የብዙ ሰዎች ፍቅር ትቀዘቅዛለች» ማቴ24፣12 ያለው ደርሷል። ግሪኮችና አርመኖች ተፈጣፈጡ!!



Wednesday, December 28, 2011

የኢየሱስ ክርስቶስ አስታራቂነትና አምላክነት

«ክርስቶስ ማለት በቁሙ ወደአማርኛ የተገለበጠው የግሪኩ(ጽርእ)ቃል «Χριστός»«ክሪስቶሽ ሲሆን ትርጉሙም «የተቀባ» ማለት ነው። መቀባት « χριστῷ» የሚለውን ብቻውን የሚያመለክተው ከሌላ መቀበልን ሲሆን «ክርስቶስ» የሚለው ቃል ግን የቅብእ ባለቤትነትንና የመቀባት ግብርን አያይዞ የሚጠራ ስም ነው። (ኢሳ 45፣1) ይመልከቱ። «ክርስቶስ» በእብራይስጡ «המשיח» ሀመሺያኽ ቅቡእ፣ የተቀባ ሲሆን ግእዙ «መሲህ» በሚለው ይተካዋል። የቤተክርስቲያን ሊቃውንትም «የክርስቶስን መቀባት ወይም ቅቡእ መሆን ለማመልከት ሲያስተምሩ «አብ ቀባኢ፣ ወልድ ተቀባኢ፣ መንፈስ ቅዱስ ቅብእ» በማለት ይገልጻሉ። በእርግጥ ይህ ትምሕርተ መለኰት ሰፊና ጥልቅ እንደመሆኑ መጠን በዚህ ዙሪያ የተነሱ ትምህርቶችና ክርክሮች ብዙ ሲያምሱ ቆይቷል፣ ዛሬም ቢሆን ጨርሶ የጠፋ ስለመሆኑ የሚታወቅ ነገር የለም። እኛም ያንን ላለመድገም እንደመንደርደሪያ ይህንን ያህል ካልን ወደተነሳንለት ዓላማ እናምራ!
«ክርስቶስ» የተቀባ ማለት ነው ብለናል። እንደዚሁ ሁሉ «ኢየሱስ» የሚለውን ስንመለከት የእብራይስጡ «ישוע» የሹአ ሲሆን ትርጉሙም «መድኃኒት» ማለት ነው። ግሪኩም «Ιησούς» መድኃኒት፣( ማዳን)፣ አዳኝ የሚለውን ትርጉም ይሰጣል። ከዚህ የተነሳ «ኢየሱስ ክርስቶስ» ማለት «የተቀባ፣ቅቡእ እና መድኃኒት፣ አዳኝ» የሆነ ማለት ነው። ይህንን የስም ትርጉም ካገኘን ለሚቀጥሉት ሃሳቦቻችን መረዳት መጠነኛ ግንዛቤ ጨብጠናል ማለት ነው።
የሚቀባው ማነው? የሚቀባውስ ለምንድነው?
እነዚህን ነገሮች አጥርቶ ማወቅ የብሉይ ኪዳን አስተምህሮዎችን መመርመር ግድ ይላል። ያንንም ማድረግ አስፈላጊ የሚሆነው «ስለመሲሁ» ክርስቶስነት ላይ በሚነሱ ልዩ ልዩ አመለካከቶች ከብዥታ የወጣ እይታ እንዲኖረን ይረዳናል።
ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ........>>>(እዚህ ላይ ይጫኑ