Monday, May 15, 2017

የውግዘት ፖለቲካና የቤተ ክርስቲያናችን እጣ ፋንታ


( ክፍል አንድ ) # በቀሲስ መላኩ
መግቢያ
ባለፉት ሃያዎቹ ዓመታት፥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ
ቤተ ክርስቲያን በታሪኳ አይታ የማታውቃቸው ሦስት አበይት
ክስተቶች ታይተውባታል። የመጀመሪያው አንደኛው፥ ከፍተኛ
የሆነ የሕዝብ ፍልሰት ነው። በአዲስ አበባ ያሉት አባቶች
በግልጥ ያስቀመጡት ይፋዊ አኀዙ ሰባት ሚሊየን ይባል
እንጂ፥ ከአስር እስከ አስራ አምስት ሚሊየን የሚሆኑ የቤተ
ክርስቲያኒቱ አባላት ቤተ ክርስቲያኒቱን ትተው ወደ ሌሎች
ቤተ እምነቶችና ተቋሞች ሄደዋል። ሁለተኛው ዓቢይ
ክስተት ቤተ ክርስቲያኒቱ ለሦስት መከፈሏ ነው።
የመንግሥት ለውጥን ተከትሎ አራተኛው ፓትርያክ ብፁዕ
ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ከመንበራቸው ከተሰደዱበት
ጊዜ ጀምሮ ቤተ ክርስቲያኒቱ በስደት ያለው ቅዱስ
ሲኖዶስ፥ በአገር ቤት ያለው ቅዱስ ሲኖዶስ እና ገለለተኛ
በሚል ተከፍላለች። ሦስተኛው እና ቤተ ክርስቲያኒቱ
በታሪኳ አይታው በማታውቀው መንገድ የተከሰቱ ነገሮች
ቢኖሩ በተለይ አዲስ አበባ ባሉት አባቶች ዘንድ፥ «
ውግዘት» እንደ ታላቅ መሣሪያ መያዙ ነው።
በዚህ በያዝነው በ፳፩ኛው ክፍለ ዘመን ሰዎች ተቀራርበው
አሳባቸውን በሚካፈሉበት ዘመን፥ አብያተ ክርስቲያናት
ያለፈ ውግዘታቸውን በይቅርታና በመግባባት አስተካከለው፥
አንድ በሚያደርጋቸው ነገር ላይ ለመነጋገር እየጣሩ ነው።
በቅርቡ የሮም ፖፕና የእስክንድርያው ፓትርያርክ አንዳቸው
የአንዳቸውን ምእመን ዳግም እንዳያጠምቁ
መፈራረማቸው ይታወቃል። ሆኖም ግን ባለፉት 25
ዓመታት ውስጥ በአዲስ አበባ ባሉት አባቶች አማካይነት፥
የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በሺዎች የሚቆጠሩ
ምዕመናኖቿን እና አገልጋዮቿን አውግዛለች። ከአንድ
ቢሊየን አባላት በላይ ያላት የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን
ባለፉት አንድ መቶ አመታት ያወገዘቻቸውና በአዲስ አበባ
ያሉት አባቶች ያወገዙትን ስንመለከት በቍጥር የእኛው
በልጦ እናገኛለን። በአንድ በኩል የምዕመናኑ በሚሊየኖች
ወደ ሌሎች የእምነት ተቋማት መሄድ በሌላ በኵል ደግሞ
ጳጳሳትን ሳይቀር ምእመናንን ጨምሮ በመቶ ሺዎች
የሚቆጠሩ ምእመናንን ማውገዝ ከየት መጣ ለምንድነው
ይህ ክስተት በእኛ ዘመን የተደጋገመው? ከዚህ ውግዘት
በስተጀርባ ያሉት እነማን ናቸው? ተጠቃሚዎቹስ እነማን
ናቸው የሚለውን ለመመለስ በመጀመሪያ ስለውግዘት
በሚገባ ማወቅ ይኖርብናል።
ሀ. ውግዘት ምንድነው?
ውግዘት ቃሉ፥ ወገዘ ከሚለው ግሥ እንደሚገኝ እና
ፍቺውም መገዘት መለየት መካድ መርገም ማለት እንደሆነ
የሊቁ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ
ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ ይናገራል። ከዚህ ከቃሉ አንጻር
በምንመለከትበት ጊዜ፥ ቃሉ የሚያመለክተን ከዚህ በፊት
ከአንድ አካል ጋር አንድነት (communion) የነበረውን
እንዲለይ (excommuncate) ማድረግ ነው። ይህን
ግልጥ ለማድረግ ቃሉ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በእንዴት
ያለ መንገድ እንደተቀመጠ በማየት ትርጉሙን
እንመለከታለን።
1.ውግዘት እርግማን ነው።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለገላትያ ሰዎች ሲጽፍላቸው
«ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ፥
ከሰበክንላችሁ ወንጌል የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ፥
የተረገመ ይሁን። አስቀድመን እንዳልን እንዲሁ አሁን
ሁለተኛ እላለሁ፥ ከተቀበላችሁት የተለየውን ማንም
ቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን።» ይላቸዋል። ( ገላ ፩፥፰-
፱) ግእዙም « አትሙሰ መልአክ እምሰማይ ለእመ
መሀረክሙ ካልአ እምዘ መሀርናክሙ ውጉዘ ለይኩን።
በከመ እቤ ቀዳሚ ወይእዜኒ ካዕበ እብል ለእመቦ
ዘመሀረክሙ እምዘመሀርናክሙ ውጉዘ ለይኩን።»
አስተውሉ አማርኛው « የተረገመ ይሁን የሚለውን ግእዙ
የተወገዘ ይሁን ይለዋል። ይህ ውግዘት ወይም እርግማን
ምን ማለት እንደሆነ እንመልከት፥ አዲስ ኪዳን
ለመጀመሪያ ጊዜ የተጻፈበትን የግሪኩን ቃል
በምንመለከትበት ጊዜ፥ የተወገዘ ይሁን አናቴማ ኤስቶ
(ἀνάθεμα ἔστω ) ይለዋል። አናቴማ ቃሉ በብሉይ
ኪዳን « እርም»፥ «ለእሳት የተሰጠ» ማለት ነው። ለምሳሌ
ኢያሱ በኢያሪኮ የተገኘው ሁሉ እርም እንዲሆን ሲያዝ
አካን የተባለው ሰው « እርም ከሆነው ነገር ወሰደ»
ይለናል። ኢያሱ7፥1። እንዲህ ዓይነት ብዙ ጥቅሶች
በብሉይ ኪዳን እናገኛለን። በአዲስ ኪዳንም ይህንኑ ቃል
ሳይስት፥ አናቴማ ( ውግዘት እርግማን) ማለት
በእግዚአብሔር ፍርድ ውስጥ መውደቅ ማለት ነው።
ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ በገላያ መልእክቱ ላይ በሐዋርያት
ከተሰበከው የጸጋ ወንጌል የተለየ ወንጌልን የሚሰብክ
በዚህ የእግዚአብሔር ፍርድ ውስጥ እንደሚወድቅ ሲናገር
እናያለን።
2. ውግዘት ለሰይጣን አልፎ መሰጠት ነው።
አሁንም ወደ ቅዱስ ጳውሎስ መልእክት ስንመጣ
በ1ቆሮ5፥5 ላይ «መንፈሱ በጌታ በኢየሱስ ቀን ትድን
ዘንድ እንደዚህ ያለው ለሥጋው ጥፋት ለሰይጣን
እንዲሰጥ ፍርዴ ነው።» ሲል እናገኛለን። ቅዱስ ጳውሎስ
በዚህ ስፍራ ሐዋርያዊ ውግዘቱን ያሳረፈበት ሰው፥ በሥነ
ምግባር ውድቀት ውስጥ የተገኘ ማለትም የአባቱን ሚስት
ያገባ ሰው ነው። ሐዋርያው ለቆሮንቶስ ክርስቲያኖች
ሲናገር «ይህን ሥራ የሠራው ከመካከላችሁ ይወገድ። እኔ
ምንም እንኳ በሥጋ ከእናንተ ጋር ባልሆን፥ በመንፈስ
ከእናንተ ጋር ነኝ፥ ከእናንተም ጋር እንዳለሁ ሆኜ ይህን
እንደዚህ በሠራው ላይ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም
አሁን ፈርጄበታለሁ፤ እናንተና መንፈሴም ከጌታችን
ከኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል ጋር ተሰብስበን፥ መንፈሱ በጌታ
በኢየሱስ ቀን ትድን ዘንድ እንደዚህ ያለው ለሥጋው ጥፋት
ለሰይጣን እንዲሰጥ ፍርዴ ነው።» ይላል።
ይህ የቅዱስ ጳውሎስ ቃል ስለ ውግዘት ሦስት ዋና ዋና
ነገሮችን ያሳየናል። አንደኛ፥ ይህ ነገር በጉባኤ በጥንቃቄ
የሚታይ ነው። ጉባኤው የክርስቶስ ጌትነት የከበረበት
ጉባኤ መሆን አለበት። የሐዋርያው ሥልጣን የከበረበት
መሆን አለበት። « እናንተና መንፈሴም ከጌታችን ከኢየሱስ
ክርስቶስ ኃይል ጋር ተሰብስበን» በዚህ ዘመን ያለውን
በውግዘት ዙሪያ የሚከናወነው፥ ተመሳሳይነቱ ከፖለቲካ
አደባባዮች ጋር ነው። አንደኛ ከብሮ የሚታየው ክርስቶስ
ሳይሆን የሰዎች የተንኮለኛነት ችሎታ ነው። ለምሳሌ
ባለፉት ሃያ አምስት አመታት በኢትዮጵያ ያሉት አባቶች
በአመት ሁለት ጊዜ ሲሰበሰቡ፥ ከስብሰባቸው በፊት፥
የተቃውሞ ሰልፍ፥ የክስ ደብዳቤዎች፥ ዘመቻዎች፥
ይካሄድባቸዋል። ወደስብሰባው የሚሄዱ አባቶች
ስብሰባው ከመጀመሩ በፊት ተወጋዡ ማን
እንደሚሆን፥ውሳኔው ምን መሆን እንዳለበት ተነግሮአቸውና
ተጽእኖ ተደርጎባቸው ነው የሚገቡት። ነገሮችን ከምንም
ነገር ነጻ በሆነ መንገድ ለማየት የሚሞክሩ አባቶች፥
በስድብ በስም ማጥፋት ጥላሸት ይቀባባቸዋል። በዚህ
ምክንያት አንዳንዶች ዝምታን ሲመርጡ አንዳንዶች
ለተጽእኖው ያጎበድዳሉ። ቅዱስ ጳውሎስ « ከኢየሱስ
ክርስቶስ ኃይል ጋር ተሰብስበን» ሲል « ብርታታችንና
ጉልበታችን የሚሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ይሆናል» ማለቱ
ነው። እውነት የምትነግሠውና ሐሰት ሥፍራን የምታጣው፥
በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ኃይልና በመንፈስ ቅዱስ
መሪነት ስንጓዝ ነውና።
ቅዱስ ጳውሎስ ሌላ ታላቅ ነገር ያነሣል። ይኸውም
ውግዘት ምን ያህል አስፈሪ ነገር እንደሆነ የሚያመለክት
ነው። አንድ ሰው ከእድር ቢለይ፥ ሌላ እድር ውስጥ
ይገባል። ወይም በዘመናዊው ዓለም ሌላ ዘዴ ሊጠቀም
ይችላል። ( ላይፍ ኢንሹራንስ ሊገባ ይችላል።)ፋንታ
( ክፍል አንድ ) # በቀሲስ መላኩ
መግቢያ
ባለፉት ሃያዎቹ ዓመታት፥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ
ቤተ ክርስቲያን በታሪኳ አይታ የማታውቃቸው ሦስት አበይት
ክስተቶች ታይተውባታል። የመጀመሪያው አንደኛው፥ ከፍተኛ
የሆነ የሕዝብ ፍልሰት ነው። በአዲስ አበባ ያሉት አባቶች
በግልጥ ያስቀመጡት ይፋዊ አኀዙ ሰባት ሚሊየን ይባል
እንጂ፥ ከአስር እስከ አስራ አምስት ሚሊየን የሚሆኑ የቤተ
ክርስቲያኒቱ አባላት ቤተ ክርስቲያኒቱን ትተው ወደ ሌሎች
ቤተ እምነቶችና ተቋሞች ሄደዋል። ሁለተኛው ዓቢይ
ክስተት ቤተ ክርስቲያኒቱ ለሦስት መከፈሏ ነው።
የመንግሥት ለውጥን ተከትሎ አራተኛው ፓትርያክ ብፁዕ
ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ከመንበራቸው ከተሰደዱበት
ጊዜ ጀምሮ ቤተ ክርስቲያኒቱ በስደት ያለው ቅዱስ
ሲኖዶስ፥ በአገር ቤት ያለው ቅዱስ ሲኖዶስ እና ገለለተኛ
በሚል ተከፍላለች። ሦስተኛው እና ቤተ ክርስቲያኒቱ
በታሪኳ አይታው በማታውቀው መንገድ የተከሰቱ ነገሮች
ቢኖሩ በተለይ አዲስ አበባ ባሉት አባቶች ዘንድ፥ «
ውግዘት» እንደ ታላቅ መሣሪያ መያዙ ነው።
በዚህ በያዝነው በ፳፩ኛው ክፍለ ዘመን ሰዎች ተቀራርበው
አሳባቸውን በሚካፈሉበት ዘመን፥ አብያተ ክርስቲያናት
ያለፈ ውግዘታቸውን በይቅርታና በመግባባት አስተካከለው፥
አንድ በሚያደርጋቸው ነገር ላይ ለመነጋገር እየጣሩ ነው።
በቅርቡ የሮም ፖፕና የእስክንድርያው ፓትርያርክ አንዳቸው
የአንዳቸውን ምእመን ዳግም እንዳያጠምቁ
መፈራረማቸው ይታወቃል። ሆኖም ግን ባለፉት 25
ዓመታት ውስጥ በአዲስ አበባ ባሉት አባቶች አማካይነት፥
የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በሺዎች የሚቆጠሩ
ምዕመናኖቿን እና አገልጋዮቿን አውግዛለች። ከአንድ
ቢሊየን አባላት በላይ ያላት የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን
ባለፉት አንድ መቶ አመታት ያወገዘቻቸውና በአዲስ አበባ
ያሉት አባቶች ያወገዙትን ስንመለከት በቍጥር የእኛው
በልጦ እናገኛለን። በአንድ በኩል የምዕመናኑ በሚሊየኖች
ወደ ሌሎች የእምነት ተቋማት መሄድ በሌላ በኵል ደግሞ
ጳጳሳትን ሳይቀር ምእመናንን ጨምሮ በመቶ ሺዎች
የሚቆጠሩ ምእመናንን ማውገዝ ከየት መጣ ለምንድነው
ይህ ክስተት በእኛ ዘመን የተደጋገመው? ከዚህ ውግዘት
በስተጀርባ ያሉት እነማን ናቸው? ተጠቃሚዎቹስ እነማን
ናቸው የሚለውን ለመመለስ በመጀመሪያ ስለውግዘት
በሚገባ ማወቅ ይኖርብናል።
ሀ. ውግዘት ምንድነው?
ውግዘት ቃሉ፥ ወገዘ ከሚለው ግሥ እንደሚገኝ እና
ፍቺውም መገዘት መለየት መካድ መርገም ማለት እንደሆነ
የሊቁ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ
ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ ይናገራል። ከዚህ ከቃሉ አንጻር
በምንመለከትበት ጊዜ፥ ቃሉ የሚያመለክተን ከዚህ በፊት
ከአንድ አካል ጋር አንድነት (communion) የነበረውን
እንዲለይ (excommuncate) ማድረግ ነው። ይህን
ግልጥ ለማድረግ ቃሉ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በእንዴት
ያለ መንገድ እንደተቀመጠ በማየት ትርጉሙን
እንመለከታለን።
1.ውግዘት እርግማን ነው።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለገላትያ ሰዎች ሲጽፍላቸው
«ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ፥
ከሰበክንላችሁ ወንጌል የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ፥
የተረገመ ይሁን። አስቀድመን እንዳልን እንዲሁ አሁን
ሁለተኛ እላለሁ፥ ከተቀበላችሁት የተለየውን ማንም
ቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን።» ይላቸዋል። ( ገላ ፩፥፰-
፱) ግእዙም « አትሙሰ መልአክ እምሰማይ ለእመ
መሀረክሙ ካልአ እምዘ መሀርናክሙ ውጉዘ ለይኩን።
በከመ እቤ ቀዳሚ ወይእዜኒ ካዕበ እብል ለእመቦ
ዘመሀረክሙ እምዘመሀርናክሙ ውጉዘ ለይኩን።»
አስተውሉ አማርኛው « የተረገመ ይሁን የሚለውን ግእዙ
የተወገዘ ይሁን ይለዋል። ይህ ውግዘት ወይም እርግማን
ምን ማለት እንደሆነ እንመልከት፥ አዲስ ኪዳን
ለመጀመሪያ ጊዜ የተጻፈበትን የግሪኩን ቃል
በምንመለከትበት ጊዜ፥ የተወገዘ ይሁን አናቴማ ኤስቶ
(ἀνάθεμα ἔστω ) ይለዋል። አናቴማ ቃሉ በብሉይ
ኪዳን « እርም»፥ «ለእሳት የተሰጠ» ማለት ነው። ለምሳሌ
ኢያሱ በኢያሪኮ የተገኘው ሁሉ እርም እንዲሆን ሲያዝ
አካን የተባለው ሰው « እርም ከሆነው ነገር ወሰደ»
ይለናል። ኢያሱ7፥1። እንዲህ ዓይነት ብዙ ጥቅሶች
በብሉይ ኪዳን እናገኛለን። በአዲስ ኪዳንም ይህንኑ ቃል
ሳይስት፥ አናቴማ ( ውግዘት እርግማን) ማለት
በእግዚአብሔር ፍርድ ውስጥ መውደቅ ማለት ነው።
ቅዱስ ጳውሎስ በዚህ በገላያ መልእክቱ ላይ በሐዋርያት
ከተሰበከው የጸጋ ወንጌል የተለየ ወንጌልን የሚሰብክ
በዚህ የእግዚአብሔር ፍርድ ውስጥ እንደሚወድቅ ሲናገር
እናያለን።
2. ውግዘት ለሰይጣን አልፎ መሰጠት ነው።
አሁንም ወደ ቅዱስ ጳውሎስ መልእክት ስንመጣ
በ1ቆሮ5፥5 ላይ «መንፈሱ በጌታ በኢየሱስ ቀን ትድን
ዘንድ እንደዚህ ያለው ለሥጋው ጥፋት ለሰይጣን
እንዲሰጥ ፍርዴ ነው።» ሲል እናገኛለን። ቅዱስ ጳውሎስ
በዚህ ስፍራ ሐዋርያዊ ውግዘቱን ያሳረፈበት ሰው፥ በሥነ
ምግባር ውድቀት ውስጥ የተገኘ ማለትም የአባቱን ሚስት
ያገባ ሰው ነው። ሐዋርያው ለቆሮንቶስ ክርስቲያኖች
ሲናገር «ይህን ሥራ የሠራው ከመካከላችሁ ይወገድ። እኔ
ምንም እንኳ በሥጋ ከእናንተ ጋር ባልሆን፥ በመንፈስ
ከእናንተ ጋር ነኝ፥ ከእናንተም ጋር እንዳለሁ ሆኜ ይህን
እንደዚህ በሠራው ላይ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም
አሁን ፈርጄበታለሁ፤ እናንተና መንፈሴም ከጌታችን
ከኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል ጋር ተሰብስበን፥ መንፈሱ በጌታ
በኢየሱስ ቀን ትድን ዘንድ እንደዚህ ያለው ለሥጋው ጥፋት
ለሰይጣን እንዲሰጥ ፍርዴ ነው።» ይላል።
ይህ የቅዱስ ጳውሎስ ቃል ስለ ውግዘት ሦስት ዋና ዋና
ነገሮችን ያሳየናል። አንደኛ፥ ይህ ነገር በጉባኤ በጥንቃቄ
የሚታይ ነው። ጉባኤው የክርስቶስ ጌትነት የከበረበት
ጉባኤ መሆን አለበት። የሐዋርያው ሥልጣን የከበረበት
መሆን አለበት። « እናንተና መንፈሴም ከጌታችን ከኢየሱስ
ክርስቶስ ኃይል ጋር ተሰብስበን» በዚህ ዘመን ያለውን
በውግዘት ዙሪያ የሚከናወነው፥ ተመሳሳይነቱ ከፖለቲካ
አደባባዮች ጋር ነው። አንደኛ ከብሮ የሚታየው ክርስቶስ
ሳይሆን የሰዎች የተንኮለኛነት ችሎታ ነው። ለምሳሌ
ባለፉት ሃያ አምስት አመታት በኢትዮጵያ ያሉት አባቶች
በአመት ሁለት ጊዜ ሲሰበሰቡ፥ ከስብሰባቸው በፊት፥
የተቃውሞ ሰልፍ፥ የክስ ደብዳቤዎች፥ ዘመቻዎች፥
ይካሄድባቸዋል። ወደስብሰባው የሚሄዱ አባቶች
ስብሰባው ከመጀመሩ በፊት ተወጋዡ ማን
እንደሚሆን፥ውሳኔው ምን መሆን እንዳለበት ተነግሮአቸውና
ተጽእኖ ተደርጎባቸው ነው የሚገቡት። ነገሮችን ከምንም
ነገር ነጻ በሆነ መንገድ ለማየት የሚሞክሩ አባቶች፥
በስድብ በስም ማጥፋት ጥላሸት ይቀባባቸዋል። በዚህ
ምክንያት አንዳንዶች ዝምታን ሲመርጡ አንዳንዶች
ለተጽእኖው ያጎበድዳሉ። ቅዱስ ጳውሎስ « ከኢየሱስ
ክርስቶስ ኃይል ጋር ተሰብስበን» ሲል « ብርታታችንና
ጉልበታችን የሚሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ይሆናል» ማለቱ
ነው። እውነት የምትነግሠውና ሐሰት ሥፍራን የምታጣው፥
በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ኃይልና በመንፈስ ቅዱስ
መሪነት ስንጓዝ ነውና።
ቅዱስ ጳውሎስ ሌላ ታላቅ ነገር ያነሣል። ይኸውም
ውግዘት ምን ያህል አስፈሪ ነገር እንደሆነ የሚያመለክት
ነው። አንድ ሰው ከእድር ቢለይ፥ ሌላ እድር ውስጥ
ይገባል። ወይም በዘመናዊው ዓለም ሌላ ዘዴ ሊጠቀም
ይችላል። ( ላይፍ ኢንሹራንስ ሊገባ ይችላል።)

Saturday, April 29, 2017

"ወደ አምላኬና ወደ አምላካችሁ" የብርሃኑ አድማሴ የቃላት ዝላይ

የአለት ላይ ዝላይ አያዋጣም!

"ወደ አምላኬና ወደ አምላካቸሁ"
ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በስብከቶች እየተፈራ የሚዘለል የእግዚአብሔር ቃል
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++
ሰሞኑን በየቤተክርስቲያኑ ዐውደ ምሕረት የሚነገረው ወንጌል ስለ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ ቢሆንም የማቅ ሰባክያነ ወንጌል ተብዬ እንደነ ተስፋዬ ሞሲሳ (ተስፋዬ ስለቃሉ ሞዛዛ) እና ብርሃኑ አድማሴ (ብርሃኑ ቃሉን ደርምሴ) እየዘበራረቁም ቢሆን ተያይዘውታል።
የእግዚአብሔርን ቃል እየቀነሱ እና እየዘለሉ ማስተማር ምን የሚሉት ፈሊጥ ነው?
ጌታ ኢየሱስ ከሙታን መካከል ከተነሳ በኋላ በዮሐ 20፥17 ማርያምን አትንኪኝ አላረኩምና ነገር ግን ወደ ወንድሞቼ ሄደሽ፦ እኔ ወደ አባቴና ወደ አባታችሁ ወደ አምላኬና ወደ አምላካችሁ አርጋለሁ ብለሽ
ንገሪአቸው እንዳላት በግልፅ ተፅፎ ሳለ እነዚህ የማቅ አቀንቃ  የክርስቶስ ሰው መሆኑ እንዳበቃ አርገው ወደ አምላኬና ወደ አምላካችሁ የሚለውን እየዘለሉ በድፍረት መናገራቸው ያሳዝናል።
ሰው በመሆኑ መከራን ተቀበለ እንጂ ለዘላለም ስጋን ተዋህዶ ይኖራል ብሎ እንደተናገረው ቅዱስ አትናቴዎስ። ሞትን ድል ነስቶ በአብ ቀኝ የተቀመጠው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዛሬም ለዘላለም የማይለወጥ ፍፁም ሰው: ፍፁም አምላክ ነው (ሃይማኖት አበው 1986 ገፅ 80/ ዕብ 13፥8)
ክርስቶስ በአብ ቀኝ ከተቀመጠ በኋላ የሰውነቱን ግብር አቁሞ ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር መለኮታዊ ስራውን እየሰራ ይገኛል ብሎ መስብኩ የክርስቶስን መካከለኛነት መቃወም ብቻ ሳይሆን ይኼ አባባል ኢየሱስ በአባቱ ቀኝ እስኪቀመጥ ድረስ መለኮት ስራውን ለስጋ ትቶ ስጋ ብቻ ይሰራ ነበር። አሁን በተራው ሰራውን ስለፈፀመ ስራውን ለመለኮት አስረከበ እንደማለት ነው። ይህ አባባል ደግሞ ሲያረግ ሥጋውን በመለኮት ባህርይ አረቀቀው: መጠጠው የሚለውን የአውጣኪን የክህደትአስተምህሮ መቀበል ይሆናል። ዳሩ ይኄ ስብከት በብዙዎቹ ሰባኪያን ዘንድ ሲነገር ይሰማል። መለኮታዊ ሥልጣኑን በመጠበቅ ሲባል በሥጋ ማረጉን በርቀት ይከላከላሉ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በኦፊሴል አውጣኪን ብታወግዝም አስተምህሮውን በስልት ትቀበላለች። የምሥራቅ አብያተ ክርስቲያናት አውጣኪያውያን ናችሁ የሚሏትም አለምክንያት አይደለም። የኢየሱስን እርገት የኢት/ኦር/ ቤተክርስቲያን የምትቀበለው በመለኮታዊ ባህርይ ብቻ እንጂ ዛሬም በሥጋው በአብ ቀኝ እንዳለ አይደለም ማለት ነው? በሥጋው አርጓል የምትል ከሆነም በሥጋው የማረጉን ምክንያት በድፍረት ልታስተምር ይገባታል። ከኃጢአት ለመንጻትም ሆነ ሕይወት ወደሆነው ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነት አዲስ አማኝ ለመምጣት በስጋው ቀራንዮ ላይ አንዴ በፈፀመው ድኅነት ስለእኛ አሁንም በሰማይ በአብ ይታይ ዘንድ በስጋው አለ ልትል ይገባታል። መለኮት ቃሉ ብቻ ማዳን እየተቻለው ሥጋ የለበሰው በሥጋ ያጣነውን ክብር በልጁ በኩል ልጅነትን እንድናገኝና በሰማያዊ መቅደስ የመግባት ድፍረት እንድናገኝ ስለፈለገ ብቻ ነው።
ይህንንም ሐዋርያው እንደዚህ አስረግጦ ይነግረናል።

" ክርስቶስ በእጅ ወደ ተሰራች፥ የእውነተኛይቱ ምሳሌ ወደ ምትሆን ቅድስት አልገባምና፥ ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ስለ እኛ አሁን ይታይ ዘንድ ወደ እርስዋ ወደ ሰማይ ገባ።"
(ዕብራውያን 9:24)
ከዚህ ውጪ የሆነው ሁሉ ፍፁም ሰው ፍፁም አምላክ መሆኑን የሚያስክድ ነው።
ኢየሱስ የመጣበትን በእያንዳንዳችን ፈንታ በመስቀል ላይ የማዳንን ስራ ፈፅሞ ሞቶ ከተነሳ በኋላ አምላኬ ማለቱ የማቅን ሰባኪያን አባባል ገደል ከቶታል።
ለዚህም ሃይማኖት አበው 1986 ገፅ 248 እንዲህ ሲል ይመሰክራል
" እኔ ሰው የሆንኩ አምላክ ነኝና እኔም አንድ ነኝና ይህንንም ያንንም እኔ እላለው ይላል፣ የሰውን ባህሪይ ገንዘብ አድርጌአለውና። ኋጢአት የሌለበት እርሱ እኔ ነፍስን ስጋን ተዋህጃለውና ከእኔ ጋር አንድ ላደረኩት ለስጋ ስርዓት እንደሚገባ እንዲህ አባቴን "አምላኬ" ብዬ ጠራሁት "
እናም ተወዳጆች ሆይ ጌታ ኢየሱስ እንዴ ለዘላለም ባፈሰሰው ደስ ዳግም ማፍሰስ ሳይጠበቅበት ሁል ጊዜ ሲያነፃን ይኖራል። እግዚአብሔር እኛን የሚያይበትብቸኛው መንገድ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው።
"የልጁም የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከኃጢአት ሁሉ ያነጻናል።" 1ኛ ዩሐ 1፥7
ያለፍርሃት የጌታ ምስክሮች እንሁን እኔ ይህን ታዘብኩ እናንተም እስኪ የማቅን ሰባኪያንን የሚፈሩትንና የሚዘሉትን ቃል ንገሩንና ለመማማር እንወያይበት።
የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ፀጋ የእግዚአብሔርም ፍቅር የመንፈስ ቅዱስም ህብረት ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን

Wednesday, April 12, 2017

«አሮጌውን እርሾ አስወግዱ፤ ፋሲካችን ክርስቶስ ታርዶአልና»

Saturday, April 



(በድጋሚ የቀረበ)

ዕብራውያን     פֶּסַח «ፔሳኽ» ይሉታል። ፋሲካ ማለት ነው።  በወርኀ ኒሳን በዐሥራ ዐምስተኛው ቀን ይከበራል። ሥርዓቱ የሚጀመረው በዐሥራ አራተኛው ቀን ዋዜማ ሲሆን በፋሲካው ሳምንት እርሾ የገባበት ምንም ዓይነት ምግብ መመገብ ክልክል ነው።ዕለቱን ተቦክቶ ወዲያው የሚጋገር እንጂ የኮመጠጠ ወይም የቦካና የዋለ፤ያደረ መመገብ በሕጉ እንደተቀመጠው ከእስራኤል አንድነት ያስወግዳል። ከማንኛውም እርድ ላይ ጥሬ መብላት ወይም ከበሉትም አስተርፎ ማሳደር አይፈቀድም። ለመስዋዕት የሚቀርበው የበግ ወይም የፍየል መስዋዕትም እድሜው ከአንድ ዓመት ያልበለጠ ጤናማና የተመረጠ መሆን ይገባዋል። በዐሥራ ዐራተኛው ቀን ምሽት መስዋዕቱ ይታረዳል።ሥጋውን ደግሞ ሌሊት  ከመራራ ቅጠል ጋር ቀላልቅለው ይበሉታል። 
ደሙን ደግሞ  የበሩን ሁለት ረድፍ «መቃንና ጉበኑን» ይቀቡታል።  ሁለቱን ቋሚ መቃንና የላይኛውን ጉበን ሲቀቡት ይህንን ቅርጽ ይይዛል።


ይህ ቅርጽ የዕብራውያን ስምንተኛውን ፊደል «ኼ» የተባለውን ይወክላል። (እንደአማርኛው በጉሮሮ ሳይሆን በላንቃ የሚነበብ ነው) «ኼ» ማለት በዕብራውያን ትርጉም «ሕይወት» ማለት ነው። ዕብራውያንም በፊደላቸው በ«ኼ» ቅርጽ በሚቀቡት ደም የተነሳ ወደፈርዖናውያን ሠፈር የሚያልፈው ሞት አይነካቸውም። ምክንያቱም ሕይወት የሚል ማኅተም በራቸው ጉበንና መቃን ላይ ታትሟልና። ፋሲካ ማለት ይህ ነው። በደሙ ምልክት የተከለሉ በሕይወት ለመቆየት ዋስትና የያዙ ሲሆን ይህንን ማኅተም ያላገኙና ምን እየሆነ እንዳለ የማያውቁ ደግሞ  በሞት የሚወሰዱበት  የፍርድ ምልክት ነው። ደሙ የሞትና የሕይወት መለያ ምልክት ሆኖ አገልግሏል።
ይህ ሥርዓት እስራኤላውያንን ከባርነት፤ ከጠላት አገዛዝና ከመገደል የታደገ የዋስትና መንገድ ነበር። እንደዚሁ ሁሉ የአዲስ ኪዳኑ ፋሲካ ሕዝብና አሕዛብን ከሰይጣን ባርነትና ከዘላለም ሞት የታደገ በመሆኑ ሐዋርያው ጳውሎስ «እንግዲህ ያለ እርሾ እንዳላችሁ አዲሱን ሊጥ ትሆኑ ዘንድ አሮጌውን እርሾ አስወግዱ። ፋሲካችን ክርስቶስ ታርዶአልና» 1ኛ ቆሮ 5፤7 በማለት የሚነግረን።  አሮጌውን እርሾ ካላስወገድን ፋሲካችን የሆነውን ክርስቶስ መቀበል አይቻልም። የክርስቶስን ፋሲካ እካፈላለሁ በማለት የበዓሉን አከባበር ማድመቅ፤ እንኳን አደረሰህ/አደረሰሽ መባባል ልምድ እንጂ የመለወጥ ምልክት አይደለም። የክፋት እርሾ የተባሉትን ሐዋርያው ጳውሎስ በቆሮንቶስ መልእክቱ ሲነግረን እንዲህ ይለናል። «ሴሰኛ፤ ገንዘብን የሚመኝ፤ ወይም ጣዖትን የሚያመልክ፤ ወይም ተሳዳቢ ወይም ሰካር ወይም ነጣቂ» ከመሆን መታቀብ ብቻ ሳይሆን ከሆኑትም ጋር አብሮ ባለመብላት ጭምር በመከልከል ከአሮጌው እርሾ ሆምጣጣነት መራቅ እንዲገባን ያስፈልጋል። (1ኛ ቆሮ 5፤11) የእስራኤል ዘሥጋ ፋሲካ መጻጻና የቦካ ይከለክል እንደነበረው ሁሉ የአዲስ ኪዳኑ ፋሲካም እንዲሁ ይከለክላል። በኃጢአትና በዐመጻ የቦካ የውስጣችንን ሆምጣጣ እርሾ ካላስወገድን በስተቀር በፋሲካው የሚገኘውን ሕይወት በፍጹም  አናገኝም።  የቀደመው ፋሲካ እርሾ ያለውን ነገር ከቤቱ ያላጠፋ «ከእስራኤል ጉባዔ ተለይቶ ይጥፋ» የሚል ሕግ ነበረው።  ምድራዊው ፋሲካ ይህንን ያህል ከከበረ ሰማያዊውማ እንደምን የበለጠ አይከብር? ፋሲካን መናገርና ፋሲካን አውቆ መኖር የተለያዩ ነገሮች ናቸው። ስለፋሲካ ብዙ ማስተማርና መናገር ይቻል ይሆናል። ስለፋሲካ የመልካም ጊዜ መግለጫና ስጦታም መለዋወጥ ይቻል ይሆናል። ፋሲካን ማክበር ማለት 2 ወራት በጾም አሳልፎ «እንኳን ጾመ ልጓሙን ፈታልህ/ፈታልሽ» ተብሎ ልጓም አልቦ የመሆኛ ሰዓት ደረሰ በማለት የሰላምታ መሰጣጣት ፕሮግራም አይደለም። ጾሙ ሲፈታ እንደፈለገን ልንበላ፤ ልንጠጣ፤ ልንናገር የልጓም አጥራችን ተከፈተ ማለት ከሆነ በአሮጌው እርሾ ብቻ ሳይሆን ከሰው የልማድ ስርዓት ጋር እንኖራለን ማለት ነው። የክርስቶስ ፋሲካ ግን በእነዚህ ሁኔታዎች ውስጥ አይገኝም። ፋሲካ በስግደትና በወይራ ቅጠል በመጠብጠብ የሚገኝም ጸጋ አይደለም።  ፋሲካ የአንድ ወቅት ራስን ማስገዛትና በጽኑ እሳቤና ጭንቅ ማለፍ ውስጥ የሚመጣም አይደለም።
ፋሲካ በልባችን መቃንና ጉበን ላይ የደሙን ምልክት በመያዝ ዕብራውያን ከሞት እንዳመለጡበት የ «ኼ» ምልክት ማኅተም በመያዝ ብቻ ነው የምንድነው። ያን ጊዜ ብቻ ነው ሞት በራችን ላይ ያለውን የአዲስ ኪዳኑን «ፔሳኽ» አይቶ የሚያልፈው። ይህንን የደም ማኅተም ለመያዝም ከክፋት፤ ከሀሰት፤ ከግፍና ከዐመጻ እርሾ መለየት የግድ ነው። ከዝሙት፤ ከስርቆት፤ ከጉቦ፤ ከምኞትና ከኃጢአት ሁሉ እርሾ ሳንለይ ውስጣችን የሞላውን መጻጻ ተሸክመን የፋሲካ ሕይወት የለም። እስራኤላውያን መዳን የቻሉት የፋሲካቸውን የበግ ደም ምልክት በመያዛቸው ብቻ ነው።  እኛም የአዲስ ኪዳኑ የእግዚአብሔር በግ የክርስቶስን ደም ምልክት ካልያዝን በማንም በሌላ ምልክት ወይም ጻድቅ ዋስትና ልንድን አንችልም። ሁሉም ይህንን የደም ምልክት የመያዝ ግዴታ ስላለበት ማንም ለማንም ዋስትና ሊሆን እንደማይችል ጳውሎስም «ልዩነት የለም፤ ሁሉም የመዳን ጸጋ ያስፈልገዋል» አለን። 

«እርሱም፥ ለሚያምኑ ሁሉ የሆነ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የሚገኘው የእግዚአብሔር ጽድቅ ነው፤ ልዩነት የለምና፤ ሁሉ ኃጢአትን ሠርተዋልና የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሎአቸዋል፤በኢየሱስ ክርስቶስም በሆነው ቤዛነት በኩል እንዲያው በጸጋው ይጸድቃሉ» ሮሜ 3፤22-24
እንግዲህ  ከፋሲካው ተስፋ የምናደርግ ሁላችን እስኪ ራሳችንን እንመርምር። እንደመጽሐፍ ሊያነበን በሚቻለው ከፋሲካችን ክርስቶስ ፊት እስኪ ራሳችንን እናንብበው። በእውነት እነዚህ እርሾዎች በውስጣችን ከሌሉ ከ2000 ዓመት በፊት ለሕይወት የፈሰሰውን ደም ይዘናል ማለት ነው። ያኔም ሞት በኛ ላይ ምንም ሥልጣን እንደሌለው አረጋግጠናል። እስራኤላውያን የበራቸውን ጉበንና መቃን በቀቡ ጊዜ ሞት እንደማይነካቸው እርግጠኞች እንደነበሩ ሁሉ እኛም የበለጠውንና የተሻለውን የሕይወት ደም በእምነት ስለያዝን ለዘላለማዊ ሕይወት እርግጠኞች መሆን እንችላለን። ከዚያ ባሻገር በየዓመቱ በሚመጣ በዓል የሚገኝ የደም ምልክት የለም። በጥብጠባና በስግደትም የሚገኝ የሕይወት ዋስትና እንዳለ ካሰብን የፋሲካውን ምስጢር በልምድ ሽፋን ስተነዋል ማለት ነው። የተደረገልንን ማሰብ አንድ ነገር ሆኖ ሰው ግን ዓይኑን በዚያ በዓል ላይ ተክሎ የዓመቱ ኃጢአት ወይም ሸክም እንደሚወድቅ ማሰብ ስህተት ነው። ዓመቱን ሙሉ ከክፋትና ከግፍ እርሾ በመላቀቅ፤ ለአንድም ሰከንድ የማይለይ ምልክት ልባችን ጉበንና መቃን ላይ ደሙን በእምነት ይዘን መገኘት የግድ ይሆንብናል። ያኔ ነው ፋሲካችን ታርዷል የምንለው። ያኔም ነው ሁልጊዜ በሕይወት መንገድ ላይ እንዳለን የምናውቀው። መንፈሳዊ ሕይወት እንዲኖረን፤ መንፈሳዊ ጉዞ እንዲሰምርልን ዕለት፤ ዕለት መታደስ መታደስ ይገባዋል።
«ስለዚህም አንታክትም፥ ነገር ግን የውጭው ሰውነታችን ቢጠፋ እንኳ የውስጡ ሰውነታችን ዕለት ዕለት ይታደሳል» 2ኛ ቆሮ 4፤16 ንስሐ እንግባና እንታደስ።
ፋሲካችን የሆነው ክርስቶስ ኢየሱስ ያደረገልንን ውለታ እያሰብን ውስጣችንን መፈተሽ የግድ ነው። በአምናው እኛነታችንና በዘንድሮው እኛነታችን መካከል የሕይወት ለውጥ ከሌለን ሞት በመጣ ጊዜ ምንም የመዳን ምልክት እንደሌላቸው ፈርዖናውያንን ወደዘላለማዊ ሞት መሄዳችን እውነት ነው። በወይራ በመጠብጠብ 30 እና 40 ለመስገድ ከመሽቀዳደም ይልቅ፤ ከሞት የማምለጫ የፋሲካው ዓርማ ክርስቶስን ከኃጢአት በጸዳ ማንነታችን ውስጥ ዘወትር ይዘነው እንኑር። ዝሙት፤ ውሸት፤ስርቆት፤ ሃሜት፤ ነቀፋ፤ ምኞትና ገንዘብን መውደድ ሁሉ ሳንተው ፋሲካን ማክበር አይቻልም። ከቦታ ቦታ በመዞርም ፋሲካ አይገኝም። ፋሲካ በልባችን ላይ አንዴ የተሰራው የክርስቶስ የእምነታችን ከተማ ነው። በዚያ ላይ የማይጠፋ ብርሃን አለ። ክርስቶስ ባለበት በዚያ የልባችን ከተማ ውስጥ ማስተዋል፤ ደግነት፤ በጎነትና ቅንነት አለ። ከዚያ መልካም ከተማ የሚወጣው ሃሳባችን የተራቡትን ያበላል፤ የታረዙትን ያለብሳል፤ የታመሙትን ይጠይቃል። ኑሮአችን፤ አነጋገራችንና አካሄዳችን በልክ ነው። ዕለት ዕለት በምንኖረው ሕይወት እንጂ በዓመት አንድ ቀን በሚከበር ፋሲካ ክርስቶስን መምሰል አይቻልም። ሞት የደሙ ምልክት የሌለባቸውን እስራኤላውያንን ሁሉ ይገድል ነበርና። እኛም በሰማይ የተሰጠንን ተስፋ እስክናገኝ ድረስ ሞት ከተጠበቀልን ተስፋችን እንዳያስቀረን ፋሲካችን ክርስቶስን ዕለት ዕለት በልባችን ይዘን እንኖራለን። ያኔም በክርስቶስ ያለ ተስፋችን ምሉዕ ስለሆነ ስለመዳናችን አንጠራጠርም። አብርሃም ልጅ ሳይኖረው «ዘርህ ዓለሙን ይሞላል» ሲባል በእምነቱ ተስፋውን ተቀበለ። በክርስቶስ ትንሣዔ ያመንን እኛ ደግሞ እንደምንድን ካመን የተሰጠን የመዳን ተስፋ በሰማይ እውነት ሆኖ ይጠብቀናል።  ምክንያቱም የመዳናችን የእምነት ተስፋ ክርስቶስን በልባችን ዕለት ዕለት ይዘን እንዞራለንና!!