Saturday, January 26, 2013

አባ ሕዝቅኤል ለምን ስብሰባ ረግጠው ወጡ?

ዘመነ ካሣ
             ከጀርመን
የማንም አሿሿሚ አልሆንም የሥልጣን ጥመኞችን አላገለግልምበማለት አራት ወራት የቀረውን የሲኖዶስ ዋና ጸሐፊነታቸውን የሚለቁ መሆናቸውን በደብዳቤ ገለጡ እየተባለ ሰሞኑን የሚወራላቸው አባ ሕዝቅኤል  ቀደም ሲልም ስብሰባ ረግጠው ቢወጡ የፈረሰው ቀኖና ይመለስ ብለው እንዳልሆነ መታወቅ አለበት።
አባ ሕዝቅኤልና በአዲስ አበባ የሚገኙት የሲኖዶስ አባለት ለእርቅና ለሰላም እንዲሁም ለሀያ ዓመታት የዘለቀውን የቤተ ክርስቲያን መለያየት ወደ አንድነት ለማምጣት በቅንነት እና ግልጽ በሆነ መንገድ ቢጓዙ ኖሮ ለዚህ ለከፋ መከፋፈል እንዲሁም ለመንግሥት ጣልቃ ገብነት ባልተዳረጉ ነበር ይልቁንም አባ ሕዝቅኤል  የመንግሥት ጣልቃ ገብነት አለ መባሉ ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለው እንደሆነና ቅዱስ ሲኖዶስ ለምርጫ የሚያስፈልጉ ደንቦችን ከማውጣት በቀር መንግሥት ጣልቃ አልገባም በማለት በአደባባይ ተናግረው ጸሐይ የሞቀውን እውነት የካዱ አባት ናቸው አቡነ ገብርኤልም ይሕንኑ ሀቅ ክደው በአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ በሰጡት ቃል የአባ ሕዝቅኤልን ውሸት ደግመውታል።
ይልቁንም አባሕዝቅኤል በአፋቸው ስለ እርቅና ሰላም እያወሩ እሳቸውና መሰሎቻቸው  ከእኛም ወገን ይድረሰን ከሚሉት ግብረ አበሮቻቸው የሚፈልጉትን ፓትርያርክ ለማስመረጥ የሚሄዱበት መስመር እየተዘጋ በመንግሥት የሚደገፉት የነ አባ ሣሙኤል ክንድ እየበረታ ሲሄድ  ማንንም አሿሿሚ አይደለሁም፤ የሥልጣን ጥመኞችን አላገለግልም ማለቱ እና  አራት ወር የቀረውን የጸሀፊነት ሥልጣን እለቃለሁ ማለቱ ምክንያታዊነቱ  ፈጽሞ አይታይም።

Thursday, January 24, 2013

“አንድ ጌታ፣ አንድ ሃይማኖት፣ አንድ ጥምቀት” ማለት ምን ማለት ነው?

የእግዚአብሔር መንግሥት የምትወረሰው አንዱን ጌታ በማመንና የእምነት አዋጅ የሆነውን «አንዲት ጥምቀት» በመጠመቅ እንደሆነ ቅዱስ ወንጌል ያስተምረናል። ይሁን እንጂ ዓለምን ደግሞ ዛሬ ላይ ሆነን ስንመለከታት ብዙ ጌቶች፤ ብዙ ቤተ እምነቶችና ብዙ ጥምቀቶችን እያስተናገደች ትገኛለች። ይኼው የዓለሙ አንድ ዘርፍ የእምነት እንቅስቃሴ በኢትዮጵያችን ውስጥም የሚታይ ሲሆን የየራሳቸው ጌታ ያላቸው፤ በየራሳቸው ጥምቀት የሚያምኑ፤ ልዩ ልዩ ሃይማኖቶች መኖራቸው እርግጥ ነው። ከዚህ አንጻር ከእኔ በቀር «አንድ ጌታ፤ አንድ ሃይማኖት፤ አንድ ጥምቀት» በማለት በአደባባይ ለማወጅ የመናገር መብቱና ብቸኛ ውክልና  ያለው ሃይማኖት ኢትዮጵያ ውስጥ የለም ማለት ነው።  ምክንያቱም የሚያምነውን  እምነት በማይቀበሉ ሰዎች መካከል እኔ ነኝ እውነተኛው ብሎ ቢያውጅ አንድም ሌሎቹን ለማስቆጣት ወይም እነሱንም ለተመሳሳይ እንቅስቃሴ እንዲነሳሱ ከሚያደርግ በስተቀር የትክክለኛ እምነት ባለቤት መሆኑን በየትኛውም መልኩ አያረጋግጥምና ነው። «ጸብ ያለሽ በዳቦ ካልሆነ በስተቀር» ይህ ጥበብ ያለው የስብከት ዘዴም አይደለም። በአንድ የሙስሊም በዓል ላይ ታላላቆቹ የአላህ ነብያት መሐመድ፤ ዒሳ/ኢየሱስ/ እና ሙሴ (ሰዐወ) ናቸው የሚል ጽሁፍ ያለበት ቀይ ካናቴራ ሙስሊም ወጣቶች ለብሰው አይቻለሁ። ይህ እንግዲህ «ኢየሱስ ከነብይም በላይ አምላክ ነው» ለሚሉ አማኞች ስድብ  መሆኑ ነው።   በግሉ የሚያምንበትንና የራሱ ቤተ እምነት የሆነውን ዒሳ/ኢየሱስ/  ነብይ መሆኑን ካመነ በካናቴራ ላይ ጽፎ አደባባይ መውጣቱ ምን ለማምጣት ነው? ብለን እንድንጠይቅ ያደርገናል። «ይህንን የማትቀበሉ ካላችሁ ጸብ ይዛችሁ ኑልኝ!» ብሎ ሁከት መጋበዝ ካልሆነ በስተቀር ምንም ፋይዳ የለውም።

 በሌላ በኩልም በአሁን ዘመን ታቦት ስለመኖሩ የማይቀበል  ቤተ እምነት እንዳለ እርግጥ ነው። ይኼው ቤተ እምነት በተራው « የዘመኑ ታቦት ጣዖት ነው» ብሎ ቢጽፍና ይህንኑ ይዞ አደባባይ ቢወጣ ያለምንም ጥርጥር አንዲት እርምጃ ሳይሄድ ወይ ይገደላል፤ አለያም ደሙ ይፈሳል እንጂ የሚያምንበትን በመጻፉ መብቱ ነው ብሎ የሚቀበለው ሰው አደባባይ ላይ አይገኝም።

ብዙ ኦሮሞዎች የኢሬቻን በዓል ያከብራሉ፤ ወንጌል አምናለሁ ለሚል ለሌላ ሰው ግን ኢሬቻን ለማክበር ዛፍ ስር መስገድና መስዋእት ማቅረብ ጣዖት ከማምለክ ጋር ሊያያዝ ይችላል። ይህንን የኢሬቻ አክባሪዎችን ስሜት የሚያስቆጣ ጽሁፍ በማንጠልጠል አደባባይ መውጣት ለነገር ካልሆነ በስተቀር የትኛውንም ነገር የሚያንጽና በማስተማር ሌላውን ለመለወጥ የሚሰጠው ፋይዳ አይኖርም። በተመሳሳይ መልኩ እነማኅበረ ቅዱሳንና ጎጋ ደጋፊዎቹ፤ መናፍቃን የሚሏቸውን ክፍሎች ለመሳደብ/ አስተምሮ ለመመለስ አይደለም/ በአንድ ወቅት «ያለድንግል ማርያም አማላጅነት ዓለም አይድንም» እና በሌላ ጊዜም «አንዲት ጥምቀት፤ አንዲት ሃይማኖት» የሚል ሸሚዝ ለብሰው በአደባባይ ሲንጎራደዱ ታይተው ነበር። ይኼው ድርጊት ዛሬም መቀጠሉ እየተነገረ ነው። የሌላውን ስስ ስሜት ለመኮርኮርና አምንበታለሁ የሚሉትን ጽኑ አቋም በአደባባይ በማንጸባረቅ እንደተቃዋሚ የሚቆጥሩትን ክፍል ልብ ለማቁሰል ካልሆነ በስተቀር ኢ-አማኝ የሆነውን ማንንም ሊለውጥ የሚችል ድርጊት አይደለም። ዋናው ነጥብ ለአደባባይ ጽሁፍ የሚመረጡት ጥቅሶችና ጽሁፎች በቤተ እምነቱ ውስጥ ካለው አጠቃላይ አቋም ውስጥ የሌላኛውን ወገን እምነት የሚመለከትና ስሜቱን ሰቅዞ በመያዝ ጠጣር መልእክት የሚያስተላልፈውን መምረጡ የራሱ የሆነ ዓላማና ግብ እንዳለው ለማወቅ አስቸጋሪ አይደለም። ያንን ጥቅስ ይዞ አደባባይ መገኘት ያስፈለገው የእምነቱ ተከታዮች ስለተሰወረባቸው ለመግለጽ ነው ወይስ የእምነቱ ተከታዮች ላልሆኑ ለሌሎች ክፍሎች ብትወዱም ብትጠሉም እኔ እንደዚህ እላለሁ ብሎ ለመንገር? የሚል ጥያቄን ያስከትላልና ነው።


ወንጌል ማስተማር፤ ያላመኑትን ማሳመንና የእኔ እውነት ትክክል ነው ወደሚሉት እምነት ሌላውን ለመቀየር ጥበብ የሚያስፈልገው አገልግሎት መሆኑ እሙን ነው። ወንጌልን መስበክ እንደባለ አእምሮ እንጂ በመታበይ ወይም ማን እንደእኔ በሚል ትምክህት ሊሆን አይችልምና። በዚህች ዓለም የስብከት ጥበብ ሳይሆን  እንደባለ አእምሮ መንፈሳዊ ብስለትና ሌላውን ደስ አሰኝቶ ሊለውጥ በሚችል መታደስ እንጂ በትእቢት አስተሳሰብ የሚደረግ ስብከት ከጥቅሙ ጉዳቱ ያመዝናል። ወንጌልም አበክሮ የሚነግረን ይህንኑ ነው።

«እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ ሰውነታችሁን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝና ሕያው ቅዱስም መሥዋዕት አድርጋችሁ ታቀርቡ ዘንድ በእግዚአብሔር ርኅራኄ እለምናችኋለሁ፥ እርሱም ለአእምሮ የሚመች አገልግሎታችሁ ነው። የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ።እግዚአብሔር ለእያንዳንዱ የእምነትን መጠን እንዳካፈለው፥ እንደ ባለ አእምሮ እንዲያስብ እንጂ ማሰብ ከሚገባው አልፎ በትዕቢት እንዳያስብ በመካከላችሁ ላለው ለእያንዳንዱ በተሰጠኝ ጸጋ እናገራለሁ» ሮሜ 12፤1-3


ከዚህ ተነስተን በሰሞኑ የጥምቀት በዓል ላይ «አንድ ጌታ፤ አንድ ጥምቀት፤ አንዲት ሃይማኖት» የሚለውን ጥቅስ የለበሱ የጥምቀት ተመላሾች ማኅበር ወጣቶች ማንንም ሰብከው ሳይለውጡ /በእለቱ በዚህ ጥቅስ የተለወጡ አዲስ አማኞች ስለመኖራቸው አልሰማንም/ ወጣቶቹ የመታሰራቸው ዜና ተሰምቷል። ይህንን ተከትሎ የተለያዩ የድረ ገጽ ሚዲያዎች ዜናውን አስተጋብተዋል። በእርግጥ ጥቅሱ የወንጌል ቃል ነው። ቃሉም እውነት ነው። ነገር ግን ይህንን ጥቅስ ለብሰው አደባባይ የዋሉት ወጣቶች ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው «አንድ ሃይማኖት ብቻ» መሆኑን ለማሳወቅ ወይስ ሌሎች ሃይማኖቶችን ለመስበክ? ብለን እንድንጠይቅ ያደርገናል። ነገሩ በዓለ ጥምቀትን አስታኮ እውነተኛይቱ ሃይማኖት የእኔ ስለሆነ ሌሎቻችሁ ዋጋ የላችሁም ለማለት ካልሆነ በስተቀር እንደ ወንጌል አስተምህሮና እንደ ባለአእምሮ የተለወጠ ሰው፤ ሌላውን ደስ በማሰኘት ወደእውነት እንዲመጣ በመርዳት ለሌላው የሚተርፍ አንዳችም ጥቅም ያለው  አካሄድ አልነበረም። ይልቁንም ሌላው ወገን የራሱን አጸፋዊ ጥቅስ በመልስ ምት ይዞ እንዲመጣ የሚያደፋፍረው ይሆናል። ሌላው የሚያምንበት የራሱ እውነት ለእኔ ውሸት እንደሆነው ሁሉ፤ እኔም የማምንበት እውነት ለእርሱ ውሸት ስለሚሆን የኔን ትክክል ብዬ የማምንበትን እውነት ለማስተላለፍ የምጠቀምበት መንገድ ሌላውን የሚያርቅ ሳይሆን በመረጃና ማስረጃ  የማሳምንበት ሊሆን ይገባል።ምክንያቱም ሃይማኖት የሰዎችን ስሜትና አእምሮ የመቆጣጠር ትልቅ ኃይል ያለው ስለሆነ ማንም ለማስተማር ሲፈልግ ጥበብና ስልት ያለውን መንገድ መከተሉ የግድ ነው።

ሐዋርያው ጳውሎስ በአቴና ከተማ አርዮስፋጎስ አደባባይ ላይ ከድንጋይ በተሰራና «የማይታወቅ አምላክ » የሚል ጽሁፍ ለሰፈረበት ጣዖቱ አምላኪ ሕዝብ ያስተላለፈው የትምህርት መንገድ ትልቅ ግንዛቤ ይሰጠናል። በስብከቱ መነሻ የማይታወቀውን አምላክ፤ ይህ ድንጋይ ነው ብሎ ክብሩን አዋርዶ አልጀመረም። እናንተ ጣዖት አምላኪ ሕዝቦች ወዮላቸሁ ብሎ በማስፈራራትና ጆሮአቸውን ጭው በሚያደርግ ቃል አላስበረገገም። ይልቁንም እንዲህ በማለት ለድርጊታቸው ግምት ሰጥቶ እያዋዛ ወደሚፈልገው ጎዳና መራቸው እንጂ!

Wednesday, January 23, 2013

የውጪው ሲኖዶስ ድርድሩን ቅድሚያ ከመንግሥት ጋር ቢያደርግ ሳይሻል አይቀርም!

ከከፈለኝ ምስጋናው

 የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በዘመንዋ ሁሉ ከነበሩ መንግሥታት ጋር እጅና ጓንት ሆና መቆየትዋ እውነት ነው። ከነገሥታቷና ከሹማምንቷ ጋር መሆንዋ በአንድ በኩል ጠቅሟታል። ይኸውም በፈለገችበት የሀገሪቱ አድማስ እንድትስፋፋ፤ በኢኮኖሚ አቅሟ እንድትደላደል፤ ተሰሚነት ያለው ድምጽ እንዲኖራት አግዟታል። በተቃራኒው ደግሞ ከመንግሥታት ጋር ተጠግታ መኖርዋ ራሷን ችላ እንዳትተዳደር፤ ሉዓላዊ የሆነ ሥልጣን እንዳይኖራትና ጉዳይዋን ባላት አቅም እንዳትፈታ በግልጽም፤ በቀጥታም ሲቆጣጠሯት መቆየታቸው አሁን ለደረሰችበት ፖለቲካንና ሃይማኖትን የማቀላቀል ዘመን ላይ እንድትደርስ አድርጓታል። ነገሥታቱ ሌላው ቀርቶ የአድባራትና የገዳማት አለቆችን እስከመሰየም ድረስ ግልጽ ሥልጣን እንደነበራቸው ታሪክ ይነግረናል። እስከ ደርግ መውደቅ ድረስ የጠቅላይ ቤተክህነቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ የሚሾምላት በቤተ መንግሥቱ ነበር። በዘመነ አፄ ኃ/ሥላሴ መነኮሳቱ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት አባል ሆነው በማገልገል በሕዝባቸው ላይ የገባር ሥርዓት እንዲቀጥል ታማኝ አባል በመሆን የነገሥታቱ ባለሟልም ነበሩ።  

  በዚህም ይሁን በዚያ ከመንግሥታቱ ጋር መጣበቅዋ መልካም ገጽታዎችና አሉታዊ መልኮችም አብረዋት እንዲኖር ማድረጉም እውነት ነው።
ይህንኑ ተከትሎ 4ኛው ፓትርያርክ አባ መርቆሬዎስም እንደቀደመው ታሪክ ሁሉ በደርግ መንግሥት ድጋፍና ተቀባይነት ነበራቸው።  ደርግን የሚጠላ ደግሞ እርሳቸውን ቢጠላ አይደንቅም። መደገፍ እንዳለ መቃወምም ሰውኛ ጠባይ ነውና። ገለልተኛ መሆን በማይቻላቸው የቤተክርስቲያን መሪዎች የተነሳ  አንዱ ሄዶ አንዱ ሲመጣ መንግሥታት እንደምትመቻቸው ለማድረግ በመድከም ቁጥጥራቸው ለቤተክህነቷ ቅርብ ነው።  ከዚህም የተነሳ ለደርግ የነበራቸውን አቋም በመመልከትና በእሳቸው ላይ የነበረውን ጥላቻ በራሱ መንገድ ለመፍታት በመፈለግ  ከደርግ ውድቀት በኋላ ወደ ሥልጣን የመጣው የኢህአዴግ መንግሥት እንደቀደሙት መንግሥታት በቤተክርስቲያኒቱ ጉዳይ ላይ እጁን ማስገባቱ አልቀረም።  እውነት እውነቱን ስንነጋገር፤ የአባ መርቆሬዎስን ከሥልጣን መልቀቅ ይፈልግ የነበረው ተረኛው መንግሥት ብቻ ሳይሆን የመንበረ ፓትርያርኩ ብዙዎቹ ኃላፊዎችና ሊቃነ ጳጳሳቱም ጭምር እንደነበር በወቅቱ ከስልጣን የማባረር ተሳታፊዎችን ዘመቻና ግርግር ያስተዋለ አይዘነጋውም። 
  መንግሥትም ሆነ አባ መርቆሬዎስን ለመጣል ጊዜው አሁን ነው ባዮች የዘመቻው አባላት መጻኢውን የቤተክርስቲያን መከፋፈል ከግምት ውስጥ ባለማስገባታቸው የፈጸሙት ስህተት እስከአሁን ላለው ልዩነት ዳርጓል። ቤተክርስቲያን ነጻነቷን ሳታስደፍር እንዳትኖር መሪዎቿ ከመንግሥታት እየተለጠፉ ከመኖራቸው የተነሳ ደርግ መራሹ ቤተክህነት ወደኢህአዴግ መራሽ ተለውጧል። ለዚህ ድጋፍ ሥልጣን ናፋቂ አባላቶችዋ ከፍተኛ ድርሻ አላቸው።
በእርግጥ ቤተክህነት ውስጥ የተሰገሰገው እውነተኛ አማኝ ብቻ አይደለም።  በቆብና በቀሚስ ስር የተሸሸገ አደገኛ ፖለቲከኛም በመኖሩ መንግሥታት በሌላኛው  ዓይናቸውን ቤተክርስቲያኒቱን ቢከታተሏት ሊደንቀን አይገባም። በዘመነ ደርግ የፓርቲው አባላት ቤተክህነቱ ውስጥ ሥልጣን ሲኖራቸው ሌሎቹ ቀን እስኪያልፍ ሳይወዱ እየሳቁ ቀኑን ማሳለፋቸው አይዘነጋም።  የቤተክርስቲያኒቱ መለያየት ለሃይማኖታዊ ፖለቲከኞችም ሆነ ለግልጽ ፖለቲከኞች መሸሸጊያ  ዋሻ በመሆንዋ መንግሥታት በፖለቲካዊ ፍርሃት የተነሳ እጃቸውን እንዲያስገቡ በመደፋፈር ትንፋሿን ይቆጣጠራሉ።  የእግዚአብሔርን መንግሥት ብቻ የሚያገልግሉ ብቻ ሳይሆን የፖለቲካ መንግሥትንም አጣምረው የሚያገለግሉ ሞልተውባታል። ቤተክህነት ለሁለት ጌቶች ከተገዛች ደግሞ አንዱንም ማጣትዋ የግድ ነው። የሃይማኖተኛ ሰው ፖለቲካው ሃይማኖቱ ብቻ መሆን ነበረበት። ዛሬ የሚታየው ሃይማኖተኛ ግን ፖለቲካዊ ሃይማኖተኛ እንጂ ሃይማኖተኛ አማኝ አይደለም። 

"ከፍሬአቸው ታውቁአቸዋላችሁ"

(በጮራ ቊጥር 5 ላይ የቀረበና ከድረ ገጹ የተወሰደ)
ምሁር ነኝ የሚሉ አረጋዊ ከሰዎች ጋር ሲነጋገሩ፥የእኛን ሃይማኖት የሚያህል ፈጽሞ የለምብለው የማውራት ልምድ ተጠናውቷቸዋል፡፡ እንዲህም ሲናገሩ ስመ ሃይማኖታቸውን እየጠሩ ነው፡፡ ቅያሬ የሌለውና የተጋነነው ከቃል ንግግር በቀር የሕይወት ምስክርነት ያልነበረው ወሬአቸው ወዳጆቻቸውንና ቤተ ሰባቸውን ጭምር አሰልችቷቸው ኖሮአል፡፡
አንድ ቀን ከአንድ ወዳጃቸው ጋር ይጨዋወቱ ነበር፡፡ እንደ ተለመደውየእኛን ሃይማኖት የሚያህል የለም፤ ብቻ ምን ያደርጋልሲሉ፤ በተከታዮች ብዛት ከሆነ እምነት ተከታዮች ይባልጣሉኮ! አለና መለሰላቸው፡፡ ትልቋ ልጃቸው ግንአባባ የእኛ ሃይማኖት ካለማመን የሚለይበትን አንድ ነጥብ ቢነግሩኝብትላቸው ምን ለማለት እንደ ፈለገች አልተረዱላትም፡፡ ልጅቷ የመደነጋገር ምልክት በአባቷ ፊት ላይ እንዳየች በሌላ የአገላለጽ ዘዬ ልታስረዳቸው ሞከረች፡፡ አባቷም ሲረዱ በጣም ተቈጡ፡፡
የአረጋዊው ምሁር አስተሳሰብ እምነታችን ጥሩ ነው፤ የእምነታችን ፍሬ ግን መራራ ነው፤ ወይም እምነታችን ፍሬ አልባ (መካን) ነው እንደ ማለት ነው፡፡ ሊሆን ግን አይችልም፡፡ አንድ ሰው ወይም ቡድን የተቀበለውና የሚመራበት የክርስትና እምነት ሕያው ከሆነ የቃል ምስክር ሳያስፈልገው ጣፋጭ ፍሬ አንዠርግጎ ይታያል፡፡

Saturday, January 19, 2013

እንኳን ለ1975ኛው ዓመት በዓለ ጥምቀት በሰላም አደረሳችሁ!




ውሃ ለሥጋችን ሕይወት ነው። ከዚያም በላይ የፍሳችንን መዳኛ የሆነው የኢየሱስ ክርስቶስን ሞት የምናዘክርበት ትልቅ ተስፋችን ነው። ውሃ በዘመነ ኖኅ የኃጢአት በትር ሆኖ የሰው ልጆችን የቀጣ ቢሆንም ነገሮችን አዲስ ማድረግ የባህሪው የሆነው እግዚአብሔር ውሃን በልጁ  ሞት ሞተን ፤ በኃይል ስለመነሳታችን  የምስክርነት ተስፋ አድርጎ ሰጥቶናል።
ውሃ የሞት መሣሪያ በሆነበት ዘመን «ለቀደመውም ዓለም ሳይራራ ከሌሎች ሰባት ጋር ጽድቅን የሚሰብከውን ኖኅን አድኖ በኃጢአተኞች ዓለም ላይ የጥፋትን ውኃ ካወረደ» 2ኛ ጴጥ 2፤5  ካጠፋቸው በኋላ በዘመነ ሐዲስ ደግሞ የትንሣዔው ኅብረት ምልክት ሆኖ፤«በጥምቀትም ከእርሱ ጋር ተቀብራችሁ፥ በጥምቀት ደግሞ፥ ከሙታን ባስነሣው በእግዚአብሔር አሠራር በማመናችሁ፥ ከእርሱ ጋር ተነሣችሁ» ቆላ 2፤12 በማለት  በትንሣዔው  ያለንን አንድነት ነግሮናል።
እንደዚሁ ሁሉ በክርስቶስ ያመኑቱ ሁሉ ሊያደርጉት የሚገባና የሕያውነት ምስክርነታቸውን የሚሰጡበት የጥምቀት ዝክረ በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከከተራው ጀምሮ የጌታ ጥምቀት ተፈጽሞበታል ተብሎ እስከሚታሰበው እለት ድረስ ብዙ ሺህ ሕዝብ በተገኘበት፤ የውጪ ቱሪስቶች ለጉብኝት በሚገኙበት ሥርዓት ጥር 11/2005 ዓ/ም በጃንሜዳና በየአድባራቱ ተከብሮ እንደሚውል ይታወቃል።  በአዲስ አበባ ጃንሜዳ የተከናውነውን ሥነ ሥርዓት  ከፊል ምሥል አቅርበናል።

Friday, January 18, 2013

የአሜሪካው ሲኖዶስ መግለጫ አወጣ!


በ4ኛው ፓትርያርክ አቡነ መርቆሬዎስ የሚመራው የአሜሪካው ሲኖዶስ ጠንከር ያለና መሠረታዊ የልዩነት ነጥቦችን የሚያመላክት መግለጫ አውጥቷል። የሀገር ቤቱ ሲኖዶስ ሕጋዊ እንዳልሆነና ሕጋዊ ሊባል የሚቻለው በአቡነ መርቆሬዎስ የሚመራው ሲኖዶስ እንደሆነ ሕገ ቤተክርስቲያንን አጣቅሶ ያቀረበ ሲሆን ከመንበር ላይ በመሰደድ ቅዱስነታቸው በቤተክርስቲያን ታሪክ የመጀመሪያ እንዳልሆኑ በማመልከት ሁሉም ስደቶች የአባቶች ጥንካሬና የምእመናን ብርታት አሰዳጆችን እምቢ በማለት አንድነትና ኅብረትን ያሳየ ሆኖ ከማለፉ በስተቀር ለመኳንንቱ ፍላጎት ይሁንታን በመስጠት ኅብረታቸውን በታትነው እንደዚህ እንደዛሬው አለመታየታቸውን በመግለጽ  መግለጫው ሰፊ ሀተታ አቅርቧል።
ወደ 6ኛ ፓትርያርክ ምርጫ ለመግባት ጥቂት የሥልጣን ጥመኞች ጳጳሳት መንግሥትን ተገን አድርገው ያቀናበሩት እንደሆኑ በማመልከት በቤተክርስቲያናችን ታሪክ  ሌላኛውን ስህተት ለመፈጸም በመቋመጥ  ወደምርጫ የመሄድ አድራጎቱን በውግዘት ኮንኖታል።
 ከአባ ሰላማ ብሎግ ላይ ያገኘነውን ሙሉውን መግለጫ ለማንበብ እዚህ ላይ( Click here )

Wednesday, January 16, 2013

ሰበር ዜና፤ ቅዱስ ሲኖዶስ ስድስተኛውን ፓትርያርክ ለመምረጥ ውሳኔ አሳለፈ

ጥር 8/2005 ዓ/ም  ምሽት ላይ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ባስተላለፈው ዜና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ከጥር 6 ጀምሮ ባደረገው ስብሰባ ማጠቃለያ ላይ በሰጠው መግለጫ 6ኛውን ፓትርያርክ ለመምረጥ ውሳኔ ማስተላለፉን ገልጿል።


ዜና ዘገባው አያይዞ እንደገለጸው በአሜሪካ ካሉ አባቶች ጋር ሲደረግ የቆየው ድርድር ሁሉ ተቀባይነት ባለማግኘቱ ሲኖዶሱ በቀጥታ ወደምርጫ ለመግባት የተገደደ መሆኑን በመጠቆም፤ ነገር ግን የአሜሪካው ሲኖዶስ ወደእርቁ ተመልሶ አብሮ ለመሥራት ፈቃደኛ ከሆነ ለመቀበል ፈቃደኝነቱ እንዳለም አያይዞ አስረድቷል።
  ይህም ቀደም ሲል ሲነገር እንደቆየው አቡነ መርቆሬዎስ በፈለጉት ቦታ በጡረታ ከሚቀመጡ በቀር 5ኛ ፓትርያርክ ስንል ቆይተን፤ ቁልቁል ተመልሰን 4ኛ ፓትርያርክ በማለት የራሳችንን ሥራ የምናፈርስበት ምክንያት የለም የሚለውን ሃሳብ በደንብ ያንጸባረቀና ግልጽ ያደረገ መግለጫ ነበር። በሞት የተለዩትን ፓትርያርክ ሕገ ወጥ ናቸው በማለት የውጪው ሲኖዶስ ሲሞግት የቆየበትን ጥያቄ ተቀብሎ 4ኛውን ፓትርያርክ ወደመንበር መመለስ ማለት በ5ኛው ፓትርያርክ የተሰሩትና የተሾሙትን ጳጳሳትም በሕገ ወጥ ስልጣን የተገኘ ሹመት በማሰኘት ጥያቄ ውስጥ የሚከትና ወይም እንደገና ሊታደስ ይገባዋል የሚልን መንፈስ የሚያስነሳ ስለሆነ ከወዲሁ ስለአራተኛ ፓትርያርክ መመለስ ጉዳይ የሚነሳውን ፋይል ዘግተን ወደ 6ኛው ተሸጋግረናል በማለት እቅጩን የተናገረ ዘገባ ይመስላል። ይህም በፓትርያርኩ በራሳቸው አንደበት በቀጥታ  ባይሰማም በእነ አቡነ መልከ ጼዴቅ ይነሳ የነበረው የ4ኛው ፓትርያርክ ወደሥልጣን የመመለስ የእርቅ ክርክር እዚሁ ላይ ያቆማል ማለት ነው። 
የሀገር ቤቱን ሲኖዶስ እንደብቸኛ ሲኖዶስ በመቀበል፤ የውጪው ሲኖዶስ ከሀገር ቤቱ ጋር ለመቀላቀል ዝግጁ ይሆን? ያ ካልሆነ የእርቁ ፋይል እዚህ ላይ ይዘጋል!  ሁሉም ወገን ሥልጣን አይቅርብኝ የሚል ፈላጊ ስለነበር አንድ መሆን አልተቻለም። ሥልጣን የማያስጎመጅ አማራጭ ይኖር ይሆን?

«ሐራ» ነኝ ማለትህ ቅጥፈትይሆንብሃል!



የማኅበረ ቅዱሳን አባላት ሆነውና ያሉበትን ሥፍራ ተተግነው እንደልዩ የመረጃ ምንጭ መስለው ቅጥፈት የሚዘሩ ብሎጎች ብቅ ብቅ ማለታቸውን ስናይ ቆይተናል። ከእነዚህም አንዱ «እኔ የቤተክርስቲያን ወታደር ነኝ» በማለት ራሱን ያስተዋወቀው አንድ ብሎግ ወታደርነቱን እጠብቃታለሁ ለሚለው ቤተክርስቲያን ዓላማ ብቻ ማዋል ሲገባው ሲፈልግ ለግለሰቦች ጋሻና መከታነቱን የሚያሳይ፤ ዛሩ ሲነሳበት ደግሞ ጋሻ የሆነላቸውን ሰዎች ቆሌ በመግፈፍ ካርታው እንደጠፋበት ወታደር እዚህም፤ እዚያም የሚዳክር ሆኖ ይስተዋላል።
በእጃችን ያሉ መረጃዎችን መሠረት አድርገን፤ ነገር ግን መረጃዎቹን ትተን ጥቅል ችግሮቹን ብቻ ከዚህ በፊት ስለዝዋይ ገዳም አስነዋሪ ተግባራት በዘገብን ጊዜ ይህ ወታደር ነኝ ባዩ ብሎግ ሽንጡን ገትሮ ለሊቀጳጳሱ በመከራከር እንባ ቀረሽ ልቅሶውን በጽሁፍ ባስነበበን ጊዜ ወታደር ነኝ የሚለው ዲስኩሩን ትተን «የዓይጥ ምስክር ድንቢጥ» በማለት አልፈነው ነበር።
ይኸው የቤተክርስቲያን ወታደር ነኝ ባዩ ብሎግ ስለዝዋዩ ሊቀጳጳስ ጠበቃ መሆኑን በጽሁፉ ባሰፈረ ጊዜ በልማት፤ በማኅበራዊና በመንፈሳዊ  እድገት ትልቅ እመርታ ማሳየታቸውን ጠቅሶ ሊቀጳጳሱ ላይ የስም ማጥፋት እርምጃ ለመውሰድ የፈለጉ ወገኖች መነሻ ምክንያታቸው «የኦሮሞ ፓትርያርክ ለማሾም የሚራወጡ ቡድኖች ጠባብ አስተሳሰብ ያመጣው ችግር ነው»  በማለት ነጭ ውሸቱን በድጋፍ ዘመቻው በማከል ጠበቃነቱን ማሳየቱ አይዘነጋም። ጽሁፉን ያነበብን አንዳንድ ወገኖች  የኦሮሞ ፓትርያርክ ዝዋይ ላይ መሾም እንዴት እንደሚቻል አዲሱን ግኝት አያይዞ ባለማብራራቱ ግር ብንሰኝም እንደአስፈጋጊ ቀልድ እውነታውን ስለምናውቅ በወቅቱ አልፈነው ነበር። ይኼው ብሎግ ለሊቀጳጳሱ በወቅቱ ከሰጠው ምስክርነት ጥቂቱን ጠቅሰው ወደሌላው «በአንድ ራስ ሁለት ምላስ» ጽሁፉ እናመራለን።
«ሁለቱም አካላት በተለያዩ መንሥኤዎች የገዳሙንና የብፁዕነታቸውን ስም ለማጥፋት ይሞክሩ እንጂ በአንድ ጎራ ያሰለፋቸው ስጋት ተመሳሳይ እንደኾነ ምንጮቹ ጨምረው ያስረዳሉ፡፡ ይህም ስጋት ብፁዕነታቸው በቀድሞው ፓትርያሪክ እንደ እንደራሴም እንደ ተተኪም መታጨታቸውና ለዚህም ዓላማ ፓትርያሪኩ ከከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት ጋራ እንዳስተዋወቋቸው የሚነገርላቸው ብፁዕ አቡነ ጎርጎሬዎስ ስድስተኛው ፓትርያሪክ  ለመኾን በመንግሥት ታጭተዋል በሚል የመነገሩ ወሬ ነው»
ይህ ከላይ በቀይ የተቀመጠው ጽሁፍ የቤተክርስቲያን ወታደር ነኝ ባዩ ብሎግ የሊቀጳጳሱ ወታደር ሆኖ በወቅቱ የጽሁፍ ምስክርነቱን በመስጠት በብሎጉ ላይ ያሰፈረው ነበር። ይኼው ብሎግ  ከወራት በኋላ ማለትም ጥር 6/2005 ጀምሮ የተደረገውን የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባዔ ተከትሎ በሚወጡ ዘገባዎች ላይ የሊቀጳጳሱ ጫና እያየለና ተሰሚነታቸው እየተጠናከረ መምጣቱን ተከትሎ ወደ ፓትርያርክነት የሚያደርጉትን የእጩነት ጉዞ በማጥላላት ዘመቻ ውስጥ ገብቶ፤በመዘገብ ላይ መጠመዱ ነገሩን ሁሉ አስገራሚ ያደርገዋል። 

Saturday, January 12, 2013

ያቆመንና ሊያቆመን የሚቻለውን ትተን ማንን ስንይዝ መቆም ይቻለናል?

ብዙ መጠላላትና መነቃቀፍ ብዙ ቦታ ተሰጥቶት መገኘቱን በየእለት ውሎአችን እናያለን።  እውነት፤ እውነቱን መነጋገር ቢቻልም መነቃቀፍ በበዛበት ዓለም እውነቱን በእውነታ ለመቀበል የሚቸገርም ሞልቷል። የሚቀበል ቢኖርም፤ ባይኖርም እውነት ነው ብለን ያመንበትን መናገር እንዳለብን ስለምናምን መናገራችንን አናቋርጥም። ዛሬም በዚህ ጽሁፋችን የምናውቃቸውን እውነታዎች፤ አንዳንዱ እውነት ነው ብሎ እንደሚቀበልና የዚህ ተጻጻሪው ደግሞ ጥላሸት በመቀባት ልምዱ የቆመበትን ስፍራ በቃሉ እንደሚያሳየን በማሰብ ጥቂት ለመግለጽ  የምፈልጋቸው ነገሮች አሉን። ጽሁፋችንም በቤተክርስቲያናችን ዙሪያ ያጠነጥናል።

 የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የእምነት ዓምድ /ዶግማ/ ማለትም ምሥጢረ ሥላሴን አብርታ፤ አምልታና አስፋፍታ በማስተማር፤ እንዲሁም ከሦስቱ አካላት አንዱ አካል ሥጋ የለበሰበትን ረቂቅ ምሥጢር ፤ ምሥጢረ ሥጋዌውን አብራርታ በመስበኳ የታነጸችበትን ሃይማኖታዊ አለት/ ኰክሕ/ ስንመለከት በእውነትም የእግዚአብሔር ደጅ ናት ብንላት ቢያንሳት እንጂ አይበዛባትም። በክርስቶስ መሠረት ላይ የታነጸች፤ በሐዋርያት ትምህርት ያደገችና በሊቃውንቱ በእነአትናቴዎስ፤ ባስልዮስ፤ ጎርጎርዮስ ወዘተ የምሁራን አስተምህሮ የበለጸገች መሆኗን ማንም ሊክደው የማይችል የታሪክ እውነት ነው።

ዳሩ ግን ይህንን መሠረቷን የሚንዱ፤ ወንጌሏን ወደጎን የሚገፉ፤ አጋንንታዊ ልምምዶችን በስመ ሥሉስ ቅዱስ የሚያስፋፉ፣ ተከታዮቿ ዓይናቸውን ከክርስቶስ ላይ ነቅለው በየምናምኑ ላይ  እንዲተክሉ የሚያበረታቱ ብዙ አሳዛኝ መጻሕፍት በተረት፤ በእንቆቅልሽ፤ በወግና በአስማት ተሸፍነው የቤተክርስቲያኒቱን የወንጌል አስተምህሮ ማእድ በመበከል መርዛቸውን ታቅፋ እንድትኖር መገደዷን አስተዋዩ በደንብ ሲረዳው፤ እልከኛውም  በአፉ ለመመስከር ያቅተው እንደሆን እንጂ ችግር እንዳለ ልቡናው እንደሚመሰክርበት እናስባለን። 

ልበ ጠማሞች ደግሞ «በድሮ በሬ ያረሰ የለም» የሚለውን ብሂለ አበውን ከአፋቸው ሳያወርዱ ፤ በዚያው መራር አፋቸው ደግሞ በድሮ ስር ለመደበቅ «የቀደመውን ድንበር አታፍርስ»  ከማለታቸውም በላይ ከእኔ ወዲያ ለአባቶቼ ርስት ቀናዒ የለም! በሚል የኩራት ካባ በመደረብ የቤተክርስቲያኒቱን የወንጌል ማእድ የመረዙትን ህጸጾች መነካት የለባቸውም በማለት የግብር አባታቸውን ሥራ ተረክበው ሳያስተጓጉሉ  ለማስጠበቅ ሲታገሉ ኖረዋል፤እየታገሉም ይገኛሉ ። ደግሞ እናንተ እነማን ናችሁ? በማለት ለጥያቄዎች መልስ የመስጠት ብቃቱ ሳይኖራቸውና መልስ ይሰጡ ዘንድ ማንም ሳያስቀምጣቸው ራሳቸውን ሰይመው መገኘታቸውም የሚገርም ነው።