Thursday, February 28, 2013

የሰነበተ ዜና በሰበር፦ ብፁዕ አቡነ ማትያስ ፮ኛው ፓትርያርክ ሆኑ

ብፁዕ አቡነ ማትያስ በ500 ድምዕ

ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ98 ድምፅ
 ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል70 ድምፅ
 ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ98 ድምፅ
 ተመራጩ ፓትርያሪክ ብፁዕ አቡነ ማትያስ
 በዚህም መሠረት ብፁዕ አቡነ ማትያስ የካቲት 24 ቀን 2005 . በመንበረ ተክለ ሃይማኖት የሚሾሙ ስድስተኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያሪክ ይኾናሉ፡- ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያሪክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት !!!
 በዛሬው የመራጮች መዝገብ 808 መራጮች ተመዝግበዋል፡፡  806 መራጮች መርጠዋል፡፡
 15 ድምፆች ዋጋ አልባ ኾነዋል፡፡ አንድ ባዶ የድምፅ መስጫ ወረቀት ተገኝቷል፡፡
 ተመራጩ ፓትርያሪክ ብፁዕ አቡነ ማትያስ ንግግር አድርገዋል፡፡
 ለምርጫው በአጠቃላይ ብር 3,650,000 ወጪ መደረጉን የአስመራጭ ኮሚቴው ሰብሳቢ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ ተናግረዋል፡፡

Wednesday, February 27, 2013

ሞት በምልጃ፤ የበረሃ ጣዕር! ማስለቀቂያ ካልተከፈለ – ኩላሊት ለገበያ

www.goolgule.com
     የጽሁፍ ምንጭ፤ ጎልጉል የድረ ገጽ ጋዜጣ                                                                                

አቧራ ይጨሳል። ከዚያ ያፈኑትን ይዘው ይሰወራሉአስደንጋጩ ታሪክ ውስጥ ያለው ስዕላዊ ገለጻ ነው። አንድ ወቅት አዲስ አበባ የህጻናት ሌቦች ተበራክተው ነበር። በወቅቱ በርዳታ ስም ተመዝግበው የፈጣሪ ስም እየጠሩ ህጻናትን በመነገድ የከበሩ ወረበሎች በደንብ የተደራጁና የሚቀናቀናቸውን የማስወገድ አቅም ስለነበራቸውአቧራው ጨሰየሚል ስያሜ የኮድ ስም ተሰጥቷቸው ነበር። አሁንም አሉ።ህጻን እናሳድጋለንእያሉ በዘረጉት ሰንሰለት የህጻናትን ደም የሚጠጡአንቱየተባሉ ሰዎች!! የውጪ አገር ዜጎች ጭምርበሱዳን ሰዎችን በማፈን ሲና በረሃ የሚሰውሯቸው ራሻይዳዎች የተደራጁ ናቸው። ከአረብ ምድር የፈለሱ ናቸው የሚባልላቸው እነዚህ ጎሣዎች በሱዳንና በኤርትራ የሚገኙ ሲሆን በተለይ በኤርትራ ያሉቱ ከዘጠኙ ጎሣዎች መካከል የሚቆጠሩ ናቸው፡፡ አኗኗራቸው የዘላን በመሆኑ ከኤርትራ መንግሥት ቁጥጥር ውጪ እንደሆኑ ይነገርላቸዋል፡፡ እነዚህ ጎሣዎች እጅግ አሰቃቂ የሆነ የአፈናና የጭከና ድርጊት ሲፈጽሙ በወጉ ታጥቀውና ዘመናዊ ተሽከርካሪ በመያዝ ነው። የሚታፈነውን ሰው ከተቆጣጠሩ በኋላ አዋራ ይነሳል። የሚከንፉበት ተሽከርካሪ አሸዋውን ተርትሮት ሲወረወር የሚነሳው ጭስ ሲበተን እነሱ የሉም። ቀሪው ተግባርሚስትህን፣ ወንድምህን፣ እህትሽን፣ ዘመድሽን ለሚያርዱ የሰውነት ክፍል ሌቦች አሳልፈን ሳንሰጥ ዶላር ክፈል ወይም ክፈይየሚለው ድርድር ነው። ይህ ድራማ መሰል ንግድ ሲከናወን ተገደው ይሁን የንግዱ ተባባሪ በመሆን በውል በማይታወቅ ሁኔታ የድርድሩ አስተርጓሚ ሆነው የሚሰሩት ኤርትራዊያን እንደሆኑ ተሰምቷል። ኢትዮጵያዊያኖችም አሉበት ይባላል። ማንም ይስራው ማን ድርጊቱ አሰቃቂ መሆኑ ብዙዎችን አስለቅሷል። አስጨንቋል።
በደላሎች እስራኤል ለመግባት ጉዞ ከጀመሩት ወገኖች መካከል ስንቶቹ በሲና በረሃ ሟምተው እንደቀሩ መረጃ የለም። ከሱዳን ምድር ወጥተው ግብጽ በመሻገር ሲና በረሃ እንደ ከብት ተበልተው የሚጣሉት ወገኖች ስቃይ ለሰሚው ግራ ነው። ወገኖቻችን ላይ የሚደርሰው አሰቃቂ መከራ ከቀን ቀን እየተባባሰ ነው። አሰቃቂ ዜናዎች መስማት ለየእለቱ የሚያስፈልገን መሰረታዊ ጉዳይ እስኪመስል ተለመዷል። ይህ አሳሳቢ ጉዳይእስከመቼ በዚህ ይቀጥላልየሚለው የሁሉም ወገንዳር ቋሚዎችጥያቄ ነው።
ለጆሮ የሚሰለች ነው፣ እርዳታ መስጠት ታከተን፣ የሚል መልስ የሚሰጡ አጋጥመውኛል። ድርጊቱ ተደጋግሞ ለጆሮ የሚያሰለች ደረጃ እስኪደርስ እነዚህ ወገኖች የት ነበሩ? ቢያንስ ሌሎች ላይ ተመሳሳይ ችግር እንዳይደርስ ምን ሰሩ? በውጪ አገር ያለን ወገኖች የሚረዳውንና የማይረዳውን መለየት የተሳነን ይመስለኛልበማለት በሚኔሶታ የሚኖሩት / ሰብለ አስተያየታቸውንና ተማጽኗቸውን ያሰማሉ።
የካቲት 32005 (2/10/2013) የቪኦኤ አማርኛ ክፍለ ጊዜ ያሰማው እረፍት የሚነሳ ዜና እስካሁን አልተቋጨም። ሱዳን ሸገራብ በሚባለው ሰፊ የስደተኞች ጣቢያ ከባለቤታቸውና ከሁለት ልጆቻቸው ጋር ይኖሩ የነበሩ / ትዕግስት ገብሬ ጥር 22 ቀን 2005 ቤተ ክርስቲያን ለመሳለም ከቤታቸው ይወጣሉ። በካምፕ ውስጥ ከሚገኘው ቤታቸው ወጥተው በግምት ሰላሳ ሜትር ሳይርቁ ታፈኑ።

ቀልድ እንደ እውነት!

 ከጥበበ ሲራክ ዘጉንዳጉንዶ


ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ  ማ…………ቴዎስ        
                           
                            ………….ትያስ


ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም፤ ወእጨጌ ዘመንበረ ተ/ሃይማኖት መልካም የሥራ ጊዜ  እንዲሆንልዎ እንመኛለን።

ቀልደኞች እንደእውነት ሲያደርጉት ለእኛስ መልካም ምኞት አይከለከልም አይደል?