Wednesday, May 2, 2012

ባለጭድ

በጮራ ቊጥር 3 ላይ የቀረበ 
from chorra blogger

ለፈገግታ


ገበሬው ባለው አንድ በሬ ከሌሎችም አቀናጅቶ ማረሱ ከፍተኛ ችግር ይፈጥርበትና ያንን ሸጦ ሁለት መለስተኛ በሬዎችን መግዛት ይፈልጋል፡፡ በሬው ለዐይን ሞላ ብሎ ጥሩ ዋጋ እንዲያወጣለት በማሰብ ጭድ በገፍ ሲያበላው ይሰነብትና ለገበያ ያቀርበዋል፡፡ 

በሬውን ሊገዛ የመጣ ነጋዴም የበሬው አቋም ከሩቅ ይስበውና ጠጋ ብሎ ተዟዙሮ በደንብ ይመለከተዋል፤ በመጨረሻም ከወደ ሆዱ ጐሸም እያደረገ፤ «ባለ ጭድ ዋጋውስ?» ይለዋል በሽሙጥ፡፡ 

ነገሩ የገባው ገበሬም «ለጠንቋይ አይሸጥም» በማለት አጸፋውን መለሰለት ይባላል፡፡

ጴንጤናዊው ጲላጦስ



A Scientific approach to more Biblical mysteries
ከተሰኘውና  Robert W. Faid  ከተጻፈው መጽሐፍ የተወሰደ
                                         ......to read in PDF ( Click Here )
በጥንታዊት ሮም ዘመን በጣም የታወቀ ነገር ግን በመልካም ሥራው የማይታወቅ ንድ ይሁድ ገዢ ነበር፡፡ ይሄ ሰው ጴንጤናዊው ጲላጦስ ይባላል፡፡ በዚህ ገዢ ውሳኔ ነበር በኢየሱስ ላይ የስቅላት ፍርድ የተፈረደበት፡፡ ይህ ሰው በመጽሐፍ ቅዱስ የሚታወቀው የሱስ ፍርድ ጋር በተያያዘ ብቻ ነው፡፡ ለመሆኑ ጴንጤናዊው ጲላጦስ መጨረሻውስ ምን ነበር? ማን ነው? እንዴት የይሁዳ  ገዢ ሊሆን ቻለ?
ስለዚህ ክፉና ግልጽ ያልሆነ ታሪክ ስላለው ሰው ነገር ግን ለክርስትና እምነት ወሳኝ በሆነው የናዝሬቱ የኢየሱስ ስቅላት ዋንኛ ተሳታፊ ስለነበረው ሰው ጥቂት ነገር እንመልከት፡፡
ስለጴንጤናዊው ጲላጦስ ተጽፈው ከሚገኙ መረጃዎች በመጀመሪያ የምናገኘው ከወንጌል መጽሐፍት፣ ጆሲፈስ የተባለ Aይሁዳዊ የታሪክ ጸሐፊ በይሁዳ ስለነበረው ገዛዝ ከጻፈው ከፊሎ ጋር ከተገናኘው ሁኔታ ነው፡፡ ታኪተስ የተባለ ጸሐፊ ደግሞ Annals of Imperial Rome በተሰኘ ጽሑፉ ከክርስቶስ ስቅለት ጋር በተገናኘ ሁኔታ ስለዚህ ሰው ጽፏል፡፡ በቂሳሪያ ንድ የቄሳር ጢባሪዮስ የጴንጤናዊ ጲላጦስ ስም ተቀርጾበት የተቀበረ ጠፍጣፋ ድንጋይ ተገኝቷል፡፡ ተቀብሮ የተገኘው ጽሑፍ ያልተሟላና የሚያሳየው የሁለቱን ታዋቂ ስሞች ለዛውም ከስሞቹ ንዱን ስም የመጀመሪያውን ቆርጦ ነው፡፡ ሆኖም ግን ትክክለኛ የሆነና ጴንጤናዊው ጲላጦስ የይሁዳ ገዢ ንደሆነ የሚያስረዳ የሥነ ምድር ቁፋሮ /ርኪሎጂ/ ማስረጃ ነው፡፡ጴንጤናዊ የሚለው የቤተሰብ ስም ብዛኛው በመላው የመካከለኛው የሰሜን ጣሊያን ክፍለ ግዛት በየትኛውም የማህበረሰብ ደረጃ ላሉ ቤተሰብ የሚሰጥ መጠሪያ ነው፡፡ ከዛ ቤተሰብ የሆነ ሰው የሮም መንግስት ቆንሲል ሆኖ ከክርስቶስ ልደት በኋላ 17 . ስከ 37 . ድረስ ሠርቷል፡፡ ጲላጦስ የሚለው መጠሪያ ስም በጥንታዊት ሮም በጣም የሚያስገርምና ሰዎች ለመጠሪያነት ጅግ ጥቂት ሰዎች ብቻ የሚመርጡት ስም ነው፡፡ ትርጓሜውምበጦር የታጠቀንደ ማለት ነው፡፡ ጌታ ኢየየሱስ በመስቀል ላይ በዋለ ሰዓት ሞቱን ለማረጋገጥ ጎኑን በጦር በመወጋቱ ንዲሰቀል ያዘዘው ሰውና ድርጊቱ የተገናኘ ንደሆነ ማስተዋል ይቻላል፡፡ 

Tuesday, May 1, 2012

"የጥንቸል ውሃ ጥም"


በሰላማዊት አድማሱ  Selam.admassu@yahoo.com

 ከእለታት በአንዱ ቀን ዱር ገደሉን ቤታቸው ካደረጉት እንስሳቶች መካከል ትንሿ ጥንቸል ውሃ በእጅጉ ተጠማች፡፡ በማን አለብኝነት ያለስስት ጨረሯን የለቀቀችውን ጸሐይ ጥሟን ስላባሰችባት በኩርፊያ ቀና ብላ ተመለከተቻት፡፡ አጠገቧ ያለው ዙሪያዋን የከበበውም መሬት ከሰማዩ ጋር ያበረ ይመስል በእንፋሎቱ እግሯቿን ጠበሳቸው፡፡ ጥንቸሊት ተንሰፈሰፈች  . . ውሃ ጥሙ አንገበገባት  . . ከዚህ በላይ መታገስ አልቻለችም ፡፡ ያላትን አቅም ሁሉ አሰባስባ በአቅራቢያዋ ወደሚገኝ አንድ ጥልቅ ወንዝ አመራች፡፡ በዚያ በረሃ ውስጥ እያስገመገመ ከሚንዠቀዠቀው ወንዝ አጠገብ ደረሰች፡፡ ውሃውን በምላሷ እየዘገነች ወደ አፏ ከዚያም ወደ ጉሮሮዋ እየላከች ትጠጣ ጀመር፡፡ ጠጥታ  . . ጠጥታ  . . ጠጥታ ስታበቃ ካንገቷ ቀና በማለት ለጥማቷ እርካታ የቸራትን ሽንጠ ረዥም ወንዝ በምስጋና አይን አማተረችው፡፡ ከላይ እየተወረወረ ከሚመጣው ነጭ ፏፏቴ ጀምሮ በእሷ አጠገብ እስከሚያልፍ ድረስ ጠበብ ያለ ነበር፡፡ ከዚያ ትንሽ እንደተጓዘ ግን ሰፊውን ሜዳ ይዞ በጸጥታ ይጓዛል፡፡ አዎን  . . ሰፊ ነው!! . . በእሷ አቅም ለእይታዋ እስኪሰወር ከአድማስ ጥግ እስኪገባ ድረስ ሰፊ ነው፡፡ በጣም ሰፊ!፡፡ ትንሿ ጥንቸሊትም ለቃጠሎዋ ማብረጃ፤ለጥማቷ እርካታ የቸራትን ይህንን ትልቅ ወንዝ እያየች በትልቅነቱም እየተገረመች አንድ ነገር ተናገረች ‹‹ እኔ የቱንም ያህል  ውሃ ብጠማና ከዚህ ወንዝ ደጋግሜ እየተመላለስኩ የቻልኩትን ያህል በየጊዜው ብጠጣ ይህ ወንዝ አንዳችም ሊጎድልበት አይችልም ›› አለች፡፡ ስለዚህ ጥንቸሊትም ወንዙን ሁልጊዜ ለጥሟ እርካታ ውሃ ብትለምነው እንደማይነፍጋት ፤ለእሷ ቢሰጣት እንደማይጎድለበት አስባ ልቧ በኩራት ተሞላ፡፡ ለሁልጊዜውም ቢሆን የእሷ ችግር ከሱ አቅም በታች እንደሆነ አውቃ ተማመነችበት፡፡