Friday, April 27, 2012

የአቡነ ገብርኤል ቡድን አጉራ ዘለል ሰባክያንን በድጋሚ በመጋበዝ ከሲኖዶስ ውጪ መንቀሳቀሱን ቀጥሎበታል


 ዘሪሁን ሙላቱ እና ፋንቱ ወልዴ እንደተጋበዙ ውስጥ ዐዋቂ ምንጮቻችን ገልፀዋል።

"ማኅበረ ቅዱሳን" የሀዋሳ ንዑስ ማዕከል አስተባባሪነት በሀዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ስብከተ ወንጌል ክፍል ስም ከሚያዘያ 19 እስከ 21/ 2004 . እና ከግንቦት 3 እስከ 5/2004 . የሚቆዩ ሁለት ጉባዔያት በመዘጋጀት ላይ መሆናቸው ተሰማ፡፡
የአቡነ ገብርኤል ሀገረ ስብከት ከየካቲት 25 እስከ የካቲት 27/2004 በሕገ ወጥነት ያካሄደው ጉባዔ እንዳይካሄድ የካቲት 22 ቀን 2004 . በቁጥር 221/54/2004 በወጣ ደብዳቤ የዕግድ ደብዳቤ ቢታዘዝም፣ ትዕዛዙን ባለመቀበል፣ የኢትዮጵያ ሲኖዶስን ህልውና የማይቀበለውን መምህር ዘበነ ለማን፣ ዳንኤል ክብረትንና ምሕረተአብ አሰፋን በመጋበዝ ፍጹም ለማኅበረ ቅዱሳን የወገነ ድራማን ተጫውቷል፡፡
አሁንም፣ መምህር ዘበነ ለማን በድጋሚ በመጥራት፣ ፋንቱ ወልዴን ከአሜሪካ፣ ጎረምሳውን ዘሪሁን ሙላቱንና ዘማሪ ይልማ ኃይሉን በመጋበዝ ፍጹም የሆነውን ማኅበረ ቅዱሳናዊ ግዛት ለማስፋፋት ደፋ ቀና በመባል ላይ መሆኑ ታውቋል፡፡

Thursday, April 26, 2012

የጎንደር ደብረ ኀይል ወደብረ ጥበባት በዓታ ለማርያም የአቋቋም ምስክር ትምህርት ቤት ግንባታ ውል ተፈረመ፡፡


(ከደጀ ብርሃን) ጅምሩ ጥሩ ነበር። የሰበሰባችሁትን የቤተክርስቲያን ገንዘብ  ከማስወረሳችሁ በፊት ወይም  ስትነግዱብን ኖራችሁ የሚሉትን ድምጾች ለማፈንና ይህንን የመሰለ ትሩፋት እየሰራን ነው ለማለት ያደረጋችሁት ይመስላል። ባካፋ ዝቃችሁ እጣንና ጧፍ ከመበተን ያለፈ ቋሚ ስራ ስትሰሩ አልነበራችሁም። ይሁን እንጂ ገንዘባችንን ከቀበራችሁበት ስላወጣችሁና ምንም ይሁን ምንም እንጥፍጣፊው ስለደረሰን አመስግነናል።

በእንዳለ ደምስስ
Gedamate 3ማኅበረ ቅዱሳን በሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት የሚገኘውን የደብረ ኀይል ወደብረ ጥበባት በዓታ ለማርያም የአቋቋም ምስክር ትምህርት ቤትን በ4.6 ሚሊዮን ብር ለመገንባት ሚያዚያ 12 ቀን 2004 ዓ.ም. የግንባታ ውል ስምምነት ከአስማማው አያሌው ሕንጻ ሥራ ተቋራጭ ጋር ተፈራረመ፡፡ በማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ልማት ዋና ክፍል አስተባባሪነት የሚከናወነው ይኸው ፕሮጀክት ማኅበረ ቅዱሳንን በመወከል የማኅበሩ ዋና ጸሐፊ ዲ/ን ሙሉጌታ ኀ/ማርያምና የሕንፃ ሥራ ተቋራጩ ባለቤትና ሥራ አስኪያጅ አቶ አስማማው አያሌው አማካይነት የፊርማ መርሐ ግብሩ ተፈጽሟል፡፡
በማኅበረ ቅዱሳን ዋና ጽ/ቤት በተከናወነው የፊርማ መርሐ ግብር ላይ የማኅበሩ ዋና ጸሐፊ ዲ/ን ሙሉጌታ ኀ/ማርያም ባደረጉት ንግግር ‹‹ 4.6 ሚሊዮን ብር የሚፈጅ ፕሮጀክት ቀርጾ የአቋቋም ምስክር ትምህርት ቤት ለመገንባት ከዚህ በፊት አድርገነው አናውቅም፡፡ ይህ ትልቅ እድገት ነው፡፡ ምእመናንም ማኅበረ ቅዱሳንን ማመን የቻሉበት ነው፡፡ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ አውጥቶ ማኅበረ ቅዱሳን ይሥራው ለማለት መቻል ሙሉ ለሙሉ በማኅበሩ ላይ እምነት እንዳሳደሩ ነው የሚያሳየው፡፡ እኛም በታማኝነት ትኩረት ሰጥተን እንድንሠራ የሚያደርገን ነው፡፡ ጨረታውን ከብዙዎቹ የሕንጻ ሥራ ተቋራጮች ጋር ተወዳድሮ ያሸነፈው ድርጅት በማኅበሩ ውስጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያደረገና አብሮ የኖረ ነው፡፡ ሥራውንም በጥራትና ከተያዘለት ጊዜ ቀደም ብሎ በማጠናቀቅ ያስረክባል የሚል እምነት አለኝ፡፡ በማኅበረ ቅዱሳን በኩልም ሥራውን ለማፋጠን አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ እንደሚያደርግ አረጋግጣለሁ›› በማለት ገልጸዋል፡፡

«የማኅበረ ቅዱሳን ዲግሪና የካንጋሮ እጅ አንድ ነው!»



/ን ሙሉጌታ ወልደገብርኤል
Email: yetdgnayalehe@gmail.com
ጥብቅ ማሳሰቢያ:
በቅድሚያ ጽሑፉን ለምታነቡ ወንዶችንም ሴቶችም የእግዚአብሔር ልጆች ሁሉ ሰላም ይሁን! እያልኩ በጽሑፉ ከተካተቱ እውነታዎችና ከጽሑፉ ከፊል ይዘት የተነሳ ጽሑፉ ከጸሐፊው መልእክት ዓላማና ከመልእክቱም ግብ ውጭ ሌላ አንድምታ እንዳይዝና እንዳይሰጠው ይህን ጥብቅ የሆነ ወንድማዊ ማስጠንቀቂያ ለመጻፍ ግድ ብለዋል:: ጸሐፊው በስራ ክቡርነት ያምናሉ: በየትኛውም የስራ መስክ ተሰማርተው ከራሳቸው አልፈው ለቤተሰብና ለሀገር የሚተርፉት ዜጎችንም የላቀ ክብር አላቸው:: ክብር ስለማያውቅ: ሰላሙን አጥቶ በሰላማዊያን ዜጎች የህይወት ጎዳና ላይ እየቆመ እሾክና አሜከላ ስለሚዘራ: እርግማን ቀለብ ስለሆነለት: የራሱ ያለሆነውን በማጭበርበርና በማደናገር የራሱ በማድረግ የሚታወቀው እልል ያለ ህጋዊ ሽፍታ ማህበርና አባላቶቹ ብቻ ላይ ያነጣጠረ እውነታ መሆኑን ተገንዝባችሁ ጽሑፍን በቅንነት ታነቡት ዘንድ በአክብሮት እጠይቃለሁ::