መንፈሳዊ ፍርድ ቤቶች አቅም ግንባታ የላቸውም!
ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነው ሪፖርተር ጋዜጣ በሚያዚያ 17/2004 ዓ/ም እትሙ ያወጣውን ስለሃይማኖት ተቋማት ይልቁንም
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የወርቁ ሠፈር ማርያም ቤተክርስቲያን አገልጋይ በነበሩት 6 ካህናት ላይ «ሰበር ሰሚ ችሎት» የሰጠውን ብይን አስመልክቶ
«ደጀ ሰላም» ብሎግ ደስታውን በመግለጽና የሪፖርተርን ዘገባ በማድነቅ መልሶ መረጃውን ለማስተጋባት የሄደበት መንገድና ስለመንፈሳዊ
ፍርድ ቤት በማቀንቀን የተጓዘበትን የምኞት መንገድ ስህተት ለማሳየትና መልስ መስጠት በማስፈለጉ ይህን ጽሁፍ ማቅረብ አስፈልጓል።
የሰበር ችሎት የህግ ትርጉምን በተመለከተ፣
በመዝገብ ቁጥር 18419 ግንቦት 4 ቀን 1998 ዓ.ም. የቀረበለትን የይግባኝ አቤቱታ የተመለከተው ሰበር ሰሚ ችሎት
የሰጠው ብይን በስር ፍርድ ቤቶች ሁሉ አሳሪ የሆነውን ውሳኔ የሰጠው የጠቅላይ ፍርድ ቤትን ሥልጣንና ኃላፊነት ለማቋቋም በወጣው
አዋጅ ቁጥር 42/97 አንቀጽ 2/4 ላይ ላይ የተሰጠውን መብት በመጠቀም መሆኑ ይታወቃል።