Thursday, December 22, 2011

መጋቤ ሀዲስ በጋሻው ደሳለኝ የአራዳውን ምድብ ችሎት በመሳጭ ስብከቱ አስደመመ


ጽሁፉን በፒዲኤፍ ማንበብ ከፈለጉ ........>>>To read in PDF click here


ታህሣሥ 9 ቀን 2004 ዓ.ም በዋለው የአራዳው ምድብ ችሎት የዐቃቤ ሕግ አንደኛ ምሥክር ሆኖ የቀረበው መጋቤ ሀዲስ በጋሻው ደሳለኝ ችሎቱን ፍጹም ወደ ሆነ መንፈሳዊ ድባብ ለውጦ አስተምሮ መውጣቱን የዜና ምንጮቻችን አረጋገጠዋል፡፡ ዘመድኩን በቀለ በግሉ አርማጌዶን ቁጥር አንድ እና ቁጥር ሁለት ሲዲና ቪሲዲ በማሠራጨት እና የተሳሳተ መልዕክት በማስተላለፍ ምዕመናንን በማወናበዱና በወንድሞች ላይ የስም ማጥፋት ዘመቻ በመክፈቱ በአራዳው ምድብ ችሎት ላይ ክስ የተመሠረተበት ሲሆን እርሱ ራሱ የ"ማኅበረ ቅዱሳን" አባል የሆነ ጠበቃ አቁሞ ለመከላከል ሞክሯል፡፡ በዚሁ ዕለት ከቀኑ 8፡00 ሰዓት እስከ 10፡25 በቆየው የክርክር ሂደት የዘመድኩን ጠበቃ የተልፈሰፈሰ መስቀለኛ ጥያቄ ለማቅረብ ሞክሮ በታዳሚው ሲሳቅበት እንደዋለ እነዚሁ ምንጮቻችን አስታውቀዋል፡፡

ጠበቃው ባቀረበው መስቀለኛ ጥያቄ ቤተክርስቲያንን "አሮጊቷ ሣራ" ብለህ ተሳድበሃል፤ ታዲያ ቤተክርስቲያንን በምንፍቅና ጥለው ከሄዱት ከእነ አባ ዮናስ በምን ትለያለህ? ብሎ የጠየቀው ሲሆን፣ መጋቤ ሀዲስ በጋሻው በሰጠው ምላሽ፣ እናታችን ሣራ በዕድሜ ብታረጅም፣ እግዚአብሔር አከበራት፤ ልጆችን ሰጣት፡፡ እኔም፣ ጥንታዊት ቤተክርስቲያናችን በአሁኑ ሰዓት በማገልገል ላይ ያሉትን ወንድሞችና እህቶች አገልጋዮችን አፍርታለች ነው ያልኩት፡፡ የእኛ ሣራ ልጆችን ወልዳለች፤ የእነ አባ ዮናስ ሣራ ግን ስለመወለዷ አይታወቅም፤ በዚህ እንለያለን በማለት መመለሱ ታውቋል፡፡

መጋቤ ሀዲስ በመቀጠል የቀረበለት ጥያቄ፣ ራስህን በራስህ ሰባኪ አድርገሃል፤ የቤተክርስቲያን ትምህርት ሳይኖርህ ታስተምራለህ፤ ለመሆኑ ዲቁናውን ማን ሰጠህ? መጋቤ ሀዲስ የሚለውንስ ማዕረግ ከወዴት አገኘኸው? የሚል ነበር፡፡ እርሱም በበኩሉ ሲመልስ፣ ዲቁናውን የተቀበልኩት ከብፁዕ አቡነ በርተለሜዎስ የቀድሞው የሲዳማ፣ ጌዴኦ፣ አማሮና ቡርጂ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ነው፡፡ የስብከት መምህርነት ኮርስም ተከታትዬ የተሰጠኝ የምሥክር ወረቀት አለኝ፡፡ የመጋቤ ሀዲስነት ማዕረጉንም ሰባ ሺህ ያህል ሕዝብ ባለበት የሰጡኝ ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል በዚያን ወቅት የሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ ናቸው፡፡

መምህር በጋሻው ሌላው የቀረበለት ጥያቄ የእኛ ጌታ ተኝቶ ይገዛል ብለሃል፡፡ ይህ አባባልህ ልክ ነው? የሚል ነበር፡፡ እርሱም ሲመልስ ታዲያ ይሄ ምን ስሕተት አለው? ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከደቀመዛሙርቱ ጋር በጀልባ ሲጓዝ፣ ተኝቶ ነበርና ማዕበሉ በተነሳ ጊዜ ሲቀሰቅሱት፣ እምነት የጎደላችሁ ስለምንድርነው አላላቸውም? በከርሰ መቃብር ሦስት መዓልትና ሦስት ሌሊት ባደረበት ወቅት ዓለምን አልገዛም? ጌታችን፣ አምላካችን በሰው አስተሳሰብ የተኛ ፣ የሞተ ቢመስልም እርሱ ግን ሁሉንም በኃይሉ ይጠብቅ ነበር፤ በማለት መልሷል፡፡ መጋቤ ሀዲስ በጋሻው ሌሎችንም ተጨማሪ ማብራሪያዎችን የሰጠ ሲሆን፣ እርሱ ጥያቄዎችን በሚመልስበት ወቅት ሁሉም ከመመሰጡ የተነሳ የችሎቱ ሂደት ስብከተ ወንጌል አዳራሽ እስከሚመስል ደርሶ እንደነበር በስፍራው የነበሩ እማኞች ገልጸዋል፡፡

Wednesday, December 14, 2011

ማደናገር ይቁም! የሰንበት ት/ቤቶች ማ/መ ድረገጽ


«ADOBE OF GOD»በሚል ርእስ የክርስቶስ ኢየሱስን የማዳን ስራ የሚያጥላላና ፍጹም ክህደት የተሞላበት ፊልም ኢትዮጵያ ውስጥ ሊሰራ እንደነበር በባለፈው ወር የወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ። በእርግጥም ከ75% በላይ ሕዝብ ክርስትናን በአንድም በሌላ ምክንያት ተቀብሎ የሚኖርና በአብዛኛውም ይህንኑ የእለት ከእለቱ መመሪያ አድርጎ በሚቀበል ሀገር ላይ ይህንን መሰሉን ፊልም መስራት መርገም ካልሆነ በረከት ያመጣል፣ ተብሎ አይታሰብም። ክርስቶስን ለማዋረድ መፈለግ ከክርስቶስ ማንነት ላይ አንዳች የሚያጎለው ነገር ባይኖርም
«የማያምኑ ቢኖሩ አለማመናቸው የእግዚአብሔርን ታማኝነት ያስቀራልን?» ሮሜ 3፣3 እንዳለው ክርስቶስ ዛሬም፣ ነገም ያው እሱ መሆኑ ሳይጎድል አምልኰና ክብር በሚገባው ቦታ ተሳልቆና ክህደት ሲተካ ግን የረድዔትና የበረከት እጁን ላለመቀበል በፈለግነው ልክ የዚህ ዓለም ገዢን ማስተናገድ በመሆኑ ሊያስደነግጠን እንደሚገባ ለአፍታ መዘናጋት የለብንም። ይህንን ድርጊት ለምእመናንና ምእመናት በማዳረስ በመረጃው ላይ የወል ግንዛቤ ወስዶ አቋማችንን ለሚመለከተው ለማድረስ ሚዲያዎች ሰፊ ዘገባቸውን ሰጥተው ሰርተዋል። ይህ ሊመሰገን የሚገባው መንፈሳዊ ተግባር ነው። ይሁን እንጂ አንዳንዶች ራሳቸውን የዚህ ጥረትና ትግል ዋነኛ አካል አድርገው የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ማእከላዊ ጽ/ቤት ግን «ፊልሙ እንዲሰራ ፈቅዷል» በማለት ድካምና ጥረቱን ውሃ በመቸለስ ከችግሩ ጎን ለጎን የችግሩ ዋነኛ ምህዋር እንደነበር ለማሳየት መሞከራቸው አስገራሚ ሆኗል። ከነዚህም መካከል የማኅበረ ቅዱሳኑ ሌላኛው እጅ የ«ደጀሰላም» ድረገጽ ከለጠፈው በኋላ ቤተክህነቱን የወነጀለበትን ጽሁፍ ያውርድ እንጂ ወንድሙ የሆነው «አንድ አድርገን» ለማንበብ ይህን ይጫኑ
እስካሁን ያስነብበናል። «ማኅበረ ቅዱሳን የቤተክህነት እዳ» በተሰኘው መጽሐፍ እንደተጠቆመው «እንቁ» መጽሔት የማኅበረ ቅዱሳን የእጅ አዙር መጽሔት መሆኑን ለመረዳት ብንችል ሁሉም በአንዴ ተቀባብለው ቤተክህነቱን ያለስራው ስም ሰጥተው «ADOBE OF GOD» ለተሰኘው የክህደት ፊልም ትብብሩን ሰጥቷል ሲሉ መጻፋቸው ካንድ ወንዝ መቀዳታቸውን እንደሚነግሩን እንገነዘባለን። የቤተክህነቱ ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ነገሩ እጅግ ቢያስመርረው በድረገጹ ለተባለው ፊልም ከታቃውሞ ውጪ ድጋፍ አለመስጠቱን አስነብቦናል።
ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ

Friday, December 9, 2011

የጳጳሳት ጆሮ የተነፈገው የአዲስ አበባ ካህናት ጩኸት!


የጳጳሳት ጆሮ የተነፈገው የካህናት ጩኸት(to read in PDF click here)

ከደጀብርሃን፣

የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የገንዘብና የንብረት ዘረፋ ሀገር ያወቀው፣ፀሐይ የሞቀው ጉዳይ ነው። ኰሌጅ፣ ሙአለ ህጻናት፣ አውቶቡስ፣ ታክሲ፣ ሆቴል፣የተለያየ ደረጃ ያላቸው ህንጻዎች፣ ሱቆች፣ የሚከራዩ አፓርትማዎች፣ የቤትና የንግድ መኪናዎች ያላቸውን አስተዳዳሪዎች፣ ፀሐፊዎች፣ ሂሳብ ሹሞች፣ የቁጥጥር ሠራተኞች፣ገንዘብ ያዢዎችና ንብረት ክፍሎችን ማየት እንግዳ ነገር አይደለም። ይህንን ሁሉ ሀብት ሲያጋብሱ የቀድሞ ደመወዛቸው ቢበዛ የአስተዳዳሪው ከአንድ ሺህ አምስት መቶ ብር የሚበልጥ አልነበረም። የሌሎቹ ደግሞ ሺህ ብር ባልገባ ደመወዝ ነበር ይህንን ሁሉ ሃብት ማፍራት የቻሉት። የዘረፋ ቁንጮ እንደሆነ የሚነገርለትና አውቶቡስ፣ ት/ቤት፣ ትልቅ ህንጻ እንዳለው የሚነገርለት (ሊቀ ሊቃውንት)አባ እዝራ የሚባለው የሽማግሌ ማፊያ ለዚህ የሚጠቀስ አብነት ነው። ሊቀሊቃውንት ብላ ቤተክርስቲያን የምትጠራው ጡቷን ምጎ፣ ምጎ አጥንቷን ስላወጣው እውቀቱ ይሆን? ይህንን እንግዲህ እውቅና የሰጠው ሲኖዶስ የሚባለው የአባቶቹ ማኅበር ያውቃል። ሌሎቹንም የዘረፋ ሊቀ ሊቃውንት በስምና በአድራሻ ማንሳት ይቻላል። የሚያሳዝነው ግን ንቡረ እድ አባ ገ/ማርያም ገ/ሥላሴን ከአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ሥራ አስኪያጅነት ለማስነሳት የዘመቻው ፊት አውራሪዎች እነዚህ የቤተክርስቲያንን ሀብት እያገላበጡ የሚዘርፉ የቀን ጅቦች መሆናቸው ነው። ከማሳዘን አልፎ የሚገርመው ንቡረ እድ አባ ገ/ማርያም የቀን ጅቦቹን አፍ የዘጉት በየትኛውም የቤተክርስቲያን ገንዘብና የንብረት ቆጠራ ላይ አስተዳዳሪው፣ ፀሐፊውና ሂሳብ ሹሙ እጃቸውን ሳያስገቡ ቁጭ ብለው እንዲመለከቱና አገልጋይ ካህናቱ ብቻ በአንድነት ቆጥረው የተገኘውን ገንዘብ በሞዴል 64፣ የገባውን ንብረት በሞዴል 19 ገቢ አድርገው በግልጽ መጠበቅና ማስጠበቅ መቻላቸውን ሲኖዶስ የሚባለው ስብስብ እያወቀ ወይም ማወቅ ሲገባው ለዘራፊዎቹ ጩኸት ምላሽ በመስጠት ባለፈው ጉባዔ ሥራ አስኪያጁን ከቦታው እንዲነሱ አድርጓል።
ከ5 ሚሊዮን ያላለፈውን ለጳጳሳት ደመወዝና ሥራ ማስኬጃ ፈሰስ የሚደረገውን የጠቅላይ ቤተክህነት ገቢ ወደ 27 ሚሊዮን ከፍ ስላደረጉላቸው ሽልማት መስጠቱ ይቅርና ይህንን አጠናክረህ ቀጥል ማለት አቅቷቸው እንደጥፋተኛ ሰው የልማቱን አባት ለቦታው አትሆንም ብሎ ማንሳት ሲኖዶስ በእውነት በመንፈስ ቅዱስ የሚመራ ነው? የሚያስብል ነገር ነው። የአባ ገ/ማርያምን መነሳት የሚሹ ወገኖች(ፓትርያርኩን ጨምሮ) የዝውውር ጥያቄ ውድቅ ሊያስደርግ የሚችል ተግባር ለማየት ሲኖዶስ የሚባለው ክፍል በመንፈሳዊነት ደረጃ ይቅርና በመስማትና በማሽተት እንዴት ሳይረዳው ቀረ? ይልቁንም ጊዜውን በአባ ሠረቀ ጉዳይ ላይ የማኅበረ ቅዱሳንን ውክልና በማስፈጸም መጠመዱን ስራዬ ብሎ ዋለ እንጂ!! እውነትም የመንፈስ ቅዱስ ጉባዔ!!!!!!!
ከታች የቀረበው በሰዓታቱ፣በማኅሌቱ፣በቅዳሴው፣በፍትሃቱ ሌሊትና ቀን እየጮሁ ቤተሰቦቻቸውን የሚያስተዳድሩ ካህናት ጩኸትና ትዳር አንፈልግም፣ እኛ መንኩሰናል፣ እያሉ ግን ብዙውን ጊዜያቸውን ሽቶ የተለወሰ ቀሚሳቸውን አስረዝመው፣ ወለተማርያም፣ወልደ ማርያም እያሉ የመበለት ቤቶችን የሚበዘብዙ አስተዳዳሪዎች መካከል የተደረገው የአቤቱታ ክርክርና ከላይ እስከታች ረዳት የሌለውን ካህን ድምጽ የሚያሳይ ነውና መልካም ንባብ ይሁንልዎ!! ኅሊናዎትም ፍርዱን ይስጥ!!ከታች ያለውን ተጭነው ያንብቡ!(http://dejebirhan.blogspot.com)