Thursday, December 8, 2011

መጽሐፈ ሰዓታት ምን ይላል?

                               መጽሐፈ ሰዓታት.............to read in PDF click here





«ሰዓሊ ለነ ሰንበተ ክርስቲያን ቅድስት፣
ለውሉደ ሰብእ መድኃኒት፣
ወእስከ ለዓለም ሰፋኒት» ትርጉም--ለሰው ልጆች መድኃኒትና እስከዘለዓለም ገዢ የሆንሽ፣ የክርስቲያን ሰንበት ሆይ ለምኝልን ማለት ነው።
ሰንበተ ክርስቲያን የተባለችው ዕለት ለሰው ልጆች መድኃኒት በመሆኗ እንዲሁም እስከዓለም ፍጻሜ የሰው ልጆች ገዢ ስለሆነች እንድታማልደን እንጠይቃት ማለቱን መጽሐፈ ሰዓታት ይጠቁመናል።
እዚህ ላይ ጥቂት ጥያቄዎችን እናንሳ።
1/ሰንበተ ክርስቲያን የምትባለው ምናልባትም ዕለተ እሁድ ናት። ሐዲስ ኪዳን ግእዙ «ወበእሁድ ሰንበት መጽአት ማርያም መግደላዊት ኀበ መቃብር»ዮሐ20፣1 «ማርያም መግደላዊት ወደመቃብር በሳምንቱ መጀመሪያ ቀን መጣች»ይላል። ምንም እንኳን የእብራይስጡም ሆነ የጽርዑ መጽሐፍ ቅዱስ እሁድ ሰንበት የሚል ቃል ባይዝም እሁድ ብለው ያስቀመጡትን የግእዝ ተርጓሚዎች ተከትለን ብንሄድ እሁድ የተባለችው ቀን---
ሀ/እንዴት ሆና ነው የሰው ሁሉ ገዢ የምትሆነው?
ለ/ እሁድ በምን አፏ ነው የምልጃ ቃልን የምታሰማው?
ሐ/ እሷስ ከማነው የምታማልደን?
ሐ/ከሳምንቱ እለታት የተለየች ናት ካልን የጌታ እለታት ያልሆኑት የትኞቹ ናቸው?
መ/ድርሳነ ሰንበት የተሰኘው መጽሐፍ «ሰንበት» ማለት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ይለናል። ታዲያ ሰንበት የተባለው መድኃኔዓለም ያማልደናል ማለታቸው ነው?
2/ አስታራቂና አማላጅ የሆነችው እለተ ሰንበት ስለመሆኗ የተቀመጠ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ ምንድነው?
ሐዋርያው ጳውሎስ ለገላትያ ሰዎች ወንጌልን ከሰበከላቸው በኋላ ወደቀደመው ከንቱ የሆነ አምልኰ ሲመለሱ ተመልክቶ እንዲህ ብሎ ነበር።
«ነገር ግን በዚያን ጊዜ እግዚአብሔርን ሳታውቁ በባሕርያቸው አማልክት ለማይሆኑ ባሪያዎች ሆናችሁ ተገዛችሁ» ገላ 4፣8
እንደዚሁ ሁሉ እለተ እሁድ እግዚአብሔር ከቀናት እንደአንዱ የሰራት መሆኗ ተረስቶ ልክ አማልክት ወደመሆን የተቀየረች ይመስል አስታርቂን፣አማልጂን ማለት ጳውሎስ በባህሪያቸው አማልክት ለማይሆኑ ባሪያዎች ሆናችሁ የተገዛችሁ ነበረ ያለውን ቃል እኛ ዛሬም እየፈጸምን መገኘታንን ያሳያል።

Wednesday, December 7, 2011

የጴንጤ መዝሙር ያዳመጠስ?

የበጋሻው ግጥም ስህተት የለውም!
በጋሻው ደሳለኝን በተመለከተ አንዴ ጻድቅ ነው፣ አንዴ ደግሞ ኀጥእ ነው እንደሚለው ማኅበረ ቅዱሳንና ልሳኖቹ በሆኑት ደጀሰላም፣ አንድ አድርገን  በመሳሰሉት እንደሚናገሩት ኀጥኡን ለመኮነን ወይም ጻድቁን ለማጽደቅ የኛ ድርሻ ስላልሆነ እንዲሁም  ቃለእግዚአብሔር አይፈቅድልንምና በዚህ ዙሪያ የምንለው ነገር አይኖርም።
ሁለተኛው ደጀሰላም የሆነው «አንድ አድርገን» የበጋሻውን ከሀዲነት የሚገልጽ የግጥምና የመዝሙር ቅንብር በማቅረብ ለማጋለጥ ሞክሯል። እስኪ በዚያ ላይ ተንተርሰን ጥቂት ሃሳብ እንስጥ። ለፍርድ ያመች ዘንድ ግጥሙን ለማሳያነት በጥቂቱ ኮፒ አድርገነዋል።

የፕሮቴስታት                                                                  የኦርቶዶክስ
ካልባረከኝ አለቅህም ካልባረከኝ አለቅህም-                      ካልባረከኝ አለቅህም ካልባረከኝ አለቅህም
 አምላኬ ነህ ለዘላለም                                                 -አምላኬ ነህ ለዘላለም
ጌታዬ ነህ ለዘላለም                                                       ጌታዬ ነህ ለዘላለም
ለብቻዬ ልኖር ፈቃድህ ከሆነ                                           ሊነጋ ሲጀምር ሰማዮ ሲቀላ
ሌላው አይገደኝም ህይወቴ ከዳነ                                      ወዴት እሔዳለው ነፍሴ እንዲህ ዝላ
ሲሆን እስከ ንጋት ልታገልህና                                           እያለቀስሁ ሁሉ እከተልሀለሁ
ስደደኝ ጌታዬ ሆይ ሕይወቴን ባርክና                                   እጅህን ዘርጋልኝ በረከት እሻለሁ
በመንበርከክ ብዛት በጸሎት ትግል                                        ለብቻዬ ልኖር ፈቃድህ ከሆነ
ፈቃድህ ከሆነ ጉልበቴ ይዛል                                               ሌላውን አልሻም ሕይወቴ ከዳነ
እያለቀስኩ ሁሉ እከተልሀለሁ                                           ሲሆን እስከ ንጋትታግለሃልና ል                                                                              
እጅህን ዘርጋልኝ በረከት እሻለሁ                                       ስደደኝ ጌታዬ ሕይወቴን ባርክና

የግጥሙን መመሳሰል ወደኋላ ላይ እናቆየውና የሚታየውን እውነት ኢአመክንዮያዊ (fallacy)በመስጠት በጋሻውን ከሃዲ ለማድረግ የተሞከረበትን ስነ ሞገት እንመርምር።

Monday, December 5, 2011

ይከራከሩኛል!


                 ይከራከሩኛል
ይከራከሩኛል፣ እየተጋገዙ
በከንቱ ላይረቱኝ፣ አምላክን ሳይዙ።
እንዳገሩ ልማድ- ለተማረ ዳኛ፣
ቅጣት ይገዋል-ይህ ደፋር አፈኛ፣
ብሎ ፈረደብኝ- የወንጌል ምቀኛ።
ክርስቲያን የሆነ-ሲኖር በዓለም፣
መመርመር ነው እንጂ- ክፉና መልካም።
እውነት እስኪገለጽ አጥብቆ መድከም፣
እንዲሁ ቢያከፉት- የወንድምን ስም፣
እጅጉን ነውር ነው-ጌታ አይወደውም።
ማርያምን ጻድቃንን-አይወድም ያሉት፣
በምቀኝነት ነው- ስሜን ለማክፋት።
በክስ ቢጠይቁኝ- ስለሃይማኖት፣