Friday, April 22, 2016

በዲሲ ቅ/ማርያም ቤተክርስቲያን የሥልጣንና የገንዘብ ጦርነቱ ተባብሶ ቀጥሏል!


በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ እየተለመደ የመጣ ችግር አለ። በተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ በሁለትና ሦስት ጎራ ተከፋፍሎ የመጣላት፤ የመደባደብና ፍርድ ቤት ድረስ የመካሰስ አደጋ ከመቼውም ጊዜ በላይ እየሰፋ መጥቷል። መሠረታዊው የግጭቱ ምክንያት ሲገመገም በሁለት ነጥቦች ላይ ያጠነጥናል።


                       የሴራው መነሻ፤
1/ በተለያየ መንገድ ገንዘብ ለመዝረፍ እና

2/ በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ የማይነቃነቅ ባለሥልጣን  ለመሆን ነው።


                      የሴራው ተሳታፊዎች፤
የተወሰኑ ምዕመናንና ምዕመናት ግን በሴራው ተዋናዮች ዓላማ ተጠልፈው በቅንነት ቤተ ክርስቲያናቸውን ከአደጋ ለመከላከል ሲሉ ወደጦርነቱ ይገባሉ። የፖለቲካ ክፍፍሉም የራሱ ሚና ይኖረዋል። የሁለት ጎራ ሴረኞች ሕዝቡን የሚቀሰቅሱት ለቤተክርስቲያን ያለነሱ የተሻለ አሳቢ የሌለ በማስመሰል እንጂ ሁለቱም ጎራዎች ድብቅ ዓላማቸው አንዱ አንዱን በመንቀል በቦታው ላይ ራሳቸውን ለመትከል ነው። ይህ ሲባል በቅን አስተሳሰብ የተነሱ የለም ማለት አይደለም። ነገር ግን ቅኖቹ «ከነገሩ ጦም እደሩ» ብለው ራሳቸውን ስለሚያገሉ በመፍትሄው ላይ ተሳታፊ አይደሉም። ሁከቱና ብጥብጡ በውጪው ዓለም ባሉ አብያተክርስቲያናት ማለትም በለንደን፤ በሮም፤ በደቡብ አፍሪካ፤ በሰሜን አሜሪካ እየከፋ ሄዷል።


                            የሴራው ተዋናዮች
የሴራው ተዋናዮች ዓይነት ደግሞ የተለያዩ ናቸው። በአብዛኛው በየአኅጉረ ስብከቱ የሴራው ባለቤቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሲሆኑ በየአድባራቱ ደግሞ አስተዳዳሪዎች፤ ቦርዶች፤ የሰበካ ጉባዔ አባላትና ማኅበረ ቅዱሳን  ናቸው።  ከታች የተመለከተው ቪዲዮ ጦርነቱ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሲካሄድ ያሳያል።
«ነገር ግን እርስ በርሳችሁ ብትነካከሱና ብትበላሉ እርስ በርሳችሁ እንዳትጠፋፉ ተጠንቀቁ» ገላ 5፤15




Thursday, April 14, 2016

ውስጤ መኖር ያለበት ቃና ቲቪ ሳይሆን መንፈስ ቅዱስ ነው!!

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከወዳጅ ጓደኞቼ ጋር በተገናኘን ቁጥር የመወያያ አጀንዳችን የሆነው ጉዳይ የዛሬውን ፅሁፍ እንድፅፍ አስገደደኝ፡፡ ዋና መቀመጫውን በዱባይ አድርጎ በቅርብ ጊዜ በሀገራቸን ስርጭቱን የጀመረው ቃና ቴሌቪዥን በአማረኛ እየተረጎመ (dubbing) በሚያቀርባቸው የቱርክ፣ የጣሊያን፣ የህንድ፣ የጃፓን እና የመሳሰሉት ሀገሮች ተከታታይ ፊልሞቹ የበርካታ ሰወችን ቀልብ እንደገዛ ሁላችንም እናውቃለን፡፡ በእጅጉ የሚገርመው ደግሞ በዙሪያየ ያሉና የማውቃቸው በርካታ ክርስቲያኖች ጭምር ለእነዚህ የባህር ማዶ ፊልሞች እጅ ሰጥተው በጉጉትና በከፍተኛ ናፍቆት ሲጠብቁ ማየት ነው፡፡ የቃና ቲቪ ፊልሞች የሚታዩበት ሰዓት ደግሞ ወላጆች ከስራ፣ ልጆች ከትምምርት ቤት፣ ወጣቶችም ከሚውሉበት ስፍራ በቤት በሚሰበሰቡበት፣ የእግዚአብሔርን ቃል በሚያጠኑበት፣ በጋራ በሚፀልዩበት ሰዓት ነው፡፡ እውነትም በስጋ አይን ለተመለከታቸው ፊልሞቹ በከፍተኛ ሁኔታ የሰውን ቀልብ የመግዛት አቅም እንዲኖራቸው ሆነው ተሰርተዋል፡፡ አንደኛው ፊልም ሲያልቅ በቅፅበት ሌላው ይቀጥላል፡፡ በዚህ ሁኔታ ከምሽት 12፡00 ሰዓት የተቀመጠ ሰው እስከ ምሽት 4፡00 ሰዓት ሌላ ስራ ሳይሰራ ያለምንም እንቅስቃሴ ይቀመጥ ዘንድ ግድ ይለዋል ማለት ነው፡፡ እንግዲህ ልብ እንበል የተቀማነው ወትሮ ለፀሎትና ለእግዚአብሔር ቃል ጥናት በእጅጉ ይመቸን የነበረውን ሰዓት ነው፡፡ ከዛም ደክሞን እንተኛለን፡፡ እዚህ ጋር ግን እንደመንፈሳዊ ሰው ልንነቃ የሚገባን ይመስለኛል፡፡ ሰባት በየቀኑ ለየአንድ አንድ አዓት የሚታዩ መሳጭ የባህር ማዶ ፊልሞች እቤታችን ድረስ መጥተው በራሳችን ቋንቋ እየተመለከትናቸው ነው፡፡ በተቃራኒው ደግሞ ቀድሞ ለጌታ የምንሰጠውን ሰዓት እየተውን፣ በፀሎት የምናሳልፈውን ጊዜ እየሸረሸርን ከክርስትና በእጅጉ የራቁ ሐገሮች ሰርተው በሚልኩልን ነገር ስንጠመድ የእነሱን ባዕድ፣ አምልኮ ኢ-ክርስትናዊ ነገሮች በሙሉ ወደ ውስጣችን እየሰገሰግን ነው፡፡ ልጆቻችንም ከክርስትና በእጅጉ ያፈነገጠ ነገር በየቀኑ እየተመለከቱ እንዲያድጉ እየተፈረደባቸው ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱሳችን በቆላስይስ 2፥8 ላይ ‹‹ እንደ ክርስቶስ ትምህርት ሳይሆን፥ እንደ ሰው ወግና እንደ ዓለማዊ እንደ መጀመሪያ ትምህርት ባለ በፍልስፍና በከንቱም መታለል ማንም እንዳይማርካችሁ ተጠበቁ›› ብሎ በዓለማዊ ነገር እንዳንጠመድ ያስጠነቅቀናል፡፡ ኢየሱስም በማርቆስ ወንጌል 4፥24 ‹‹ምን እንድትሰሙ ተጠበቁ›› ብሎ ከምንሰማውና ከምናየው እንድንጠበቅ ያዘናል፡፡ ዓለማችን ከየትኛውም ጊዜ በበለጠ ኢየሱስ በማቴዎስ ወንጌል ስለመጨረሻው ዘመን የተናገራቸውን የዘመን መጨረሻ ምልክቶች አንድ በአንድ አስተናግዳ ወደ ማገባደደዱ ትገኛለች፡፡ ብዙ ነገሮች ሆነዋል ብዙ ነገሮች ተፈፅመዋል፡፡ ባጠቃላይ ሰይጣን ዲያብሎስ ጥቂት ጊዜ እንደቀረው አውቆ ከመቸውም ጊዜ በላይ በኃይለኛ ቁጣ እየተጋ ያለበት ዘመን ነው፡፡ ዲያብሎስ በዚህ ዘመን በተለይም ወጣቱን ክፍል ከቤተክርስቲያን ለማራቅ ወደ እግዚአብሔር ቃል ትኩረት እንዳያደርግ ከሚጠቀምባቸው ዋና ነገሮች መሀል የፊልምና የሙዚቃው ኢንደስትሪ እጅግ ወሳኙን ድርሻ ይዟል፡፡በዘመናችን የሚሰሩ ፊልሞች በአብዛኞቹ ሰወችን ለዓለማዊ ምኞትና ለርኩሰት አብዝተው የሚጋብዙ ናቸው፡፡ ስለዚህም እኛ ክርስቲያኖች እንንቃ። ሰይጣን በረቀቀ መንገድ በእኛ ላይ እንዲሰለጥን እድል አንስጠው፤ የቱርክና የህንድ ፊልሞችን እያሳየ ከእግዚአብሔር መንግስት የሚለየን ጣቢያ ውስጣችን "ቃና ውስጤ ነው" እያልን ውስጣችን ሊሆንብን አይገባም፡፡ ምክንያቱም እኛ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ የእግዚአብሔር ቤተመቅደስ ነን፡፡ ውስጣችን እሱ ብቻ ነው መኖር ያለበት። ብናምንም ባናምንም ዘመኑ የመጨረሻ ነው፡፡ ያኛው መንግስት እኛን በመዝናኛ ነገር ጠምዶ ከጌታ መንግስት ሊለየን እየተጋ ነው። እኛ ታዲያ ነቅተን ብዙ ምርኮ ልንበዘበዝ ሲገባን በወጥመዱ ከገባንለት እጅግ ከባድ ይሆናል፡፡ ስለዚህም እንንቃ በኢንተርቴመንት ስም ውድ ጊዜያችንን እንዳናስበላ፤ ይልቀንስ የእግዚአብሔርን ዓለምን በልጁ የመጠቅለል አላማ ለማሳካት አብሮ ሰራተኞች እንሁን!ስለወንጌል ግድ ይበለን፡፡
እኛ "መንፈስ ቅዱስ ውስጣችን ነው!"

Friday, April 8, 2016

ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም!!!


ማቴ 7፣21
በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ፥ ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም። እንዳለው ጌታችና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌላውያን ነን ባዮቹ የእግዚአብሔርን ቃል እንዲሰደብ እያደረጉ. "ጌታ ሆይ፣ ጌታ በማለታቸው የዳኑ ቢመስላቸውም የተጠበቁት ለፍርድ ነው። በነሱም የከፋ አድራጎት ሰዎች ወደተገለጠው እውነት እንዳይደርሱ በማድረግ ላይ ተጠምደዋል። በተለይም በአፍሪካ ክፍለ አህጉር ክርስቲያን ነን በሙሉ ፓስተሮች እየተፈፀመ ያለው ዘግናኝ ድርጊትና በቤታችን በኢትዮጵያ ላይ መርገም የሚያመጣ ፀረ ክርስትና ሁኔታ እየተፈፀመ ነው። ሌብነት፣ ዝሙት፣ የእግዚአብሔርን ቃል ማጣመም፣ መዋሸት፣ አድማና ክፍፍል ዋነኛ መለያ ሆኗል።  ከዚህ በታች የቀረበው ጽሁፍ (ከምስባከ ጳውሎስ) የፌስቡክ ገጽ የተወሰደ ሲሆን ነገሩ ከዚህ በፊት እየታየ ከቆየው አሳፋሪ ተግባራት አንዱ ክፍል ነው።

ነገሩ መታወቅ የጀመረው እንዲህ ነው፡፡ አንድ ወዳጃችን በራሱ ምክንያት “ፓስተር” ተዘራ ያሬድ ወደሚያስተዳድሯት ቤ/ክ ይሄዳል፡፡ በዕለቱ የአምልኮ ፕሮግራም እየተካሄደ ነበር፡፡ መባ እና ዐሥራት ተሰበሰበ፤ ከዚያ በኋላ ማስታወቂያ ተነገረ፡፡ ማስታወቂያው ይህን መሳይ ነው፤ “ፓስተራችን የተዘራ ያሬድ ዳግመኛ የተወለደበትን ዕለት በየዓመቱ እንደምናከብር ይታወቃል፡፡ ለዚህም ዓመት ክብረ በዓል ብዙዎቻችሁ ገንዘብ ማዋጣታችሁ ይታወቃል፡፡ ነገር ግን ገንዘብ መስጠት እየፈለጋችሁ ሳትሰጡ ለገንዘብ ማሰባሰቡ የተመደበው ጊዜ ያለፈባችሁ ሰዎች መቸገራችሁን ነግራችሁናል፡፡ በመሆኑም ፓስተራችንን ተጨማሪ ዕድል እንዲሰጣችሁ ለምነነው፣ አንድ ዕድል ብቻ - ይኸውም ዛሬን ሰጥቶናል፡፡ ስለዚህ ገንዘብ መስጠት የምትፈልጉ ሰዎች ዛሬ ካልሰጣችሁ በቀር ሌላ ዕድል አይኖራችሁም፡፡ ምናልባት የተለየ ፈቃድ በፓስተራችን ካልተሰጠ በቀር …”፡፡

ከዚያ ደግሞ፣ ሌሎችም መረጃዎች በየጊዜው ብቅ ብቅ ማለት ጀመሩ፡፡ በእርግጥ ፓስተሩ ለልደታቸው ራቭ4 መኪና ስጦታ የተሰጣቸው በመሆኑ፣ በልደት ማክበር ስም የሚገኘው ጥቅማጥቅም ይጠፋቸዋል ተብሎ አይታሰብም፡፡

በቅርቡ ለማጣራት እንደ ተሞከረው ደግሞ፣ መዳናቸውን እንኳን ከሰውዬው መዳን ጋር የሚያስተሳስሩ አባላት መኖራቸው ነው፡፡ ለልደቱ ገንዘብ የሚያዋጡት መዳናቸውን እያሰቡ ነው!

እኚህ “ፓስተር” “ሬማና ሎጎስ” የተሰኘ መጽሐፍ ሲኖራቸው፣ ለጉባኤያቸው እንደተነናገሩት ከሆነ፣ “ማንም ሰው መጽሐፋቸውን አንብቦ መጠቀም የሚችል ሲሆን ከዚያ ባሻገር ግን መጽሐፋቸውን የመተቸትም ሆነ የመቃወም መብት እንደሌለው፣ ለዚህም ከፌዴራል መንግሥት ፈቃድ እንደ ተሰጣቸው” ይናገራሉ፡፡ “ፓስተር” ተዘራ፣ ከአባላቶቻቸው መካከል በርካታ የደኅንነት አባላት መኖራቸውንና የሚፈልጉትንም ነገር በቀላሉ ማስፈጸም እንደሚችሉ በድፍረት በመናገር ይታወቃሉ፡፡

እንዲህ ዐይነት አገላለጾች “ፓስተር” ተዘራ ያሬድ ስለ ራሳቸው ያላቸውን ግምት የት ድረስ የተወጠረ እንደሆነ ያስረዱናል፡፡