Monday, April 6, 2015

አስነዋሪው የአሸናፊ መኮንን ንስሐ አልቦ ተግባር

(ሲሳይ ንዳው ለድሬ ቲዩብ ከላከው የደረሰን መረጃ)

ግብረ-ሰዶማዊው ዲያቆን

ቅዱሳት መጽሐፍትን ስንመለከት የእምነት አባቶችን የሕይወት አደራ ያላንዳች ሽፋን፤ ድክመታቸውንም ይሁን ብርታታቸውን እየገለጡ፤ ምስክርነታቸውን ለእኛ አስቀርተው ያስተምሩናል፡፡ ቅዱሳት መጽሐፍት ስለ አብርሃም ሲዘግቡ፡- ልጁ ይስሐቅን በእምነት በእግዚአብሔር ፊት ይሰዋ ዘንድ እስከ መጨረሻው ደቂቃ የታመነ ‹‹የእምነት ሰው›› መሆኑን ብቻ አስረድተው አላለፉም፤ ይልቁንም የተስፋው ቃል የዘገየ የመሰለው አብርሃም ከእግዚአብሔር ፈቃድ አፈንግጦ ከሚስቱ ሳራ ውጭ ከአጋር ጋር ተኝቶ ‹‹እስማኤልን›› እንደወለደ አስፍረውልናል፡፡ ንጉሥ ዳዊት ምን ያህል የእምነት ሰው ሆኖ በእግዚአብሔር ዘንድ ‹‹እንደ ልቤ›› ቢባልም፣ የወዳጁን ሚስት በመድፈሩ የወደቀውን ታላቅ አወዳደቅ ሳይደብቁ መጽሐፍቱ ዘግበውልናል፡፡ ከዚህም የተነሳ የእምነት አባቶቻችንን ብርታትና ድካም ተመልክተን ለሕይወታችን የሚበጀውን ትምህርት እንድንቀስምና ምንም ነውርና ነቀፋ የሌለውን ኢየሱስን ግን በማየት ከፊታችን ያለውን ሩጫ እንድንሮጥ፤የዕብራውያን መልዕክት ጸሐፊ እንዲህ ሲል አመለከተን፡- ‹‹እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፥ እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና።›› ዕብ 12፡-1-2፡፡

   ዛሬም በእግዚአብሔር ፈቃድና ሐሳብ ስር ተጠልሎ፤ ‹‹የግብረ-ሰዶማዊነቱን›› ጥም እየቆረጠ ስላለው ‹‹ዲያቆን አሸናፊ መኮነን›› ማንነት በአደባባይ ለሕዝብ ሁሉ መግለጥ ምን ያህል ተገቢ ነው? የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ ሳምንታት የፈጀ ሙግት ከራሴ ጋር አድርጌያለሁ። ነገር ግን የእግዚአብሔርን ሥራ እሰራለሁ እያለ የኃጢአትን ኑሮን እያቀላጠፈ ያለን አጭበርባሪ ማንነት መግለጽ ለክርስቲያኖች ጥቅም ሲባል አስፈላጊነቱን አምኜበታለሁ። የዲያቆን አሸናፊ መኮነን ግብረ-ሰዶማዊነት በተመለከተ ‹‹ይህ መልዕክት››ለሕዝቡ ሁሉ እንዲሰራጭ የፈለኩበት ምክንያት ምን እንደሆነ በግልጽ በማስረዳት፤ የዲያቆኑን ማንነት በማስረጃዎች መግለጥ እጀምራለሁ፡-

1ኛ/ የወንድም የእህቶችን ምክር አልሰማም በማለት ይሄን ዘግናኝ ዓመጻ በገዛ ሰውነቱ ላይ ሾሞ በመቀጠሉ፤
2ኛ/ ሰዶማዊ መሆኑን ‹‹በአዞ እንባም›› ቢሆን ካመነ በኋላ፣ በምን ተፍረት ዳግም ተመልሶ‹‹በአንድ አፍ ሁለት ምላስ›› እንዲሉ አበው ‹‹እኔ ግብረ-ሰዶማዊ አይደለሁም›› ሲል በመዋሸቱ፤
3ኛ/ ሰዶማዊው ዲያቆን እድሉን ተጠቅሞ ንስሐ ከመግባት ይልቅ ወደ ልቡ ይመሰለስ ዘንድ የሚመክሩ ሰዎችን ‹‹በቅናት ተነሳስተውብኝ እንጂ እኔስ ግብረ-ሰዶማዊ አይደለሁም በሐሰት ስሜን እያጠፉብኝ ነው›› ሲል በመክሰሱ፤
4ኛ/ ሰዶማዊው ዲያቆን አሸናፊ መኮነን በእግዚአብሔር ቃል ተከልሎ ነውሩን በማስፋፋት ሥራ ላይ በመጠመዱ፤
5ኛ/ አበው ‹‹ሳይቃጠል በቅጠል›› እንዲሉ የእነዚህ የግብረ-ሰዶማውያን ዓመጻ ሥር ሰዶ፤ ወደፊት ሐገርን ጎድቶ ትውልዱን ሳያበላሽ ከአሁኑ በእንጭጩ ሳለ ‹‹እርቃኑን በአደባባይ ገልጦ ማሳየቱ›› እጅግ መልካም በመሆኑ፤
6ኛ/ ስለ ዲያቆን አሸናፊ መኮነን ግብረ-ሰዶማዊነት የተሳሳተ መረጃ ላላቸውና በአንድም በሌላመንገድ ከእርሱ የዓመጻ ግብር ሥር ተጠልለው ለሚገኙ ወገኖች ግልጽ ማስረጃ ለመስጠትና እራሳቸውን ከኃጢአትም ከወንጀልም እንዲለዩለመምከር፤
7ኛ/ ግብረ-ሰዶማዊነት በኢትዮጵያ ህግ የተወገዘና በወንጀለኞች የመቅጫ ሕግ መሰረት ከፍተኛ ቅጣት ከሚያሰጡ አደገኛ ወንጀሎች መካከል አንዱ መሆኑን ተከትሎ፡- ይሄን ጉድ ደጋግሞ ለወገን ራሱን እንዲጠብቅ ማሳወቁ ሐገራ ዊግዴታዬ መሆኑን በማስተዋል የዲያቆን አሸናፊ መኮነንን ግብረ-ሰዶማዊነት በማስረጃዎች ለመግለጥ ተገደናል፡፡
10ኛ/ ግብረ-ሰዶማዊነት በእግዚአብሔር ቃል በከፍተኛ ደረጃ ኃጢአትነት የተፈረጀ በመሆኑ

ግብረሰዶማዊነት ምንም አይነት ማመቻመች ሳይደረግበት የተወገዘና እንዲያውም የአእምሮ መለወጥ ወይም የተፈጠረበትን ዓላማ መሳት ውጤትመሆኑ ስለተገለጸ የዲያቆን አሸናፊ መኮነንን ‹‹የግብረ-ሰዶማዊነት ቅሌት›› በማስረጃነት እያወጣን የምንገልጥበት ምንጫችን፡- እርሱ በሥራ አስኪያጅነት የሚመራበት‹‹የቅዱስ አትናቴዎስ የወንጌል አገልግሎትን›› የመሰረቱት አባላት ባለባቸው ኃላፊነትና ግዴታ መሰረት ማሕበሩን የለቀቁበት ጉዳይምን እንደሆነ ‹‹ለፌደራል ጉዳዮች ሚኒስተር ለሐይማኖት ጉዳዮች ዳይሮክቶሬት በቀን 28/11/2006 ዓመተ ምህረት ያስገቡትን ባለ አራት ገጽ የስንብት ደብዳቤን›› እየጠቀስን የምናወጣ በመሆኑ፤ የነገሩን ሐቀኝነት ልብ ይሏል፡፡
በፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስተር በፋይል ቁጥር 0096 በሕዳር 16 ቀን 2006 ዓመተ ምህረት በወጣው የወንጌል አገልግሎት ፈቃድ መሰረት የተቋቋመው ‹‹ቅዱስ አትናቴዎስ የወንጌል አገልግሎት›› ዋና ዓላማው ወንጌልን ለፍጥረት ሁሉ በመመስከር ላይ ያጠነጠነ ቢሆንም፤ እነዚህ በቁጥር ስድስት የሆኑት የድርጅቱ መስራቾች ማህበሩን በይፋ የለቀቁበት ምክንያት፡- በእግዚአብሔር ዘንድ እጅግ አጸያፊ በሆነው ዓመጻ ዲያቆን አሸናፊ መኮነን ግብረ ሰዶማዊ በመሆኑ ነበር (በደብዳቤው ገጽ 2፤ አንቀጽ 5 ላይ ይመለከቷል)፡፡
በመጀመርያ የዲያቆኑን ሰዶማዊነት ከስድስት ወራት በፊት በወሬ ደረጃ የሰሙት የወንጌል አገልግሎቱ መስራቾች፤ እየዋለ ሲያድር የወሬው ነገር ስር መስደዱናብሎም በኢንትርኔት በልዩ ልዩ ማስረጃዎች ዜናው መታወጁን ተከትሎ ስለተፈጠረባቸው ድንጋጤ እንዲህ ሲሉ በደብዳቤያቸው ሰይመውታል፡-‹‹ከሁለት ወር በፊት ወዲህ ግን ይህ ነገር ከወሬነት አልፎ ተጨባጭ ማስረጃዎች ሲገኝበት፤ ነገሩ ፈጠረብን ድንጋጤ በወቅቱ ይህንእውነት ለሰማንና ላረጋገጥን ወንድሞችና እህቶች ከቁጥጥራችን በላይ ሆኖብን ነበር፡፡›› በድብዳቤያቸው ገጽ 2 አንቀጽ 4 ያገኙታል፡፡በድርጅቱ የመተዳደሪያ ደምብ መግቢያ ቁጥር 3 ላይ፡- ‹‹የወንጌልን አገልግሎት በመስጠት፣ የክርስቶስ ምሳሌ በመሆን መንግስትና ሕዝባችን የሚጠበቅብንን የዜግነት ግዴታችንን ለመወጣት›› የሚለውን መሰረታዊ ሐሳብ በመጻረር ዲያቆን አሸናፊ መኮነን ነውረኛ የሶዶማዊነቱንጥም ይቆርጥ ዘንድ የጥቃት ሙከራ ያደረሰባቸው የማህበሩ ሰዎች እንዳሉ በደብዳቤው ገጽ 2፤ አንቀጽ 5 ላይ እንዲህ ሰፍሯል፡-‹‹ነገሩ ምንም አስቸጋሪ ቢሆንም እንደ መንፈሳዊ ሰው ተረጋግተን፤ ለማየት በመሞከር በተናጠል ምስክርነቶቻቸውን ከሰጡን የተወሰኑየግብረ ሰዶም ጥቃት ሙከራ ከደረሰባቸው ጋር እና ከሌሎች ወንድሞችና እህቶች ጋር በመሆን በአጠቃላይ አስራ አንድ ሰዎች ያሉበትስብሰባ ተቀመጥን ...›› ማለቱን ይመለከቷል፡፡ አስራ አንድ (11) በመሆን ስብሰባውን ካደረጉ በኋላ፡- በተፈጠረው ጉዳይ ላይእንደ መጽሐፍ ቅዱስ ቃል አንዱ የአንዱን ሸክም መሸከም አለበትና ስለ ወንድም አሸናፊ መኮነን ‹‹ግበረ-ሰዶማዊነት›› በትጋት በእግዚአብሄርፊት አስቀድሞ መጸለይ እንዳለበት በማመንና በመጨረሻም ዲያቆን አሸናፊን በአካል ለመነጋገር ይወሰናል፡፡

በመጀመሪያ አካባቢ ነገሩ የሚፈለገውን ውጤት ይዞ እየሄደ እንደነበር የሚገልጸው ደብዳቤው ዲያቆኑ ሰዶማዊ መሆኑን በማመኑ ለንስሐም ራሱን ዝግጁ በማድረጉንስሃ እንዲገባና እና አንዲመለስ ጥረት ከማድረግ ባለፈ የተፈጠረ ነገር አልነበረም። ‹‹ለፌደራል ጉዳዮች ሚኒስተር ለሐይማኖት ጉዳዮች ዳይሮክቶሬት›› የገባው ደብዳቤ ዲያቆን አሸናፊ ግብረ-ሰዶማዊ መሆኑን እንዳመነ እንዲህ ሲል አስምሮበታል፡- ‹‹አንድ ወንድም በደረሰውመረጃ መሰረት አጣርቶ ባገኛቸው መረጃዎች ተመርኩዞ፤ ዲያቆን አሸናፊን አነጋግሮታል፤ ዲያቆኑም ድርጊቱን መፈጸሙንና መጸጸቱን ገልጾነበር፡፡ ዲያቆን አሸናፊ በዚሁ ዕለት ጉዳዩን ለሚያውቁ ወንድሞች የይቅርታ መልዕክት በሞባይላቸው ልኳል፡፡ አንዳንዶችንም በአካልጠርቶ ይቅርታ ተይቋል፡፡›› በማለት በገጽ 2፤ አንቀጽ 5 ላይ ይናገራል፡፡ በዲያቆን አሸናፊ መኮነን በግዳጅ የግብረ-ሰዶም ጥቃትሙከራ ያደረሰባቸው ወንድሞች የእርሱን የይቅርታ መልእክት ስለሰሙ በአካል ‹‹ይቅርታውን›› ሊያደምጡ በነጋታው ቀጠሮ በስልክ ተነጋግረውቢይዙም፤ አሸናፊ ግን ወደ ክፍለ ሐገር እንደሄደ በስልክ ሜሴጅ አሳውቋቸው ሳያገኙት ይቀራሉ፡፡ በእዚህ ድርጊቱ ልባቸው ያዘንባቸውናሌሎች የጥቃቱ ሙከራ ያልደረሰባቸውን ወገኖች በመጨመር ‹‹የጠቅላላ ጉባኤ ሰብሳቢ›› የሆነውን ወንድም የሽጥላ ብርሃኑን ቢሮ ድረስበመሄድ ‹‹ዲያቆን አሸናፊ መኮነን በግዳጅ ላደረሰባቸው ግብረ-ሰዶማዊ የጥቃት ሙከራ›› ሊያናግሩት እንደሚፈልጉ በጽኑ አስረድተውትይለያያሉ፡፡ ይህ ከሆነ በኃላ የተፈጠረውን ሁናቴ ደብዳቤው እንዲህ ሲል ይተርካል፡- ‹‹አነጋግረውት ከወጡ በኃላ (ወንድም የሽጥላን)በግምት በአንድ ሰዓት ጊዜ ውስጥ ዲያቆን አሸናፊ እራሱ ደውሎ ‹‹ያለሁበት ቦታ ኑ›› በማለቱ በወቅቱ ሦስት ሙከራው የተደረገባቸውና ሌሎች ሦስት ወንድሞች በአንድነትሆነው ዲያቆን አሸናፊ ወዳለበት ሄደው በጉዳዩ ላይ ተነጋግረው፤ ዲያቆን አሸናፊ መኮነን ያደረገውን ድርጊት በማመኑ እና እግራቸውላይ ወድቆ ‹‹ማሩኝ›› በማለቱ፤ ንስሃ እንዲገባ እና የንስሃን ፍሬ እንዲያሳይ ተነጋግረውበቀጣይ ለመገናኘት ተስማምተው ይለያያሉ፡፡ ከእነዚህ ለምስክርነት ከተገኙ ወንድሞች መካከል አንዱ የጠቅላላ ጉባኤ መስራች አባልየሆነ ወንድም ነው፡፡›› ገጽ 3 አንቀጽ 1 ላይ ሰፍሯል፡፡

እንግዲህ ካላይእንዳየነው ‹‹በቀን 28/11/2006ዓ/ም ቅዱስ አትናቴዎስ የወንጌል አገልግሎት መስራች አባላት ለፌደራል ጉዳዮች ሚኒስተር ለሐይማኖትጉዳዮች ዳይሮክቶሬት›› ባስገቡት ባለ አራት ገጽ የስንበት ደብዳቤ ላይ ዲያቆን አሸናፊ መኮነን ግብረ-ሰዶማዊ መሆኑን፣ በዚህምግብረ-ሰዶማዊነቱ ሳያበቃ በተለያዩ ወንድሞች ላይ አስገድዶ የግብረ-ሰዶም ጥቃት ማድረሱን፣ ይህም ድርጊቱ ሲወራ ቢቆይም እየዋለሲያድር ግን አስደንጋጭ ማስረጃዎች እንደተገኙበት፣ በግልጽም ስለ ግብረ-ሰዶማዊነቱ በማስረጃዎች ጥያቄ እንደቀረበለት እርሱም ግብረ-ሰዶማዊመሆኑ፣ በዚህም ጥማቱ ተነሳስቶ ጥቃት ለማድረስ በጽዎታ እሱን መሰል በሆኑ ወገኖች ላይ ሙከራ እንዳደረገ በጸጸት ማመኑንና እንዲሁምማሩኝ ሲል እንደተማጸናቸው፤ ይሄንንም ነገር ላወቁ ወንድሞች በአካልም በስልክም ይቅርታውን እንዳቀረበ ይናገራል፡፡ ታዲያ ይህ መሆኑባልከፋ ዲያቆን አሸናፊ መኮነን እጅግ አጸያፊ ዓመጻ ሥር መሆኑን አምኖ ወደ ንስሃ ገብቶ ይመለሳል፣ የንስሃንም ፍሬ አሳይቶ ሕይወቱንበእግዚአብሔር እጅ ያኖራል ተብሎ ሲጠበቅ፤ እርሱ ግን ባልተጠበቀው መንገድ ‹‹ሥም የማጥፋት ዘመቻ ተከፍቶብኛል›› እያለ የሞትሽረቱን ግብረ-ሰዶማዊነቱን ለመደበቅ ማስወራት ጀመረ፡፡ በዚህም የሞኛ ሞኝ ሥራው ያታለላቸውን ሰዎች በመሰብሰብ ‹‹እኔ ግብረ-ሰዶማዊአይደለሁም ነገር ግን የእኔን ስም ለማጥፋት ተብሎ ነው የሚወራብኝ›› ማለቱን ተያያዘው፡፡ ይህን ነገሩን ሰምተው የተታለሉና በአንድምበሌላ መንገድ በጥቅማጥቅም ከተሳሰሩት ሰዎች ጋር በጥምረት ‹‹የአይደለሁም›› ትግሉን አሁንም ቀጥሎበት ይገኛል፡፡

ታዲያ ግን! ዲያቆንአሸናፊን ምን ነካው? የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ይላል፡- ‹‹ኃጢአቱን የሚሰውር አይለማም የሚናዘዝባትና የሚተዋት ግን ምሕረትን ያገኛል።›› ምሳ 28፡-13፡፡ ወንድም አሸናፊ ከእግዚአብሔር ቃል ውጭ በአጸያፊ ርኩሰትና ዓመጻ ሥር መሆኑ ሳያንሰው፤ ኃጢአቱን ለመደበቅ የገዛ አዕምሮውን አስቶ ‹‹ንስሃ ግባወደ እግዚአብሔርም ተመለስ ሲሉ በጾም በጸሎት የተጉለትን›› ወንድም እህቶቹን ስሜን ለማጥፋት ነው ሲል መደመጡ፤ በርግጥም ምንያህል በርኩሳን መናፍስት ጥላ ስር ስለማደሩ ምስክር ነው፡፡ ዲያቆን አሸናፊ አሁንም ቢሆን ‹‹ኃጢአቱን አምኖ በንስሃ ወደ እግዚአብሔርመመለስ፣ ፍሬንም አፍርቶ መገኘት እንጂ፤ ኃጢአቱን መሰወር የለበትም፤ ይህ ካልሆነ ግን የእግዚአብሄር ቃል ‹‹‹‹ኃጢአቱን የሚሰውር አይለማም የሚናዘዝባትና የሚተዋት ግን ምሕረትን ያገኛል።›› እንደሚል ፍሬ የሌለበት ተክል፣ ውሃ የሌለበት ደመና ሆኖ ሞቱን ይጠብቃልና፡፡ በባህላችንም ይሁን በሕግበተለይም በእግዚአብሔር ቃል እጅግ የተወገዘውን ርኩሰት ተሸክሞ ግብዝ ሆኖ በመንፈሳዊ ሽፋን ተሸፋፍኖ እራስን ሲያስቱ መኖር፤ ብርሃንየበራለት ሰው ሕይወት ሳይሆን ያልዳነ ሰው ማንነትና መለያ ነው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በሮሜ መልዕክቱ እንዲሲል ገለጠው፡-‹‹ስለዚህም እግዚአብሔርን እያወቁ እንደ እግዚአብሔርነቱ መጠን ስላላከበሩትና ስላላመሰገኑት የሚያመካኙትአጡ፤ ነገር ግን በአሳባቸው ከንቱ ሆኑ የማያስተውለውም ልባቸው ጨለመ።›› በማለት የእግዚአሔርን ፍቅር፣ አባትነት፣ ሁሉን ቻይነት፣ ምህረት ርህራሄውን እያወቁ ነገር ግን ያወቁትን እግዚአብሔርን እንደሚገባው የማያመልኩትና የማያመሰግኑት ሰዎች፣ ምን ያህል በአስተሳሰባቸው ከንቱና በልባቸውም ጨለማ መሆናቸውንይናገራል ሮሜ1፡-20-21፡፡ ዛሬም በወንድም አሸናፊ የምናው እግዚአብሔርን አውቃለሁ ብሎ የወንድ ዳሌና ሽንጥ ሲናፍቅ መኖሩ በአሳቡከንቱ በልቡም ጨለማ የመላ መሆኑ ግልጥ ነው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ እግዚአብሔርን እያወቁት እንደ እግዚአሔርነቱ መጠን ስላላከበሩት ሰዎችሲናገር በመጨረሻ ከእግዚአብሔር ዘንድ ስላገኛቸው ርግማን እንዲህ ሲል ገለጠው፡- ‹‹ስለዚህ እግዚአብሔርለሚያስነውር ምኞት አሳልፎ ሰጣቸው፤ ሴቶቻቸውምለባሕርያቸው የሚገባውንሥራ ለባሕርያቸው በማይገባውለወጡ፤ እንዲሁም ወንዶች ደግሞ ለባሕርያቸው የሚገባውንሴቶችን መገናኘት ትተው እርስ በርሳቸው በፍትወታቸውተቃጠሉ፤ ወንዶችም በወንዶች ነውር አድርገው በስሕተታቸው የሚገባውን ብድራት በራሳቸው ተቀበሉ። እግዚአብሔርን ለማወቅ ባልወደዱት መጠን እግዚአብሔርየማይገባውን ያደርጉ ዘንድ ለማይረባ አእምሮ አሳልፎ ሰጣቸው፡፡›› ሮሜ 1፡-26-28፡፡ እንግዲህበአሸናፊም ያየነው ይሄኑ ቃል ነው፡፡ እግዚአብሔርን አውቃለሁ፣ ክርስቶስን እሰብካለሁ፣ ቅድስት ቤተክርስቲያን ተሐድሶ ያስፈልጋታል፣እያለ በግብዝነት በዓመጻ እየኖረ በሕያው አምላክ በእግዚአሔር ላይ ሲዘባበት ለክፉ አዕምሮ ምኞት ተላልፎ ተጣለ፡፡

ወንድ ድመት ከወንድ ድመት ጋር አብሮ ዕለት ዕለት ሲሴስን ያየ ሰው አለን? ሴት ላም ከሴት ባልንጀራዋ ላም ጋር አብራ ስትዳራ በግልሙትናም ስትባዝን የሰማ አለን? ወይስ ወንድ አንበሳ ከወንድ የአንበሳ ደቦል ጋር በፍቅር ተሳስሮ ሲሴስን የተመለከተ አለን? ለማይረባ አዕምሮ ተላልፎ መስጠት፤ አዕምሮ እያለው የእንስሳ እንስሳ መሆን ማለት እንዲህ ነው፡፡ መጽሐፍ እንደሚል፡- ‹‹ሰው ግን ክቡር ሆኖ ሳለ አያውቅም እንደሚጠፉ እንስሶች መሰለ።›› መዝሙር 49፡-12፡፡ ዲያቆን አሸናፊ መኮነን እነሆ ስለ ግብረ-ሰዶማዊነቱከእንስሳ ብሶ አዕምሮ ያለው ግና የእንስሳ እንስሳ ሲሆን የወንድ ዳሌና ሽንጥ ናፋቂ፣ እግዚአብሔርም በፍጥረታቱ ዓለም የዘረጋውንስርዓተ-ተዋልዶን ስቶ ይገኛል፡፡ አሁንም ቢሆን በንስሃ መውደቅ ወደ እግዚአብሔር መመለስ እንጂ ከዚህም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያወጣ ዘንድ በእውነት ፍጹም ብቃት አለው፡- ‹‹የልጁም የኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከኃጢአት ሁሉ ያነጻናል።›› 1ዮሐ 1-7፡፡ ከኃጢአት ‹‹ሁሉ›› ያነጻን ዘንድ የታመነ ጻድቃችንነውና አምላካችን፡፡
በአንድም በሌላ መንገድ የዲያቆን አሸናፊ መኮነንን ግብረ-ሰዶማዊነት አምናችሁም ይሁንሳታውቁ አብራችሁት ላላችሁ ወገኖች፤ እነሆ በእግዚአብሔር ቃል እንጂ አንዳች በስንፈት ቃላት ወደ እናንተ አንመጣምና አድምጡን?በጌታችንንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አምኖ የእግዚአብሔር ልጅ የሆነ ሕዝብ በእውነትይሄን ጉድ ምን የሚል ይመስላችኋል? አዕምሮአቸው የሳተባቸው ጥቁሩን ነጭ፣ ብርሃኑን ጨለማ፣ የሚሉ የአሮጌው ሰው ወኪሎችን አያስተውልምን?ለገንዘብና ለሆዳቸው ሲሉ ከብርሃን ይልቅ ጨለማን የመረጡ ዓይን እያላቸው የማያዩ ታላላቅ ዕውራንን አይመለከትምን? እንግዲህ እናንተ ከማን ወገን ናችሁ? ከእግዚአብሔር ወይስ ከዲያብሎስ? ሕብረታችሁ ማንን ገለጠ? በቃለ እግዚአብሔር ላይ ልባቸውን አስገዝተው አንዳች እንኳ ከቃሉ ፈቀቅ ለማይሉና ለማያመቻምቹ እንዲህ እንላለን፡- አዕምሮው የሳተበት ግብረ-ሰዶማዊን ወደ አምላክህ ወደ እግዚአብሔር ተመለስ በሉት እንጂ ከእርሱ ጋር አንዳች እንኳ አትተባበሩ!! የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ይላል፡- ‹‹በኃጥኣን መንገድ አትግባ፥ በክፉ ሰዎችም ጎዳና አትሂድ። ከእርስዋ ራቅ፥ አትሂድባትም ፈቀቅ በል ተዋትም። ክፉ ካላደረጉ አይተኙምና፥ካላሰናከሉም እንቅልፋቸውይወገዳልና። የኃጢአትን እንጀራ ይበላሉና፥ የግፍንም ወይን ጠጅ ይጠጣሉና።›› ምሳሌ 4፡-14-17፡፡ በመሆኑምትውልድ የማይረሳው የታሪክ ስህተትን ፈጽማችሁ የታሪክ ተወቃሽ ሆናችሁ ከምታልፉ አሁኑኑ ወደ ልባችሁ ተመለሱ!!
በመጨረሻምበዚህ አጋጣሚ ለኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሳዊ መንግስታችን የምናስተላልፈው፡- ‹‹በቅዱስ አትናቴዎስ የወንጌል አገልግሎት ድርጅትውስጥ በግብረ-ሰዶማዊነት ወንጀል፤ በዲያቆን አሸናፊ መኮነን ስለሚሰራው ዓመጻ አስፈላጊውን የማጣራትና የመመርመር ስራ ተካሂዶ ተገቢውንሕጋዊ እርምጃ ይወሰድ ዘንድ ነው›› መልዕክታችን፡፡ የእግዚአብሔር ቃል ‹‹ፍሬም ከሌለው ከጨለማ ሥራ ጋር አትተባበሩ፥ ይልቁን ግለጡት እንጂ፡፡›› እንደሚል በተጨማሪ ማስረጃዎች እመለሳለሁ ኤፌሶን 5፡-11!!
እግዚአብሔር የሰዶማዊውን አሸናፊ መኮንን ልብ ይመልስልን!!

Tuesday, March 24, 2015

ቤተ ክርስቲያን ግን እያሽቆለቆለች፤ አስተዳደሯ እየሞተ ነው። እየገደላት ያለው ማነው?


  በቤተ ክርስቲያን ድክመትና የቁልቁሊት ጉዞ ትልቁን ድርሻ የሚወስደው ከውስጥ የሚነሳው ሽኩቻ እንደሆነ ታሪክ ይነግረናል። ከኬልቄዶን ጉባዔ አንስቶ በየዘመናቱ ሂደት በየክፍልፋይ አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ ሲታይ የቆየው መለያየትና መናቆር መነሻው በመንፈሳዊ ሥልጣን ላይ በሚቀመጡ መሪዎችና ሊቅ ነን በሚሉ ሹመኞች እንደሆነ ብዙ ዋቢ ማቅረብ ይቻላል። ተመሪው ሕዝብም በሚናቆሩ መሪዎች ሁለት ወገን ቆሞ ለአንዱ ወገን አሸናፊነት የቤተክርስቲያኒቱን ግድግዳ እየነቀለ የማፍረሱን ሂደት ማፋጠኑ ሌላው ጉዳት ነው። ሥልጣኑ መንፈሳዊ ሆኖ ሳለ ሽኩቻው ወደሥጋዊ ሕይወት በማድላቱ በመደማመጥ መፍትሄ ለማምጣት ባለመቻሉ ምክንያት ቤተ ክርስቲያን እየተዳከመች በመሄድ ላይ ትገኛለች። በዚያው አንጻር ያሉባትን ተግዳሮቶችና ጊዜውን የዋጀ ክህሎት ያለው ብቁ አመራር በመፍጠር ስላልተቻለ ችግሩ እንዳለ ሊቆይ ችሏል። በዓለም ላይ ካሉ አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ አንዷ የሆነችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንም አንዷ የችግሩ ሰላባ ቤተ ክርስቲያን መሆኗን መካድ አይቻልም።


   የሩቁን ትተን የራሷን ቤተ ክርስቲያን ላዕላይ መዋቅር ራሷ መምራት ከጀመረችበት ከ1950ቹ አንስቶ ብንመለከት ችግሮች እየገዘፉ እንጂ እንየቀነሱ አለመሄዳቸው አስገራሚ ነው። በተለይም ከአፄው ስርወ መንግሥት መውደቅ ጀምሮ አሁን እስካለው እስከ ዘመነ ኢህአዴግ ድረስ ቤተክርስቲያን በአስተዳደሯ ተዳክማ፤ በተከታዮቿ አሽቆልቁላ መሄዷገሃዳዊ እውነት ነው። ጳጳሳቶቿ ፓትርያርካቸውን ከሰው በላው ደርግ ጋር ወግነው የበሉት ሥልጣን እናገኛለን ብለው ካልሆነ ስለእውነትና ስለቤተ ክርስቲያን ዝም ማለታቸው ሌላ ምን ሊሆን ይችላል? ደርግ ፓትርያርክ ሲሾምላቸው አሜን ብለው መቀበላቸው ሥጋዊ ፍርሃት አሸንፏቸው ካልሆነ በስተቀር ለቤተ ክርስቲያን ልዕልናና ስለክርስቶስ ወንጌል ግድ ብሏቸው ሊሆን አይችልም። እንዲያም ሆኖ ከነፈሰው ጋር የሚነፍሱት ጳጳሳት «ብፁዕ ወቅዱስ» ሲሉ በነበሩት ፓትርያርክ ላይ ሌላ ፓትርያርክ ለመሾም ሰላማዊ ሰልፍ በመውጣት ወደምርጫ የገቡት ለቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ እድገት ተጨንቀው አለመሆኑንም አስረግጦ መናገር ይቻላል።


   በዘመነ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፕትርክና የተሻለ አስተዳደርና የልማት ምልክቶች የታየበት ጊዜ ቢሆንም ዘመኑን የዋጀ መዋቅራዊ አደረጃጀት ባለመኖሩ የሰውና የሀብት ብክነቱ ግን ወደር ያልተገኘለት ሆኖ አልፏል።  በሌላ መልኩም ከታዩት ስህተቶች ውስጥ ደግሞ ወደመንፈሳዊ ሥልጣን እንዲመጡ የተደረጉት ኤጲስ ቆጶሳት ሹመት ለለውጥ ሳይሆን ለውድቀት በር የከፈተ መሆኑ ሌላው ጉዳይ ነው። እንኳን ለሊቀ ለሊቀጳሳትነት ይቅርና ለደላላነት የማይመጥኑ ሰዎች በአፈፋ በገፈፋ መሾማቸው በአሳፋሪነቱ ወደር የለውም። ጳጳሳቱ የታወቀና ያልታወቀ የግል ኃጢአታቸው በአደባባይ የተነበበት እንዲሁም በዘረኝነት፤ በጎጠኝነት፤ በአፍቅሮ ንዋይ ፤ በሥልጣን ጥመኝነት፤ በአድመኝነት ራሳቸውን በተግባር ያሳወቁበት ጊዜ መሆኑ ለቤተ ክርስቲያኒቱ ድክመት ትልቁን ድርሻ መውሰዱን መሸፈን ከእውነታው ማፈግፈግ ይሆናል። 


  እነዚሁ ጳጳስ የተባሉት ሰዎች ከማኅበረ ቅዱሳን ጋር አብ’ረው ለነውራቸው መሸፈኛ ያገኙ መስሏቸው ቤተክርስቲያኒቱን ሲያምሱ መገኘታቸው ለወንጌል አገልግሎት መዳከምና  እረኛ አልቦ የሆኑ ተከታዮቿ ከመቼውም ጊዜ በላይ እንዲኮበልሉ የሆነበትም ዘመን ነበር። አስቀድሞ በተደረገ ፖለቲካዊ ምርጫ ወደፓትርያርክነት የመጡት አባ ማትያስም ከነበረው የተሻለ አስተዳደር ለመፍጠር ይቅርና የነበረውን ለማስቀጠል አለመቻላቸው ሌላው የቀጣይ ውድቀት አንዱ ማሳያ ነው።
የመሻሻል ምልክት የሌለውንና የጅምላ ሹመኞቹን የጳጳሳት ጉባዔ በርዕሰ መንበርነት የሚመሩት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ እንዴት አድርገው ቤተክርስቲያኒቱን ወደአንድ የአመራር ከፍታ ሊያሳድጉ ይችላሉ? በጭራሽ አይችሉም! ምክንያቱም ፓትርያርክ ከመሆናቸው በፊት ያልነበራቸውን ችሎታ ዛሬ ከወዴት ያገኙታል? በብዙ ሚዛን አሁን ካለበት ሁኔታ የተሻለ የነበረውን የአቡነ ጳውሎስን አስተዳደር በምኒልክና አስኳል ጋዜጣ ላይ በመተቸት ይታወቁ የነበሩት አቡነ ማትያስ የሥልጣኑ ሉል እጃቸው ላይ ሲወድቅ ወሬውን በተግባር ከማሳየት ይልቅ ለባለጉዳዮች «ተኝቷል በሉልኝ» በማለት በር ዘግተው መደበቅን ምርጫቸው ማድረጋቸው በሰፊው ይወራል።


  ከዚህ በፊት በዚሁ መካነ ጦማር ላይ የሙስና ታሪኩን በቅጽል ስሙ ያወጣነውና ማኅበረ ካህናቱ «ኑረዲን» የሚሉት(ንቡረእድ) ማንም እንዳይገባ በሩን ዘግቶ ለፓትርያርኩ የብቃት ጉድለት ተጨማሪ ድርሻ የወሰደ መሆኑ እንዳለ ሆኖ በሩ ቢከፈትስ ፓትርያርኩ መፍትሄ የመስጠት ብቃት አላቸው ወይ? ብለው የሚጠይቁ ብዙዎች ናቸው።  አንድ ሰሞን ትኩስ በሚሆንና ቆይቶ በሚባረድ ስሜት ውስጥ ሆነው ፈታኝ የሆነውን የቤተ ክርስቲያን ችግር መፍታት አይቻልም። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ትኩስም፤ በራድም በመሆን የለውጥ ሰው መሆን አይችሉም። አንዱን መያዝ የግድ ይላል። በር እየዘጉ መደበቅም ችግሮቹንና ሸክሙን ከሚያበዛ በስተቀር እንከኖችን ሊሰውር የሚችል የምትሃት መንገድ አይደለም። መደበቅን እንደምርጫ ከወሰዱ ደግሞ ሲመተ ፓትርያርኩን ለቤተ ክርስቲያኒቱ ተከታዮች ሰጥተው ወደገዳም መሄድ ይሻላል።


 ሌላው የቤተ ክርስቲያኒቱ የአመራር ጉድለት «ቋሚ» የሚባለው ነገር ቋሚ ያልሆነው ተለዋዋጭ ሲኖዶስ ጉዳይ ነው። ጳጳሳት ስለሚገኙት ብቻ «ቋሚ» ሊባል አይችልም። በየ3 ወሩ በሚደረግ መለዋወጥ «ቋሚ» የሆነ አመራር ሊሰጥ የሚችለው በምን መለኪያ ነው? የሲኖዶስ ውሳኔዎች አፈጻጸም የሚዘገዩት ወይም ለችግሮች አፋጣኝ መፍትሄ ከመስጠት ይልቅ በውዝፍ እየተተወ የሚቀረው 3 ወራት ለሥራ በቂ ጊዜ ባለመሆኑ የተነሳ እንደሆነም መዘንጋት የሌለበት ነጥብ ነው። ቢያንስ ለአንድ ዓመት የሚቆይና ቋሚ ሊያሰኝ የሚችል ሥራ መፈጸም የሚችል የቋሚ ሲኖዶስ ያስፈልጋል። በየ3 ወራት መቀያየር ያስፈለገው ጳጳሳቱ ከአዲስ አበባ ውጪ መቆየቱ ስለሚሰለቻቸው እንደእረፍት ጊዜ የመለዋወጫ መንገድ የወሰዱበት ዘዴ ሊሆን ይችላል እንጂ ሥራ ለመስራት አይደለም። ለዚያውም መሥራት የማይችሉ ሠራተኞች አድርገው አድርገን ከቆጠርናቸው ነው።  ከራሱና ከዘር ጉዳይወጥቶ የቤተ ክርስቲያን ችግር ግድ የሚለው ጳጳስ ከቶውኑ አለን? እነ አባ ማቴዎስ አሁን ባሉበት ሥልጣን እየሰሩ ያለው ሲታይ ለፓትርያርክነት መወዳደራቸው በራሱ ቤተ ክርስቲያኒቱን ራስ ዳሽንን ከሚያክል የተራራ ሸክም ገላገላት የሚያሰኝ ነው። ዛሬ ካሉት ጳጳሳት መካከል ጵጵስና ከመሾማቸው በፊት የጵጵስና የክብር ልብስ በማሰፋት በጉጉት ሲጠባበቁ የቆዩ እንደነበሩ እናውቃለን። አንዳንዶቹም ጳጳስ ሳይሆኑ በፊት የጵጵስናውን ድስት አጥልቀው ፎቶ ተነስተውም ታይተዋል። ዘመቻና ዲናር የሲመት መስፈርት በመሆኑ የተነሳ የተሻለ የአስተዳደር ለውጥ አልታየም፤ ወደፊትም አይታይምም። አንድ ጳጳስ፤ «በኛ ጊዜ ይሄን ያህል ገንዘብ ያስከፍል ነበር» ሲሉ ሰምተን አፍረንባቸዋል።


  ከዚህ በታች የምንመለከተው ፎቶ ግራፍም የዚያ የሹመት ስካር ውጤት ነው። አባ ገ/ሚካኤል ይባላል። ከዚህ በፊት በቃሲም ሥላሴ ሰባኬ ወንጌል ነበር። ከዚያም ኬንያ ከተላከ በኋላ ፈርጥጦ ከአፈንጋጩ ሲኖዶስ የተቀላቀለ ነው። አሁን ደግሞ ሳይሾም በፊት የሲመት አራራውን እየተወጣው ይገኛል። ነገ ደግሞ ወይም በፈርጣጩ ሲኖዶስ አለያም በዘመቻ መልክ በሀገር ቤቱ ልማት የለሽ ሲኖዶስ ሊሾም ይችል ይሆናል።

 ጳጳስ ከሆኑት መካከልም እንደዚሁ ሲያደርጉ የነበሩ ተሹመው ታይተዋል። ነገ ስላለመሆኑ ማረጋገጫ የለም። የጵጵስናውን ሹመት በተስፋ የሚጠባበቁትም ልብሱ ብል እስኪበላው ድረስ አሰፍተው ጥቅምትና ግንቦትን በህልም ይቋምጣሉ።


ቤተ ክርስቲያን ግን እያሽቆለቆለች፤ አስተዳደሯ እየሞተ ነው። እየገደላት ያለው ማነው?

Friday, February 20, 2015

«ኃጢአት፤ ይቅርታና ተሐድሶ»

አንዳንድ የዋህ የሆኑ ሰዎች የልበ ደንዳኖችን አሳብ ተከትለው ወይም እልከኞቹ የዋሃንን እየነዱ «ቤተ ክርስቲያን አትታደስም» ሲሉ ይደመጣሉ። እነዚህን ሰዎች ስለኃጢአት፤ ንስሐ፤ ይቅርታና ተሐድሶ በማስተማር የሕይወትን መንገድ ማስረዳት ከባድ ነው። ምክንያቱም መነሻቸው እውነትን ላለመቀበል እልክ የገባ መንፈስና የተዘጋ ልብ ስላላቸው እያዳመጡ አይሰሙም። እግዚአብሔርን ከማንም በተሻለ እንደሚያውቁ ይናገራሉ። ነገር ግን እግዚአብሔር ካዘዘው ትዕዛዝ ውስጥ አንዱንም አይሰሩም። ምክንያቱም ሁል ጊዜ ራሳቸውን ከራሳቸው ጋር የሚያስተያዩትና የሚመዝኑስለሆነ እውነትን ወደማወቅ ሊደርሱ አይችሉም። በራሳቸው እውቀት ያለልክ ይመካሉ። ነገር ግን እውነት በማደግ ካልተገለጸ በስተቀር በራሱ በተመካ እውቀት ሊሰፋና ወደሌሎች ሊደርስ ባለመቻሉ ዕለት ዕለት ያሽቆለቁላሉ። እድሜአቸውንና ብዙኅነታቸውን እንደእውነት ምስክር አድርገው ለራሳቸው ያቀርባሉ። ራስን ከራስ ጋር የማስተያየት በሽታ አደገኛ ነው። በዚህ ድርጊት አይሁዳውያን በብዙ ተበድለዋል።አይሁዳውያን የእምነት መሠረቶች እንደነበሩ ግልጽ ነው። ነገር ግን ሕግና መጻሕፍት ይዘው መቆየታቸው በራሱ ወደእውነት አላደረሳቸውም። ምክንያቱም ራሳቸውን ይለኩ የነበረው ከራሳቸው ጋር ነበርና ነው።  በምድረ በዳ ውስጥም የ40 ቀን መንገድ 40 ዓመት ያዞራቸው ያ እልከኛ ልባቸው ነበር። በዚያ ብቻ ሳያበቃ እልከኛ ልባቸው ወደእረፍቱ እንዳይገቡ ከለከላቸው።
«ዛሬ ድምጹን ብትሰሙት፥ በማስመረር እንደሆነ ልባችሁን እልከኛ አታድርጉ። ሰምተው ያስመረሩት እነማን ነበሩ? በሙሴ ተመርተው ከግብጽ የወጡ ሁሉ አይደሉምን? አርባ አመትም የተቆጣባቸው እነማን ነበሩ? ሬሳቸው በምድረ በዳ የወደቀ፥ ኃጢአትን ያደረጉት እነርሱ አይደሉምን? ካልታዘዙትም በቀር ወደ እረፍቱ እንዳይገቡ የማለባቸው እነማን ነበሩ?» ዕብ3፤15-18
ራስን ከራስ ጋር ባለመመዘንና ራስን ከራስ ጋር ባለማስተያየት ችግር ካልተያዙ ዛሬ ያለውን የእግዚአብሔር ድምጽ ለመስማት ካለመፈለግ እልከኝነት ነጻ መሆን ይቻላል። የአባቶች አምላክ መንፈስ ቅዱስ ዛሬም ስለሚናገር «በየት በኩል አልፎ ወደእናንተ ደረሰ?» ከሚል እልከኝነት መውጣት እስካልተቻለ ድረስ ወዳዘጋጀው እረፍት መግባት ከባድ ነው። በአንድ ወቅት ሐዋርያው ጳውሎስ ለቆሮንቶስ ቤተ ክርስቲያን እንደተናገረው «እምነት እያደገ፤ ወደሌላው ሰውና ሀገር ሁሉ በሥራው እየጨመረ ካልሄደ በእግዚአብሔር ላይ ያለው መመካትና ምሥጋና ፈተናውን የተወጣ አይደለም ይለናል። ምክንያቱም ራሱን ከራሱ ጋር የሚያስተያይ ራሱን የሚያመሰግን ከመሆኑ የተነሳ ነው። 2ኛ ቆሮ 10፤12-18
እልከኝነትና ደንዳናነት ከኃጢአተኝነት ነጻ ነኝ ከሚል ስሜት የሚመጣ ነው። እልከኝነት የልብን አሳብ ትቶ እውነት የሆነውን ነገር ለመስማት ፈቃደኛ አለመሆን ነው። ደንዳናነት ደግሞ እንደብረት የጠነከረ ግትርነትና ከማንአህሎኝ ድፍንነት የሚነሳ ነው። እልከኛ በኃጢአቱ ከሚመጣ ቅጣት ይማራል። ደንዳና ግን ሳይሰበር ከኃጢአቱ መማር አይችልም ።  የደነደነ ልብ የተሸከመው ፈርዖን በፊቱ የተደረጉትን ተአምራት አይቶ ከመማር ይልቅ ቀይ ባህር ውስጥ ሰጥሞ እስኪቀር መመለስ እንዳልቻለው ማለት ነው። ሁለቱም በደል የእግዚአብሔር ሕዝብ እንደሆነ በሚነገርለት በእስራኤል ላይ ታይቷል። ወደዚህ ያደረሳቸው ነገር ኃጢአት ነው። በእልከኝነታቸው ተቀጥተውበታል፤ በደንዳናነታቸውም ተሰብረውበታል።  ኃጢአትን መተው ፤ ንስሐ ማድረግን፤ ይቅርታን መጠየቅና በተሐድሶ አዲስ ሰው የመሆን ስጦታን ያለመቀበል ውጤት ምንጊዜም በእልከኝነትና በደንዳናነት ውስጥ ይጥላል። ከዚያም የዘሩትን የኃጢአት ፍሬ በፍርድ ማጨዳቸው ደግሞ አይቀሬ ነው። ለዚህም ነው በዚህ ጽሁፋችን መታደስን ስለሚጸየፉ ሰዎች ጥቂት ማለትን የወደድነው። መታደስን መጥላት ኃጢአትን የመውደድ ውጤት እንደሆነ ቅዱስ መጽሐፋችንን ዋቢ አድርገን እንገልጣለን።

1/ ኃጢአት

ሥጋ ከለበሰ ከአዳም ልጆች ውስጥ ከክርስቶስ በቀር ከኃጢአት ነጻ መሆን የተቻለው ማንም የለም። ኃጢአት በአንዱ በአዳም በደል ወደሁሉ ደርሷል። ከሰማይ ወረደው ሁለተኛው አዳም የኃጢአትን በደል በመስቀል ላይ ጠርቆ ካስወገደው በኋላ በውርስ ወደሁሉ ይደርስ የነበረው ኃጢአት ተወግዷል። ከእንግዲህ በወል በኃጢአት ቀንበር ሥር መውደቅ ቀርቶልናል።  በክርስቶስ አዲስ ሰው የሆነ ማንም ቢሆን ኃጢአትን እንዳያደርግም ተነግሯል። ነገር ግን ሰው በክርስቶስ አምኖ ከዳነ በኋላ ከሥጋ ድካም የተነሳ ኃጢአትን ቢያደርግ ከኃጢአቱ እንዴት ሊነጻ ይችላል? ኃጢአት በተፈጥሮው ተጠያቂነት አለበት። ኃጢአት የፈጸመ ማንም ቢኖር ዋጋ ሳይከፍል መንጻት አይችልም። በመጽሐፉም ስለኃጢአት ደም ሳይፈስ ስርየት የለም እንደተባለ ለዚህ የምናቀርበው ዋጋ ምንድነው? እኛ ምንም የለንም።ነገር ግን ኃጢአትን አንድ ጊዜ በመስቀሉ ላይ በደሙ የደመሰሰ ክርስቶስ ለእኛ ከኃጢአት የምንድንበት ዋስትናና ጠበቃችን ነው። 1ኛ ዮሐ 2፤1

ጥብቅና ሲባል የክርስቶስን አምላክነት አሳንሶ እንደምድራዊ ችሎት ሙግትና ክርክር የሚገባ የሚመስላቸው ሞኞች አሉ። በቅድሚያ ኃጢአት በተፈጥሮው  ተጠያቂነትን ማስከተሉን ማመን የግድ ይለናል። በዚህም የተነሳ በኃጢአቱ ማንም በእግዚአብሔር ዘንድ ሳይጠየቅ የሚቀር የለም።  ደም ሳይፈስ ስርየት ስለሌለ በክርስቶስ አምነን ለተመጠቅን ሁሉ በኃጢአት ምክንያት ለሚመጣ ተጠያቂነት መልስ መስጠት የቻለ የክርስቶስ ደም ብቻ ነው። ሰዎች ኃጢአት ስለሚያመጣው ጥያቄ መልስ መስጠት ስለማንችል ስለእኛ ምትክ ሆኖ በቤዛነቱ ደም ያዳነን በኃጢአት ምክንያት ለሚመጣ ጥያቄ መልሳችን የሆነው ክርስቶስ ጠበቃችን የምንለው ያንን ነው። ኃጢአት ዋጋ እንደማስከፈሉ መጠን ንስሐ ስንገባ ስለፈጸምነው ኃጢአት የምንከፍለው ዋጋ ስለሌለን የክርስቶስ ሞት ስለእኛ ምትክ ወይም ጠበቃ ሆኖ ይቅርታን ያስገኝልናል ማለት ነው። በሰውና በእግዚአብሔር መካከል የነበረና በኃጢአት የመጣውን ጥል ተከራክሮ በሞቱ ያሸነፈ ጠበቃ በሰማይ አለን የምንለውም ለዚህ ነው።  ወንጌላዊው ዮሐንስም በመልእክቱ የነገረን ያህንኑ ነው። እንዲህ እንዳለ፤
«ልጆቼ ሆይ፥ ኃጢአትን እንዳታደርጉ ይህን እጽፍላችኋለሁ። ማንም ኃጢአትን ቢያደርግ ከአብ ዘንድ ጠበቃ አለን እርሱም ጻድቅ የሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እርሱም የኃጢአታችን ማስተስሪያ ነው፥ ለኃጢአታችንም ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን ለዓለሙ ሁሉ ኃጢአት እንጂ» 1ኛ ዮሐ 2፤1-2
ኃጢአትን የሚያስተሰርየው ክርስቶስ ብቻ ነው። ከሰው ልጅ ይህንን ማድረግ የተቻለውና የሚቻለው ማንም የለም። ኃጢአትን የሚደመስሰው 41 ስግደት ወይም መስቀል መሳለም አይደለም። ስለኃጢአት ንስሐ ለሚገቡ አስተማማኝ ይቅርታን ማስገኘት የተቻለው መስዋዕት ክርስቶስ ብቻ ነው። «ማንም ኃጢአትን ቢያደርግ በአብ ዘንድ ጠበቃ አለን» በማለት ወንጌላዊው የነገረን ያንን የደም ስርየት ነው።

2/ ይቅርታ

 «ኃጢአትን የሚያደርግ ከዲያብሎስ ነው፥ ዲያብሎስ ከመጀመሪያ ኃጢአትን ያደርጋልና» 1ኛ ዮሐ3፤8  የኃጢአትም ዋጋው ሞት ነው። (1ኛ ቆሮ 15፤56) ከዚህ ሞት ለመዳን ኃጢአትን ስለመፈጸሙ የተጸጸተና ዳግመኛ ወደንስሐ የቀረበ ማንም ቢኖር የሞት ስርየቱ ያው አንዱ የቀራንዮው መስዋዕት ብቻ ነው። በዚያም ይቅርታን ያገኛል። «ኃጢአታችንን ይቅር በለን» ብለን እንጸልይ ዘንድ ተነግሮናል። ምክንያቱም « በኃጢአታችን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነጻን የታመነና ጻድቅ ነው» 1ኛ ዮሐ 1፤9
 ሲሞን መሰርይ የተነገረውን ትእዛዝ ከመፈጸም ይልቅ ጉዳዩን ወደሐዋርያው ሲመልስ ከማየታችን ውጪ ሐዋርያው ጴጥሮስም ለሲሞን በትክክል ስለኃጢአት የነገረው ቃል ይህንኑ ነበር። «እንግዲህ ስለዚህ ክፋትህ ንሰሐ ግባ፥ ምናልባትም የልብህን አሳብ ይቅር ይልህ እንደ ሆነ ወደ እግዚአብሔር ለምን» የሐዋ 8፤22
ስርየት የንስሐ ውጤት ነው። በዚህም የይቅርታን ጸጋ ይጎናጸፋል። ስርየታችንም የክርስቶስ ደም ነው። ኃጢአታችንን ስንናዘዝ በክርስቶስ የይቅርታን ሕይወት እናገኛለን።  «አሁን ግን ከኃጢአት አርነት ወጥታችሁ ለእግዚአብሔርም ተገዝታችሁ፥ ልትቀደሱ ፍሬ አላችሁ፤ መጨረሻውም የዘላለም ሕይወት ነው» ሮሜ 6፤22 ንስሐ የገባ ሕይወት ከእምነት በሆነ መጸጸትና መመለስ ከእግዚአብሔር ይቅርታን ያገኛል። ንስሐ የጨፈገገ ልብ ነው። ሀዘን የተጎዳኘው። ይቅርታ ተስፋ ነው። ከሀዘን ወደ ሕይወት ፍካት የመመለስ ጎዳና። ተሐድሶ ዋስትና ነው። በገባው ንስሐና በተገኘ ይቅርታ ላይ የሚኖሩት አዲስ የለውጥ መንገድ ነው።

3/ ተሐድሶ

ተሐድሶና አዲስ ነገር መፍጠር የተለያዩ ነገሮች መሆናቸውን መለየት ይገባናል። ተሐድሶ የነበረው ማንነት ሲያረጅ፤ ሲፈርስ ወይም ሲበላሽ ወደቀድሞ ማንነቱ የመመለስ ወይም የማስተካከል አካሄድን ያመለክታል። በበደል ከንጽሕና የመጉደል ማንነት ደግሞ ኃጢአተኝነት ነው። ከኃጢአት የመንጻት ማንነት ደግሞ ወደቀደመው የሕይወት ማንነት መመለስ ማለት ነው። ይህም አሠራር መታደስን፤ መለወጥን፤ መስተካከልን፤ ዳግም መመለስን ያመጣል።
አዲስ መሆን ማለት ግን ያልነበረ አዲስ ግኝት፤ አዲስ ነገርን መጎናጸፍን፤ መፍጠርና መሥራትን ያመለክታል። ብዙ ጠማማዎች መታደስንና አዲስነትን በማምታታት የዋሃንን ለማሳሳት ሲሞክሩ ይስተዋላል። ስለተሐድሶ ምንነት መጽሐፍ ቅዱሳችን በደንብ አድርጎ የተናገረ ቢሆንም ያንን እውነት በጥመት እየተረጎሙ ከእግዚአብሔር ቃል ውጪ ሲያፈነግጡ እናያቸዋለን።  ከላይ በመግቢያችን ላይ ለመጠቆም እንደሞከርነው «ቤተ ክርስቲያን አትታደስም» የሚሉ ወገኖች መታደስን አዲስ ነገር ከመፍጠር ጋር በማያያዝ ቃሉን በማጣመም የመተርጎም ግትርነት የተነሳ ነው። ቤተ ክርስቲያን ወይም ኤክሌሲያ ማለት የክርስቲያን ጉባዔ ማለት ነው። የክርስቲያኖች ጉባዔ ደግሞ በክርስቶስ ያመኑ ሰዎች ማኅበር ማለት ነው። ጉባዔ ክርስቲያን ለግል ጸሎት፤ ለማኅበሩ ለራሱ፤ ለሀገርና ለዓለሙ ኃጢአት ስለይቅርታው ይጸልያሉ። በግል የበደሉ ሰዎች በንስሐ ይታደሳሉ። የጎደለው እንዲመላ፤ የጠመመው እንዲቀና፤ የስህተት መንፈስ እንዲወገድ ምህለላና ልመና ያደርጋሉ። የእግዚአብሔር ፈቃድ ያለበት ተሐድሶቱ እንዲመጣ አበክረው ይጸልያሉ። መታደስን ከሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ጋር የሚያያዙ ካሉ የማትታደስ ህንጻ ቤተ ክርስቲያን በዚህ ምድር የለችም።በአክሱም ያለችው የታቦተ ጽዮን ማደሪያ ቤት እንኳን ስንት ጊዜ ታደሰች? እነሆ አሁንም እየታደሰች ነው። የሳር ክዳን በቆርቆሮ ክዳን ይታደሳል። የጠመመው ግድግዳ፤ የፈረሰው ጣሪያ ይቃናል። ይታደሳል። በክርስትናው ዓለም ሰውም፤ ቤተ ጸሎቱም ይታደሳል። ቤተ ክርስቲያን ማለት ሰውም፤ ቤተ ጸሎቱም ማለት ከሆነ የማይታደሰው ምኑ ነው? እስከሚገባን ድረስ ቤተ ጸሎቱም ቤተ ሰዎቹም ይታደሳሉ። ዘማሪው ዳዊት «ነፍሴ ሆይ» በሚለው ዝማሬው እንዲህ ይላል።
«ኃጢአትሽን ሁሉ ይቅር የሚል፥ ደዌሽንም ሁሉ የሚፈውስ፥
ሕይወትሽን ከጥፋት የሚያድናት፥ በምሕረቱና በቸርነቱ የሚከልልሽ፥
ምኞትሽን ከበረከቱ የሚያጠግባት፥ ጕልማስነትሽን እንደ ንስር ያድሳል» መዝ 103፤1-5

ማደስ የእግዚአብሔር ሥራ መሆኑን ልንክድ አይገባም።
ሕዝበ እስራኤል ከባቢሎን ምርኮ ይመለስ ዘንድ በተፈቀደለት ጊዜ ነህምያ የቤተ መቅደሱን ቅጥር ለማደስ ከተወሰኑት ጋር ከባቢሎን ወደፈረሰችው ኢየሩሳሌም ወጥቶ ነበር። (ነህምያ 2፤1-20) ነገር ግን  ቅጥሩን የማደስ ሥራ እንቅፋት ገጠመው። ገሚሱ ፈቃድ ከሰጠው ከንጉሡ ጋር ለማጋጨት ሞከረ፤ ገሚሱም ጠላት ሆኖ መታደስ የለበትም በማለት በቀጥታ ጦርነት ገጠመ። የነህምያ የተሐድሶ ሥራ ፈተናው የጠፋውን ቅጥር ወደነበረበት መመለስ ብቻ ሳይሆን ከተቃዋሚዎች ጋር መዋጋትም ነበረው።
«ቅጥሩንም የሚሠሩትና ተሸካሚዎቹ በአንድ እጃቸው ይሠሩ ነበር፥ በአንድ እጃቸውም የጦር መሣሪያቸውን ይይዙ ነበር። አናጢዎቹም ሁሉ እያንዳንዱ ሰይፉን በወገቡ ታጥቆ ይሠራ ነበር ቀንደ መለከትም የሚነፋ በአጠገቤ ነበረ» ነህምያ 4፤17-18
የቤተ መቅደሱ መታደስ ፈተና በዚህ ብቻ ያበቃ አልነበረም። የራሱ ሰዎች ዘመነ ድርቁን ተገን አድርገው የተቸገሩ ሰዎቻቸውን በወለድና በአራጣ ብድር አስጨንቀው ያዟቸው። ንብረቶቻቸውን በወለድ አገድ በመያዝ ባዶ አስቀሯቸው። ለንጉሥ የሚከፈለውን ግብር መክፈል እስኪያቅታቸው ድረስ ግድ አሏቸው። በዚህም የተነሳ የቤተ መቅደሱ መታደስ ፈተና ላይ ወደቀ። ለመታደሱ የእግዚአብሔር እጅ ስለነበረበት በሰዎች ወጥመድ ተስተጓጉሎ የሚቀር አልነበረም።
«በወንድሞቻቸውም በአይሁድ ላይ ትልቅ የሕዝቡና የሚስቶቻቸው ጩኸት ሆነ። አያሌዎቹም። ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችን ብዙዎች ናቸው በልተንም በሕይወት እንድንኖር እህልን እንሸምት ይሉ ነበር። አያሌዎቹም። ከራብ የተነሣ እህልን እንሸምት ዘንድ እርሻችንና ወይናችንን ቤታችንንም አስይዘናል ይሉ ነበር። ሌሎቹም። ለንጉሡ ግብር እርሻችንንና ወይናችንን አስይዘን ገንዘብ ተበድረናል አሁንም ሥጋችን እንደ ወንድሞቻችን ሥጋ፥ ልጆቻችንም እንደ ልጆቻቸው ናቸው እነሆም ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችን ባሪያዎች ይሆኑ ዘንድ ሰጥተናል፥ ከሴቶችም ልጆቻችን ባሪያዎች ሆነው የሚኖሩ አሉ ታላላቆችም እርሻችንና ወይናችንን ይዘዋልና ልናድናቸው አንችልም ይሉ ነበር። እኔም ጩኸታቸውንና ይህን ቃል በሰማሁ ጊዜ እጅግ ተቈጣሁ። በልቤም አሰብሁ፥ ታላላቆቹንና ሹማምቱንም። ሁላችሁ እያንዳንዳችሁ ወለድ ትወስዳላችሁ ብዬ ተጣላኋቸው ትልቅም ጉባኤ ሰበሰብሁባቸው። እኔ ለአሕዛብ የተሸጡትን ወንድሞቻችንን አይሁድን በፈቃዳችን ተቤዠን እናንተስ ወንድሞቻችሁን ትሸጣላችሁን? እነርሱስ ለእኛ የተሸጡ ይሆናሉን? አልኋቸው። እነርሱም ዝም አሉ፥ መልስም አላገኙም።  ደግሞም አልሁ። የምታደርጉት ነገር መልካም አይደለም ጠላቶቻችን አሕዛብ እንዳይሰድቡን አምላካችንን በመፍራት ትሄዱ ዘንድ አይገባችሁምን? እኔም ደግሞ ወንድሞቼም ብላቴኖቼም ገንዘብና እህል ለእነርሱ አበድረናል እባካችሁ፥ ይህን ወለድ እንተውላቸው። እርሻቸውንና ወይናቸውን ወይራቸውንና ቤታቸውንም ከእነርሱም የወሰዳችሁትን ገንዘቡንና እህሉን፥ ወይን ጠጁንና ዘይቱን ከመቶ እጅ አንድ እጅ እባካችሁ ዛሬ መልሱላቸው። እርሱም፦ እንመልስላቸዋለን፥ ከእነርሱም ምንም አንሻም እንደ ተናገርህ እንዲሁ እናደርጋለን አሉ። ካህናቱንም ጠርቼ እንደዚህ ነገር ያደርጉ ዘንድ አማልኋቸው። ደግሞም ልብሴን አራገፍሁና። ይህን ነገር የማያደርገውን ሰው ከቤቱና ከሥራው እንዲሁ እግዚአብሔር ያራግፈው እንዲሁም የተራገፈና ባዶ ይሁን አልሁ። ጉባኤውም ሁሉ። አሜን አሉ፥ እግዚአብሔርንም አመሰገኑ ሕዝቡም እንደዚህ ነገር አደረጉ»  ነህምያ 5፤ 1-13
የመታደሱ ሥራ እንቅፋት ሌላ ሦስተኛ እንቅፋት ገጠመው። የአገሩ ገዢ ሆኖ በነጉሡ የተሾሙት ሰንባላጥና ዐረባዊው ጌሳም ነህምያን ለመግደል ቅድ ነደፉ።  ሰንባላጥም ከቆላውም ስፍራ እንገናኝ ብሎ አምስት ጊዜ መልእክት ጻፈለት። ነህምያ ንጉሥ ሆኖ በኢየሩሳሌም ተቀምጧል እያሉ ከንጉሡ ሊያጣሉህ ነውና ተገናኝተን መፍትሄ እንስጠው በማለት ለጻፈለት ደብዳቤ ነህምያ የሰጠው መልስ መታደሱን ለማስተጓጎል የተፈጠረ የአንተ ድርሰት ነው የሚል ነበር።
«እኔም አንተ ከልብህ ፈጥረኸዋል እንጂ እንደ ተናገርኸው ነገር ምንም የለም ብዬ ላክሁበት።  እነርሱም ሁሉ ሥራው እንዳይፈጸም እጃቸው ይደክማል ብለው ያስፈራሩን ዘንድ ወደዱ አሁንም፥ አምላክ ሆይ፥ እጄን አበርታ» ነህምያ 6፤ 8-9
የመታደስ አገልግሎት ወደቀመ ማንነት የመመለስ ጎዳና በመሆኑ ተቃዋሚው ብዙ ነው። በአሮጌው ሕይወት ወድቀው እንዲቀሩ፤ የቀደመ ክብራቸውና ከእግዚአብሔር ዘንድ የተሰጣቸውን ጸጋ እንዳያገኙ የሚያደርግ ተቃውሞ ፈታኝ ቢሆንም እግዚአብሔር ለተሐድሶት ያለው ዓላማ ሰዓቱ ከሆነ ማንም ሊያስቀረው አይችልም። በነህምያ ሕይወትም ያየነው እውነት ይህንኑ ነበር። የመታደሱ ሥራ ለእግዚአብሔር ቃል አገልግሎት እና ክብር እንጂ ለሰውኛ ጥቅም እስካልሆነ ድረስ ተሐድሶቱ እውን መሆኑ አይቀሬ ነው። ብዙ ሴራዎችና እንቅፋቶች ሊገጥሙ ይችላሉ። አሸናፊው ግን የእግዚአብሔር ዓላማ ነው። በእስራኤላውያንም የተሐድሶ ትግል ያየነው ነገር ይህንኑ ነበር። የቅጥሩ ሥራ እንደተፈጸመ የሕጉ መጽሐፍ ከተሸሸገበት ወጥቶ ይነበብ ጀመር። ነህ 7፤1-18 ያን ጊዜም «
ዕዝራም ታላቁን አምላክ እግዚአብሔርን ባረከ ሕዝቡም ሁሉ እጃቸውን እየዘረጉ። አሜን፥ አሜን ብለው መለሱ። ራሳቸውንም አዘነበሉ፥ በግምባራቸውም ተደፍተው ለእግዚአብሔር ሰገዱ» ነህ 7፤6
ከሞዓባውያንና አሞናውያን ጋር የተደባለቁ ሰዎች የእግዚአብሔር ሕዝቦች ሊባሉ እንደማይችሉ ከሕጉ መጽሐፍ ውስጥ ተጽፎ ስለተገኘ እንዲለዩ ተደረገ። ተከድኖ የኖረው የሕጉ መጽሐፍ ሲገለጥ የተሸሸገው ስህተት ይፋ ይወጣ ጀመር። ተሐድሶቱ ሲመጣ እግዚአብሔር ብቻ ይከብራል።
«በዚያም ቀን የሙሴን መጽሐፍ በሕዝቡ ጆሮ አነበቡ አሞናውያንና ሞዓባውያንም ወደ እግዚአብሔር ጉባኤ ለዘላለም እንዳይገቡ የሚል በዚያ ተገኘ። የእስራኤልን ልጆች በእንጀራና በውኃ ስላልተቀበሉአቸውና ይረግማቸው ዘንድ በለዓምን ስለ ገዙባቸው ነው ነገር ግን አምላካችን እርግማኑን ወደ በረከት መለሰው። ሕጉንም በሰሙ ጊዜ ድብልቁን ሕዝብ ሁሉ ከእስራኤል ለዩ»  ነህ 13፤1-3
ካህኑ ዕዝራም ከቤተ መቅደሱ መታደስ በኋላ በመጽሐፉ እንደተጻፈው ይኖሩ ዘንድ ሕዝቡን ግድ ሲላቸው ነበር። የሕንጻው መታደስ እስራኤላውያንም ለእግዚአብሔር ቃል እንደሚሆን መታደስን ካላመጣ ምንም ስላልነበር ቃሉ በሚያዘው መንገድ እንዲታደሱ አድርጓቸዋል።
«ካህኑም ዕዝራ ተነሥቶ ተላልፋችኋል፤ የእስራኤልን በደል ታበዙ ዘንድ እንግዶችን ሴቶች አግብታችኋል። አሁንም ለአባቶቻችሁ አምላክ ለእግዚአብሔር ተናዘዙ፥ ደስ የሚያሰኘውንም አድርጉ፤ ከምድርም አሕዛብና ከእንግዶች ሴቶች ተለዩ አላቸው» ዕዝ 10፤10-11
እንግዳ ጋብቻን ከልዩ ልዩ አማልክት ጋር የሚፈጽሙና የሚያስፈጽሙ መጻሕፍትና አዋልድ እስካልተወገዱ ድረስ ንጹህ አምልኮተ እግዚአብሔር ሊኖር አይችልም። መዳን በአንዱ በእግዚአብሔር ብቻ እንደሆነ እስካልተነገረ ድረስ የእንግዶች አማልክት ጋብቻ አደገኛ ነው። «ዐሥርቱ ቃላተ ወንጌልን ይሁን ስድስቱ ቃላተ ወንጌልን ከመጠበቅ ይልቅ ተአምሯን ለመስማት ተሸቅዳደሙ» ከሚለው አምልኮተ ጣዖት ጋር ውልን እስካላፈረሱ ድረስ እግዚአብሔርን ማምለክ አይቻልም። «ሥሉስ ቅዱስን የካደ ተአምሯን ሰምቶ ዳነ» ከሚል አጋንንታዊ ትምህርት እስካልተላቀቁ ድረስ እውነተኛ አስተምህሮ በጭራሽ አይታሰብም።  በሰዎች ላይ የመዳን ተስፋ እንድናደርግ በማበረታታት ከራሳችን አልፎ የማናውቃቸውን ሠላሳ እና ዐርባ ትውልድ ዘሮቻችንን እንደሚያስምሩ ቃል ተገባላቸው በተባለ፤ የቂጣ፤የንፍሮ፤ የአፈር፤ የፍርፋሪ፤ የተቅማጥ ወዘተ የተስፋ መንገዶች ሆነው ከእግዚአብሔር ተሰጥተውናል የሚሉ ቢኖሩ በቃለ ኤጲፋኒዮስ የተረገሙ ናቸው።
«ወኢኮነ ተስፋ መድኃኒትነ በሰብእ፤ ወኢክህለ ሰብእ ያድኅነነ እምአዳም እስከ ተፍጻሜተ ዓለም አላ ውእቱ እግዚአብሔር ቃል ዘተሠገወ። ከመ ኢይኩን ተስፋነ በሰብእ ወኢንኩን ርጉማነ ወዳእሙ በእግዚአብሔር ሕያው» ሃይማኖተ አበው ዘኤጲፋንዮስ 59፤9-12
«የድነታችን ተስፋ ፍጡር በሆነ ሰው የተገኘ አይደለም። ከአዳም ጀምሮ እስከፍጻሜ ዓለም ሊያድነን የተቻለው(የሚቻለው) የለም። ርጉማን እንዳንሆን በሕያው እግዚአብሔር እንጂ ፍጡር በሆነው ሰው ላይ ተስፋ እንዳናደርግ።
ማጠቃለያ፤
ተሐድሶ ከውድቀት ለተነሳ፤ ወደእውነት ለመጣ ማንነት፤ ከስህተት ለተመለሰ ሕይወት የሚሰጥ ስያሜ ነው። መታደስ ጥንትም የነበረ፤ ዛሬም ያለ፤ ነገም የሚኖር ከእግዚአብሔር የሆነ ለሰዎች የተሰጠ መንገድ ነው። ኃጢአት በንስሐ ስርየትን ታመጣለች። ስርየት ይቅርታን ታስገኛለች። ይቅር የተባለ ደግሞ የታደሰ፤ የተስተካከለ ማንነትን ይጎናጸፋል። በሕጉ፤ በቃሉ እንደቀድሞው ለመኖር ዳግመኛ ቃል የሚገባበት ተስፋ ነው። በዚህ ተስፋ እስራኤላውያን መቅደሳቸውንም፤ ራሳቸውንም ከስህተት አድሰዋል።  ተሐድሶ የሚያስፈልገው የቀደመውን መንገድ መልሶ ለመከተል ነው። «መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን ጆሮ ያለው ይስማ» በተባለ ጊዜ የተነገረው ቃል ይኸው ነበር። «የቀደመውን ፍቅርህን ትተሃልና» ተባለ። ስለዚህም ምን እንዲያደርግ ተነገረው?
«እንግዲህ ከወዴት እንደ ወደቅህ አስብ ንስሐም ግባ የቀደመውንም ሥራህን አድርግ፤ አለዚያ እመጣብሃለሁ ንስሐም ባትገባ መቅረዝህን ከስፍራው እወስዳለሁ» ራእይ 2፤4-5
የኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን ወደቀደመ ማንነቷ፤ ለእግዚአብሔር ብቻ ወደነበራት ቀናዒነትና ፍቅር እንድትመለስ በዮሐንስ በኩል በእግዚአብሔር የታየላት ራእይ ቢደርሳትም ለመስማት አልፈለገችም። ከጣዖት ጋር መሰሴኗን አልተወችም። እንደኤልዛቤልም እውነቱንና የዋሃኑን መግደል አላቆመችም። የንስሐ እድል ቢሰጣትም ከዝሙትና ግልሙትናዋ አልታቀበችም። ነገር ግን በውስጧ የነበሩ ትያጥሮናውያን የኤፌሶንን ቤተ ክርስቲያን ድርጊትና ሰይጣናዊ አስተምህሮ ላልተቀበሉት ተስፋ ተሰጣቸው። እስከመጨረሻውም ጽኑ ተባሉ። የተነገረውን ተቀብላ ተግባራዊ ማድረግ የተሳናት የኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን መቅረዟ ተወስዶ ከነአነዋወሯ ከጠፋ እነሆ ሁለት ሺህ ዘመናት ሆነ። የኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን ዛሬ በኤጂያን ባህር ዳርቻ ፍርስራሾቿ የሚጎበኙ የቱርክ ኢስላማዊ ግዛት ከተማ ሆናለች።
የኛይቱ ኤፌሶንም ከትያጥሮን ቤተሰዎቿ የሚነገራትን ተሐድሶ ትቃወማለች። ነገር ግን በቁጥር መሳ ለመሳ እየሆናት ከመጣው ኢስላም ጋር በአንድ ወንበር ቁጭ ብላ ስለሰላም አወራለሁ ትላለች። እንዲያውም ከሕዝቡ ቁጥር 50-60% ኢስላም ነው እያለ የራሱን መንግሥት ናፋቂ ከሆነ ሃይማኖት ጋር ጊዜዋን ከምትገድል ከእግዚአብሔር ዘንድ የሚጠበቅባትን ፈጽማ የቀድመ ኃይሏን ማደስ አይሻላትም ነበር? ዝሙትና የዝሙት ወሬ፤ ግፍና ቅሚያ፤ በደልና ዐመፃ፤ ስካርና ባዕድ አምልኮዋን ማስወገድ አይሻላትም ነበር? ከንቱ ተስፋና ስሁት ምክንያተ ድኂን ከምትዘራ ይልቅ እውነቱን በአደባባይ ብትመሰክርና የቀደመ የንጉሥ ፍቅሯን ብትመልስ አይሻላትም? ከንቱ ጋብቻቸውን እንዳፈረሱ እስራኤላውያን በሰዎች ላይ የተንጠላጠለ ከንቱ ጋብቻዋንና የጋብቻ መጽሕፍቶቿን ጥላ ልብን በሚያቃጥለው በንጉሡ መጽሐፍ ላይ መጣበቅ አይበጃትም ነበር?
 እምቢ አልሰማም ብትል ግን ንጉሥ በቃሉ ከተናገረው አንዳች አያስቀርም። እነዚያ ተሟጋች ነን ባይ ልጆችሽን ጨምሮ ስሁቱን አስተምህሮዋን እንደእውነት ለተናገሩ ሁሉ ዋጋቸውን ይሰጣቸዋል።  «ልጆችዋን በሞት እገድላቸዋለሁ» ራእይ 2፤23
«መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት ያለውን ይስማ» ማለቱ ለዛሬዋም ቤተ ክርስቲያንም ጭምር መሆኑን ልናስተውል ይገባናል።