Saturday, December 7, 2013

መነኩሴው በግብረሰዶም ወንጀል በእስራት ተቀጡ



በአሸናፊ ደምሴ /ሰንደቅ ጋዜጣ፤ ህዳር 25 እትም/

ዐቃቤ ሕግ ለአካለ መጠን ባልደረሰ ታዳጊ ላይ የግብረ ሰዶም ጥቃት ፈፅመዋል ሲል ክስ የመሰረተባቸው የ33 ዓመቱ ተከሳሽ አባ ገብረፃዲቅ ወልደሩፋኤል በቀረበባቸው ማስረጃ ጥፋተኛ ሆነው በመገኘታቸው የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 7ኛ ወንጀል ችሎት ህዳር 19 ቀን 2006 ዓ.ም ውሎ በ4 ዓመት ፅኑ እስራት የቅጣት ውሳኔ ሰጠ።
የፌዴራሉ ዐቃቤ ህግ የክስ መዝገብ እንደሚያስረዳው፤ ተከሳሽ ከእርሱ ጋር ተመሳሳይ ፆታ ካለውና ዕድሜው ለአካለ መጠን ባልደረሰው ልጅ ላይ የግብረ ሰዶም ጥቃት ለመፈፀም አስበው ነሐሴ 22 ቀን 2005 ዓ.ም በግምት ከቀኑ 8፡00 ሲሆን፤ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 13/15 አካባቢ ልዩ ቦታው ዳንኤል ሆቴል ውስጥ ዕድሜው 15 ዓመት ከሆነው የግል ተበዳይ ጋር ግንኙነት ለማድረግ በመስማማት በሆቴሉ ሽንት ቤት ውስጥ ተከሳሽ አባ ገብረፃዲቅ ወልደሩፋኤል የግል ተበዳይን ካስገቡት በኋላ የግብረ ሰዶም ግንኙነት ሊፈፅሙ ሲል ሌሎች ግለሰቦች እየተከታተሏቸው መሆኑን ሲያውቁ ሱሪያቸውን አጥልቀው መሸሻቸውን ድርጊቱም በጅምር የተቋረጠ መሆኑን ያትታል። በመሆኑም ዐቃቤ ሕግ ተከሳሹ ለፈፀመው ለአካለ መጠን ባልደረሰ ልጅ ላይ የሚፈፀም የግብረ ሰዶም ጥቃት ለሥነ-ምግባር ተቃራኒ በሆነ ሌላ ድርጊት ሙከራ ወንጀል ክስ መስርቶባቸዋል።  
የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት 7ኛ ወንጀል ችሎትም የጉዳዩን ግራና ቀኝ ሲመረምር ከቆየ በኋላ ተከሳሹ የዐቃቤ ሕግን ማስረጃዎች በሚገባ ማስተባበል ባለመቻሉ ጥፋተኛ ነው ሲል ብይን ሰጥቷል። ይህም በመሆኑ ባሳለፍነው ሐሙስ ህዳር 19 ቀን 2006 ዓ.ም በዋው ችሎት ተከሳሹ ጥፋተኛ ሆነው በተገኙበት ወንጀል በአራት አመት ፅኑ እስራትና ለአራት አመታት በሚዘልቅ የመምረጥ መመረጥ እና ከማንኛውም ህዝባዊ መብቱ እንደታገድ ቅጣት ተጥሎበታል።

Wednesday, December 4, 2013

አይ አበሻ! አበሻና ሆድ!

 
አይ አበሻ! አበሻና ሆድ፤
Posted on
by መስፍን ወልደ-ማርያም (Mesfin Wolde-Mariam)
ጥቅምት 2006


አበሻ ድግስ ይወዳል፤ ድግስ የሚወደው መብላትና ማብላት ስለሚወድ ነው፤ ለመብላት የአበሻ ምክንያቱ ብዙ ነው፤ ልጅ ተወለደ ብሎ መብላት ነው፤ ልጅ ክርስትና ተነሣ ብሎ መብላት ነው፤ ልጅ አገባ ብሎ መብላት ነው፤ ልጅ ሞተ ብሎ መብላት ነው፤ አበሻ ሰው ቀብሮ ሲመለስ በንፍሮ ይጀምርና ቀስ በቀስ ወደሌላው ይተላለፋል።
ሃይማኖትም ቢሆን ለመብላት ካልሆነ የነፍሱ ጉዳይማ በጣም ሩቅ ነው፤ ሕያዋን ለነገሥታት፣ ሙታን ለካህናት ይገብራሉ፤ በሚለው መመሪያ መሠረት
ግብር መቀበል ያለ ነው፤ ክርስቶስ ተወለደ መብላት ነው፤ ክርስቶስ ተጠመቀ መብላት ነው፤ ክርስቶስ ሞተና ተቀበረ መብላት ነው፤ ክርስቶስ ተነሣ መብላት ነው፤ ማርያም አረገች መብላት ነው።
ማኅበርም የሚጠጣው (የሚበላው ለማለት ነው፤) ለመብላት ነው፤ አምላክ በተለያዩ ስሞቹ፣ ቅድስት ማርያም በተለያዩ ስሞችዋ፣ መላእክት፣ ቅዱሳን፣ ሰማዕታት ሁሉ ለመብላትና ለማብላት ያገለግላሉ፤ ወደመንግሥተ ሰማያት ለመግባት አማላጅ ሊሆኑ የሚችሉ ሁሉ ማኅበር ለመብላት ምክንያት ሊሆኑ ይችላሉ፤ የሌሎች አገሮች ክርስቲያኖች በመብል አይመለሱም፤ ገበያቸው በጠገራ ብር ነው፤ ስለዚህም አብሮ መብላት ብሎ ነገር የለም።
አበሻ የሚበላው የመጣውን ሲቀበል ብቻ አይደለም፤ የሚሄደውን ሲሰናበትም  መብላት ይወዳል፤ ሞትም ቢሆን ለመብላት ምክንያት ነው፤ ቀብር ብሎ እዝን እያቀረቡ መብላት ነው፤ ሠልስት ብሎ መብላት ነው፤ ለሰባት መብላት ነው፤ ለዓርባው መብላት ነው፤ የሙት-ዓመት ደግሶ መብላት ነው፤ በቀብር ላይም  ቢሆን ለቅሶውም ‹‹ሆዴ! ሆዴ!›› ነው።
ለአበሻ ጾምም ቢሆን ለመብላት ነው፤ የጾም ትልቁ ምሥጢሩ ምግብ እንዲናፍቅ ለማድረግ ነው፤ የፍስኩ የተትረፈረፈ ምግብና ጥጋብ ባይኖር ማን ይጾማል? የለየላቸው ጠጪዎች በሁዳዴ መለኪያውንና ብርጭቆውን አርግፍ አድርገው የሚተውት ሲፈሰክ በናፍቆት ዊስኪውንና ቢራውን ለመጋት ነውኮ! ይህ ባይሆን አንድ ጊዜ ሞጣ ያየሁትየበግ ሌባ ለምን ይጦም ነበር? ታሪኩ እንዲህ ነው፤ በሞጣ አውሮጵላን ማረፊያ አንድ የበግ ቆዳ የያዘ ሰውዬ በፖሊሶች ይጠበቃል፤ እንደሰማሁት በግ ሰርቆ ጫካ ይወስድና ቆዳውን ገፎ ለመሸጥ ወደገበያ ሲሄድ ተይዞ ነው፤ የሁዳዴ ጾም ስለነበረ ሥጋውን ለማይጾሙ አውሬዎች ጫካ ውስጥ ጥሎ ነው! አሁን ይህ ሰውዬ የሚጾመው ሲፈሰክ ደህና አድርጎ በናፍቆት ለመብላት ካልሆነ ለሌላ ለምንድን ነው ሊባል ነው?
ሥራም ቢሆን ለመብል ነው፤ ከመኝታው ሲነሣ ጀምሮ እስኪተኛ ቢበላ ደስታውን አይችለውም፤ለገና፣ ለፋሲካ፣ ለእንቁጣጣሽና ለመስቀል ለገናና ለፋሲካ፣ ለእንቁጣጣሽና ለመስቀልም ከሌሊት ጀምሮ ከአንዱ ቤት አንዱ ቤት እየተዘዋወሩ በመብላት ቀኑ ያልፍ የለም እንዴ! በእውነት አበሻ መብላት የሚወደውን ያህል ማብላትም ይወዳል፤ ስሞት! ስቀበር! አፈር ስገባ! … ወዘተ. እየተባባለ የጠገበውን ሰው በቁንጣን እንዲሰቃይ ማድረግ የአበሻ ልዩ የፍቅር መግለጫ ነው! መጎራረስም አለ፤ ፍቅርና ጉርሻ ሲያስጨንቅ ነው እየተባለ ፍቅርና ሆድን ያያይዛል፤ አነጋገሩ አበሻ ለመብላት ያለውን እንጂ ፍቅርን አይገልጽም፤ ማሰጨነቅንና ፍቅርን ምን አገናኛቸው! አበሻ ሌላም ተረት አለው፤ የወለዱትን ካልሳሙለትና የሠሩትን ካልበሉለት ደስ አይለውም ይባላል፤ የልጅ ፍቅር ከምግብ ፍቅር ጋር ተስተካክሎ የቀረበ ይመስላል፤ ደሞም ብቻውን የበላ ብቻውን ይሞታል፤ ይላል፤ ጉድ ነው! ሲሞትም ተከተሉኝ የሚል ይመስላል!! ለነገሩማ ፍቅርምኮ አበሻ ዘንድ ምግብ ነው፤ ሆዴ! አንጀቴ! ጎንደሬዎች ሲያሳምሩት ደግሞ ራቴዋ! ይሉታል።
ዛሬ ዛሬ አበሻ ከማብላት ይልቅ ማጠጣት ይወዳል፤ እስቲ ሰዎች ሰብሰብ ብለው በሚጠጡበት ቦታ ብቅ በሉ፤ ያቺን የፈረደባትን ጉበት ለማቃጠል በአቦ፣ በሥላሴ የማይል የለም፤ ቸገረኝ ብሎ ገንዘብ የሚጠይቅ አይምጣ እንጂ ለማብላትና ለማጠጣት፣ ለአንድ ጥሪኝ ፈሳሽ አበሻ ቸር ነው፤ በላኤ ሰብስ በማርያም ስም አንድ ጥሪኝ ውሀ ሰጥቶ አይደለም እንዴ የበላው ሰው ሁሉ የተሰረዘለት? አበሻ በሆድ አይጨክንም።
ለአበሻ ምግብ ክቡር ነው፤ ስለዚህም ምንም ነገር ሲበላ ተቀምጦ ነው፤ ፈረንጅ ቂሉ በየመንገዱ እንደመጋዣ ያመነዥካል፤ በየመንገዱ ማመንዠክ ምግቡን ማዋረድ ነው፤ ከዚያም በላይ ቆመው ሲበሉ ወደጉልበት ይወርዳል ይላል፤ ለአበሻ ጨጉዋራና ጉልበት በቀጥታ የተገናኙ ናቸው፤ ሳይንሱ የሚለው ሌላ ቢሆንም አበሻ አበሻ ምን ቸገረው?
ለመሆኑ ከሆድ ጋር ያልተያያዘ ነገር አበሻ ምን አለው?  ነገርን በሆድህ ያዘው ምን ማለት ነው? ነገርን ማብላላት የማሰብ ምትክ መሆኑ ነው፤ ልጆች ሆነን አይጥ አበላሁት እንል ነበር፤ አሸነፍሁት ለማለት ነው፤ ዛሬም ቢሆን ቁማርተኞች በላሁ-ተበላሁ ይባላሉ፤ አይጥ ከማብላት ገንዘብ ወደማብላት ተለወጠ እንጂ ከሆድ አልወጣም፤
አበሻ በሆዱ የማይዘው ምን ነገር አለ? ፍቅርም፣ ጥላቻም በሆድ ነው፤ ቂምም በሆድ ነው፤ ምኞትም ፍላጎትም በሆድ ነው፤ ተስፋም በሆድ ነው፤ መጥኔ ይስጠው የአበሻ ሆድ! ሁሉን ከተናገሩት ሆድ ባዶ ይቀራል፤ አይ የአበሻ ሆድ! የነገር ስልቻ ከመሆኑ በላይ ነገር አልቆበት ‹‹ነገር እንዳይርበው(!)›› ጥንቃቄ ማድረግ አለበት! የአበሻ ሆድ እህል ቢያጣና ከእህል ባዶ ቢሆንም ከነገር ባዶ መሆን የለበትም፤ እህል ቢጠፋም ነገር አይጥፋ!
የአበሻና የሆድ ነገር በዚህ አያበቃም፤ አበሻ ሲያመው ቡዳ በልቶት ነው፤ ቆንጆውን ሁሉ ቡዳ ይበላዋል፤ ልብ በሉ ለአበሻ በዓይንም ይበላል ማለት ነው! አንዳንዴም ሲያመው መድኃኒቱ ምግብ ነው፤ ለሆድ ቁርጠት ብላበት፤ አበሻ ሲሞትም ለቅሶው ሁሉ ስለሆድ ነው፤ ‹‹የኔ ሆድ፣ ሆዴ እንዴት ይቻለው! ፋሲካን የት ልፈስክ?››
እስከናካቴው ‹‹ሆድ›› የሚባል ቃል ከአበሻ ቋንቋ ፈጽሞ ቢሰረዝ ቋንቋው ብቻ ሳይሆን አበሻም ጉድ ይፈላበታል፤ አእምሮ፣ ኅሊና የሚባሉትን ቃላት አበሻ አያውቃቸውም፤ ተግባራቸውንም ሁሉ ለሆድ ሰጥቶታል።

Monday, December 2, 2013

የአፍሪካ ኅብረት ቅ/ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን የገንዘብ ምዝበራ ተጋለጠ!

ለውድ ደጀ ብርሃን  ብሎግ በቤተክርስቲያናችን ያሉ ሕገ ወጥ አሰራሮችን በመቃወም የምታደርጉትን እንቅስቃሴ የምንደግፍ ሲሆን የቤተክርስቲያን አገልጋዮች በእውነት የሚታመኑ መሆን እንዳለባቸው እናምናለን እኛ የአፍሪካ ኅብረት ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ሰንበት ተማሪዎች ከእኛው አብራክ የወጡ ቤተክርስቲናችንን ይጠብቁልናል ባልናቸው ወንድምና እህቶቻችን ቤተክርስቲያን እየተመዘበረች ነው፡፡ ስለዚህ ሁሉም ይህንን እውነት ተረድቶ በስመ ታማኝነት ከሌቦች ጋር የተሰለፉ ሰንበተማሪዎችን እንዲጠብቅና እንዲያጋልጥ በቅርቡ የተፈጸመውን ምዝበራ በብሎጋችሁ እንድታወጡልን እንጠይቃለን፡፡

የአፍሪካ ኅብረት ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን በህዳር 12 ከተሰበሰበ ገንዘብ 200.000.00 (ሁለት መቶ ሺህ ብር ) በላይ ገንዘብ ተመዘበረ፡፡ የደብሩ አስተዳዳሪ የዓመት ፍቃድ በመሆናቸው በእለቱ ቆጠራ አልተገኙም ይህንንም እንደ መልካም አጋጣሚ በመቁጠርና የሰበካ ጉባዔ ምክትል ሊቀ መንበር ስልክ ተደውሎላቸው ቆጠራውን አቋርጠው በመውጣታቸው የደብሩ ዋና ጸሐፊ መ/ስ አብርሃም አቧይ  የወረዳው ስራ አስኪያጅ የአባ አእምሮ የቅርብ ዘመድ ከወረዳ የተወከሉት ወ/ሮ አባይ እና የሀገረ ስብከቱ ጸሐፊ ወ/ሮ አዲስ ዓለም እንዲሁም በአዲስ አበባ ሙስናና ዘረፋን በማበረታታት እነ የካ ሚካኤልን እንዳያገግሙ አድርጎ በዘረፋ ባዶ ያስቀራቸው በአዲስ አበባ ከተማ ለተለያዩ የውጪ ሀገር ኗሪዎች 7 ፎቅ ቤቶችን በተለያዩ አካባቢዎች  ሰርቶ የሚያከራየው ቀድሞ አለቃ የአደራው ንጉሤ ሴት ልጅ  ወ/ት እጸገነት አደራው በገንዘብ ያዥነት እንዲሁም በካቴድራሉ መልካም ሰው በመምሰል ለሁሉ ወዳጅ የሆነው አቶ ፋንታሁን ምረቴ እና ሊቀ ቀትጉሃን ኃ/ጊዮርጊስ በጋራ ዘረፋውን ማከናወናቸው ታውቋል፡፡የአፍሪካ ኅብረት ቅ/ሚካኤል በህዳር 12 ቀን ከምእመናን የተሰበሰበውን ገንዘብ ግማሹን በመቀነስ 280 ሺህ ብር ብቻ ወደ ደብሩ ባንክ እንዲገባ ሲደረግ ሌላውን ግን በቆጠራው የተገኙት ስማቸው የተዘረዘሩት ግለሰቦች ተካፍለውለታል፡፡ የደብሩ ጸሐፊ አብርሃም አቧይ ለአቡነ እስጢፋኖስ ቀራቢ ነኝ በማለት ደብሩን እየበጠበጠ ሲሆን፤ በትዳሩ ላይ በመወስለት እና ከሙስሊም ሳይቀር ዲቃላ በመውለድ ቤተክርስቲኒቱን ያሰደበ ተግባር መፈጸሙንና በአባ እስጢፋኖስ ዘንድ አለኝ በሚለው ተሰሚነት ሰራተኛውን እያስፈራራና እያሸበረ እንደሚገኝ ለማወቅ ተእሏል፡፡ በደብሩ ሰንበት ት/ቤት ተማሪ የነበሩና በኋላ በግል ጥቅም ታውረው የምዷየ ምጽዋት ገንዘብ የጣማቸውና ወደ ሰራተኛነት ያደጉት ዲ/ን ዳዊት ወርቁ ከሰበካ ጉባዔ አባልነት በተጨማሪ የደብሩ የእለት ገንዘብ ሰብሳቢ ተደርጎ የተመደበ ሲሆን ሌላዋ ሰንበት ተማሪ የመ/ር እንቁ ባሕርይ ቅምጥ የደብሩ ምክትል ሒሳብ ሹም በመሆን ስትሰራ የነበረቸው ወ/ት ምንጭቱ ከሒሳብ ሹሙ ጋር  ባለት የፍቅር ግንኙነት ቤተክርስቲኑ ውስጥ ያልተገባ ተግባር በመፈጸሟ ወደ ሌላ ቤተክርስቲያን መዛወሯን ለማወቅ ተችሏል፡፡
የገንዘብ ምዝበራውን ለማን አቤት ይባላል? ባለቤት የሌላት ቤተ ክርስቲያንን ከታች እስከላይ ወሮበሎች ወረዋታልና።