Wednesday, June 12, 2013

ጥያቄ፤ በክርስትና ሕይወቴ ኃጥአትን እንዴት ማሸነፍ እችላለሁ?






       ምንጭ፤    (michaelyemane.blogspot.com) 


ጥያቄ፤ በክርስትና ሕይወቴ ኃጥአትን እንዴት ማሸነፍ እችላለሁ?
መልስ፤ በጥረታችን ኃጥአትን ለማሸነፍ ይረዳን ዘንድ መጽሐፍ ቅዱስ ብዙ የተለያዩ መንገዶችን ያቀርባል፡፡ በዚህ ዕድሜ በኃጥአት ላይ ፍጽሞ በሚገባ ባለድል አንሆንም (1ኛ ዮሐንስ 1፡8)፤ ነገር ግን ያ አሁንም የእኛ ግብ ሊሆን ይገባል፡፡ በእግዚአብሔር ዕርዳታ እና የቃሉን መርሆች በመከተል በሂደት ኃጥአትን ማሸነፍ እና በበለጠ ክርስቶስን መምሰል እንችላለን፡፡
በጥረታችን ኃጥአትን ለማሸነፍ መጽሐፍ ቅዱስ የሚጠቅሰው የመጀመሪያው መንገድ መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን ሰጥቶናል ስለዚህም በክርስትና ህይወታችን ባለድል መሆን እንችላለን፡፡ እግዚአብሔር ወደ ገላትያ ሰዎች 5፡16-25 ውስጥ የሥጋ ሥራዎችን ከመንፈስ ፍሬዎች ጋር ያነጻጽራል፡፡ በዚያ ምንባብ ውስጥ በመንፈስ እንድንሄድ ተጠርተናል፡፡ ሁሉም አማኞች አስቀድሞ መንፈስ ቅዱስ አላቸው፤ ነገር ግን ይህ ምንባብ ለእሱ ቁጥጥር እየተገዛን በመንፈስ መሄድ እንደሚገባን ይነግረናል፡፡ ይህ በቋሚነት መንፈስ ቅዱ በህይወታችን ውስጥ ሥጋን ከመከተል ይልቅ በተከታታይ የመንፈስ ቅዱስን ምሪት መከተል መምረጥ ማለት ነው፡፡
መንፈስ ቅዱስ ማድረግ የሚችለው ልዩነት፤ በመንፈስ ቅዱስ ከመሞላቱ በፊት ኢየሱስን ሦስት ጊዜ በካደው በጴጥሮስ ህይወት ታይቷል፤ እናም ከዚህ በኋላ ክርስቶስን እስከሞት ድረስ እንደሚከተለው ተናግሮ ነበር፡፡ በመንፈስ ከተሞላ በኋላ በጴንጤቆስጤ በዓል ላይ በአደባባይ በድፍረት ለአይሁዶች ነገራቸው፡፡
የመንፈስን ምሪት ላለማጥፋት ለመሞከር በመንፈስ እንሄዳለን (በ1ኛ ተሰሎንቄ 5፡19 እንደተነገረው) እና በምትኩ በመንፈስ መሞላትን እንፈልግ (ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5፡18-21)፡፡ አንድ ሰው በመንፈስ ቅዱስ እንዴት ይሞላል? በብሉይ ኪዳን ውስጥ እንደነበረው ከሁሉ በፊት የእግዚአብሔር ምርጫ ነው፡፡ እሱ እንዲከወን የፈለገውን ሥራውን የሚያስፈፅሙ ግለሰቦችን መረጠ እና በመንፈሱም ሞላቸው (ኦሪት ዘፍጥረት 41፡38፤ ኦሪት ዘፀአት 31፡3፤ ኦሪት ዘዳግም 24፡2፤ 1ኛ ሳሙኤል 10፡10) በእግዚአብሔር ቃል ራሳቸውን እየሞሉ ያሉትን እነዚያን ሊሞላቸው እንደሚመርጥ ወደ ኤፌሶን ሰዎች 5፡18-21 እና ወደ ቆላስያስ ሰዎች 3፡16 ውስጥ ማረጋገጫ አለ፡፡ ይሄ ወደ ሁለተኛው መንገድ ይመራናል፡፡
የእግዚአብሔር ቃል፤ መጽሐፍ ቅዱስ፤ እግዚአብሔር ለየትኛውም በጎ ሥራ ሁሉ እኛን ለማስታጠቅ ቃሉን ሰጥቶናል ይላል (2ኛ ጢሞቴዎስ 3፡16-17)፡፡ እንዴት መኖር እንዳለብን እና ምን ማመን እንዳለብን ያስተምረናል፣ የተሳሳቱ ጎዳናዎችን በመረጥን ጊዜ ይገልጥልናል፣ ወደ ትክክለኛውም ጎዳና እንድንመለስ እና በዚያ ጎዳና እንድንቆይም ይረዳናል፡፡ የእግዚአብሔር ቃል ሕያው እና የሚሰራ እንደሆነ፣ ሥር ለመስደድ ወደ ልቦቻችን ዘልቆ ለመግባት እና ጥልቅ የሆኑትን የልባችንን ኃጥአቶች እና አመለካከቶችን ማሸነፍ እንደሚችል ወደ ዕብራውያን ሰዎች 4፡12 ይነግረናል፡፡ ዘማሪው በመዝሙረ ዳዊት 119 ውስጥ ስለ እሱ የህይወት ቀያሪነቱ ኃይል በጥልቀት ይናገራል፡፡ ኢያሱ ጠላቶቹን የማሸነፍ ውጤታማነት ቁልፉ ይህንን መንገድ ያለመርሳት እንዳልሆነ ነገር ግን በምትኩ በቀን እና በማታ ማሰላሰል እና እሱን መታዘዝ እንደሆነ ተነግሮታል፡፡ እግዚአብሔር ባዘዘ ጊዜ እንኳ በውትድርናው ስሜት የማይሰጥ ነገር ባይሆንም ይህን አደረገ፤ እና ይሄ ለተስፋይቱ ምድር ላደረገው ጦርነት የድሉ ቁልፍ ነበር፡፡
እኛ ራሳችን ብዙውን ጊዜ በቀላሉ የምናየው መንገድ መጽሐፍ ቅዱስ ነው፡፡ ወደ ቤተክርስቲያን መጽሐፍ ቅዱሶቻችንን በመሸከም ወይም የቀን ጥሞና ወይም በቀን አንድ ምዕራፍ እያነበብን ምልክታዊ አገልግሎት እንሰጣለን፣ነገር ግን እሱን ማሰቡን ፤ እሱን ማሰላሰሉን ወይም በኑሮዎቻችን ላይ ተግባራዊ ማድረጉን ትተናል፣ እሱ የሚገልጣቸውን ኃጥአቶቻችንን መናዘዝ ወይም ለእኛ ለሚገልጣቸውን ስጦታዎች እግዚአብሔርን ማመስገን ትተናል፡፡ ወደ መጽሐፍ ቅዱስ በሚመጣበት ጊዜ እኛ ብዙውን ጊዜ ምግብ ያስጠላቸው ወይም አመጋገባቸው የተዛባብን ነን፡፡ ከቃሉ በመመገብ በመንፈሳዊው እንዲያው በህይወት እንዲያቆየን ያህል (ነገር ግን ጤናማ እና የሚፋፉ ክርስቲያኖች እንድንሆን ፈጽሞ የሚበቃንን ያህል አንበላም) ወይም ብዙ ጊዜ ልንመገብ እንመጣለን ነገር ግን መንፈሳዊ ምግብን ከእሱ ለማግኘት ለረጅም ጊዜ በፍጹም አናሰላስለውም፡፡
እሱ ጠቃሚ ነው፣የእግዚአብሔርን ቃል በየቀኑ የማጥናትና የማሰላሰል ልምድ ካላደረግህ ያን ማድረግ ትጀምራለህ፡፡ ጥቂቶች የሚረዳ ጅማሬ ሆኖ አግኝተውታል፡፡ ከእሱ ያገኘኸውን አንድ ነገር እስከምትጽፍ ድረስ ቃሉን ላለመተው ልምድ አድርገው፡፡ ጥቂቶች እነርሱን በተናገራቸው ዙሪያ ይለወጡ ዘንድ እንዲረዳቸው በመጠየቅ ወደ እግዚአብሔር የሚደረጉትን ፀሎቶች ይመዘግባሉ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ በሕይወታችን ውስጥ መንፈስ የሚጠቀምበት መሳሪያ (ወደ ኤፌሶን ሰዎች 6፡17)፤ እግዚአብሔር መንፈሳዊ ውጊያዎቻችንን እንድንዋጋ የሰጠን ጠቃሚ እና ዋነኛ የጦር ዕቃ አካል (ወደ ኤፌሶን ሰዎች 6፡12-18) ነው፡፡
በኃጥአት ላይ ለምናደርጋቸው ውጊያዎቻችን ሦስተኛው ዋነኛ መንገድ ፀሎት ነው፡፡ አሁንም ብዙውን ጊዜ ክርስቲያኖች የከንፈር አገልግሎት የሚሰጡበት መንገድ ነው ነገር ግን ጥቅሙን ደካማ ያደርጋል፡፡ የፀሎት ስብሰባዎች፣ የፀሎት ጊዜያቶች ወ.ዘ.ተ. አሉን ነገር ግን ጸሎትን የጥንቷ ቤተክርስቲያን በምትጠቀምበት መንገድ አልተጠቀምንበትም (የሐዋርያት ሥራ 3፡1፣4፡31፣6፡4፣13፡1-3)፡፡ ጳውሎስ ያገለግላቸው ለነበሩት እንዴት ይፀልይ እንደነበር በተደጋጋሚ ይጠቅሳል፡፡ እግዚአብሔር ጸሎትን በተመለከተ የሚያስደንቁ ተስፋዎችን ሰጥቶናል (የማቴዎስ ወንጌል 7፡7-11፣ የሉቃስ ወንጌል 18፡1-8፣ ዮሐንስ ወንጌል 6፡23-27፣ 1ኛ ዮሐንስ መልዕክት 5፡14-15)፣ እና ጳውሎስ ለመንፈሳዊ ውጊያ በመዘጋጀት ምንባቡ ውስጥ ፀሎትን ያካትታል (ወደ ኤፌሶን ሰዎች 6፡18)፡፡
በኑሮዎቻችን ኃጥአትን በማሸነፉ ፀሎት እንዴት ጠቃሚ ነው? ልክ ከጴጥሮስ ክህደት በፊት በጌተሰማኔ የአትክልት ሥፍራ ለጴጥሮስ የክርስቶስ የሆኑ ቃላቶች አሉን፡፡ ኢየሱስ እየጸለየ ጴጥሮስ እየተኛ ነው፡፡ ኢየሱስ አነቃውና እናም አለው “ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ፤ መንፈስስ ተዘጋጅታለች ሥጋ ግን ደካማ ነው አለው።”(የማቴዎስ ወንጌል 26፡41) እኛ እንደ ጴጥሮስ ትክክል የሆነውን ማድረግ እንፈልጋለን ነገር ግን ጥንካሬውን እያገኘን አይደለም፡፡ መፈለጋችንን ፣ ማንኳኳታችንን፣ መጠየቃችንን ለመቀጠል የእግዚአብሔርን ተግሳጽ መከተል ያስፈልገናል እናም ያ የምንፈልገውን ጥንካሬ ይሰጠናል (የማቴዎስ ወንጌል 7፡7)፡፡ ጸሎት ምትሃታዊ ዘይቤ አይደለም፡፡ ጸሎት በቀላሉ የእኛን የራሳችንን ድክመትና የእግዚአብሔርን የማይወሰነውን ኃይል ማረጋገጥ እና እኛ ማድረግ የምንፈልገውን ሳይሆን እሱ እንድናደርገው የሚፈልገውን ለማድረግ ለዚያ ጥንካሬ ወደ እሱ መዞር ነው (1ኛ ዮሐንስ መልዕክት 5፡14-15)
ኃጥአትን ለመማረክ በምናደርገው ጦርነታችን ውስጥ አራተኛው መንገድ፤ የሌሎች አማኞች ህብረት፤ ቤተክርስቲያን ነው፡፡ ኢየሱስ ደቀመዛሙርቱን በላከበት ጊዜ ሁለት ሁለት አድርጎ ላካቸው (የማቴዎስ ወንጌል 10፡1)፡፡ በሐዋርያት ሥራ ውስጥ ያሉ ሚሲዮኖች በአንድ ጊዜ አንድ ሆነው አልወጡም ነበር ነገር ግን ሁለት ወይም ከዚያ በላይ በሆነ ማህበር ነበር፡፡ ኢየሱስ አንድ ላይ መሰብሰባችንን እንዳንተው ነገር ግን ያን ጊዜ በፍቅር እና በመልካም ሥራዎች እርስ በራሳችንን ለማበረታታት እንድንጠቀምበት አዞናል (ወደ ዕብራውያን ሰዎች 10፡24)፡፡ አንዳችን ለአንዳችን ስህተታችንን እንድንናዘዝ ይነግረናል (የያዕቆብ መልዕክት 5፡16) በብሉይ ኪዳን በጥበብ መጽሐፍ ውስጥ ብረት ብረትን እንደሚስል ተነግሮናል፥ ስለዚህ አንድ ሰው ሌላውን ይስላል (መጽሐፈ ምሳሌ 27፤17)። በቁጥሮች ውስጥ ጥንካሬ አለ (መጽሐፈ መክብብ 4፡11-12)፡፡
ብዙ ክርስቲያኖች የሚከብዱ ኃጥአቶችን በማሸነፉ ረገድ ኃላፊነትን የሚወስድ ወዳጅ መኖር በጣም ትልቅ ጥቅም መሆን እንደሚችል ያን አግኝተዋል፡፡ ከአንተ ጋር ሊያወራ፤ ሊፀልይ፣ ሊያበረታታህ፤ እና እንዲያውም የሚገጽህ የሚችል ሌላ ሰው ማግኘት ትልቅ ዋጋ አለው፡፡ ፈተና ለሁላችንም ያለ ነው (1ኛ ቆሮንቶስ 10፡13) ኃላፊነትን የሚወስድ ወዳጅ ወይም ኃላፊነትን የሚወስድ ማህበር መኖሩ እንዲያውም በጣም ከባድ የሆኑትን ኃጥአቶችን ለማሸነፍ የሚያስፈልገንን የመጨረሻውን የማበረታቻ እና የመነሳሳት መጠን ሊሰጠን ይችላል፡፡
አንዳንድ ጊዜ በኃጥአት ላይ ድል መንሳት በፍጥነት ይመጣል፡፡ ሌላ ጊዜ ድል በጣም በዝግታ ይመጣል፡፡ እግዚአብሔር የእሱን መንገዶች ስንጠቀም ለውጥን በህይወታችን በሂደት እንደሚያመጣ ቃል ገብቷል፡፡ ኃጥአትን ለማሸነፍ ጥረታችንን በቀጣይነት መቀጠል እንችላለን ምክንያቱም እሱ በቃሉ ታማኝ እንደሆነ እናውቃለን፡፡

Thursday, June 6, 2013

የፕሬዚዳንት ሞርሲና የፓርቲዎች ጉባዔ በዐባይ ጉዳይ


መምሪ በተባለው የግብጽ ቴሌቪዥን የቀጥታ ስርጭት የተደረገ ውይይት) 

የነጻነትና ዲሞክራሲ ፓርቲ ሊቀመንበር እንዲህ አሉ፤ 

«ድምጼን አሰምቼ በግልጽ መናገር የምፈልገው ነገር ሁሉም አማራጮች ለእኛ አስፈላጊዎች መሆናቸውን ነው። እናም ሁሉንም አማራጮች እንደግፋለን፤ ነገር ግን ሂደቱ በየደረጃው መሆን ይገባዋል። የንግግር ግንኙነታችን ሂደቱን መቀየር ካልቻለ ወደዓለም ዐቀፉ የግልግል አካል እናቀርበዋለን። ይህም ካልተሳካ ማንም ሊገምተው እንደሚችለው የውሃ ዋስትናችንን ለመከላከል ወደሌላ አማራጭ እንገባለን። ምክንያቱም የውሃ ዋስትና  ለእኛ የሞት ወይም የሕይወት ጉዳይ ነውና።


የአልኑር ፓርቲ ፓርቲ ሊቀመንበር በተራቸው እንዲህ አሉ፤

አሁን እየተካሄደ ባለው የዐባይ ስምምነት ማዕቀፍ ላይ ግብጽ ከተስማማች አደገኛ ስትራቴጂካዊ ስህተት መፈጸሟ ነው። ምክንያቱም በዚህ ጉዳይ ላይ አሜሪካ፤ እስራኤልና ኢትዮጵያ ከጉዳዩ ጀርባ አሉና። ምክንያቱም በዚህ ስምምነት ግብጽን በመጉዳት ርካሽ የፖለቲካ ጫና ለማሳረፍ ሲሉ ነው። እኛም እንደእነሱ ለማድረግ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ውስጥ 35%  ኦሮሞ ስለሆነና ኦሮሞም ለመገንጠል የሚዋጋለት ኦነግ የሚባል ድርጅት ስላለው ለእሱ ሁለመናዊ ድጋፍ ማቅረብ አለብን። በሀገር ቤት ያለው ፖለቲካዊ የተቃውሞ መድረክ ደካማና ልፍስፍስ ስለሆነ ለመገንጠል በሚዋጉት እንደኦጋዴን ነጻነት ግንባር ያሉትን መደገፍ ይገባናል። ይህም በኢትዮጵያ መንግስት ላይ የተቀናጀ ጫና እንድናሳርፍ ያስችለናል። ይህ ሁሉ ተደርጎ  ውጤት ካላስገኘልን ሌላው አማራጭ ለግብጽ ኅልውና አደገኛ የሆነ ማንኛውንም ግድብ ለማውደም የምንችልበት ሁኔታ መፍጠር ነው። ለዚህም አስተማማኝ የደኅንነት መረጃ መኖር አለበት። ምክንያቱም አንዳንድ ጠበብቶች ግድቡን መጀመር በራሱ አደገኛና ጦርነት የማወጅ ያህል እንድንቆጥር በቂ ማስረጃ ነው እያሉን ነውና።

የአል አዝሃር ዩኒቨርሲቲ የሃይማኖት መምህር የሆኑት ደግሞ በተራቸው፤

አስታውሳለሁ፤ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ግብጽ በመጣበት ወቅት በግብጽ ሕዝብ ላይ አላግጦ ነው የሄደው። ዐባይ ክንፍ የለውም፤ ወደእስራኤልም አይበርም አለ፤ ነገር ግን ማንኛውም ህዝብ እንደሚያውቀው የግብጽ ሕዝብም ያውቃል። የዓባይ ወንዝ በቀይባህር ስር የሚሄድበት የራሱ የቧንቧ መስመር ስውር ክንፍ አለው። ማንም ሀገር በቧንቧ መስመር ውሃ ወደሀገሩ እንደሚያስገባ ይታወቃል፤ ሲሉ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩን በመቃወም ዐባይ ክንፍ አለው ብለዋል።  

የገድ አልተውራ ፓርቲ ሊቀመንበር ደግሞ ተራቸውን ጠብቀው እንዲህ አሉ፤

እንደዚህ ይባል ወይም አይባል እንደሆነ አላውቅም፤ ነገር ግን አንዱ ጓደኛዬ ቅድም እንዳለው ኢትዮጵያ ብዙ ተቃዋሚዎች እንዳሏት ይታወቃል፤ እዚያም የተለየ እንቅስቃሴ እያየን ነው። የግብጽ ኤምባሲ ኢትዮጵያ ውስጥ መኖሩ ምን ያደርግልናል? አስፈላጊ ነገር አሁን የፖለቲካና የመረጃ ክፍሎቻችን ብቻ ናቸው። በኢትዮጵያ ወቅታዊ ተጨባጭ ሁኔታ ላይ ተመርኩዘን ሚና መጫወት አለብን። ይህንን ማስኬድ መቻል በትንሽ ወጪ ብዙ መስራት የሚያስችለን ሲሆን አጸፋዊ አደጋውም የቀነሰ ነው። በደንብ አድርገን በውስጥ ጉዳያቸው ብዙ መስራት ከቻልን ማዳከም ይቻለናል። አንድ የኢትዮጵያ ጋዜጣ እንዲህ አለ፤ ግብጽ የጦርነት ሃሳብ የላትም። ይህንን የማድረግ ብቃት የላትም፤ ሚሳይል የላትም፤ አውሮፕላን የላትም፤ ቢኖራትም ሱዳን በክልሏ ላይ ይህ እንዲደረግ አትፈቅድም ብሏል። በእርግጥም የሱዳኖች ሁኔታ ለእኛ በጣም የሚያሳምም ነው። ሁኔታዋ ማድረግ ከሚገባት አንጻር ሲታይ በጣም ደካማ ነው።  በእኛም በኩል መረጃ ፍሰት ችግር አለ።  ግብጽ የጦር አውሮፕላን ልትገዛ ነው፤ በአየር ላይ ነዳጅ መሙላት የሚችል አውሮፕላን አላት ወዘተ የሚሉት መረጃዎች መውጣት አለባቸው፤ በእርግጥ ባይሆንም እንኳን መረጃው በዲፕሎማሲያዊ ጥረታችን ላይ የራሱን ተጽዕኖ ያሳርፋል።

የሪፎርምና ደቨሎፕመንት ፓርቲ ሊቀመንበር ደግሞ ተራውን ተረክበው እንዲህ ዶለቱ፤

እኛ ባለን ግንዛቤ የብሔራዊ ቡድናችን ኢትዮጵያ ሄዶ ባደረገው ጫወታ ተጽእኖ በመፍጠር ማሸነፍ መቻሉን ነው። ብሔራዊ ቡድናችን የአፍሪካ ሻምፒዮን መሆኑና እጅግ በአመርቂ ውጤት ጫና መፍጠር መቻሉ በራሱ የሚያሳየው እውነትም ግብጻውያን ጫና የመፍጠር ጥበብ እንዳለን ነው። ትልቅም ተጽዕኖ የመፍጠር አቅም አለን። የግብጽን ቤተክርስቲያንና የአልሃዛር ስኮላሮችን በዚህ ጉዳይ መጠቀም እንችላለን። አንዳንዶች የጦርነት አማራጮች ሊኖር እንደሚችል ያወራሉ። የሚወራውን ነገር ለመተግበር አስቸጋሪ ነው። እንደዚህ ዓይነቱን እሳቤ መነቀፍ ይገባዋል። ከዚህ ይልቅ የግንኙነት ምህዋራችንን ከኤርትራ፤ ከሶማሊያና ከጅቡቲ ጋር ብናደርግ ለደኅንነታችን ክፍሎች ትልቅ መስክ ነው።  ይህንን ማድረግ ጥሩ ከመሆኑም ባሻገር ግንኙነት የማድረግ መብታችንም እንደመጠቀም ስለሆነ ተገቢ ነው። ተስፋችን ሲጨልም ደግሞ ሃሳባችንን መፈጸም የምንችልባቸው በተዘዋዋሪ አንድ መቶ መንገዶች ስላሉን ሁሉንም እናደርጋለን።

የኢስላሚክ ሌበር ፓርቲ ሊቀመንበር ደግሞ ምኞታቸውን ከፍ አድርገው ተናገሩ፤

እኔ ከጠላቶቻችን ጋር ጦርነት የምናደርግበት ቀን ናፍቆኛል፤ በእርግጥም ከእስራኤልና ከአሜሪካ ጋር። ጦርነቱ ከፍተኛ ዋጋ አስከፍሎ ተገቢውን ፍትህና እርጋታ የሚያመጣ መሆን ከቻለ። ምንም እንኳን ይህ ውይይት ምስጢራዊ ውይይት እንደመሆኑ ሁሉንም ነገር በምስጢር መያዝ ይገባናል። ውይይታችን ወደሚዲያ ሾልኮ መውጣት የለበትም። በእህታችን በባኪናም በኩል በግልጽ ከሚወጣው በስተቀር። ሕዝባዊ የሀገራዊ ደኅንነት እቅድ በግልጽ እንዲኖር እንፈልጋለን። እኛ እንዲህ ቢሆንም እንኳን………. (አቋረጡ) ቀጠሉና እሺ…..መልካም………እኔ የማነሳቸው ነጥቦች አግባብ ከመሆናቸው ጀርባ በእርግጥም ምንም ምስጢርነት የላቸውም። ውጊያችን ከአሜሪካና ከእስራኤል ጋር እንጂ ከኢትዮጵያ ጋር አይደለም። ስለዚህ ውጊያችንን ለማስኬድ ፤ ይህ የኔ ሃሳብ ነው……….( ፕሬዚዳንት ሙርሲ ጣልቃ ገቡና፤ ይህ ውይይት እኮ በቀጥታ ስርጭት እየሄደ ነው ያለው! አሉ) የኢስላሚክ ፓርቲው ሊቀመንበርም፤ እኔም የምስጢር እቅድ ወይም ፕላን ማብራሪያ እየሰጠሁ አይደለም!  ሲሉ በጉባዔው ሳቅ ሆነ።  ቀጥለውም «እኔ ያልኩትን እኮ ማንም ሀገር የሚያደርገው ነው፤ በሌሎችም ሲባል የቆየ ነው» አሉ። (የጉባዔው ረጅም ሳቅ!!)
ማንም ሀገር ለከባቢያዊ ጥቅሙ የሚያደርገው ነው። እኔ ለግብጽ ሕዝብ የምለው ማንም ተነስቶ የውሃ አቅርቦትህን ሊዘጋ አይችልም ነው። የግብጽን ሕዝብ የዓለም አደገኛው የጽንፈኝነት መንገድ እንዲገባ ካልፈለጉ በስተቀር ይህን አያደርጉም። እስኪ አስቡት 80 ሚሊዮን ግብጻዊ ውሃ ሲዘጋበት በአሜሪካና በእስራኤል ላይ ምን የሚያደርግ ይመስላችኋል?

ፕሬዚዳንት ሙርሲ፤ የልባቸውን በልባቸው ይዘው፤ በዲፕሎማሲያዊ  ቋንቋ ደስ የተሰኙበትን ገታራ ውይይት አለዝበው እንዲህ ሲሉ ደመደሙ።  

«እኛ ለሰሜንና ደቡብ ሱዳናውያን የከበረና የተትረፈረፈ አክብሮት አለን» አሉና የሱዳንን ዳተኝነት ሸነገሉ። «ውሳኔዎቻቸውን ሁሉ እናከብራለን» ሲሉ በማሞካሸት ጠላት ማፍራት እንደማይገባ በውሰጠ ታዋቂ ጠቆሙ። እንደዚሁም ሁሉ «ለኢትዮጵያ ሕዝብም ያለን አክብሮት ተመሳሳይ ነው!» አሉና ዙሪያ ገባህን እሳት እንለኩሳለን ሲል ለቆየው ጉባዔ ማለስለሻ ቫዝሊን ቀቡት። እኛ የትኛውንም ጀብደንነት ጀማሪዎችና በማንም ላይ አሳቢዎችም አይደለንም አሉ። ነገር ግን አሉ ፕሬዚዳንት ሞርሲ፤ ነገር ግን መታወቅ ያለበት  እያንዳንዷን የዐባይ ውሃ ጠብታ ለመከላከል እጅግ የጠነከረ እርምጃ የምንወስድ መሆናችን ነው። ለእያንዳንዷ ጠብታ ውሃ!
(ተፈጸመ)

Wednesday, June 5, 2013

የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት እንዲሰነጣጠቅ ሲኖዶስ የወሰነው ለምንድነው?( ከዚህ በፊት የቀረበ ጽሁፍ)

            መንበረ ፓትርያርክ ቅ/ማርያም ቤ/ክ 1921 ዓ/ም (ፎቶ ምንጭ፤ ሰሎሞን ክብርዬ) 
          
ይህንን ጽሁፍ በጥቅምት/2004 ዓ/ም ሲኖዶስ ማብቂያ ላይ በዚሁ መካነ ጦማራችን አውጥተን ነበር። ዛሬ እንደገና መድገም ያስፈለገን በወቅቱ ቅዱስ ሲኖዶስ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከትን አራት ቦታ መከፋፈሉን በመቃወም ፤ ተገቢ እንዳልሆነና ጥናት ያልተደረገበት አሠራር ስለሆነ ውጤቱ ኪሳራ መሆኑን አመልክተን የነበረው በትክክል እንዳልነው ውጤቱ ኪሳራ ሆኖ በመገኘቱ ቅ/ሲኖዶስ በ2005 ዓ/ም ጉባዔው  ከግብታዊ ውሳኔው በመውጣት ሀገረ ስብከቱን ወደነበረበት ሲመልስ በማየታችን ነው። አሁንም ደግመን የምንለው የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ወደነበረበት የቀድሞ ተቋማዊ መልኩ መመለስ ብቻ ሳይሆን የሥልጣን ክፍፍል እንዲኖረው ማስቻል ገና የሚቀረው ሂደት ነው እንላለን። ይኸውም የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት በሠራተኛ ብዛት፤ በገቢ አቅም፤ በማዕከላዊ ተቋምነቱ ሠፊና ትልቅ ሀ/ስብከት ስለሆነ ሥልጣንን ሁሉ አንድ ቦታ ሰብስቦ እንዲይዝ የሚያደርገው ሁኔታ ስላለ ከሙስና፤ ከአድልዎ፤ ከፍትህና ውሳኔ አሰጣጥ መዛባት አንጻር ለቁጥጥር የማያመች፤ የአሰራር ዝርክርክነት የሚያስፋፋ ችግር እንደበፊቱ ተመልሶ ሊመጣ ስለሚችል ሥልጣን መከፋፈል አለበት እንላለን። ይህንንም የሥልጣን ክፍፍል በታወቀና በተወሰነ የአሠራር ደንብ ላይ ተመርኩዞ በወረዳዎች ደረጃ ወደታች መውረድ ይኖርበታል። ስለሆነም እንደእኛ እምነት ሀገረ ስብከቱን በአራት የወረዳ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በተሟላ አደረጃጀት አዋቅሮ ሥልጣን  መውረድ ካልቻለ ከችግሮች አዙሪት አለመውጣት ብቻ ሳይሆን ሀ/ስብከቱ የትናንሽ መንግሥታት ቢሮ ከመሆን አይዘልም። ሀገረ ስብከቱን ወደነበረበት ተቋማዊ አደረጃጀቱ መመለስ  ማለት የሥልጣን ጡንቻውን እንደገና አንድ ቦታ ማፈርጠም ማለት ሳይሆን ሥራን ከፋፍሎ ለመሥራት ያለመና የተሻለ ርእይ የያዘ መሆን ስለሚገባው አሁንም ይህ ይፈጸም ዘንድ ከችግሮች በፊት አበክረን እናሳስባለን።
በወቅቱ የሀ/ስብከቱን ክፍፍል በመቃወም ያወጣነውን ጽሁፍ ለማስታወስ ቀንጭበን ከታች አቅርበናል።

 ከዚህ ውስጥ ዋነኛውና አስደናቂው ውሳኔ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከትን ሰነጣጥቆ የማጠናቀቁ ሂደት አንዱ ነበር።
የአዲስ አበባ ሀ/ስብከትን ችግር ጠንቅቆ የሚያውቅ የሲኖዶስ አባል የለም። ጳጳሳቱ የተመደቡባቸውን ሀ/ስብከቶች ለሥራ አስኪያጆቻቸው አስረክበው ሁለትና ሦስት ወራት ከአዲስ አበባ ቤቶቻቸው መሽገው ወለተ ማርያምንና ገ/ማርያምን እያሳለሙ እንደሚቀመጡ ይታወቃል። ግድ እየሆነባቸው እንጂ ሐዋርያዊ ተልእኰ ለመፈጸም ዝግጁዎቹ ጥቂቶች ናቸው። ስለዚህ አብዛኛዎቹ ጳጳሳት በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ለመመደብ ያላቸው ፍላጎት ጫን ያለ ነው። ይህንኑ ጽኑ ምኞት ለመተግበር የአዲስ አበባ ሀ/ስብከትን ከፓትርያርክ ጳውሎስ ልዩ ሀ/ስብከትነት  በማላቀቅ 4 ቦታ እንዲከፈልና 4 ሊቃነ ጳጳሳት ሊመደቡበት ይታገሉ እንደነበር ያለፉት ጉባዔያቶቻቸው ያስረዱናል። ተፈላጊው ነገር የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ችግሮች ምን እንደሆኑ በማወቅ መፍትሄ ለማምጣት ሳይሆን የአቡነ ጳውሎስን ስልጣን ከሀ/ስብከቱ ላይ በመቀማት 4 ጳጳሳት ተመድበውበት የሞቀ የደመቀውን በማግኘት ከክፍለ ሀገር ሀሩርና አቧራ ለመገላገል ብቻ ነበር። የሚገርመው ነገር ዛሬ አቡነ ጳውሎስ በሌሉበት ሁኔታ ውስጥ ፍላጎታቸውን ተግባራዊ ለማድረግ መቻላቸው ሳይሆን ለምን? እንዲከፈል እንደተፈለገ አለማወቃቸው ነው። ምክንያቱም ሀ/ስብከቱን እንደዓይናቸው አምሮት ከመሰነጣጠቃቸው በቀር ለምን መሰነጣጠቅ እንዳስፈለገ የተናገሩት አሳማኝና ጥናታዊ መረጃ ያለውን ዝርዝር ነገር ሲነግሩን አለመደመጡ ነው። እንደ ደጀብርሃን ብሎግ እምነት የአዲስ አበባ ሀስብከት መሰንጠቅ የተፈለገው በሁለት ምክንያት እንደሆነ ከፍላጎቶቻቸውና ከዓላማዎቻቸው አንጻር እንረዳለን።
1/ ከሚመጣው ፓትርያርክ ልዩ ሀ/ስብከትነት ነጻ በማውጣት ለሚመደቡ ጳጳሳት ልዩ የደስታ ግዛት ለመፍጠር፤
2/ ለአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የአንድ ሰው ግዛት አድርጎ ከማቆየት ይልቅ ከፋፍሎ ለሌሎችም ቶሎ እንዲዳረስ ለማስቻል ነው ብለን እንገምታለን። ምክንያቱም መሰነጣጠቅ ያስፈለገው ምን ለማምጣት እንደሆነ አሳማኝ ነገር አለመቅረቡ ነው።
በኛ እምነት የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት መሰንጠቅ ትክክለኛ ያልሆነ ውሳኔና የሀ/ስብከቱን ችግር ያልተመለከተ ስሜታዊ ውሳኔ ነው እንላለን። ምክንያቶቻችንም ለሀ/ስብከቱ የተሻለ መንገድ መኖሩን በማመላከት ይሆናል።
1/ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የሀገሪቱና የአፍሪቃ ዋና ከተማ ከመሆኑም ባሻገር የቤተክርስቲያኒቱ ማእከላዊ ሀ/ስብከት  በመሆኑ ሁኔታዎችን የገመገመና ወቅቱን ያገናዘበ  ልዩ መተዳደሪያ ደንብ ሊኖረው የተገባ ነው።
2/ የሀ/ስብከቱ ጽ/ቤት አወቃቀር የመንግሥትንና ዓለምአቀፍ ተቋማትን ደረጃ ያገናዘበ ዘመናዊ፤ ሙያዊና ችሎታን የተመረኮዘ የአስተዳደር መዋቅር  የያዘ መሆን ይገባው ነበር።
3/ አሁን ያሉትን ስድስት ሥራ ፈት የወረዳ ጽ/ቤቶችን ወደ አራት በማጠቃለል በአውራጃ ጽ/ቤት ደረጃ ሥልጣንና ኃላፊነት ከሀ/ስብከቱ  ከፍሎ በመስጠት እንደአዲስ ቢደራጅ ስልጣን የተሰበሰበበትን የሀ/ስብከቱን  ማእከል ጫናና ድርሻ ከመቀነሱም በላይ ተጠያቂነት ያለው አሠራርን ማስፈን ይቻል ነበር።
4/  የሀ/ስብከቱ አድባራትና ገዳማት የአስተዳደር መዋቅር በሀ/ስብከቱ መተዳደሪያ ደንብ በትክክል የተቀመጠውን የተከተለ መሆን የሚገባው ሲሆን ሙያን፤ ችሎታን፤ ብቃትን፤ ልምድንና መልካም ሥነ ምግባር የተከተለ የአስተዳደር መዋቅር ሊፈጠርበት ይገባዋል።
5/ በየአድባራት ያሉትን ከመጠን በላይ ያለውን የሠራተኞች ቁጥር  ወደሌላ የልማት ዘርፍ በመቀነስ እንደ አዲስ ማደራጀት የግድ መሆን አለበት።ይህ የልማት ዘርፍ ከደመወዝ ጠባቂነት ይልቅ አምራች ዜጋ እንዲኖርና የሚፈልሰውን ቅጥር ፈላጊ ለመከላከል የሚያስችል ነው።
6/ የሀ/ስብከቱ  ጽ/ቤት አድባራቱ በጋራ  ያላቸውን ካፒታል በማሰባሰብ በሚያቋቁሙት የልማት ተቋም የገቢ አቅም እንዲፈጥሩና ከልመና ገንዘብ እንዲላቀቁ ማድረግ ይጠበቅበታል። ለምሳሌ በጋራ ገንዘባቸው፤ ማተሚያ ቤት ወዘተ ማቋቋም ይቻላል።
7/ ቤተክርስቲያኒቱ ብዙ ባለሙያና አዋቂ ምእመናንና ምእመናት እያሏት ከዳር ሆነው ድክመቷን እየተመለከቱ፤ እሷም ልትጠቀምባቸው ሳትችል መቅረቷ ይታወቃል። በሀ/ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ የሚደራጅ የምሁራን ልጆቿ የአማካሪ ቦርድ ቢኖረው ሀ/ስብከቱ ተጠቃሚ ይሆናል።
ሌሎች ተጨማሪና አስፈላጊ ነጥቦችን ለመፍትሄው በማስቀመጥ አሁን ያለውን የአዲስ አበባ ሀ/ስብከትን ችግር ማቃለል እየተቻለ ሲኖዶስ ሀ/ስብከቱን መሰነጣጠቅ መፈለጉ ትክክል አይደለም። የትኞቹን ችግር በየትኞቹ መንገዶች ለማቃለል ተፈልጎ ነው ሀ/ስብከቱን በብዙ ሊቃነ ጳጳሳት ስር መሰንጠቁ ያስፈለገው? ለሚለው ጥያቄ  አሳማኝ መልስ የለም።
የአዲስ አበባ መስተዳደር እንኳን የሚተዳደረው በአንድ ከንቲባ ሥር ሆኖ ራሳቸውን ችለው በተወሰነ ሥልጣንና ኃላፊነት በተደራጁ ክ/ከተሞች እንጂ በልዩ ልዩ ከንቲባ ተሰነጣጥቆ አይታይም። የኛዎቹ በብዙ የሊቀ ጳጳስ ከንቲባ ሥር ሀ/ስብከቱን ከፋፍለው ሲያበቁ በሀ/ስብከቴ ጣልቃ አትግባ የሚል ድምጽ ለማስማትና አንድ ሠራተኛ  ከአንድ ክፍል ውስጥ ወደ ሌላኛው ክፍል እንዳይዘዋወር የሚያደርግ ስለሆነ ይህንን መፈለጋቸው አስገራሚም አሳዛኝም ነው። ውጤቱም አሳዛኝ ከመሆን አይዘልም።
ለወትሮውስ ቢሆን ርዕይና ግብ ከሌለው ጉባዔ ከዚህ የተሻለ ምን ሊጠበቅ ኖሯል? ሲኖዶሱ ራሱ ተሰነጣጥቆ አዲስ አበባንም በፈቃዱ ሰነጣጥቆ አረፈው። የ10 ቀናት ውጤት ይህ መሆን ነበረበት? ለአንባቢዎች የምናስገነዝበው ጽሁፋችን ለነቀፋ ሳይሆን በተገቢ ሂስ፤ አሳማኝ መልስ የሚሰጥ ካለ ያንን ለማግኘት ሲሆን መሠረቱም በሚታይ ገሃዳዊ እውነታ ላይ ተመስርተን ብቻ መሆኑን እንድታውቁልን ነው።