Wednesday, March 6, 2013

የይሖዋ ምስክሮች መሠረት ምንድነው?


ይህንን መረጃ ለማውጣት መነሻ የሆነን አንድ ጠያቂያችን ባቀረበው ጥያቄ ሲሆን ሌሎችም ስለይሖዋ ምስክሮች አነሳስ የበለጠ ግንዛቤ እንዲያገኙ በማለት እንዲያነቡ ወይም ዳውንሎድ እንዲያደርጉ አቅርበነዋል።በቀኝ ጠርዝ ያለውን ምልክት ተጭነው ገጹን ማስፋት ይችላሉ።

Monday, March 4, 2013

«ያዘዝሁህንም ቃል ኪዳኔንና ሥርዓቴን አልጠበቅህምና መንግሥትህን ከአንተ ቀዳድጄ ለባሪያህ እሰጠዋለሁ»

ከኒቆዲሞስ

 የተወደዳችሁ ደጀብርሃኖች እንደስማችሁ ብርሃንናሰላም ሊያመጣ የሚችል ጽሑፍ እያወጣችሁ እያስነበባችሁንና እንድንረዳላችሁ እየሞከራችሁ ነውና እግዚአብሔር ይስጥልን::በተቻለ መጠን በተለይ በተከፋፈልችው ቤ/ክርስቲያናችን ውስጥ ሰላም እንዲሆን የምትጽፉት ጽሑፍና ጥረታችሁ ያስመሰግናችኋል::ግን አንድ ነገር አስተውለን ይሆን?መለያየትና መከፋፈል መልካም ጎን የለውም እንደምንል ሁሉ መለያየት በመጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር ራሱ ያደረገበትን የእስራኤል ነገድን ሕዝብ ታሪክ በማን ልናላክክ ነው?በሰይጣን ወይስ በሰው?ታውቃላችሁ በ1ኛ ነገሥት ምዕራፍ 11:9-13 እና 29-40 ድረስ ያለውን ስናነብ የምናየው የማንን ሥራ ነው?ታዲያ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ ብትከፋፈል ምን ያስደንቃል?እኔ ፈራጅ ባልሆንና ባልናገር እውነቱንና ሐቁን ግን ለማሳየት እሞክራለሁ!!
 ( ቀሪውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ )

ጥንቆላ - በሀገራችን ፣ በቤተ ክርስቲያናቸን እንዲሁም በእያንዳንዳችን ላይ ሊኖረው የሚችለው ተጽዕኖ


ክፍል ሁለት         (www.abaselama.org)


ባለፈው ጽሑፌ ጥንቆላ ምን እንደሆነ ጥቂት ለማሳየት ሞክሬያለሁ፤ በሰፊው ግን አልገለጥሁትም። የሰይጣንን ክፋት በሰፊው ከመግለጥ የእግዚአብሔርን ደግነት አጉልቶ መግለጥ ይሻላል የሚል እምነት ስላለኝ ነው። ነገር ግን ወገኖቼ በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ጥንቆላን እንደቀላል ልማድ በማየት በጨለማው ገዢ ሥር ሲወድቁ እያየሁ ስለማዝን እውነታውን ለማሳየት ምክሬያለሁ። ዛሬ ደግሞ አንዳድ መናፍስት ጠሪዎችና ደጋሚዎች የሚያጠምቁበትን ዘዴ ከአንድ ደብተራ ጓደኛዬ ያገኘሁትን ምስጢር በጥቂቱ መግለጥ እሞክራለሁ።


አስማቱ በመስቀል፤ በጣት ቀለበት እና በመቁጠሪያ ሊሠራ ይችላል። በመስቀል ቅርጽ እንዲሁም በመቁጠሪያነት ለድግምቱ የሚያገለግሉ እጸዋት ሁለት ናቸው። አንደኛው አርግፍ የሚባል ሲሆን ሁለተኛው ጠንበለል ይባላል። እጸዋቱ በደጋማ ሥፍራዎች ይገኛሉ። በትክል ድንጋይና በሰከላ በብዛት ይገኛሉ። የአስማቱ ባለሙያዎችም ከላይ በጠቅስሁአቸው ቦታዎች አሉ። በተለይ አርግፍ የሚባለውን እንጨት በአካባቢው ያሉ ገበሬዎች እየጠረቡ ለሕጻናት ከሰይጣን እና ከቡዳ ይጠብቃል እያሉ ባንገታቸው ያደርጉላቸዋል።

 ይህ እንጨት የማይሰራበት አስማት የለም ይባላል፤ ሰዎችን ለክፉዎች አሳልፌ እንዳልሰጥ ሁሉን ከመግለጥ እቆጠባለሁ። ለማጥመቅ ሲጠቀሙበት ግን የሚያደርጉትን መናገር ግድ ሆኖብኛል። እንጨቱን ሲቆርጡት የሚደግሙት አላቸው። ሰባት ቀን ሲደግሙ ቆይተው የዶሮ ወይም የሰው ደም ቀብተው ይቆርጡታል። ቅጠሉን በአዲስ ሸክላ[ውሃ ወይም እህል ያልነካው] ዘፍዝፈው አርባ ቀን ከደገሙበት በኋላ ዋናው ለማጥመቅ የተዋረሰው ግለሰብ ይጠመቅበታል። አጥማቂው አርባ ቀን በተደገመበት ውሃ ሲጠመቅ መናፍስት ያለ ከልካይ በብዛት እንደሚያድሩበት ይነገራል።