Saturday, May 26, 2012

ቁም ነገር በፈገግታ

«ወሶበሂ ይነብብ ሐሰተ እምዚአሁ ይነብብ….ሐሰትን ሲናገር ከራሱ ይናገራል»


 በመምህር ፈንታ
የማኅበረ ቅዱሳን አፈቀላጤ የሆነው ደጀ ሰላም በወርሃ መጋቢት መጨረሻ ላይ የሚከበረውን የመድኃኔዓለም ዓመታዊ በዓል አስታኰ በዛሬማ ወንዝ ላይ እየተገነባ ያለውን የመንግሥት የስኳር ልማት ለማጥናት ሳይሆን ለሽብር ፍጆታ የሚሆን መረጃ ለመሰብሰብ የማኅበሩን አባላት በተሳላሚ ሽፋን ወደ ገዳሙ ከላካቸው አባላቶቹ የተገኘውን ዘገባ ደጀ ሰላም በገጹ አውጥቶ ነበር።
የስኳር ልማቱን ለማስቆም ሕዝቡ ለጦርነት ተመመ፤ መንግሥት አካባቢውን ለቆ ወጣ፤ ፖሊሶች አለቁ፤ ሬሳ ቆጠራው ቀጥሏል …..ወዘተ የብስጭት ማስተንፈሻ ስሜቶቻቸውን ከልካይ በሌለበት ድረ ገጽ ውሸቱን በቆርጦ ቀጥል ጥበባቸው  እንቶ ፈንቶአቸውን አስነብበውናል።
አሁን ደግሞ ጉዳዩ በወሬ የማይቆም መሆኑን ሲያረጋግጡ ለጫወታ ወግ ፍለጋ ጥቂት ጊዜ እረፍት የወሰዱ መስለዋል። አንድ ነገር ፈጥረው የሽብር ዜና እስኪያሰሙን ድረስ የሚያስተምሩት የወንጌል ቃል ስለሌላቸው ጥሩ የእረፍት ጊዜ ይሁንላችሁ ብለናቸዋል።
ይህንን ያህል ለመግቢያ ካልን የጽሁፋችን ርእስ ወደ ሆነው ጉዳይ እናምራ። ከሁከት ውጪ ነገረ መለኰትን የማያውቁ ሽፍቶች» በሚለው ጉዳይ ተንተርሰን ወደ ርእሳችን ስንገባ ደጀ ሰላም በተሳላሚ ሽፋን በማቅ አባላቶቿ ያስጠናችው  የጥናት አንዱ ክፍል በዋልድባ ገዳም «የዘጠኝ መለኰት አማኞች» መኖራቸው መዘገብ ነበር።   ስለዋልድባ መነኰሳት መናፍቅነትና ክሃዲነት ያገኘሁት ውጤት ነው በማለት  በስኳር ጥናቱ ለውሶና ስኳር አድርጎ በማቅረብ ስለዘጠኝ መለኮት አማኞች ሊያስነብበን ፈልጎ ይህንኑ በኢንተርኔት ላይ ሰቅሎት አግኝተናል።
ከጽሁፏ የተወሰደው  ዘገባዋ ይህንን ይመስላል።

ይሁን እንጂ እነ በጋሻውን፤ እነ አባ ሠረቀ ብርሃንንና ሌሎችንም ሁሉ በአንድ ሙቀጫ አስገብታ በተሐድሶ ስም የምትወቅጠው ይህች ብሎግና ማኅበር ድሮውን በፈጠራና ስም በማጥፋት ላይ ተመስርታ እንጂ የሃይማኖት እውቀት ስላላት በዚያ ላይ ተመስርታ ወይም የመናፍቃን ጉዳይ የሚያሳስባት ሆኖ አይደለም።

Friday, May 25, 2012

ፋሲካ

             ምንጭ፦http://bethelhemm.blogspot.com
በሚያስፈራው ሌሊት ጩኸት ሲበረታ
ግብጽ ተሸበረች ጌታ በኩሯን መታ
ሞት መግባት አልቻለም ወደ እስራኤል ቤት
ታትሞ ስላየ የደም ምልክት
ደጃቸውን ዘግተው ፋሲካ አደረጉ
በደም ተከልለው ሌሊቱን አነጉ
ባሕሩን ተሻግረው ከነዓን ሲገቡም
የልጅ ልጆቻቸው ፋሲካን አልረሱም
ይህ ሥርዓት አልፎ የእግዚአብሔር በግ መጣ
ሰውን የገዛውን የሞት ኃይል ሊቀጣ
የሰው ፍቅር ስቦት ከሰማያት ወርዶ
ጠላትን ረታው ፋሲካችን ታርዶ 

በመስቀል ተሰቅሎ ስለሆነ ቤዛ
ወገኖቹን ዋጅቶ በራሱ ደም ገዛ
ንጉሡ እንዲገባ ደጆች አይዘጉም
ሌሊቱ አልፏልና የሚያሰጋን የለም
የሕይወታችን ጉበን በደም ታጥሯልና
ሞት እያየ አለፈን ኃይሉን አጥቷልና
ለምሕረት በሚጮኸው የደሙ ምልክት
ባሕሩን ከፍለን አልፈን እንገባለን ገነት
የዘላለም አምላክ የምስጋና ጌታ
ምርኮን የማረከ ማኅተሙን የፈታ
ሞትን ድል የነሳው የናዝሬቱ ኢየሱስ
በዙፋኑ ያለው የአርያም ንጉሥ
ከፍ ከፍ ይበል ይድረሰው ምስጋና
መከራን ታግሶ ለእኛ ታርዷልና
ፋሲካን ስናደርግ ኖረን በእድሜ ጸጋ
ክርስቶስ ፋሲካ መሆኑን አንዘንጋ፡፡