Showing posts with label መረጃ. Show all posts
Showing posts with label መረጃ. Show all posts

Friday, January 1, 2016

ስለአንዳንድ በኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክ ላይ…ከአንዳንድ የኦሮሞ ጸሐፍት የተሰነዘሩ…ያስቀየሙኝ ክታቦች!!


 (በአማን ነጸረ ክፍል 4)

(7.1) ግርማዊ ቀዳማዊ አጼ ኃይለሥላሴ በጻፉት በመጀመሪያው ‹‹ሕይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ›› መጽሐፋቸው ገጽ-137 ይሕንኑ ሁኔታ (የቶፋ ሥርዓት) በጥቁምታ ያመላክቱናል፤እንዲህ ሲሉ ‹‹በኢትዮጵያ የካሕናት ቁጥር እጅግ ብዙ ነው፡፡ለነዚሁም ሁሉ መንግሥት ከያውራጃው ከግማሽ እስከ አንድ ጋሻ መሬት ለእያንዳንዱ ካሕን ርስት እያደረገ ሰጥቷቸዋል፡፡ይኸውም ርስት እየሆነ የተሰጠው መሬት ለልጅ ልጅ የሚያልፍ [በመሆኑ] ቤተክርስቲያን ልታዝዝበት አትችልም፡፡በዚህም ላይ ከንጉሠ-ነገሥቱ ዠምሮ መሳፍንቱ መኳንንቱም ሌላውም እነሱን የመሰለው ሁሉ ወይዛዝርት እንኳ ሳይቀሩ የቤተክርስቲያን ገበዞች እየሆኑ ከ200 እስከ 700 ጋሻ መሬት ንጉሠ-ነገሥቱ ርስት እያደረገ ይሰጣቸዋል...›› በማለት ይዞታው በወሬ የኢኦተቤክ እየተባለ ስመ-ንብረቱ (title deed) ግን በተግባር በንጉሡ፣በመሳፍንትና ወይዛዝርት እጅ እንደነበረ፤እነዚህ መሳፍንትና ወይዛዝርት ሲያልፉም ልጆቻቸው የቤ/ክ ትምህርት ባይማሩም ‹ገበዝ› በሚል መጠሪያ ርስቱን ወርሰው ደሃ ካሕናትን እያስቀደሱ በስመ ተዋሕዶ የሚያደርጉትን ብዝበዛ (የቶፋ ሥርዓት) ስሙን ሳይጠሩ ያብራሩልናል፡፡
(7.2) በ1967 ዓ.ም የመሬት-ላራሹ ዐዋጅ ሲታቀድ በካሕናት እጅ እንደዜጋ የነበረውን መሬት ሁሉ በነባሩ ‹‹የሲሶ መሬት ይዞታ›› ትረካ አጠቃሎ የመውረስ አዝማሚያ አስፈርቶ ነበር፡፡ሁኔታው ያሳሰባቸው የጊዜው የኢኦተቤክ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ በ1967 ዓ.ም ለደርግ በጻፉት ደብዳቤ ተቃውሞአቸውን ሲገልጹ ‹‹...ተጋኖ ሲነገር የኖረው ጨርሶ ያልነበረ የመንግሥት ሥልጣን ድርሻና የሀገሪቱ ሲሶ መሬት ወሬ ፈጽሞ ተረት ቢሆንም ያው ያለው መጠነኛ ድጋፍ እስካሁን ድረስ ከመንግሥት ሲሰጣት ቆይቷል›› በማለት ‹‹ያው ያለው መጠነኛ ድጋፍ›› እንዲቀጥል ተማጽነው ነበር፡፡ፓትርያርኩ ጥያቄያቸውን በ7 ነጥቦች አብራርተው ነበር ያቀረቡት፡፡2ቱን ብቻ ልጥቀስላቸው ‹‹1ኛ. የኢትዮጵያ ገዳማት መሬት ያንድነት ማኅበር እንደ መሆኑ መጠን ይኸው በይዞታቸው ያለው የንፍሮ መሬታቸው በይዞታቸው ስር እንዲቆይ እንዲፈቀድላቸው፣እንዲሁም ‹በርሷ (በኢኦተቤክ) ስም ተይዘው ሌሎች ወገኖች ሲጠቀሙባቸው የኖሩ መሬቶች ቢወሰዱ የምትጎዳበት ባይኖርም› እስከ ዛሬ በቀጥታ ስትረዳባቸው የቆዩ አንዳንድ መሬቶች በይዞታዋ ስር እንዲቆዩላት፤2ኛ. በግብርና ስራ የሚተዳደሩ ካሕናት ሁሉ ካሕንነታቸው ኢትዮጵያዊ ማንነታቸውን ስለማይሽረው እንደ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ የመሬት ድርሻቸውን የማግኘት መብታቸው እንዳይዘነጋባቸው››ብለው ጠይቀው ነበር (መምህር ኪዳነማርያም ጌታሁን፡ገ.102)፡፡
(7.3) በደስታ ተክለወልድ የአማርኛ መዝገበ ቃላት ገጽ 1267 ‹‹ወኪል፣ምትክ፣ተጠሪ፣ገባሪ›› ተብሎ ስለተተረጎመው ‹‹ቶፍነት›› ሌላ ዋቢ እንቁጠር፡፡‹‹የኢኦተቤክ አስተዳደር በየዘመናቱ››የተሰኘው መጽሐፍ ደራሲ ብፁዕ አቡነ ገሪማ (ዶ/ር) ስለዚህ ጉዳይ ሲተርኩ ‹‹ለቤተክርስቲያን መግባት የሚገባውን የግብር ገንዘብ መሳፍንቱ፣መኳንንቱ፣ባላባቶችና ወይዛዝርት በግብዝና በእልቅና፣በመሪጌትነት፣በድብትርና፣በቅስና፣በዲቁና እና በልዩ ልዩ [የ]ክሕነት [አገልግሎት] ስም ርስት እየያዙ በግል እየተጠቀሙ በተወሰነ ክፍያ ወይም በቶፍነት ካሕናትን ያስገለግሉ ነበር›› ይሉናል፡፡አቡነ ገሪማ ታሪኩን ሲቀጥሉ ‹‹…የቤ/ክ መተዳደሪያ ብዛት ጎልቶ ከመታየቱ በቀር ለካሕናቱ መተዳደሪያ ይሆን ዘንድ የተፈቀደው ርስተ - ጉልት የሚሰጠው ጥቅም የአገልጋዮች ካሕናትን ችግር ከመሸፈን አኳያ በቂ አልነበረም፡፡…ከሚያጋጥሙት ችግሮች መካከል፡- ያልቀናውንና በረሃማውን መሬት እየሰጡ የለማውን መሬት መቀማት፣ለም የሆነውን መሬት በጠፍ መሬት መለወጥ፣የኩታ ገጠም አቀማመጥ ያለውን ርስት ወደ ግል ይዞታ ማስገባት…ይገኙበታል›› ይላሉ (አቡነ ገሪማ፡ገ.64-70)፡፡
(7.4) ከላይ ያለችውን የ“ቶፍነት” ሥርዓት ጽንሰ - ሐሳብ ለመረዳት ከመርስዔኀዘን ‹‹ትዝታዬ›› መጽሐፍ ገጽ-92 ማሳያ እንጨምር፡፡የድጓ መምህር የነበሩት ኣባታቸው ሲሞቱ የአባታቸውን መሬት ወርሰው እንደ ባለርስት መገበራቸው ቀርቶ እንዴት ወደ ቶፍነት እንደተሸጋገሩ ሲተርኩ ‹‹…እንግዲህ የምትገብረው በአባትህ ሥም አይደለም፣መሬቱ ለፊታውራሪ ጥላሁን ስለተሰጠ ሥመ - ርስቱ ተዛውሯል፤ሆኖም ለፊታውራሪ ጥላሁን በቶፍነት ልትገብር ትችላለህ…›› እንደተባሉ ይገልጻሉ፡፡ከመርስዔኀዘን አባባል እንደምንረዳው የመንግሥት ሹም የነበሩት ፊ/ሪ ጥላሁን ለድብትርና ተብሎ ለይስሙላ የተመደበውን ርስት ወርሰው ይዘው ደብተራውን (መርስዔኀዘንን) ‹‹ቶፋ›› አድርገዋቸዋል፡፡ታሪክ ግን ፊታውራሪ የያዙት ርስት ለስሙ የኢኦተቤክ ስለተባለ ብቻ ‹‹ሲሶ የቤተክሕነት ድርሻ›› ብላ ያልበላነውን ልታስተፋን ትጥራለች!!ቆዩማ ይቺን ታሪክ የሚሏትን ጉድ በጎጃምኛ ልስደባት ‹‹ኧግ!ይቦጭቅሽ!››
(7.5) ይሄን ሀቅ ጠጋ ብለው ያላዩልን እነ መኩሪያ ቡልቻ እና አባስ ሐጂም ነዋሪ ነባሪውን ስሑት የወሬ ጫፍ ይዘው <<...the clergy were....landlords,they owned Oromo peasants as Gabbars...>> ይሉናል!እርግጥ ይሕ በነአቶ አጽሜ ጸረ-ካሕናተ-ኦርቶዶክስ ጥላቻ ተከትቦ እስካሁን የሚናፈስ የታሪክ አረዳድ ኢህአዴጋውያንን ጨምሮ የብዙኃኑ ልሂቅ አረዳድ ስለሆነ እነ መኩሪያ ቡልቻንና አባስ ሐጂን ነጥሎ መውቀስ ኢ-ፍትሐዊ ሊሆን ይችላል፡፡በቁሳዊ ሀብትና በካሕናት ኑሮ ረገድ የዛሬዋ የኢኦተቤክ ያለችበትን ከቅድመ-1967 ዓ.ም የመሬት ዐዋጅ የተሻለ ኢኮኖሚያዊ አቅም ያስተዋለ ሰውማ በእርግጥም አቡነ ቴዎፍሎስ እንዳሉት በኦሮሚያም ሆነ በሌሎች የሀገሪቱ ክፍሎች የሚተረከው ‹‹የሲሶ መሬት›› ድርሻ ‹‹ፈጽሞ ተረት›› እንደነበረ ይገለጽለታል፡፡እኛማ ትናንት በተወረሱባት ሕንጻዎች ምትክ ከደርግ የ5 ሚሊዮን ብር ምጽዋት ትጠብቅ የነበረች ቤ/ክ ዛሬ ገንዘብ አያያዟ ባያስደስተንም እንኳ በጀቷ ቢሊዮን መሻገሩን አይተናል፡፡እናም የትናቱ የተረት ተረት ‹‹ሲሶ ግዛት›› ከቶም አያቃዠንም!!አባቴ እንዲህ ይል ነበር ‹‹ድሮ ካሕን ስሙና ማዕረጉ ብዙ ነው፤በቤቱ ግን ሙሉ እንጀራ ቆርሶ የሚበላ ከስንት አንድ ነው፤በነገሥታቱ ከባቢ ካሉት በቀር ድሆችን ካሕናት የሚፈቅድ የለም፤ከነተረቱም ‹የካሕን ልጅ ስም ይጠግባል፤እንጀራ ግን አይጠግብም› ይባል ነበር፤መምህራኖቻችን የኖሩት ተማሪ ለምኖ እያበላቸው ነው፤አየ!፤ተውኝማ ልጄ!››
(7.6) ትውልዱ ባይገለጽለትም እኛ መከራና ስቃይ ከካሕናት ወላጆቻችን የወረስነው ‹ምድጃ የላቀን፤አመድ የወረሰን፤ደሃ የድሃ ልጆች› ወላጆቻችንን ዘበናይ ሁላ ተማርኩ ብሎ ‹‹ሲሶ-ሲሶ!›› እያለ በእንግሊዝኛ ሲዘባነንባቸው እንገረማለን፡፡በተሳልቆ ‹‹ኡኡቴ!ድንቄም ሲሶ!›› እንላለን፡፡ትናንት በነበሩ ብዙኃን ካሕናት ወላጆቻችን ያልተጠገበ ጥጋብ የዛሬዎቹ ሕያዋን ልጆቻቸው እንድንሸማቀቅ የሚሹትን የባለቅኔውን ድንቅ አባባል ተውሰን፡-
‹‹እስመ-እንዘ-ቦ፡ሕያወ፡እሞተ-ሥጋ፡ግዙፍ፣
ሞተ-ዮሴፍ፡አኃዊሁ፡ነገርዎ፡ለዮሴፍ፡፡››እንላቸዋለን--ለቀባሪው ማርዳት!!ሁሉን ትተን የታላላቆቹን ሊቃውንት የነክፍለ ዮሐንስ መራብና መታረዝ የሚያመላክቱና ቅኔያዊ ቁዘማዎቻቸውን የገለጹባቸውን ቅኔያት እንጠቃቅሳለን፡፡እንዲህ፡-
‹‹...ልብስየሂ፡ምንንት፡መንጦላእተ-ርኅቅት፡ነፍስ፣
እስመ-አነ፡ከመ-ዶርሆ፡እምላእለ-አብራክየ፡እለብስ፡፡››
እያሉ እኒያን የመሰሉ ሊቃውንት እርቃናቸውን እንኳ በቅጡ መሸፈን አቅቷቸው እንደ ዶሮ ከጉልበት በላይ ተራቁተው በ‹‹ሲሶ ግዛት››ተረት አእጽምቶቻቸው እረፍት ሲያጡ ከማየት የሚደርስብንን ሕማም በቅኔያቱ እናስታምማለን፡፡ደግሞም የዋድላው የኔታ ሲራክ ራሳቸውን ከአህያና በቅሎ ጋር እያነጻጸሩ የ30 ብር ዓመታዊ ደሞዝ ሰቆቃዊ አኗኗራቸውን፡-
‹‹አእዱግ፡ወበቅል፡እንዘ-ያወጽኡ፡ስልሳ፣
ሲራክ፡አምላከ-ዋድላ፡ተሰይጠ፤ለሠላሳ፡፡››
እያሉ የገለጹባቸውን ቅኔያት እያስታወስን እንግሊዝኛ ተናጋሪ ደባትሮቻችን ወደ ልባቸው ተመልሰው ሚዛኑን የጠበቀ ጽሑፍ እንዲያቀርቡል እንጸልያለን፡፡አንዳንዴም እንጎተጉታለን፡፡አልፎ አልፎም ሕመማቸው ሕመማችን መሆኑን ሳንስት በተጋነነ ቅሬታና ፍረጃ መስመር ሲለቅቁብን ከወዲህ የላላውን ለመወጠር ከወዲያ የተወጠረውን እንጎትታለን--እንዲህ እንዳሁኑ!
የላላው ይወጠር፤የተወጠረው ይርገብ፡፡ወይኩን ማዕከላዌ!አሜን!ይኹን፤ይደረግ!
፡፡፡፡፡፡፡፡በአማን ነጸረ፡፡መስከረም 2008 ዓ.ም፡፡፡፡፡፡፡፡
ማጣቀሻዎቼ!
ሀ. መጻሕፍት(ሃርድ ኮፒ)
1. ብፁዕ አቡነ ገሪማ (ዶ/ር)፣የኢኦተቤክ አስተዳደር በየዘመናቱ፣ጥቅምት 2000 ዓ.ም፣ትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት
2. ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ(M.A)፣የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ታሪክ፣1986 ዓ.ም፣2ኛ እትም፣ትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት
3. በኦርቶዶክሳውያን ሊቃውንትና ጳጳሳት፣የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ከልደተ ክርስቶስ እስከ ፳፻(2000 ዓ.ም)፣በ2000 ዓ.ም፣ትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት
4. አባ አንጦንዮስ አልቤርቶ (ዶ/ር) (ካፑቺን)፣የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ታሪክ በኢትዮጵያ፡ከብፁዕ አቡነ ጉሊየልሞ ማስያስ እስከ ብፁዕ አቡነ እንድርያስ ጃሮሶ (1841-1941 ዓ.ም)፣1993 ዓ.ም፣ንግድ ማተሚያ ድርጅት
5. ታቦር ዋሚ፣የውገና ድርሰቶችና የታሪክ እውነቶች፣በ2007 ዓ.ም፣3ኛ እትም፣አርቲስቲክ ማተሚያ ድርጅት
6. መርስዔኀዘን ወልደቂርቆስ፣ትዝታዬ፡ስለራሴ የማስታውሰው፣2002 ዓ.ም፣አስቴር ነጋ አሳታሚ ድርጅት፤ሮኆቦት አታሚዎች
7. ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ፣ሕይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ (1ኛ መጽሐፍ)፣1965 ዓ.ም፣ብርሃንና ሰላም ወዳማዊ ኃይለሥላሴ ማተሚያ ቤት
8. አለቃ ተክለኢሱስ ዋቅጀራ (ሐተታ በዶ/ር ስርግው ገላው)፣የኢትዮጵያ ታሪክ፣2000ዓ.ም፣ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት
9. በቀለ ወልደማርያም አዴሎ፣የካፋ ሕዝቦችና መንግሥታት አጭር ታሪክ፣1996 ዓ.ም፣ሜጋ ማተሚያ ድርጅት
10. ዶናልድ ሌቪን (ትርጉም በሚሊዮን ነቅንቅ)፣ትልቋ ኢትዮጵያ፣2007 ዓ.ም፣አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ
11. ቅዱስ ያሬድ፣መጽሐፈ-ድጓ፣1988 ዓ.ም፣ትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት
12. ከአባቶች ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ፣የውዳሴ ማርያም አንድምታ ትርጉም፣1990 ዓ.ም፣ትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት
13. የእጅ ጽሕፈት የግእዝ መማሪያ ግስ/መዝገበ-ቃላት(በራሴ ተቀድቶ የተማርኩበት)፡፡
14. እነ አለቃ አፈወርቅ ዘውዴ፣የግእዝ ቅኔያት የስነጥበብ ቅርስ-2፣1980 ዓ.ም፣ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት
15. መምህር ኪዳነማርያም ጌታሁን፣የሐሰት ምስክርነት፣1994 ዓ.ም፣ንግድ ማተሚያ ድርጅት
16. ሰሎሞን ጥላሁንና ሥምረት ገ/ማርያም፣ደማቆቹ፣2000ዓ.ም፣
17. ደስታ ተክለወልድ፣ዐዲስ ያማርኛ መዝገበ ቃላት፣1962 ዓ.ም፣አርቲስቲክ ማተሚያ ቤት
18. የኢትዮጵያ መጽሐፍቅዱስ ማኅበር፣የመጽሐፍቅዱስ መዝገበቃላት፣1992 ዓ.ም፣6ኛ እትም፣ባናዊ ማተሚያ ቤት
19. ላጵሶ ጌ.ድሌቦ (ዶ/ር)፣የኢትዮጵያ ረጅም ሕዝብና ታሪክ አንደኛ መጽሐፍ፣1982 ዓ.ም፣ንግድ ማተሚያ ድርጅት
ለ. የኢንተርኔት መጻሕፍት(ሶፍት ኮፒ) እና መጣጥፎች!
1. የመኩሪያ ቡልቻ፣የገመቹ መገርሳ እና የቶማስ ዚትልማንን ጽሑፎች ለማግኘት http://www.diva-portal.org/…/get/diva2:277262/FULLTEXT01.pdf
2. የመሐመድ ሐሰንን ጽሑፍ https://zelalemkibret.files.wordpress.com/…/jos-volume-7-nu…
3. የአባስ ሐጂን http://69.162.74.242/~iprenewi/r.php… ወይም http://69.162.74.242/~iprenewi/r.php…
4. በወለጋ ስለነበረው የሚሽኖች እንቅስቃሴ GILCHRIST, HORACE ERIC የጻፈው የ2ኛ ዲግሪ ማሙያ http://repository.lib.ncsu.edu/…/bits…/1840.16/844/1/etd.pdf
5. ፕ/ር ታምራት አማኑኤል የአለቃ ዐጽመጊዮርጊስን እና የነአለቃ ታዬ ታሪክ ጨምሮ የቀደምት ጸሐፍያንን ስራዎች ባጭሩ የዳሰሱበት መጽሐፍ http://www.ethioreaders.com/…/About-Ethiopian-Authors-Prof-…
6. ስለኦሮሞ ሕዝብ የሃይማኖት ተዋጽኦ https://en.wikipedia.org/wiki/Oromo_people#Religion
7. ‹‹ጋላ›› የሚለው ቃል በሶማሌ ሕዝብ ታሪክ ውስጥ ያለው የተለያየ ትርጉም https://www.yumpu.com/…/the-galla-myth-on-somali-history-or…
8. ስለ Krapf ሚሲዮናዊ ሕይወት https://en.wikipedia.org/wiki/Johann_Ludwig_Krapf
9. ‹‹ጋላ›› የሚለው ቃል ኬንያም ውስጥ በታሪክ መጻሕፍት ጥቅም ላይ ሲውል ስለመኖሩ የሚያሳይ ደብዳቤ http://yassinjumanotes.blogspot.com/…/stop-use-of-word-gall…
10. በዚች መዝሙር ላሳርግ Ethiopian Orthodox Mezmur in Afaan Oromo- Waldaa Qulqullootaa - Galanni Waaqayyoof haa ta'u https://www.youtube.com/watch?v=tER05f165A8
http://www.diva-portal.org/…/get/diva2:277262/FULLTEXT01.pdf

Tuesday, October 27, 2015

ስለአንዳንድ በኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክ ላይ…ከአንዳንድ የኦሮሞ ጸሐፍት የተሰነዘሩ…ያስቀየሙኝ ክታቦች!!

ከአማን ነጸረ (ክፍል 3)
(6.6) እስኪ እነዚህ ምዕራባውያን ሚሽነሪዎች ስለ ኦሮሞ ሕዝብ ባሕል የነበራቸው አመለካከት ከኢኦተቤክ ሊሻል ይቅርና ምን ያህል የዘቀጠ እንደነበረ በራሳቸው መነጽር እንፈትሽ፡፡ Eric Gilchist የተባለ አሜሪካዊ በነመኩሪያ ቡልቻ ‹‹የአቢሲኒያ ትርክት›› ተጽእኖ ስር ሆኖ እንኳ በሠራው የ2ኛ ዲግሪ (ማስትሬት) ማሙያ ጥናት <<....as a result of their fundamental beliefs, SIM [Sudan Interior Missonary] missionaries viewed all non-Chiristean religious practices as evil and they demanded that their converts compeletly change their life style, with no compromise to accommodate local customs....>> በማለት ሚሲዮናውያኑ ለነባሩ የኦሮሞ ባሕል የነበራቸውን የተዛባ አመለካከት ካሳየን በኋላ Dough Priest የተባለውን በወለጋ ከ10 ዓመታት በላይ የሚሲዮናውያን መሪ የነበርን ትምክተኛ ሰው ጽሑፍ በመጥቀስ <<...the lives of the Galla people in general were one round after another of drunkness,adultery,thievery,lying,fighting,cheating,and worshiping false gods....today,many of the lives in our area have changed greatly....>> እያሉ (ሚሽኖቹ) ራሳቸውን ወለጋን የታደገ መሲኅ አድርገው ይመጻደቁ እንደነበር ጽፏል--ይቅርና ባሕሉን እንደ ባሕል ሊቀበሉ ( Eric Gilchist፡p.74)፡፡አናሲሞስ ነሲብም ቢሆን ሁሉንም የኦሮሞ አኗኗርና ባሕል ‹‹ቅዱስ›› ብሎ የተቀበለ አይመስልም፡፡በአንድ ደብዳቤው ላይ በስብከታቸው ስላመጡት ለውጥ ሲገልጽ ‹‹...በጋብቻ ላይ የሚፈጸም ጋብቻን እና በአካባቢው የሚታዩ ጎጂ ልማዶችን አጥብቀን ተፋልመናል፤እናም በዚህ በኩል ተሳክቶልናል፡፡ከዚህ ሌላ በኅብረተሰቡ መካከል ይዘወተር የነበረው የጥንቆላ፣የድግምት፣ለክፉ መናፍስት መሥዋዕት የማቅረብ ልማድ፣ሐሰተኛ ምስክርነት፣ውሸትና ሌላም ጎጂ ልምዶች ከዓመት ወደ ዓመት እየቀነሱ መጥተዋል›› ብሎ ነበር (ደማቆቹ፡ገ.35)፡፡እዚህ ላይ አንድ ሀቅ ላስታውስ፡፡በሰሜን ኢትዮጵያም ቢሆን አናሲሞስ ያነሳቸው ከክርስትና ጋር የሚቃረኑ ባሕላዊ ጎጂ ልማዶችና አምልኮዎች ነበሩ፡፡ዛሬም ርዝራዣቸው አለ፡፡ችግሩ በኦሮሚያ ብቻ የነበረ/ያለ አይደለም፡፡ስለሆነም ማንም በማንም ላይ ሊመጻደቅ አይችልም፡፡
(6.7) እስልምና የኦሮሞን ባሕል በምልዓት ይቀበላል የሚል ካለም እስኪ እንፈትሽ!! ‹‹Islamic Front for Liberation of Oromia›› የሚል ሃይማኖት ጠቀስ የኦሪሚያ ነጻ አውጪ ሽምቅ ተዋጊ በሼክ አብዱል ከሪም (ሼክ ጃራ አባ ገዳ) መፈጠሩን፣በባሌ አካባቤ ‹‹የሶማሌ አቦ...›› የሚባል አፍቃሬ-ሶማሊያ የኦሮሞ ሙስሊሞች የፖለቲካ ቡድን በታሪክ መታየቱን፣ይኸው ቡድን በ1969 ዓ.ም ከዚያድ ባሬዋ ሶማሊያ በእስልምና ስም ተቃቅፎ ኢትዮጵያን ያውም ሐረርጌን መውጋቱን፣ከሽግግር መንግስቱ ምስረታ ጀምሮ በተደጋጋሚ በምድረ-ኦሮሚያ እየተንቀሳቀሱ በወሐቢያና በሃዋርጃ ስም ብሔር ሳይለዩ ኦርቶዶክሳውያንና ለዘብተኛ ሙስሊሞችን እንዲሁም ፕሮቴስታንቶችን በተለይ ደግሞ የመካነ-ኢየሱስ ሉተራውያንን ያጠቁ የሙስሊም አክራሪዎችን ድርጊት እንደቀላል የእኩልነት ጥያቄ ብቻ እንድናየው እነ አባስ ሀጂ ስለመከሩን እንዳላየ እንለፈው፡፡ነገር ግን ከአክስት ልጅ ጀምሮ መጋባትን የሚፈቅደው የእስልምና ስብከት እንኳንስ ከአክስት ልጅ ጋር ከጎሳ አባል ጋርም ጋብቻን ከሚከለክለው የኦሮሞ ብሉይ ልማዳዊ ሕግ ያለው ተቃርኖ፣ኦሮሙማን በምድረ-ኦሮሚያ ለመገንባት ከሚታገለው የኦሮሞ ብሔርተኝነት ጋር ‹ድንበር-ለምኔ› የሚለው ዘመናዊው እስልምና ያለው አለመጣጣም፣እንዲሁም ወደ ድሬ ሼክ ሁሴን መሄድን ወደ አባ ሙዳ እንደሚደረግ ምትክ መንፈሳዊ ጉዞ (ጂላ) የማይመለከተው የዘመኑ እስልምና (ወሀቢዝም) በነአባስ ሐጂ (Abas Haji:p.110-113) ቀደም ሲል ለስላሳ ትችት ሲደርስበት የነበረ ቢሆንም አሁን አሁን ግን እስልምና በኦሮሚያ ኤሊቶች ዙሪያ ኃይል እየተሰማው ስለመጣ ነው መሰለኝ ትንፍሽ የሚል የለም፡፡በነገራችን ላይ የልሂቁን ኦሮሞ ድምጽ የሚቃኙት በዋናነት ሙስሊም የመደብ ጀርባ ያላቸው ኦሮሞ ልሂቃን ሲሆኑ በተከታይነት የምዕራብ ኦሮሚያ ፕሮቴስታንቶች ያጅቧቸዋል፡፡ለሃይማኖት ልዩነት ልበ-ሰፊ ከነበረው ሜጫ እና ቱለማ መፍረስ በኋላ ባሉ ኦሮሞ-ተኮር አደረጃጀቶች ኦርቶዶክሳውያን ኦሮሞዎች በኅቡዕና በገሀድ ክፉኛ እንዲሸማቀቁና ከኦሮሞነት እንደወረዱ እንዲሰማቸው ሰፊ አግላይ ፕሮፖጋንዳ ተሰርቷል፤እየተሰራ ነው፡፡
(6.8) ካቶሊክስ ለምን ይቅርባት?!ትፈተሸ::የካቶሊክ ሚሽነሪዎች ገና ወደ ክርስትና ያልገባችውን ምድረ-ኦረሚያ (ፊንፊኔ) እንዴት ይመለከቷት እንደነበር አባ አንጦንዮስ ሲጽፍ ‹‹...የፊንፊኔና የአካባቢው ሕዝብ በጨለማ ውስጥ በሞት ጥላ ስር ይኖር ስለነበር የወንጌል ስርጭት በእርግጥ አስፈላጊ እንደነበር አባ ቶረን ሻኽኝ አስረድተው በአካባቢው የወንጌል ትምህርት ለማድረስ ቢያንስ አራት ወይም አምስት ተጨማሪ ሚሲዮናውያን እንደሚያስፈልጉዋቸው ኣሳስበው ነበር››ይሉናል (አባ አንጦንዮስ፡ገ.126) የአባ ቶረን ሻኽኝን የጥቅምት 14 ቀን 1868 ዓ.ም ደብዳቤ ጠቅሰው፡፡የባሪያ ንግድ፣ሴት ልጆችን ያለፈቃዳቸው መዳር፣በጋብቻ ላይ ጋብቻ የመሳሰሉ በኦሮሞና ሲዳማ ግዛቶች የሰፈኑ ልማዶች ለካቶሊካውያን ሚሽነሪዎች ፈተና ሆነው እንደነበርም አባ አንጦንዮስ በዚሁ መጽሐፍ ከገጽ 120 ጀምሮ ለስለስ ባለ የሚሲዮናውያን ቋንቋ በጊዜው የነበረውን ጎጂ ባሕል ተችተው ተርከውታል፡፡
(6.9) ከላይ የቀረቡት በኦሮሞ ባሕልና እምነት ላይ ያሉ አመለካከቶች ከራስ አስተሳሰብ/ሃይማኖት ውጭ ያለውን ባሕላዊ/ሃይማኖታዊ አመለካከት በራሱ በባሕሉ ዐይን ሳይሆን ‹‹በግል›› መለኪያ መለካት የሚያመጣውን የተዛነፈ ችግር ያንጸባርቃሉ፤ችግሩ ይብዛም ይነስም በሁሉም ወገን አለ--በሁሉም--የኢኦተቤክ ምዕመናንና የዋቄፈና አማንያንን ጨምሮ፡፡የዚህ አመለካከት አንጸባራቂ ከሆኑ ግለሰቦች አንዱ የሆነው Krapf የጻፈውን የኛው መሐመድ ሐሰን እንዳለ ገልብጦ በኦሮሞ ጥናት መጽሔት ቁጥር-7 ላይ በገጽ-118 ያሰፈረውን እንይ! <<...the Amhara Clergy were not sensitive to Oromo food habits in which milk, butter and meat were central>> ሲል አስቀምጦታል፡፡በKrapf ፕሮቴስታንታዊ እይታና በመሐመድ የከረረ ብሔርተኛ ምልከታ መሰረት የኢኦተቤክ የዐማራ ብቻ ናት፤የኢኦተቤክ ዶግማና ቆኖና አፈጻጸሙም ከብሔር-ብሔር እየተለያየ መተግበር አለበት!በነመሐመድ እምነት ለምሳሌ፡- የደብረብርሃን ዐማራ ኦሮቶዶክሳውያን በፍልሰታ ከሥጋና ቅቤ ሲታቀቡ የእነሱ ጎረቤት የሆኑት የልቼ እና የሸኖ ኦሮሞዎች ግን በፍልሰታ ስጋና ቅቤ የተከለከሉት በሃይማኖቱ ዶግማና ቀኖና ሳይሆን በዐማራ ቸልተኝነት ነው!!የደጀን (ጎጃም) አባይ ዳር ያሉ የቅ/ሩፋኤል ቤ/ክ አካባቢ ዐማራ ጸዋሚዎች በጾም ከስጋ ታቅበው፤በሌላ በኩል በሰ/ሸዋ ገርበ-ጉራቻ የፍልቅልቅ እና አካባቢዋ የቅ/ሩፋኤል የአባይ ዳር (የደራ?) ኦሮሞ ኦርቶዶክሳውያን ጾማቸውን ከስጋና ወተት ጋር ማከናወን ነበረባቸው!!ይሄ ያልሆነው የኢኦተቤክ ኋላቀር ስለሆነች ነው--በመሐመድና በKrapf አረዳድ!!እሺ!የኢኦተቤክ የጾም ስርዓትስ በነመሐመድ ጥልቅ የነገረ-ኦርቶዶክስ ጥናት የዐማራ ቀሳውስት ፈጠራ ነው ተብሏል!ሰው እንዴት ከግብጽ እስከ ሕንድ፣ከሶርያ እስከ አርመንያ፣ከአቴንስ እስከ ሞስኮ፣ከአስመራ እስከ አልባኒያ ያሉ ኦርቶዶክሳውያን ሁሉ በጾማቸው ወራት ጥሉላት ምግቦችን (የእንስሳት ተዋጽኦዎችን) እንደማይመገቡ ጎግልን ጎልጉሎ መረዳት ያዳግተዋል??መሐመድ ሐሰንን የሚያክል የታሪክ ባለሙያ ለጾም ያን ያህል የተደነገገ ዝርዝር ቀኖና ከሌለው የክርስትና ዘውግ (ፕሮቴስታንት) ሃይማኖታዊ ግንዱ የሚመዘዘውን (ፓስተር?) Krapf ምንጩ አድርጎ እንዴት ስለ ኢኦተቤክ የጾም ቀኖና ብይን ይሰጣል? ከሰጠስ ለምን የረመዳን አጽዋማት በኦሮሚያ ያላቸውን አቀባበል ጨምሮ መርምሮ በንጽጽር አይተነትንልንም?‹‹ሌሊት እየተመገቡ ቀን-ቀን መጾምን የሚደነግገው ረመዳን ከኦሮሞ ባሕል ጋር ያለው ተዛምዶ እንዴት ይታያል?በሙስሊምና በኦሮሞ ኦርቶዶክሳውያን መካከል ያለው የሃይማኖት ሕገጋት አቀባበል ከኦሮሞ ባሕል ጋር ያለው አንጻራዊ ውሕደትስ?›› ብለን ብንጠይቅስ?
7-- ክስ-ሰባት፡- የኢኦተቤክ እንደመሬት ከበርቴ (ባለ‹‹ሲሶ›› ግዛት)!!
በሁሉም የሀገራችን ጸሐፍያን የኢኦተቤክ ባለሲሶ ይዞታ የነበረች መሆኗ በስፋት ተጽፏል--በራሷ መጻሕፍት ሳይቀር፡፡እነ መኩሪያ ቡልቻም ይህንኑ ደጋግመው ጽፈውታል፡፡አባስ ሐጂም የቡልቻን ጽሑፍ ጠቅሶ <<...the clergy were given land that was confiscated from the Oromo peasants and become landlords, they owned Oromo peasants as Gabbars (serfs) and thrived upto their labour...>> በማለት ብሶቱን ያቀርባል (Mekuria cited in Abas Haji:p.104)፡፡ጥሩ፡፡እዚህ ላይ አንድ እውነት አለ::በኦሮሞም ሆነ በተቀሩት ብሔር-ብሔረሰቦች (ዐማሮችንና ትግራውያንን ጨምሮ) ‹የሰሞን መሬት› የሚባል የቤ/ክ ይዞታ አይነት ነበር፡፡ነገር ግን የዚህ መሬት ይዞታ ለስሙ የኢኦተቤክ ይባል እንጂ ባለቤቶቹ ተመልሰው መኳንንቱና መሳፍንቱ ነበሩ፤ያዙበታል፤ምርቱን ይቆጣጠራሉ፤እንዲሁም ሲሞቱ ለልጆቻቸው ያወርሱታል--መሳፍንቱ፡፡የካሕናቱ እጣ-ፈንታ በመሳፍንቱ ስር ቅጥረኛ ሆኖ በድርጎ (የእለት ምግብ) ብቻ ማገልገል ነው፡፡በሌላ አነጋገር ካሕናቱ የበላይነታቸው በመንፈሳዊ ጉዳዮች እንጂ በቤ/ክ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች የማዘዝ መብት አልነበራቸውም፡፡ስለሆነም መሳፍንቱ በካሕናት ስም በተቆጣጠሩት ይዞታ መልሰው ካሕናቱን በእለት ምግብ ብቻ እየደለሉ በማስገልገል የተረፈውን ምርት ለግላቸው ይጠቀሙበታል፡፡ይሕ የባላባትና የደሃ ካሕናት ሥርዓታዊ የብዝበዛ ግንኙነት በተለምዶ ‹‹የቶፋ ሥርዓት›› ይባላል፡፡እንዲሕ ስር ሰድዶ የኖረው ሥርዓት ብዙም አይተረክም፡፡በቤተክሕነት ወገኖች የቀደሙ ነገሥታትንና ባላባቶችን አንዳንድ የማይካዱ ውለታዎች እንደማሳነስ ስለሚቆጠር ይመስለኛል የማይተረከው፡፡በዓለማዊ ጸሐፍት ደግሞ አንድም አሰራሩን በቅርብ ካለማወቅና ከቸልተኝነት፣ሁለትም ባለፉት 40 እና 50 ዓመታት ተራማጆቻችን (ተራ-ማጆች!) የኢኦተቤክ’ንን በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ በጅምላ ፈርጆ ማሳቀል ቀላል ስራ ስለሆነላቸው ይመስለኛል፡፡እንጂማ የኛ ወላጆች (ወላጅ አባቴ ካሕን ነበር!) በልመና እንጀራ ተማሩ፤ከእጅ ወደ አፍ እንኳ ሊባል በማይችል የሰቆቃ ኑሮ እድሜያቸውን ገፉ፤የረባ ጥሪት ለልጆቻቸው ሳያኖሩ ድኅነትን አውርሰውን ያለእድሜያቸው ተንከራተው አለፉ፡፡ሞቱ፡፡‹‹ሕያዋን ለነገሥታት፤ሙታን ለካሕናት ይገብራሉ›› በሚለው ብሂል በሙታን ተዝካርና የሙት አልባሳት ሲደጎሙ ኖረው ሞቱ፡፡በዋናነት 5ቱ ቀዳስያንና በዙፋኑ ዙሪያ ያሉ ‹‹ካሕናተ-ደብተራ›› ብቻ ነበሩ የንጉሡና የምዕመኑ እርጥባን ተቋዳሾች፡፡የተቀረው ለማኝ ነው፡፡በካሕናቷ ‹ምንዳቤ ወረኀብ› የኢኦተቤክ ‹የልመና ሃይማኖት› ተብላ ትጠራ ነበር፤አሁንም ይሕ ስያሜ በከፊል አለ፡፡ይሄ ይታወቃል፡፡ታሪክ ሲጻፍ ግን ‹‹ባለሲሶ ግዛት›› ይባልልናል!!ግና እንዲያ እንዳልሆነ ይታወቅ ነበር፡፡ስለመታወቁ ማስረጃ እንቁጠር...

Saturday, October 10, 2015

ስለአንዳንድ በኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክ ላይ…ከአንዳንድ የኦሮሞ ጸሐፍት የተሰነዘሩ…ያስቀየሙኝ ክታቦች!!


 ከበአማን ነጸረ (ክፍል ሁለት)


5-- ክስ-አምስት፡- በኦርቶዶክስ እልህ ወለጋ ጰነጠጠ፤ወሎ-አርሲ-ጅማ-ሐረር ሰለሙ!!
መኩሪያ ቡልቻ ‹‹...In Wollo in the North, in Arsi in Bale and Hararghe in the South and Sout-East, and in Jimma in the South-West Islam was adopted to avoid the often forced mass conversion by the clergy of the Abyssinian Orthodox Church.In Wallaga, in the West many Oromos including most of the traditional elites became protestants>>ይለናል (Being and Becoming Oromo:p.55)፡፡እስኪ ይቺን የመኩሪያ ጽሑፍ ገላልጠን እንያት--አንድ በአንድ!!
(5.1) ወሎ እነ መኩሪያ ቡልቻ ‹‹አቢሲኒያ›› ብለው ከሚጠሩት ግዛት ራሱን ገንጥሎ የኖረ ሳይሆን በግዛቱ ውስጥ ተዋናይ ነበር፡፡‹‹ወሎ በእልህ እስልምናን ተቀበለ›› የሚል ታሪክ ምናልባት ከካቶሊካዊው አቶ አጽሜ አግኝተው እነ መኩሪያ ቡልቻ ‹የአዋቂ አጥፊ› እንሁን ካላሉ በቀር ታሪኩ በራሳቸው በሙስሊም አማንያንና በውጭ ሀገር ጸሐፊዎች ተተርኳል--ወደ ወሎ እስልምና የገባበት ጊዜ፡፡ለማሳያ ያሕል ታቦር ዋሚ ሙስሊም ጸሐፍትንና ፖርቱጋላዊው አልፋሬዝ በ1520ዎቹ ስለሙስሊምና ክርስቲያን ወለየዎች ተፋቅሮ የከተበውን ማስታወሻ ዋቢ አድርጎ የግራኝ አህመድ ጦር በአካባቢው ከመድረሱ በፊት ወሎዬ የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች እንደነበሩና ሕዝቡ [የወሎ] በሃይማኖት ሳይለያይ በሰላም አብሮ ይኖር እንደነበር አትቷል (ታቦር ዋሚ፡ገ.306)፡፡ከዚህ አንጻር ‹ወሎ በኦርቶዶክስ እልህ ሰለመ› ብሎ መጻፍ የኦርቶዶክስን ብቻ ሳይሆን የእስልምናንም ሆነ የወሎን ሕዝብ ታሪክ ያገናዘበ አይመስለም፡፡
(5.2) የአርሲን እስልምና በሚመለከት በአካባቢው ታሪክ ላይ ወረቀቶች የሠራው አባስ ሐጂ ሲገልጽ <<....among the Arsi and the Oromos of Harar where there was an old Islamic presence, Christianity failed to get foot hold>>በማለት (Abas Haji: p.107) አካባቢው የሰለመው ቀደም ብሎ ማለትም ከክርስቲያኑ ኃይል ማንሰራራት በፊት መሆኑን ያመለክታል፡፡አቶ አጽሜ ‹‹ኦሮሞ ዐማራን ስለጠላ ሰለመ›› እያሉ በካቶሊካዊ ሚሽነሪ ወገንተኛነት የጻፉትን አባስ ሐጂ ሲተችም <<This [Atsme’s] explanation is however, not adequate because Islam entered the region long before Imperial conquest...>> እያለ በአርሲ ነዋሪ ነባሪ የእስልምና እርሾ መኖሩን ይነግረናል፡፡የአባስ ትችት ለሀቅ ሳይሆን ለእስልምና ከመቆርቆር ነው ብዬ ለመጠርጠር እገደዳለሁ፤ቢሆንም ለእውነታው ከመኩሪያ እና ከአቶ አጽሜ ጽሑፍ የእሱ ይቀርባልና ተጠቀምኩት!
(5.3) የሐረር እና ጅማ ኦሮሞዎችን ቀደም ብሎ መስለምና የሸዋን ኦሮሞ ኦርቶዶክሳዊነት በሚመለከት ዶናልድ ሌቪን ሲገልጹ ‹‹ሐረር የፖለቲካ ማዕከል መሆኗ ቀርቶ የእስልምና ባህል ማስፋፊያና መስበኪያ ስለሆነች ፣ኦሮሞዎች ለሐረር ቅርብ በመሆናቸው እንዲሁም ደግሞ ምናልባት የሱማሌዎችንና የአፋሮችን ምሳሌ በመከተል ተነሳስተው አብዛኞቹ ኦሮሞዎች የእስልምና ተከታይ ሆነዋል፡፡......በላይኛው ጊቤ የሠፈሩት የኦሮሞ ጎሣዎች....በ18ኛውና በ19ኛው ክፍለ-ዘመን የራሳቸውን ነገሥታት አቋቁሙ፡፡የአቋቋሙት የዘውድ ሥርዓት የእስልምና ሃይማኖትን ተቀብሏል፡፡በአጭሩ በ19ኛው ክፍለ-ዘመን ከምኒልክ ድሎች በፊት፡፡...በሣሕለሥላሴ ዘመን (1813-1847 ዓ.ም)...አብዛኛው የሸዋ ኦሮሞ ክርስቲያን ሆነና በዐማራና ኦሮሞ መካከል የሚፈጸመው ጋብቻ የዘወትር ክስተት ሆነ፡፡››(ሌቪን፡ገ.73-75)፡፡የኢናርያውን ንጉሥ የአባ ባጊቦን አስቀድሞ መስለም የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን መጽሐፍ ጸሐፊው አባ አንጦንዮስም ገልጧል (አባ አንጦንዮስ፡ገ.83)፡፡
(5.4) ዶ/ር ላጵሶ ጌ.ድሌቦ በ‹‹የኢትዮጵያ ረጅም ሕዝብና ታሪክ፣አንደኛ መጽሐፍ›› ሁኔታውን ሲገልጹ ‹‹...በ1840 እና 1870 መካከል ከሸዋና ከሰሜን ኢትዮጵያ እስላማዊ የወርጅ-ጀበርቲ ነጋዴዎች በአምስቱ የጊቤ ማለትም የጉንጋ ኦሮሞ መንግሥታት ከንግድ ጋር እስልምና አስፋፉ፡፡›› በማለት የጊቤ መንግሥታትን ወደ እስልምና መግባት ከሙስሊም ሲራራ ነጋዴዎች ስብከት ጋር አያይዘውታል፡፡ትረካቸውን ሲቀጥሉም ‹‹....በተጨማሪም በደቡብ ምስራቅ ጥንት የባሊ የአዳልና የሀዲያ እስላም አገሮች የሰፈሩ የኦሮሞ ማኅበረሰቦች ከገዳ ሥርዓት ወጥተው በአጭር ጊዜ ውስጥ እስላሞች ሆኑ፡፡›› በማለት የእስልምናን መስፋፋት እንደ መኩሪያ እና አቶ አጽሜ አበባል ‹‹ከዐማራ ቄሶች እልህ ጋር›› ሳይሆን ከንግድ መነቃቃት ጋር አያይዘው ተአማኒ በሆነ መንገድ አቅርበውታል (ዶ/ር ላጵሶ ጌ.ድሌቦ፡ገ.252)፡፡የዶ/ር ላጵሶን አተራረክ ተአማኒ የሚያደርገው በአጠቃላይ በ19ኛው ክፍለዘመን እስልምና በንግድና በግብጻውያን መሪዎች የተጠናከረ ኢስላማዊ ስብከት በኦሮሚያ ብቻ ሳይሆን በሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች በተለይም በኤርትራ ቆላማ አካባቢ የነበሩ የትግረ፣የቢለን፣የማሪያ (የሀባብ፣የመነሳ፣የሳሆ) ጥንተ-ክርስቲያን ማኅበረሰቦች ወደ እስልምና መግባታቸው ነው (ዝኒ ከማሁ፡ገ፣258)፡፡የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ታሪክ ፀሐፊው ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ (M.A) ከዚህ የዶ/ር ላጵሶ ትረካ ጋር በሚመሳል መልኩ የኤርትራ ቆላማ አካባቢ ቀደምት ኦርቶዶክሳውያን ‹‹መሐመድ አሚን እልሚርጋኒ›› በተባለ ከግብጹ ገዥ ‹‹አህመድ ኢብን ኢድሪስ›› የተላከ ሙስሊም ሰባኪ ተሰብከው ስለመስለማቸው ጆን ስፔንሰርን ዋቢ አድርገው ጽፈዋል (አቡነ ጎርጎርዮስ፡ገ.69-71)፡፡ስለሆነም ይሕን በኦሮሚያ ብቻ ሳይሆን በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች በውጫዊ ኃይል ተልእኮና በውስጣዊ የሲራራ ነጋዴ ሙስሊም ሰባክያን የተገኘ የእስልምና መነቃቃት በኢኢተቤክ እልህ ብቻ ያውም በኦሮሚያ ብቻ እንደታየ እንግድ እንቅስቃሴ አድርጎ መተረክ አድማስን ማጥበብ ይመስለኛል፡፡
(5.5) የወለጋን በፕሮቴስታንት ተጽእኖ ስር መውደቅ በሚመለከት ድርጊቱ የተከናወነው በኦርቶዶክስ ጥላቻ ነው ብሎ መደምደም አስቸጋሪ ነው፡፡የቀ.ኃ.ሥ መንግሥት ከጣሊያን መውጣት በኋላ በነበረበት የኢኮኖሚ ድቀት የተነሳ ሚሲዮናውያን ወደ ሀገሪቱ ገብተው ማኅበራዊ አገልግሎት እንዲያበረክቱ ፈቀዱ፡፡በዚህ አጋጣሚ የኦርቶዶክስና የእስልምና ተጽእኖ ወዳልበረታበት ወለጋ ሄዶ በመስበክ የአውሮፓ ሚሽነሪዎች (ኋላ ግንባር ፈጥረው መካነ ኢየሱስን የመሰረቱት) እና የአሜሪካ ሚሽነሪዎች (ኋላ ቃለሕይወትን ያቋቋሙት) እድሉን ተጠቀሙበት፡፡ሚሽኖቹ ተደብቀው ሳይሆን በሕግ ማስታወቂያ ቁጥር 3/1937(?) (decree No.3/1944) በአካባቢው በይፋ እንዲሰብኩ ንጉሡ ፈቅደው ነው የተሰማሩት፡፡ወለጋ ፕሮቴስታንት እንዳይሆን ኃይለሥላሴ አልተከላከሉም፤ይልቅስ ፈቅደዋል ቢባል ይሻላል፡፡ይሕን ደግሞ <<...CMF [Chiristean Missionary Fellowship] ....choose Ethiopia because of Haile Selassie’s friendly policy towards Missionary groups.>> በማለት (Eric Gilchist:p.63) ያብራራልናል፡፡በአጠቃላይ የወለጋ በፕሮቴስታንት ተጽእኖ ስር መውደቅ መኩሪያ ቡልቻ እንደሚለው በኦርቶዶክስ የግዳጅ ክርስትና ሽሽት ሳይሆን ለወትሮውም በአካባቢው ስር የሰደደ የእስልምና እና የክርስትና ዘውጎች ተጽእኖ ስላልነበረ፣ስለ ኦርቶዶክስ ስላልተሰበከ፣በአንጻሩ የሃይማኖት ስብከታቸውን ከማኅበራዊ አገልግሎት (ትምህርትና ጤና) ጋር አቀናጅተው የሚሰሩ ፕሮቴስታንት ሚሽነሪዎች በመንግሥት እውቅና እና ፈቃድ በአካባቢው እንዲንቀሳቀሱ ከ1930ዎቹ ጀምሮ በሕግ ስለተፈቀደ ነዋሪው በብዛት ፕሮቴስታንት ሆነ ቢባል የተሻለ ይሆናል፡፡እንደሚታወቀው ከጣሊያን መውጣት በኋላ ለሚሽኖች በወጣው ሕግ ወለጋ እና ደቡብ ኢትዮጵያ የመሳሰሉት አካባቢዎች open area ተብለው ለሚሽኖች ሲፈቀዱላቸው ማዕከላዊና ሰሜን ኢትዮጵያ ግን closed area ተብሎ ሚሽኖች ወደዚያ ሄደው ለመስበክ ፈቃድ አልነበራቸውም፡፡የሚያሳዝነው mis-ነሪዎቹ ስላላዩትና ስላልሰበኩበት የሰሜን ሕዝብ (በእነሱ አጠራር ‹‹አቢሲኒያ››) እና ስለሚከተለው እምነት በነሲብ (በጨበጣ) እየጻፉ በእንግሊዝኛ የተጻፈን ሁሉ እንደወረደ ለመቀበል የሚያሰፈስፈውን ሐገራዊ ምሑር ስተው ያሳስቱታል፡፡‹እግዜር ይይላቸው› ከማለት በቀር ምን ይባላል!!
6-- ክስ-ስድስት፡- ኦርቶዶክስ የኦሮሞ ባሕል ጸር!!
‹‹ኦሮሙማ›› የሚለውን ቃል ከእምነት (belief)፣ከዘውግ (ethinicity) እና ከማንነት (identity) ጋራ አስተሳስሮ የሚሰብከው ባህል-ተኮሩ ገመቹ መገርሳ <<An Oromo person does not become a member of a beiliving community through a formal rite of incorporation such as baptism.An Oromo is born with Orommuma>> ካለ በኋላ የተለመደውን ‹‹አቢሲኒያ››ን እና ኦርቶዶክስን ሆን ብሎ አመሳስሎ የመጥራት ዘዴ ተጠቅሞ ሲተርክ <<…Borrowing their faith from the Judo-Chiristian tradition, Abyssinians came to revere a white God and reduced the Oromo belifs in Waqqa Guraacha to a form of Devil Worship>>ይለናል (Bieng and Becoming Oromo:p.97)፡፡ንባቡ አጭር ቢሆንም ስንሰነጣጥቀው ትርጉሙ ይበዛል፡፡እናብዛው!!
(6.1) ይቺ ትረካ በራሷ ‹‹አቢሲኒያ›› በሚል በሚገለጸው አካባቢ በውስጡ ከኦርቶዶክ የተለዩ ባሕላዊ እምነቶችና እስልምና መኖራቸውን ትዘነጋለች፡፡አዎ!ይቺ ተደጋግማ የምትነገር ‹‹የአቢሲኒያ ቤ/ክ›› የምትል ቃል ተግሳጽ ያሻታል፡፡የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ራሷን ‹‹የአቢሲኒያ ቤ/ክ›› ብላ ጠርታ አታውቅም፡፡አማንያኗም እንዲያ አይሏትም፡፡እንኳንስ እሷ የሺህ ዘመናት ታሪክ የምትቆጥረው የቅርቦቹ መካነ ኢየሱስ እና ወንጌላውያንም ራሳቸውን ሲጠሩ ‹‹የኢትዮጵያ›› የሚል ቅጽል አስቀድመው ነው፡፡ስለዚህ የኢኦተቤክ ራሷን በማትጠራበት ‹‹አቢሲኒያዊት›› የሚል ስያሜ መጥራት ‹‹ነገር ፍለጋ›› እንጂ ሌላ ስም የለውም፡፡ቤተክርስቲያኒቱን ራሷን በምትጠራበት ሳይሆን ፈረንጅ አኮላትፎ እና አጣሞ በሚጠራት ስያሜ ነው የምንጠራት ማለት የቅንነት አይመስልም፡፡ያስተዛዝባል፡፡
(6.2) በዚህ በነገመቹ መገርሳ እና የሚሽነሪ ማጠቀሻዎቻቸው ለዐማራ-ትግራይ ብቻ በመጠሪያነት በተሰጠው ስመ - ‹‹አቢሲኒያ›› ከሄድን እንደ አገው፣ቅማንት፣ነገደ-ወይጦ፣ኢሮብ፣የወሎና የትግራይ (ራያ-አዘቦ-አሸንጌ) ክርስቲያን ጥንተ-ኦሮሞዎች በትረካው ምክንያት ታሪካቸው ይጨፈለቃል፡፡ከኦሮሚያ ሕዝብ 30.5% የሚሆነው ነዋሪ የሚከተለውን ሃይማኖት እንደዋዛ በባሕላዊ ማንነት ሽፋን ምሑራዊ ቅሰጣ ተጠቅሞ ጥምቀተ-ክርስትናውን ሕሳዌ (የውሸት) ማስመሰልም ደስ አይልም፡፡ምሑራዊ አምባገነንት ይመስላል፡፡ከማንነትም አንጻር ዐማራ እና ትግራይ ራሳቸውን በዜግነታቸው (በብሔር አላልኩም) የሚገልጹት ‹‹ኢትዮጵያዊ›› ብለው እንጅ ‹‹አቢሲኒያ›› ብለው አይደለም፡፡‹‹ኦሮሞ ራሱን በሚጠራበት ስም ነው ሌሎችም ሊጠሩት የሚገባ›› ተብሎ ሁላችንም ከልባችን አምነን ተቀብለን ከተስማማን በኋላ ዐማራና ትግራይ ዐረቦችና ሚሺነሪዎች ባወጡላቸው ስም ‹‹አቢሲኒያ›› ተብለው መጠራት አለባቸው ብሎ የሌላውን ማንነት በይኖ መከራከርና የሃይማኖት ተቋሙንም በዚያ መንገድ ሰይሞ ለማክፋፋት መሞከር ተገቢ አይመስለኝም፡፡ቅር ያሰኛል፡፡አንድ ሰው/ተቋም ራሱን በይፋ የሚጠራበትን የመዝገብ ስም ለውጦ በዚህ እነ እከሌ ባወጡልህ ነው የምጠራህ ማለት ለመደማመጥና ስንጠራራ ለመሰማማትም ያውካል፡፡ራሴን በማልጠራበት ቢጠሩኝ ‹‹አቤት›› አልልም፡፡በአምልኮ ደረጃም ‹‹እ/ሔር ሰውን በአምሳሉና በአርአያው ፈጠረ›› እንላለን እንጅ ‹‹ነጩን በአምሳሉ አንጽቶ፤ጥቁሩን በጥላው አጥቁሮ ፈጠረው›› አንልም፡፡‹‹ሁሉም ሰው በአምሳለ-ፈጣሪ ተፈጥሯል›› ተብሎ ነው በይሁዲውም ሆነ በክርስትናው የሚሰበከው፡፡ከዚህ ውጭ ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ‹‹እ/ሔር ጥቁር ነው፤ነጭ ነው›› ብላ ለፈጣሪዋ ቅርጽና ቀለም የማውጣት ትውፊት የላትም፡፡እንዲያውም አብዛኞቹ በየአብያተ-ክርስቲያናቱ ያሉ ጥንታውያን ቅዱሳት ስእላት በቆዳቸው ነጭ ናቸው ተብለው የሚታመኑትን እመቤታችንን፣ጌታን፣ሐዋርያትንና ሰማእታትን ጠይም አድርገው በማቅረብ ትውፊታቸው የሚታወቁት፡፡የሐዲስ ኪዳን መርህኣችን ይኽ ነው፡- ‹‹አይሁዳዊ፡ወይም፡የግሪክ፡ሰው፡የለም፥ባሪያ፡ወይም፡ጨዋ፡ሰው፡የለም፥ወንድም፡ሴትም፡የለም፤ዅላችኹ፡በክርስቶስ፡ኢየሱስ፡አንድ፡ሰው፡ናችኹና››(ገላትያ ምዕራፍ 3 ቁጥር 28)፡፡
(6.3) ገመቹ መገርሳ ግን እንኳንስ ይሕን ሀቅ ወደመሬት ወርዶ ሊጽፍልን የሁሉም ክርስቲያኖች ሆነ ይሑዲዎች ወይም የሙስሊሞች የሃይማኖት መርህ ሐጋጊዎች (ደንጋጊዎች) የመካከለኛው ምስራቅ የፈካ ገጽታ ያላቸው (ነጮች?) ነቢያት/ሐዋርያት መሆናቸውን ሳያስተውል ክርስትናን እና ይሁዲን ከእስልምና ነጥሎ ስለ ‹ዋቃ ጉራቻ› ክብር ሲል ይሰዋቸዋል፡፡አናሲሞስ ወደ ኦሮሚፋ የተረጎመው መጽሐፍ ቅዱስ ከይሑዲ-ክርስቲያን ባሕል ውጭ ይመስል ጃሌ ገመቹ አቃቂር ይነቃቅሳል፡፡ምስጢሩ ዞሮ-ዞሮ የፈረደባትን ኦርቶዶክስ በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ነጥሎ ማነወር ነው!የዋቃ ጉራቻን የጠየመ ምስል ለማጉላት ክርስቶስን (ለስም አጠራሩ ክብር ይግባውና) እና አምላኪዎቹን ማሳነስ ነው!!ለነገሩማ ጥቁሩ አምላክ(Waqqa Guraacha) በጥቁረቱ ከተወደሰ፣ነጩ አምላከ-ሙሴ (እ/ሔር ወይም ኢየሱስ) በንጣቱ ከተወቀሰ ዘረኝነቱ አልሸሹም ዞር አሉ ነው፡፡ማን ነው የጥቁርን ዘረኝነት ቅድስና የሰጠው?!Is it not counter-racism? Is racism of black people against white brothers justifiable?
(6.4) የኦርቶዶክሳዊነት-እና-ኦሮሞነት ውኅደት በተግባር ይታይ ከተባለ የኢኦተቤክ በኦሮሞ ባሕላዊ ጭፈራዎች ታጅባ የታቦት ንግሦችንና ጥምቀትን ማክበሯን ጃንሜዳ፣ፉሪ ሃና፣የካ ሚካኤል እንዲሁም በአጠቃላይ ኦሮሞ ኦርቶዶክሳውያን ባሉባቸው አድባራት ሄዶ መታዘብ ይቻላል፡፡በተለይ በሸዋ ኦሮሞ ባሕላዊ አልባሳትን በማበረታታት፣በኦሮሚፋ መዝሙራት ባሕላዊ የሙዚቃ መሳሪያዎችን ብቻ በመጠቀም፣ጨፌ በየገዳማትና አድባራቱ በመጎዝጎዝ፣ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የእሬቻን ጤናማ ትርጉም በማጤንና በማጉላት ኦርቶዶክሳውያን የኦሮሞ ካሕናትም በአከባበሩ ተገኝተው በማክበር፣በኦሮሚያ በሚገኙ አብያተ-ክርስቲያናት (ደ/ሊባኖስ፣ቁልቢ፣ዝቋላ፣ወንጪ ቂርቆስ፣ደብረ-ፅጌ፣ዝዋይ ገዳማት፣ወዘተ…) መንፈሳዊ ጉዞዎችን በማካሄድ የሕዝብ ለሕዝብ ትስስር ሲደረግ ኖሯል፤አሁንም የበለጠ ለማዳበር ጥረት እየተደረገ ነው፡፡እነዚህ ድርጊቶች እንዴትም ቢተረጎሙ በኦሮሙማ ላይ አሉታዊ ጎን አላቸው ማለት አስቸጋሪ ይመስለኛል፡፡ኦሮሙማ እና ኦርቶዶክስ እንዳይጋጩ አድርጎ ማስቀጠል እንደሚቻል ኦርቶዶክሳውያን የቱለማ ኦሮሞዎች በበረከቱበት የሸዋ ምድር በድምቀት የሚከበሩት 2ቱ የፀደይና የበልግ እሬቻዎች ምስክሮች ናቸው፡፡
(6.5) ኦሮሙማን በማስተናገድ አቅሙ ኦርቶዶክስ በጥንታዊው የኦሮሞ እምነት ዋቄፋና እና በእምነቱ መሪ በአባ ሙዳ ዐይን ይገምገም ከተባለም ሌሎች የሃይማኖት ተቋማትና መሪዎቻቸው ስለ እሬቻ፣ቃሉ፣ቃሊቻ፣ጂላ፣ጨሌ፣ቦረንትቻ፣ዋቃ ጉራቻ፣ሀማቺሳ፣ወዘተ ያላቸው አተያይ፣እንዲሁም ለኦሮሞ አለባበስ፣ባሕል፣ሙዚቃ፣ሥነ-ልቦና ያበረከቷቸው አስተዋጽኦዎች በዝርዝር ተገምግመው ደረጃ ቢሰጠን ሸጋ ነው፡፡አሁን እየተደረገ ያለው በሕግ ተፈቅዶላቸው በኦሮሚያና በደቡባዊ ሀገሪቱ ክፍል ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ሚሽነሪዎች ሀገሪቱን በፈለግነው መጠን ፕሮቴስታንትና ካቶሊክ እንዳናደርጋት ተከላክላናለች የሚሏትን የኢኦተቤክ እያነወሩ የጻፉትን እንደወረደ እየገለበጡ በዋቄፋና ከለላነት ተጠልሎ ምሑራዊ ጥላቻ መዝራት ነው፡፡በውጤቱም ኦርቶዶክሳውያን ኦሮሞዎችን ሆድ እያስባሱ ወደ ፕሮቴስታንቲዝም ከማስኮብለል በቀር በኦሮሚያ የዋቄፋና ተከታዮች ቁጥር 4% እንኳ ሲደርስ አላየንም!

To be continued.......

Monday, October 5, 2015

ስለአንዳንድ በኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክ ላይ…ከአንዳንድ የኦሮሞ ጸሐፍት የተሰነዘሩ…ያስቀየሙኝ ክታቦች!!


በአማን ነጸረ ፣ መስከረም 10 ቀን 2008 ዓ.ም

የታላላቅ ኦሮሞ ወንድሞቼን ቅሬታ የተጫናቸው ጽሑፎች አንብቤ ቅር አለኝ፡፡መነሻ የሆናቸውን ታሪካዊ በደል ለመረዳት አልሰነፍኩም፡፡ያም ሆኖ መስመር ያለፈና ባንድ ቦይ ብቻ የፈሰሰ በመሰለኝ ቅሬታቸው ቅር አለኝ፡፡ቅሬታዬ ቆየ፡፡ፈራሁ፡፡ከዚህ በላይ በሆዴ ከቆየ ቂም ይሆንና ይጎዳኛል ብዬ ፈራሁ፡፡ስፈራ ቅሬታዬን በረጅሙ (በፌስቡክ ስሌት ነው ርዝማኔው መጉላቱ) ጻፍኩት፡፡ሆኖም ስጽፈው ከ3 ችግሮች እንደማልነጻ አምኜ ነው፡፡አንድም በሁለንተናዬ ስላደኩበትና አሁን ድረስ በዕለት ኑሮዬ ስለሚደጉመኝ እንዲሁም የማኅበራዊ መደብ ጀርባዬ ስለሚመዘዝበት ተቋም ስናገር ንግግሬ ከሚዛናዊነት ይልቅ ወደ ተከላካይነት (advocacy?) እንደሚያጋድል ይታወቀኛል፡፡ሲቀጥል አማተር ነኝና የአጻጻፍና የማስረጃ ስደራ ችግር አያጣኝም፡፡እንዲያም ሲል ከሃይማኖት-ፖለቲካ ተዛምዶ አንጻር ያለኝ አረዳድና ንባብ ድኩም መሆኑን አልስተውም፡፡በተረፈ ‹‹አንዳንድ›› ብዬ የምጠራቸውን የኦሮሞ ጸሐፍት በስም ጠቅሻለሁ፡፡ጉዳዬ ስለክታባቸው ያውም ደግሞ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን (ከአሁን በኋላ የኢኦተቤክ) በማስመልከት ስለጻፉበት ነጥብ ብቻ ነው፡፡ከዚህ ውጭ እነሱም ሆነ ሌሎች ጸሐፍያን ስለሚያነሱዋቸው ተያያዥ ጉዳዮች መጻፍ የዚች ትሑት (ታናሽ) ጽሑፍ ዐላማ ስላልሆነ ተዛማጅ ጉዳዮችን አለመንሳቴን በአትሕቶ-ርእስ እገልጻለሁ፡፡
በዚች ጽሑፍ የማተኩርባቸው ቅሬታዎች፡- (1)የኢኦተቤክ ደባትር ‹‹ጋላ›› የሚለውን ቃል ሆን ብለው ኦሮሞን ለማሳነስ ፈልስፈዋል፣(2)የኢኦተቤክ ሥርዓት እኩልነትን አይቀበልም፣(3)አቶ አጽሜ እና አለቃ ታዬ የኢኦተቤክ ደባትር ናቸው፣(4) የኢኦተቤክ ለአፋን ኦሮሞ ጽዩፍ ናት፣(5)በኢኦተቤክ እልህ የተነሳ ወለጋ ፕሮቴስታንት ሆነ፤ጅማ፣ወሎ፣አርሲ እና ሐረር ሰለሙ፣(6)የኢኦተቤክ አስተምህሮ ከኦሮሞ ባሕል ጋር ተጻራሪ ነው፣(7)የኢኦተቤክ ካሕናት በሲሶ ገዥነት በኦሮሞ ምድር የመሬት ከበርቴች ነበሩ የሚሉ ናቸው፡፡አሁን ቀጥታ ወደታመቀው ክስና ሐተታዬ….

1-- ክስ አንድ፡- ‹‹ጋላ›› የሚለው ቃል የኢኦተቤክ ደባትር ፈጠራ ነው!!

‹‹ጋላ›› የሚለው ቃል ‹‹የአቢሲኒያ ቤተክሕነት ፈጠራ ነው›› ይላሉ እነ አባስ ሐጂ(ዶ/ር)፡፡‹‹ጋላ›› = መጻተኛ (stranger/outsider) የሚለው አገላለጽ የአቢሲኒያ ቤተክሕነት ፖለቲካዊና ርዕዮተ-ዓለማዊ አመክንዮ ያለው ፈጠራ ነው-- “fabricated by an Abyssinian clergy for politico-ideological reasons” ይሉናል (Mekuria cited in Being and Becoming Oromo: Re-examining the Galla/Oromo Relationship,p.105)፡፡ይቺን አገላለጽ በክብር እቃወማታለሁ፡፡ምክንያቱም በበኩሌ ‹‹ጋላ›› የሚለው ቃል በዚያ መልኩ በኢኦተቤክ የሃይማኖታዊ ሥርዓት መከወኛ መጻሕፍት ተጽፎ እና ተተርጉሞ አላገኘሁትም፡፡አውቃለሁ፡፡ብዙ የኦሮሞ ጉዳይ ጸሐፍት በ1960ዎቹ በ‹‹ራዕየ-ማርያም›› የወጣውን ስርዋጽ (ሆን ተብሎ በእኩያን የተጨመረ--ስረ-ወጥ--ከስር ያልነበረ) ጽሑፍ ይጠቅሳሉ፡፡እንደማመጥ፡-
(1.1) እሱ ስርዋጽ በኢኦተቤክ ደረጃ በሊቃውንትና በቅ/ሲኖዶስ ተመክሮበት ወይም በማናቸውም ከኢኦተቤክ አስተዳደር ጋር ግንኙነት ባለው አካል ፈቃድ/ትእዛዝ/ የወጣ አይደለም፡፡
(1.2) ስርዋጹ የኦሮሞን ብቻ ሳይሆን የሙስሊም፣የፈላሻ (ቤተ-እስራኤል) እና የሻንቅላ (ቤንሻንጉል-ጉሙዝ) ሕዝቦች ክብርንም እየጠቃቀሰ ኢ-ክርስቲያናዊ በሆነ መንገድ ያጎድፋል፡፡ታዲያ ያስተዋለ ሰው በግእዝ ቋንቋ ‹‹ሸ›› የሚባል ፊደል የማይታወቅ ሆኖ ሳለ በስርዋጹ ‹‹ፈላሻ እና ሻንቅላ›› የሚሉ ‹‹ሸ›› የበዛባቸው ቃላት በመታየታቸው ብቻ ተራ የእኩያን ጭማሪ (ስርዋጽ) መሆኑን መረዳት ይችላል፡፡እንዲህ ዐይነት ስርዋጽ ጽሑፎች ከዚህ በፊትም ከአንዳንድ ገድላትና ዜናመዋዕሎች ጋር ጎጃምን እንደ አገርና ሕዝብ በተለየ መልኩ ለማነወር በኵሸት ሕዝቡን ‹‹በላዕተ-ሰብእ (ቡዶች)››፤ሀገሩን‹‹ሀገረ-በላእተ-ሰብእ (የቡዶች ሀገር)›› የሚል ተቀጽላ ለመስጠት ተሞክሮ ሊቃውንቱ ታግለው ስርዋጹን ከኅትመት ከልተውታል፡፡ግብጻውያን በፍትሐ-ነገሥቱ ላይ የጨመሩት ‹‹የኢትዮጵያ አዋቂዎች ከራሳቸው ሊቅ ጳጳስ አይሹሙ›› የሚለውና በስንክሳር እስከዛሬ ለታሪክ ተመዝግቦ የሚገኘው ‹‹ኢትዮጵያውያን ከራሳቸው ሰው ጳጳስ ለመሾም ስላሰቡ መቅሰፍት ወረደባቸው›› የሚል ስርዋጽ በገቢር ከ1920ዎቹ ጀምሮ ቢሻርም ስርዋጹ ዛሬም አልተፋቀም፡፡እንዲህ ሲያጋጥም ለፍረጃ ከመሽቀዳደም ስርዋጹን ለማስተካከል ከመጣር በተጓዳኝ ገቢራዊነቱንም መፈተሽ፡፡
(1.3) ገቢሩ ሲፈተሸ ብዙኃን ኦሮሞ-ኦርቶዶክሳውያን ሊቃውንት ይህ ‹‹ጋላ ጋር የተኛ…›› የሚል ስርዋጽ ከመውጣቱ በፊት፣በወጣበት ጊዜ እና ከወጣም በኋላ በኢኦተቤክ ከተራ ካሕን እስከ መዓርገ-ጵጵስና ሲያገለግሉ ነበር፡፡አሁንም ያገለግላሉ፡፡ይሕም ስርዋጹ በምንም ተአምር ከኢኦተቤክ እንደማዕከላዊ ተቋም ታዝዞና ኃላፊነት ተወስዶ እንዳልገባ ገቢራዊ ማሳያ ነው፡፡ለነገሩ በ1960ዎቹ ብልጭ ብሎ የጠፋው ባለስርዋጽ መጽሐፍ አሳታሚና ማ/ቤቱም የኢኦተቤክ ንብረት አልነበሩም፡፡
(1.4) በምዕመን ደረጃ የኢኦተቤክ ብሔር ለይታ ‹‹እከሌን አግቡ፣እከሌን አታግቡ›› አትልም፡፡የመጣው ሁሉ ክርስትና ይነሳል፡፡ክርስትና ተነስቶ አቅመ-አዳም/ሔዋን የደረሰው ሁሉ ጋብቻው በሥርዓተ-ተክሊል ይፈጸምለታል፡፡ይሕ ድርጊት ብሔር አይለይም፡፡በዚህ መንገድ ቁጥራቸው አያሌ የሆነ ኦሮሞ ኦርቶዶክሳውያን በቅድስት ቤ/ክ እርስ በርሳቸውና ከፈቀዷቸው ብሔረሰቦች ተወላጆች ጋር በሥጋ ወደሙ ተወስነው ጋብቻ ሲፈጽሙ ኖረዋል፡፡እየፈጸሙ ነው፡፡ስለሆነም ከ‹‹ጋላ ጋር የተኛ›› እያለ የኵነኔ ፍርድ የሚሰጠው ስርዋጽ የኢኦተቤክ ያላትን አሰራር በቃልም በተግባርም አይገልጽም፡፡ምክንያቱም ጽሑፉ--ስርዋጹ የእርሷ ስላልሆነ!!
(1.5) እስከማውቀው በኢኦተቤክ የኦሮሞ ሕዝብ እና ታሪክ ከሌሎች ተለይቶ በአሉታ አይታይም፡፡ምክንያቱ ግልጽ ነው፡፡በቅርብ ዓመታት በአንዳንድ የኦሮሚያ አካባቢዎች ኦርቶዶክሳውያንን በጫና የማስለምና የማጰንጠጥ ሙከራዎች ብቅ ማለት ቢጀምሩም በረጅሙ የኦሮሞ ሕዝብ ታሪክ ሕዝቡ እንደ ሕዝብም ሆነ የአስተዳደር ሥርዓቱ (ገዳ) በሌላው ሕዝብ ላይ የሃይማኖት ማንነትን በኃይል የመጫን ባሕል አልነበረውም፡፡የ16ኛው ክ/ዘ የኦሮሞ ጦርነቶችም ሃይማኖታዊ ገጽታቸው ጎልቶ ሲነገር አልሰማንም፡፡ሃይማኖት ጫና ካልተደረገበት ደግሞ ሃይማኖታዊ ሰማዕትነት የለም፡፡ስለዚህ የዮዲት፣የሱስንዮስ፣የግራኝ መሐመድ፣የደርቡሽ፣የጣሊያን፣የደርግ እና የ20ኛው ክ/ዘመን የአክራሪ እስልምና ጥቃቶች በኢኦተቤክ መዛግብት በ‹‹ዘመነ-ሰማዕታትነት›› ሲመዘገቡ የኦሮሞ ታሪክ እንደ ብሔር በዚያ መልኩ አልተካተተም፤ድሮም አሁንም፡፡ስለሆነም ያን ያህል ብሔሩን ለማሳደድና የተለየ ስም ለመስጠት የሚያበቃ ቅራኔ በኢኦተቤክ በኩል አልነበረም፤የለም፡፡
(1.6) ወደ ቤተ-መንግሥቱ ደባትር እንሂድ፡፡እውነት ነው፡፡የቀድሞ ነገሥታት ዜና-መዋዕል ጸሐፊዎች በኢኦተቤክ የተማሩ ሊቃውንት ናቸው፡፡ቅብዐ-መንግሥት ቀብተው የሚያነግሡ አንጋሾችም የኢኦተቤክ ጳጳሳት (በዜግነት ግብጻውያን ጳጳሳት) ነበሩ፡፡ነገሥታቱ ኦርቶዶክሳውያን የነበሩ መሆናቸው እውነት ነው፡፡ነገሥታቱ በአገዛዛቸው ዘይቤ ኦርቶዶክሳዊነት የተጫነው religious nationalism አዝማሚያ እንደሚያሳዩና ለኢኦተቤክ አበው የተለየ ውዴታና ከበሬታ እንደነበራቸውም አይታበልም፡፡ኦርቶዶክሳውያን አበው (ጳጳሳት) ንጉሡ በእነሱ እምነት ማደሩን እና እስከ ፍጻሜ ዘመኑም በእምነቱ እንደሚጸና ቃል አስገብተው ይቀቡት እንደነበር እሙን ነው፡፡ይሄ አሰራር ይብዛም ይነስም በሁሉም ቀደምት የነገሥታት ሥርዓት በሰፈነባቸው አህጉር ያለ ነው፡፡በኦሮሞ ጥንታዊ የገዳ ባህልም ተሞክሮው ያለ ይመስላል፡፡ለአባ ገዳነት ለመብቃት ቅብዐተ-ቃሉ (በቃሉ መቀባት) ስለማስፈለጉ ታቦር ዋሚ ብሩ ጸጋዬን ጠቅሶ ሲጽፍ ‹‹…ለአባ ገዳነት ለመብቃትም ዋነኛው መመዘኛ የዋቄፈና ሃይማኖትን አክብሮና የሕዝቡን ወግና ሥርዓቶች ተከትሎ መገኘት ሲሆን…የሉባዎች ስልጣን የሚጸድቀው በቃሉ (አባ ሙዳ) የቡራኬ፣የምርቃትና መቀባት ሥርዓት ነው›› ይላል (ታቦር ዋሚ፡ገ.248)፡፡እርግጥ የአባ ገዳ ሲመት በዘር ሳይሆን በምርጫ መሆኑ ተራማጅ ያሰኘዋል፡፡
(1.7) ወደ ሐተታዬ ስመለስ ነገሥታቱ ለኢኦተቤክ እንደሚባለው ‹‹ሲሶ መንግሥት›› ባይሆንም መጠነኛ እርዳታ ሲያደርጉ መኖራቸውም እውነት ነው፤ኦፌሴላዊ ቋንቋቸውም ለረጅም ጊዜ የኢኦተቤክ መገልገያ የሆነው ግእዝ እንደነበረም እናውቃለን፡፡ያ!ማለት ግን ዜና-መዋዕል ጸሐፊዎች በግእዝ የሚጽፉት ሁሉ የኢኦተቤክ ዶግማና ቀኖና ነው፤ወይም የኢኦተቤክ የውዳሴና ቅዳሴ ዶክመንት ነው ማለት አይደለም፡፡ግእዝ ቋንቋ ነው፡፡እምነት፣ፍልስፍና፣ኑፋቄ፣ታሪክ፣ጥንቆላ፣…ይጻፍበታል፡፡ስለዚህ ይሄን ሳያስተውሉ የኢኦተቤክ በግእዝ ቋንቋ ለተጻፈ ዶክመንት ሁሉ (በተለይ ለነገሥታ ዜና-መዋዕል) ኃላፊነት አለባት ማለት በላቲን ፊደልና ቋንቋ ለተጻፈ ሁሉ ካቶሊኮች ተጠያቂ ናቸው፤ወይም ደግሞ በዐረብኛ ለተጻፈ ሁሉ እስልምና ተጠያቂ ነው እንደማለት ይሆናል፡፡
(1.8) ‹‹ጋላ›› ወደሚለው ቃል አጠቃቀም ልምጣ፡፡ዛሬ አንዳንድ ኦሮሞ ወንድሞቻችን ሚሽነሪዎች ‹‹ጋላ›› የሚለውን ቃል ስለማይጠቀሙ ወደ ወለጋ ያቀኑ ሚሽነሪዎች ተቀባይነት አገኙ ይሉናል፡፡ሸጋ፡፡ሚሽኖችን እንስማቸው፡፡<<The Missinories referred to the Oromo as the Hamitic [non-semetic] GALLAS who spoke GALLINYA.They used this condescending term…as late as 1973, nearly ten years after working with Oromo…>>ይላሉ(GilchrristII:73) (አጽንኦቱ የኔ ነው)፡፡የሚያሳዝነው እነዚህ የፕሮቴስታንትና የካቶሊክ ሚሽኖች ከ10 ዓመትና ከዚያ በላይ (ለምሳሌ፡- የMissio-Galla ባለቤቱ ካቶሊኩ አባ ማስያስ ከ145-1880 ዓ.ም ለ35 ዓመታት እንዲሁም የVicariatus Apostolici apud Gallas Commentarium Historicum ab erectione Vicariatus usque hodie ባለቤቱ አባ ጃሮሶ ከ1882-1938 ዓ.ም ለ46 ዓመታት) በኦሮሞ ሕዝብ መካከል ቋንቋውን (አፋን ኦሮሞ) እየተናገሩ ኖረው በእንግሊዝኛና ጣሊያንኛ ተጠቃሽ መጻሕፍቶቻቸው ‹‹ጋላ›› የሚል ቃል የሚጠቀሙት ‹‹በአቢሲኒያ ቄሶች›› ተጽእኖ እንደሆነ ለማስመሰል ይሞከራል፡፡ያሳዝናል፡፡መቼም ‹‹የአቢሲኒያ ቄሶች›› ተጽእኖ አውሮፓና አሜሪካ ድረስ ተጓጉዞ ለሚታተም የሚሽነሪ መጽሐፍ እንዴት ተጽእኖ ፈጣሪ እንደሚሆን እነሱና ደቀ-መዛሙርቶቻቸው ብቻ ናቸው የሚያውቁት!!
(1.9) ወደ ቤ/ክ መጻሕፍት እንመለስ፡፡ቢያንስ ስለቅኔ ቤት እና ዜማ ቤት ምስክር መሆን እችላለሁ--ስላለፍኩባቸው፡፡በነዚህ ጉባኤያት ‹‹ጋላ›› የሚል የግእዝ ቃል አልሰማንም፡፡በሌላ በኩል በውዳሴ ማርያም የአንድምታ ትርጓሜ የ1990 እትም ላይ በገጽ-86 እንዲህ የሚል ቃል ይገኛል ‹‹…በግብፅ የሚገኙ መነኮሳት በአመት ሁለት ጊዜ ያበስላሉ፡፡…ከአኃው [መነኮሳት] አንዱ ቢታመም ትኩስ እንጀራ የሚያመጣልኝ ባገኘሁ በቀመስሁት ነበር አለ፡፡ከዚህ በኋላ አንዱ የማን ወንድም ትኩስ እንጀራ እያለ ይሞታል ብሎ በመካከሉ <በርበር የሚባል ጋላ> ያለበት ነው፤ያንን አልፎ ሄዶ አምጥቼልሀለሁ ቅመስ አለው…›› እያለ ‹‹ጋላ›› ማለትን ለሽፍታ በርበር ሰጥቶ ይተርክልናል፡፡ በቅ/ያሬድ የኅዳር 29 የተፍጻሜተ ሰማዕት ቅ/ጴጥሮስ ድጓና በእለቱ ስንክሳር ‹‹ጋላት›› (በግእዙ ‹‹ላ›› ላልቶ ነው የሚነበብ) የሚል ቃል ይገኛል፡፡ቅ/ያሬድ በዐረብ ምድር በ4ኛው ክ/ዘ ስለተሰዋው ተፍጻሜተ - ሰማዕት ጴጥሮስ ሲያዜም ‹‹…አባ ጴጥሮስ ተፍጻሜ-ሰማዕት፣መጠወ ርእሶ ለ‹ጋላት›….›› ይለናል፡፡ቅ/ያሬድና የውዳሴ ማርያም መተርጉማን ቃሉን ለሰሜን አፍሪካ ኢ-ክርስቲያን የ3ኛው መቶ ክ/ዘ በርበሮች ሰጥተው ነው የሚናገሩት፡፡ከዚህ ውጭ እኔ ባጭር ዘመኔ ባነበብኳቸው የኢኦተቤክ መንፈሳዊ መጻሕፍት ‹‹ጋላ›› ስለሚለው ቃልና ስለብያኔው አላገኘሁም፤አልተማርኩም፡፡በቅኔ ቤት ‹ደብተራ› ተብለን የተማርንበት የእጅ ጽሑፍ ግስ (መዝገበ-ቃላቱን ግስ እንለዋለን) ‹‹ጋላ›› የሚል ቃል በፍጹም የለውም፡፡የእጅ ጽሑፉ ዛሬም በመጽሐፍ መደርደሪያዬ ያለ ነው፡፡
(1.10) ስለሆነም ይሕን ቃል ‹‹የኢኦተቤክ ደባትር ፈጠራ ነው›› በሚል ድምዳሜ ቤተክርስቲያኒቱንና ሊቃውንቷን በምልዐት ከሥርዓታቱ ጋር አላጥቆ ፈርጆ በጭፍን ከማሳደደድ በፊት ግራቀኙን ማየት አይከፋም፡፡ቢያንስ በተጓዳኝ የዚህን ቃል ምንጭ ዐማራን ጨምሮ በከፋ፣ሐዲያ፣ሲዳማ፣ጋሞ፣ትግራይ፣ሶማሌ….ከመሳሰሉ ብሔረሰቦች ቋንቋ ውስጥ ማሰስ፣ወደ ጎረቤት ሶማሊያና ኬንያ የታሪክ ጽሑፎች ጎራ ብሎ መጠየቅና ሰነድ ማገላበጥ፣ከሩቅ ዘመን ጀምሮ በምድረ-ኦሮሚያ ኖረው በአውሮፓ መጻሕፍትን ያሳተሙ የሚሽነሪ ጽሑፎችን በጥንቃቄ ማገላበጥ የተሻለና ሚዛናዊ መደምደሚያ ላይ ለመድረስ የሚረዳ ይመስለኛል፡፡Thomas Zitelman የተባለው ጸሐፊ በBeing and Becoming Oromo የጥናት መጽሔት Re-Examining the Galla/Oromo Relationship የተሰኘ ጽሑፉ ዘመናዊውና የታደሰው የኦሮሞ ማንነት ቅርጽ የያዘው በስዊድን ሚሽነሪዎች ነው የሚል ምልከታውን ገልጹዋል፡፡እንጥቀሰው <<During the late 19th C the Swedish Protestant missionray activities at Monkullo [Eritrea] provided a contextual frame for a modern reformation of being Oromo, by mixing Protestant zeal,romantic European nationalism and elements of Oromo past>> >>ይላል(Being and Becoming Oromo:p.108)፡፡እንጠርጥር ካልን ይቺ ጽሑፍ የሚሽነሪዎች ተጽእኖ በጎላባቸው የኦሮሚያ አካባቢዎች ሰባክያኑ ከስብከታቸው ጋር ‹‹የአቢሲኒያዎች ቤ/ክ ለኦሮሞ ‹ጋላ› የሚል አዋራጅ ስም ስላወጣች አትሆናችሁምና አዲስ ማንነት በፕሮቴስታንታዊነት ተላበሱ የሚል ብሔር-ተኮር ቅስቀሳ በወለጋ አካባቢ ሳይካሄድ እንዳልቀረ ታመላክታለች›› ብለን መጥርጠር ይቻላል፡፡ይቺ-ይቺ ፀረ-ተዋሕዶ የሚሽኖች ስብከት ተጠራቅማ የኦሮሞ ማንነትን በአዲስ እይታ ለመቅረጽ የተጉ ምሁራነ-ኦሮሞ የሆኑ ጸሐፍት ‹‹ጋላ›› የሚለው ቃል--“fabricated by an Abyssinian clergy for politico-ideological reasons” እያሉ ለጥጠው እንዲጽፉ አበረታታች፡፡ጥርጣሬዬ ነው!!!የሚሽነሪዎቹ ተደጋጋሚ ጸረ-ተዋሕዶ ምዕራባዊ ጽሑፎች የወለዱት ጥርጣሬ!!

2-- ክስ-ሁለት፡-የኢኦተቤክ መዋቅር እኩልተኛ ስላልሆነ ኦሮሞዎች አይጋሩትም!!

የታሪከ-ኦርቶዶክስ ሊቅ ተደርጎ በነመሐመድ ሐሰን (ዶ/ር) እና በነአባስ ሐጂ (ዶ/ር) እዚህም እዚያም የሚጠቀሰው መኩሪያ ቡልቻ (ዶ/ር) <<Oromo Orthodox Christians, though they share religion with Abyssinians, do not share the political/ideological orientation of the Ethiopian Church whose main interest was the preservation [of] structural inequalities enshrined in myths and legends>>ይሉናል(Mekuria cited in Abbas Haji:106)::ታድለው!እዚህ መደምደሚያ ላይ ለመድረስ <የታለ ያደረጋችሁት የመስክ ጉብኝት፣የታለ ለኦሮሞ ኦርቶዶክሳውያን የተደረገው ቃለ-መጠይቅ፣የታለ በየሃማኖቶቹ መካከል ለንጽጽር የሰራችሁት የዳሰሳ ጥናት?> የሚላቸው የለም፡፡የፈለጉትን ቢጽፉ ቋንቋው እንግሊዝኛ እስከሆነ ድረስ ‹‹የደብተራ ተረት›› አይባልባቸውም፡፡ታድለው!ከዚህም ከዚያም እያገጣጠሙ ለያዙት ዐላማ እና ለታደሙበት ድርጅት የሚሆን ታሪክ በልክ ይሰፋሉ፡፡ወደ ሕዝቡ ወርደው አያጠኑም፡፡ብቻ መርጠው ይተነትናሉ፡፡ታሪክ ማለት ትንታኔ፤ትንታኔ ማለት ታሪክ ይሆናል፡፡
(2.1) እስኪ የኢኦተቤክ አደረጃጀት ይታይ፡፡ጥንት ‹‹የሊቃውንት ጉባኤ/ማኅበረ-መነኮሳት/ማኅበረ-ካሕናት›› የተሰኘ የውስጥ ሃይማኖታዊ አስተዳደሩን፣ዶግማና ቀኖናውን የሚበይን አካል ነበረ፡፡ከ1951 ዓ.ም ጀምሮ የኢኦተቤክ ከግብፅ መንፈሳዊ የሞግዚት አስተዳደር ነጻ ወጥታ የራሷን ቅ/ሲኖዶስ ሰይማለች፡፡ፓትርያርኩ ከፋም ለማም ላለፉት 56 ዓመታት የሚሾመው በምርጫ ነው፡፡በአጥቢያ ደረጃ ባለው አደረጃጀት ከምዕመናንና ካሕናት የተውጣጣ ‹‹ሰበካ-ጉባኤ›› የተሰኘ አካል ከ1960ዎቹ መጀመሪያ ዓመታት ጀምሮ እስካሁን ድረስ በ3ቱም ሥርዓታተ-መንግሥታት ያለማቋረጥ እየተመረጠ ቤ/ክ’ንን በማስተዳደር ላይ ይገኛል--ከፋም ለማም፡፡በደርግም አልተቋረጠም፡፡መራጩ ምዕመኑና ካሕኑ ነው፡፡እርግጥ <ዲሞክራሲ፣አሴምብሊ፣ካውንስል፣…> የሚሉ ቃላትን ባለመጠቀማችን ዲሞክራሲ ላይ በኋላቀርነታችን ለሰራነው በደል ዘመናዊ ዲሞክራት ጸሐፊዎቻችንን መጠየቅ ይኖርብናል!!
(2.2) እገምታለሁ፡፡ይሕ የ40 እና የ50 ዓመታት ተሞክሮ የሃይማኖቱን ብሉይ ታሪክ አይገልጽም ይባል ይሆናል፡፡ገዳማቱ ይመርመሯ!!!በስተሰሜኑ ማዕከላዊ ኦሮሚያ ያለውን ገዳም እንምረጥ--የሰላሌውን ደ/ሊባኖስ!!የገዳሙ መሪ ጥንት ‹እጨጌ› አሁን ‹ፀባቴ› ይባላል፡፡ብቻውን በገዳሙ ላይ የማዘዝ መብት የለውም፡፡<ምርፋቅ> በሚል ስም የሚጠራ 12 ተመራጭ መነኮሳት የሚሰየሙበት የመማክርት ጉባኤ አለ፡፡መራጮቹ የገዳሙ አባላት (መነኮሳት) ናቸው፡፡ተመራጮቹ አጠቃላዩን የገዳሙን ሕግ ከጸባቴው (አስተዳዳሪው) ጋር በመሆን ይደነግጋሉ፤ያጠፋውን ቀኖና ይሰጣሉ፤የአባላትን ቅሬታ ይፈታሉ፤ፀባቴውን ይቆጣጠራሉ፤በገዳሙ ወጣ ያለ ባሕርይ የሚያሳይ መነኮስ ካለ ጾምና ስግደት በመበየን በገዳሙ ማረሚያ ቤት እስከመላክ የሚያደርስ የውስጥ ሕግ ነበረ፡፡የገዳሙ አባል መነኮሳት በምርፋቅ አባላት ላይ ቅሬታ ካላቸው እንዲሁ ቅሬታቸውን አቅርበው ምርፋቁን አውርደው በሌላ ምርፋቅ ይተኩታል፡፡ይሕ ሥርዓት ትናንት ነበረ፤ዛሬም አለ፤ወደፊትም እስከ ምጽአተ-ክርስቶስ ይኖራል ብለን እናምናለን፤አምነን እንናገራለን!!
(2.3) ይሕን አሰራር እነ መኩሪያ ቡልቻ ከሚያወድሱት የአባ ሙዳ አሰራር ጋር እናነጻጽረው፡፡መኩሪያ ቡልቻ <<The Office of Aba Muuda was…open to the Oromo people as a whole and was visited by delegates from every ‘gosa’ and from different parts of Oromo-land, but non-Oromos were not allowed to participate in rituals>>ይላል(Being and Becoming Oromo:53)::በተጨማሪም አባ ሙዳ ወይም ቃሉ (መራሄ-ዋቄፈና) ለመሆን የሚቻለው በዘር ማለትም ከአባት ወደ ልጅ በሚተላለፍ የተወላጅነት ሰንሰለት ብቻ እና ሲመቱም እስከ እድሜ ልክ (እንደ የኢኦተቤክ የፕትርክና ቀኖና) መሆኑን ታቦር ዋሚን ጨምሮ ብዙ ጸሐፍተ-ኦሮሞ አረጋግጠዋል (ታቦር ዋሚ፡ገ.221)፡፡እንግዲህ እኩልተኛ ሥርዓት ማለት ሁሉም እንዳቅሙ እንዲወዳደር የውድድር እድል (equal opportunity) የሚከፍት ማለት ከሆነ እንደ ኦሪት ሌዋውያን ዘርና ብሔርን (ኦሮሞን ብቻ!) መሰረት አድርጎ የሃይማኖት መሪነትን የሚያወራርሰው ዋቄፈና እየተወደሰ በሌላ በኩል ላመነ፣ለተጠመቀና መንፈሳዊውን እውቀት ለጨበጠ ሁሉ እንኳንስ ብሔር ዜግነት ሳይመርጥ ለሰብዓዊ ፍጡር ሁሉ ክፍት ሆኖ የኖረው ቤተመቅደስ በpreservation [of] structural inequalities ሲከሰስ መስማት ግራ ያጋባል፡፡ብቻ ግን በዛሬው የUNDHR ዘመን ‹‹ዘእምነገደ-ይሑዳም ሆነ፤ዘእምነገ-ሙዳ ጊዜውን የዋጁ ሥርዓታት አይመስሉም›› ብለን እንለፍ!!

3-- ክስ-ሦስት፡- አለቃ ታዬ እና አቶ አጽሜ የኢኦተቤክ ደብተራዎች ናቸው!!

እነዚህን ሰዎች (አለቃ ታዬንና አቶ አጽሜን) መሐመድ ሀሰን፣አባስ ሐጂ፣መኩሪያ ቡልቻ፣ታቦር ዋሚ በስፋት ጠቅሰው ጽሑፋቸውን ሲመቻቸው ግብዐት አድርገውታል፡፡በጽሑፎቻቸው ‹‹የራሷ የኢኦተቤክ ጸሐፍት አለቃ ታዬና አቶ አጽሜ እንዲህ አሉ›› ለማለት ከሰዎቹ ስራ ሐሜት ሐሜቱን ነቃቅሰው እንደማጠናከሪያ ተጠቀመውበታል፡፡ሳይመቻቸው ቤተክርስቲያኗን ከነአለቃ ታዬ ጋር እየደረቡ ጭምር ጽሑፋቸውን በአያሌው አጣጥለውታል፡፡እሱ ችግር የለውም፡፡መብታቸው ነው፡፡ችግሩ ሰዎቹ የቤተክሕነት ወኪልና የኢኦተቤክ ደባትር እንደነበሩ ተደጋግሞ መጠቀሱ ነው--ያልሆኑትን!!እስኪ ባጭሩ ታሪካቸውን ከሃይማኖት አንጻር ብቻ በጨረፍታ እንይ…
(3.1) አቶ አጽመጊዮርጊስ (1825-1907 ዓ.ም) የሰሜን ሸዋ ተወላጅ (ዐማራ?) ናቸው፡፡ስለ ኦሮሞ በታሪክም በጸያፍም ሊታይ የሚችል ታሪክ ጽፈዋል፡፡እሱ የኔ ማጠንጠኛ አይደለም፡፡የኔ ማጠንጠኛ የእሳቸው ጽሑፍ የኢኦተቤክ አቋም ተደርጎ መወሰድ እንደሌለበት ማስረገጥ ነው፡፡ምክንያቱም እሳቸው የኦርቶዶክሳዊት ቤ/ክ አባል አልነበሩም፡፡እንዲያውም እድል ባገኙ ቁጥር ኦርቶዶክስን የሚያጥላሉና የካቶሊክ ሚሲዮናውያን በስፋት ሀገሪቱ ላይ አለመንሰራፋት የሚያንገበግባቸው፣የነአባ ማስያስ ሚኒልክን ካቶሊክ ማድረግ አለመቻል የሚቆጫቸው፣የሱስንዮስ ዘመን የሚናፍቃቸው ሰው የነበሩ ስለመሆናቸው አንዳንድ ቃላቶቻቸው ያሳብቃሉ፡፡ጭልጥ ያሉ ካቶሊክ ነበሩ፤ያውም የኢኦተቤክ እና የካሕናቷ ከሳሽ፡፡ማስረጃ እናምጣ፡፡ፕ/ር ታምራት አማኑኤል በጻፉት ‹‹ስለኢትዮጵያ ደራሲያን›› የተሰኘ ምጥን መጽሐፍ በገጽ-14 ይኸንኑ የአቶ አጽሜን ጸረ-ኦርቶዶክስ አቋም ሲገልጹ ‹‹በካቶሊክ ሃይማኖት ያዲሱ ትውልድ ዘመን ሰው ስለነበሩ ለሃይማኖታቸው የነበረባቸው ቅንኣት በኦርቶዶክሳውያን ወገን ላይ ምክንያት ባገኙ ቁጥር ከልክ ያለፈ የተግሳጽ ቃል አስጽፉዋቸዋል፡፡አንዳንድ ጊዜም ታሪኩ መንገድ ሳይሰጣቸው በኦርቶዶክሳውያን ላይ የኃይል ቃል ለመጻፍ ምክንያቱን በግድ ፈልገው ያመጡት ይመስላል›› በሚል አስፍረዋል፡፡አቶ አጽሜ ለኦሮሞ የተቆረቆሩ መስለው የሚሽኖችን አለመምጣት በቁጭት ያነሳሉ፡፡የጦሩን መሪ ንጉሥ ምኒልክ ትተው በዐማራነት የፈረጇቸውን የኢኦተቤክ ካሕናትን ክፉኛ ይወርፋሉ፡፡የእሳቸውን የአጻጻፍ መንፈስ፣የውስጣቸውን ካቶሊካዊ ቅናትና መነሳሻ (motive) ያላጤኑ እንደነመሐመድ ሐሰን አይነት ጸሐፍት የእሳቸውን የጥላቻ ቃል እንዳለ እየወሰዱ ያጮሁታል (JOS:vol-7:p119)፡፡እነመሐመድ እና ጓዶቻቸው የካቶሊኮችን፣የሙስሊሞችንና ፕሮቴስታንቶችን ጽሑፎች ብቻ እየጠቀሱ ኦርቶዶክሳውያን ዶክመንቶችንና አማንያኑን ሳያመሳክሩ ስለኢኦተቤክ መጻፍን እንደልማድ መያዛቸውን ገና ወደፊትም በዚህ አጭር የዳሰሳ ጽሑፍ እናገኘዋለን፡፡አሁን ወደሌላው የኢኦተቤክ ደብተራ ወደተባሉት ጸሐፊ እንለፍ--ወደ አለቃ ታዬ ገብረማርያም!
(3.2) አለቃ ታዬ በ1853 ዓ.ም በጌምድር (ጎንደር)ተወለዱ፡፡ከአድዋ ዘመቻ በፊት (በ1872 ዓ.ም አካባቢ) ወደ ሐማሴን (ኤርትራ) ምንኩሉ የተባለ የስዊድን ሚሲዮናውያን ማረፊያ ሄደው ፕሮቴስታንት ሆኑ፡፡እዚያ ሳሉ ከምዕራባዊው ትምህርት ይልቅ ወደ ምስራቁ አዘነበሉ፡፡የግእዝ መጻሕፍት መመርመር ጀመሩ፡፡ለዚሁ እንዲረዳቸው ወደ ጎንደር ተመልሰው በ1875 ዓ.ም ቅኔ-ቤት ገቡ፡፡በ1877 ዓ.ም ቅኔ ተቀኝተው (ቤት ሞልተው ነው የሚባለው በባሕሉ) ተመለሱ፡፡በምንኩሉ ሚሲዮን አስተማሪ ሆኑ (ደማቆቹ፡ገ.57-68)፡፡ጥሩ የንባብ ተሞክሮ በቤተ-ፕሮቴስታንት ስላዳበሩ በእነሱ እርዳታ በ1889 ዓ.ም የግእዝ ሰዋስው አሳተሙ፡፡በሚሲዮናውያኑ የተልእኮ-ድጋፍ (ስፖንሰርሺፕ) ጀርመንኛ እና ፈረንሳይኛ አጥንተው በጀርመን የግእዝ አስተማሪ እስከመሆን ደርሰዋል፡፡ከዚያ መልስ በጎንደር ያባታቸው (አቶ ገ/ማርያም) ርስት ተፈቅዶላቸው እስከ 1903 ዓ.ም ይኖሩ ነበር፡፡‹‹...ይሁን እንጂ በደብረ ታቦር ሳሉ ‹ጻድቃን አያማልዱም› በሚል ክርክር ከካሕናት ጋር ስለተጋጩ ብዙ ጭቅጭ አገኛቸው፡፡በመጨረሻም በዚሁ ክርክር ምክንያት ወደ አዲስአበባ ተላለፉና ከአቡነ ማቴዎስ [ግብጻዊው] ፊት ቀርበው ነገሩ ከታየ በኋላ ከኢኦተቤክ [በውግዘት] ተለይተው የሚሲዮን ማኅበር አባል ሆነው ተቀመጡ፡፡›› (መርስዔኀዘን ወልደቂርቆስ፡ገ.146)፡፡ከዚህ ጊዜ ጀምሮ አለቃ ታዬ ከኢኦተቤክ ተገልለው እስከ እለተ-ሞታቸው ነሐሴ 15 ቀን 1916 ዓ.ም በመንግሥት ሠራተኛነት ታሪክ ሲጽፉ የነበረ መሆኑ አይካድም፡፡ነገር ግን ምንም እንኳ ከ19 ዓመታቸው ጀምሮ በፕሮቴስታንት እምነት በድብቅ ገብተው የኖሩ ቢሆንም የኢኦተቤክ ልጅነታቸው የታሪክ መጽሐፉን ከመጻፋቸው ከ13 ዓመታት በፊት (በኅቡዕ ፕሮቴስታንት መሆናቸው ከታወቀ ከ31 ዓመታ በኋላ) በ1903 ዓ.ም በይፋ ተቋርጡዋል፡፡ይሄው የብላታ መርስዔኀዘን መጽሐፍ በገጽ-147 ኅዳግ እንደሚተርከው አለቃ ታዬ በተወለዱ በ63 ዓመታቸው (ፕሮቴስታንት በሆኑ በ44ኛው ዓመት) በሞት ሲለዩም በኢኦተቤክ ለመቀበር ተናዝዘው ስለነበር አስከሬናቸውን ለማሳረፍ የቅ/ሥላሴ ካቴድራል ካሕናት በንግሥት ዘውዲቱ ሳይቀር ቢለመኑ ‹‹ይሕ ጸረ-ማርያም በቤተክርስቲያናችን አይቀበርብንም›› ሲሉ ተቃውሞ በማንሳታቸው የአለቃ ታዬ አስከሬን ወደ ጉለሌ ተወስዶ በፕሮቴስታንት መካነ-መቃብር ተቀብሯል፡፡እንግዲህ የኢኦተቤክ በቁም አውግዛ የለየችው፣በሞቱም ‹ሃይማኖት የለያየንን መቃብር አንድ አያደርገንም› ብላ ባመነበት አዲስ እምነት ካረፉ አዳዲስ አማንያን ወገኖቹ መቃብር ጎን እንዲያርፍ የጥምቀት ልጅነቱን ገፍፋ ቅጽሯን የዘጋችበት እና አንድም ጽሑፉን ያልተቀበለችው ዐለቃ ታዬ ነው ‹‹የኢኦተቤክ ደብተራ›› እየተባለ በየቦታው ከላይ በጠቀስኳቸው የኦሮሞ ጸሐፍት ስሟ የሚብጠለጠለው፡፡በዚህ አያያዝ ዛሬ ከኦሮሞ ብሔርተኞች ጋር ጽንፍ ረግጠው የሚወራከቡት ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም እና ፕ/ር ጌታቸው ኃይሌም ወደፊት ‹‹የኢኦተቤክ ደባትር›› ላለመባለቸው ዋስትና የለም!!

4-- ክስ-አራት፡- ኦርቶዶክስ ኦሮሚፋን ትጸየፋለች!

እውቁ የኦሮሞ ታሪክ ጸሐፊ መሐመድ ሀሰን በJOS (Journal of Oromo Studies.volume-7) ገጽ 118 ላይ በወጣ ጽሑፉ ጆቴ የተባለ ደራሲ ጠቅሶ <<The Amhara clergy failed to capture the hearts and minds of the Oromo by their total failure to use the Oromo language for their missionary work.Infact upto 1993, the Oromo language was considered too profane to be used by the Church>> ይለናል፡፡ሸጋ፡፡በምስማማበት ተስማምቼ ልጀምር፡፡የኢኦተቤክ ኦሮሚፋን ለስብከተ-ወንጌል ድሮም ሆነ አሁን (አሁን ላይ እጅግ መሻሻል ቢኖርም) በቅጡ ተጠቅማበታለች ብዬ አልዋሽም፡፡ነገር ግን ይሕ የሆነው መሐመድ እና ጆቴ እንደሚሉት ለኦሮሚፋ በተለየ መልክ ጽዩፍ (too profane) ሆና ነው ብየ አላምንም፡፡ላስረዳ፡-
(4.1) ዐማርኛ ራሱ በሊቃውንቱ ለቅዱሳት መጻሕፍት ትርጉም አገልግሎት መስጠት የጀመረው በጎንደር ዘመነ-መንግሥት ወቅት ያውም ካቶሊካውያንና ፕሮቴስታንቶች የሰሜኑን ሕዝብ በአካባቢው ቋንቋው እያስተማሩ ምዕመኑን ማስኮብለላቸው ባሳደረው ጫና ነው፡፡ዐማርኛ በተደራጀ መልኩ ለመጻሕፍት ትርጓሜ የዋለበትን (የወቅቱ የትርጓሜ መንገድ በራሱ የግእዝ ተጽእኖ እጅግ ቢበረታበትም) ትክክለኛውን ጊዜ ስናስቀምጠው በአጼ አድያም ሰገድ ኢያሱ ዘመን (ከ1674-1694) ስለመሆኑ በሚሊኒየሙ የታተመው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ከልደተ ክርስቶስ እስከ ፳፻ (2000ዓ.ም) መጽሐፍ በገጽ 187 አብራርቶ ያቀርብልናል፡፡ዐማርኛ በሥርዓተ-ቅዳሴ መካከል ለመነገር የበቃው ደግሞ ከ1913 ዓ.ም ወዲህ አባ ኪዳነማርያም በተባሉ የዋድላ (ወሎ) መነኩሴ አማካይነት ስለመሆኑ መርስዔኀዘን በገጽ 143 ተርከውልናል፡፡
(4.2) ከትርጉም ጋር በተያያዘ ጥቂት ግነት ያለበት ቢመስልም ሐቁን ያላጣውና ተስፋዬ ቶሎሳ በተባሉ አጥኚ የአፋን ኦሮሞን ጽሑፋዊ የታሪክ ሂደት የሚዳስስ የጥናት ወረቀት ገጽ-77 የተጠቀሰው የጀምስ ብሩስ አስተያየት ይታይ፡፡ብሩስ <<...there is an old law in this country (Ethiopia), handed down by tradition only, that whoever should attempt to translate the holy scripture into Amharic, or any other language his throat should be cut....>> በማለት ልማዳዊ ሕጉ ከግእዝ ውጪ ባሉ ቋንቋዎች ሁሉ ዐማርኛን ጨምሮ ይሰራ እንደነበር ይተርካል፡፡ልማዳዊ ሕጉ በአብዛኛው የሰሜን ኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊ አሁን ድረስ ሕያው ነው፡፡ጸሎትና ቅዳሴው ለግእዝ ያደላ ነው፡፡በትግራይ፣በጎጃም፣በጎንደር፣በወሎ እና በሸዋ ግእዝ ጠቅሶ የማይሰብክ ሰባኪ እንኳንስ በካሕናቱ በምዕመናኑም የሚሰጠው ክብር እምብዛም ነው፡፡ሕዝቡ ለግእዝ ያደላል፡፡እዚያ በአማርኛ/ትግርኛ ብቻ ብትንደቀደቅ ‹‹ስብከቱ ጥሩ ነበር፤ግና ‹ቦለቲካ› በዛው›› ይልሀል፡፡
(4.3) ተስፋዬ ቶሎሳ በጥናቱ የቀደሙ ነገሥታትን የኦሮሚፋ ቋንቋን ጨቋኝነት በስፋት ቢገልጽም እ.ኤ.አ በ1877 ዓ.ም አለቃ ዘነብ (እኒህ ሰው የአጼ ቴዎድሮስን ዜና-መዋዕል የጻፉ የሸዋ ተወላጅ ሲሆኑ የጉራጌ ሕዝብ ከምኒልክ ጋር በተዋጋ ጊዜ ተገድለዋል--አለቃ ዘነብ) ለአጼ ምኒልክ መጽሐፈ-ኢያሱን፣መጽሐፈ-መሳፍንትን፣መጽሐፈ-ሩትን እና መጽሐፈ-ሳሙኤልን ወደ ኦሮሚፋ ተርጉመውላቸው በአውሮፓ ሊያሳትሙ ሲሉ ለማሳተም ቃል የገባላቸው ሚሲዮናዊው Krapf ከዚህ ዓለም በሞት በመለየቱ ኅትመቱ እንዳልተከናወነ የፓንክረስትን የ1976 እትም መጽሐፍ ጠቅሶ አስቀምጦታል፡፡‹‹ደማቆቹ›› የተሰኘ በመፍቀርያነ-ፕሮቴስታንት ጸሐፍት የተዘጋጀ መጽሐፍም ስለ አናሲሞስ ነሲብ ሲተርክ ይህንኑ የአለቃ ዘነብን ውጥን አንስቶታል (ደማቆቹ፡ገ.29)፡፡አናሲሞስን ከአጼ ምኒልክ ያገናኙት አቡነ ማቴዎስ እንደሆኑ፣አናሲሞስም ለአጼ ምኒልክ የኦሮምኛውን መጽሐፍ ቅዱስ እንዳበረከተላቸው፣ንጉሡም አናሲሞስን አጃቢ ባልደረባ ሰጥተው ወደ ወለጋ እንደላኩት ይኸው መጽሐፍ (ደማቆቹ) ይገልጻል፡፡የኢኦተቤክ ያላትን አስተምህሮ ሳይቃረን እንዲያስተምር ጳጳሱ አቡነ ማቴዎስ (ግብጻዊ) ራሳቸው ለአናሲሞስ ነግረውት ነበር፡፡ጳጳሱ ለወለጋው የወቅቱ አስተዳዳሪ በጻፉት ደብዳቤም ይሕንኑ አሳውቀዋል፡፡እንጥቀሰው ‹‹...እጅግ ለተከበርከውና ለተወደድከው ደጃዝማች ገብረእግዚአብሔር እንዴት አለህ?እኔ የማርቆስ አምላክ ይመስገን ደህና ነኝ፡፡ይሕ ከወደብ (ኤርትራ) የመጣው ኦኔሲሞስ ወደ እኛ መጥቶ እንዲያስተምር ጠይቆናል፡፡ከቤተክርስቲያናችን ትምህርትና እምነት የተለየ ጕዳይ አስተምሮ እንደሆነ እንድናውቀው አድርግ፡፡ነገር ግን ከኛ ትምህርትና እምነት ያላፈነገጠ ትምህርት የሚሰጥ ከሆነ ይቀጥል፤ማንም አንዳች አይበለው›› (ደማቆቹ፡ገ.33)፡፡እርግጥ ነው በኋላ ዘመኑ አናሲሞስ ችግር አጋጥሞታል፡፡ነገር ግን ችግሩ የገጠመው ኦሮሚፋን ተጠቅሞ በመስበኩ ሳይሆን የተሰጠውን መመሪያ ጥሶ ከኢኦተቤክ ዶግማና ቀኖና የሚጋጭ ፕሮቴስታንታዊ ትምህርት በማስተማሩ ነው፡፡ ይሕ ደግሞ በእሱ ላይ ብቻ ሳይሆን ቀደም ሲል ፕሮቴስታንታዊ ትምህርት ባስተማሩት ጎንደሬው አለቃ ታዬ፣ካቶሊካዊ ትምህርት ባስተማሩት ጎጃሜው አባ ገብረሚካኤል (በአጼ ቴዎድሮስ ታስረው ሳለ ስላረፉ ቫቲካን እንደ ብፁዕ ሰማዕት ነው የምታያቸው)፣በልዩ ልዩ የጸጋ-ተዋሕዶ-ቅባት ክርክሮች ወቅት በዐማራና በትግራይ ሊቃውንትም ዘንድ የደረሰ ነው--መሳደዱ፡፡ስለሆነም ዛሬ ላይ ቆሜ አንድ ሰው በእምነቱ የተነሳ መሳደድ እንደሌለበት በሙሉ ልቤ ባምንም ገና ወለጋ ለምኒልክ ሳይገብር በአካባቢው በሰፈነው የባርነት ንግድ በ1854 ዓ.ም (ምኒልክ በዚህ ጊዜ በመቅደላ እስር ቤት የአጼ ቴዎድሮስ እስረኛ ነበሩ) ተሽጦ ኋላ በሚሲዮናውያን አርነት ከወጣ በኋላ ለኦሮሚፋ ቋንቋ ታላቅ ውለታን የሰራው አናሲሞስ የተሳደደው በኦሮሞነቱ እና በኦሮሚፋው ነው ብዬ አላምንም፡፡የወቅቱ የኢኦተቤክ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ ቋንቋ ሳይለዩ አናሲሞስ ስለኦርቶደክስ እንዲሰብክ የበኩላቸውን ጥረዋል፡፡ስብከቱን ለፕሮቴስታንታዊ ተልእኮ ሲጠቀምበት ግን ወቅቱ በፈቀደው ሕግና ሥልጣን ስብከቱን ለማገድ ተንቀሳቅሰዋል፡፡ይህ እንቅስቃሴያቸው ከሃይማኖት ነጻነት ጋር እንጂ ከቋንቋ ነጻነት ጋር አይገናኝም ብዬ አምናለሁ፡፡ሌላ ዋቢ እንጥራ!
(4.4) ከሆሮ-ጉድሩ ተማርኮ ኋላ በምድረ-ጎጃም ታላቅ ካሕን፣ጸሐፊ እና የተመሰገነ ሠዐሊ የነበረው አለቃ ተክለኢየሱስ (ነገሮ) ዋቅጅራ በ1891 ዓ.ም በኦሮሞ-ቤት (ሆሮ-ጉድሩ) ስለተካሄው የጎጃሙ ንጉሥ ተክለሃይማኖት ጉዞ (ጦርነቱ በ1871 ዓ.ም ተጠናቋልና ይሄኛው ጉዞ ለጦርነት አይደለም፤ለቤ/ክ ግንባታ እንጂ) እንዲህ ይተርካል ‹‹...የዚህ ጊዜ ንጉሥ ተክለሃይማኖት...ኦሮሞ ቤት ዲለሎ ከሚባል ቦታ ሲደርስ ቤተክርስቲያን ሲሰራ ባጀ፡፡...ኦሮሞውን ሁሉ አሳምኖ ብዙ ታቦት ተከለ፡፡ተሠሪ ሠራበት፡፡...[በ1871 ዓ.ም ከሆሮ-ጉድሩ ማርኮ] ያሳደጋቸውን ኦሮሞዎች ሁሉ ከዘመድ እያስተዋወቀ ለነሻቃ ይርባ [ሂርጳ?]፣ለነሻቃ ጉደታ፣ለነበጅሮንድ ናደው ከየአባታቸው ርስት ጉልት አድርጎ ሰጥቶ ቤት አሠራቸው፡፡...ከዲለሎ ሲመለስ አለቃ ተክለኢየሱስን ጠርቶ ዘመዶችህ እነሻቃ ይርባ [ሻቃ ሂርጳ የንጉሥ ተክለሃይማኖት ሰይፍ ጃግሬ ነበር] አገራቸው ገብተው ከዘመድ ተገናኝተው ለጉልት ሲበቁ ምነው አብረኸኝ ሳትሄድ አለው፡፡...ከርሞ የቀዎ ጊዮርጊስ ጌታ አደርግሀለሁ፡፡...እዚያው [ሥዕል] እየሣልክ ታሳምንልኛለህ፡፡ነገርግን የኦሮምኛ ቋንቋ እንዳይጠፋህ ይኹን አለው፡፡›› (አለቃ ተክለኢየሱስ፡ገ.198)፡፡ይቺ የተክሌ ሐተታና ‹‹እዚያው [ሥዕል] እየሣልክ ታሳምንልኛለህ፤ነገር ግን የኦሮምኛ ቋንቋ እንዳይጠፋህ ይኹን አለው፡፡›› የምትለዋ የንጉሥ ተክለሃይማኖት አገላለጽ በወቅቱ ዛሬ እንደሚባለው በኢኦተቤክ አካባቢ ኦሮሚፋ ‹‹ጽዩፍ›› የሚባል ቋንቋ እንዳልነበረ ፍንጭ ትሰጠናለች፡፡የንጉሥ ተክለሃይማኖት ዐላማም ጎጃም ማርኮ ያቆያቸውን ኦሮሞዎች ተጠቅሞ ሆሮ-ጉድሩን እና አካባቢውን በኦሮሚፋ እያስሰበከ በኦርቶዶክሳዊነት አሳምኖ ለማጥመቅ መሆኑን ይጠቁመናል፡፡
(4.5) የኢኦተቤክ በሰሜን በኩል ባሉ ብሔረሰቦች ውስጥ ሴሜቲክ በሚባሉት ዐማራና ትግራውያን (ሐማሴኖችን ጨምሮ) ብቻ ሳይሆን ሰሜናዊ ኩሽቲክ በሚባሉት አገዎች ዘመናትን የቀደመ ተጽእኖ አላት፡፡‹‹ላል-ይበላ›› የሚለው ስም አገውኛ ስለመሆኑና አገዎች ቤተመንገሥቱን 300 ዓመታት ተቆጣጥረውት እንደነበር ተደጋግሞ ተነግሯል፡፡ወደ ደቡብ ስንሄድ የከፋን ሕዝቦች ታሪክ የጻፈው በቀለ ወ/ማሪያም አዴሎ እንደሚነግረን የኢኦተቤክ በአካባቢው ከ600 እስከ 700 ዓመታት የቆየና የተመዘገበ ታሪክ አላት፡፡ለአብነትም በቀለ ወ/ማሪያም በ1532 ዓ.ም የተተከለው ባሃ ጊዮርጊስን ይጠቅስልናል፡፡(በቀለ ወ/ማሪያም፡ገ.122 እና 123)፡፡በወላይታም የደብረ-መንክራት ተክለሃይማኖት ቤ/ክ እድሜ ከ800 መቶ ዓመታት በላይ ይቆጠራል፡፡በ14ኛው ክ/ዘ በምድረ-ጉራጌ እነ አቡነ ዜናማርቆስ ያቋቋሙት የምሑር-ኢየሱስ ገዳም ዛሬም ከነግርማው አለ፡፡በጋሞዎች ምድር ያለችው ብርብር ማርያም ከንጉሥ ገብረመስቀልና ከንጉሥ ዘርዓያዕቆብ ጋር የተገናኘ የሺህ ዓመት ታሪክ ትቆጥራለች፡፡በሸዋ የኦሮሞ ምድር ያሉት የወንጪ(አምቦ) ቂርቆስ፣የዝቋላ/ጩቃላ አቦ፣የዝዋይ/ባቱ ደሴት ገዳማት፣የደ/ሊባኖስና የዐዳዲ ማርያም ገዳማት፣...የሚቆጥሩት እድሜ በትንሹ ከ500 ዓመታት በላይ ነው፡፡ሃይማኖቱ ከ6 ሀገራት ጋር ዶግማ ቀኖና ስለሚጋራ ከነዚህ ሀገራት የመጡ ቅዱሳን በኃላፊነት ጭምር እየተቀመጡ እስከቅርብ ጊዜ አገልግለዋል፡፡የዐረብኛ፣የሱርስት፣የግሪክ እና የእብራይስጥ ቋንቋ ሳይቀር ሊቃውንቱ እያጠኑ ቅዱሳት መጻሕፍትን ተርጉመዋል፡፡ላመነና ለተጠመቀ ሁሉ መድረኩ ክፍት ነበር፡፡እነ መሐመድ ሐሰን ይሄን ሳያጣሩ፣ወይም እያወቁ ሳያካትቱና ጥቂት እንኳ ለሚዛናዊነት ሳይጨነቁ ‹‹The Amhara clergy›› እያሉ ሃይማኖቱን የአንድ ብሔር በማስመሰል መጻፋቸው እጅግ ቅር ያሰኛል፡፡ሃይማኖቱ ለዐማርኛ ቋንቋ የሚባለውን ያህል ታሪካዊ የሥነ-ጽሑፍ ቦታ እንዳልነበረው እስኪ ቀ.ኃ.ሥ ይንገሩን፡፡
(4.6) ቀ.ኃ.ሥ በ‹‹ሕይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ›› የመጀመሪያ ክፍል መጽሐፋቸው ገጽ 136 በዘመናቸው ዐማርኛ የነበረበትን ዝቅተኛ የቤ/ክ አገልግሎት ሲገልጹ ‹‹...ቅዳሴው ሕዝቡ ሁሉ በማያውቀው በግእዝ ቋንቋ ስለነበር ብዙዎች የዜማውን ድምጽ ከመስማት በቀር ምስጢሩን የሚያስረዳ ቃል ሳይሰሙ በየቤታቸው ይመለሱ ነበር፡፡...›› ካሉ በኋላ በእሳቸው ዘመን ስለነበረው ጅማሮ ሲገልጹ ‹‹...አሁን ግን ጸሎተ-ቅዳሴው በአማርኛ ቋንቋ እንዲተረጎምና እንዲታተም አድርገን በየቤተክርስቲያኑ ስለታደለ ሕዝቡ መላውን እንኳ ባይሆን ዋና ዋናውን ቃል በቋንቋ ሲነበብ መስማት ጀምሯል፡፡ወንጌልና የሐዋርያት መልእክትም በአማርኛ ቋንቋ እንዲነበብላቸው ተደረገ፡፡›› ይሉናል፡፡በነገራችን ላይ መጽሐፈ-ቅዳሴ ከግእዝ ወደ አማርኛ በነጠላው የተተረጎመውና የታተመው በ1918 ዓ.ም ነበር፡፡ተርጓሚው መርስዔኀዘን ወልደቂርቆስ ነበሩ፡፡አማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ በነጠላ ትርጓሜ በ1832 ዓ.ም አባ አብርሃም (አባ ሮሜ) የታተመ ቢሆንም የተሟላና ሊቃውንተ-ቤተክርስቲያን የተሳተፉበት አማርኛ መጽሐፍቅዱስ የታተመው ግን በቅርቡ በ1953 ዓ.ም ነበር፡፡በዚህ ወቅት (ኧረ ቀደም ብሎ ነው!) መጽሐፍ ቅዱስን አናሲሞስ ነሲብ ወደ አፋን ኦሮሞ፤አለቃ ተወልደመድኅን ገብሩ ወደ ትግርኛ ተርጉመውት ነበር (የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ-ቃላት፡ገ.95)፡፡ድጋሚ ላስታውስ!የኢኦተቤክ በቀደመው ዘመን በስብከተ-ወንጌል ረገድ በየብሔረሰቡ ቋንቋ የመስበክ ብቃት ነበራት እያልኩ አይደለም፡፡አቋሜ የኢኦተቤክ የቋንቋ አጠቃቀም ውስንነት ልክ እስልምና ለዐረብኛ፤ካቶሊክ ለላቲን ቋንቋዎች እንደሚሳሱት (ኦሪጅናል ድርሰቶችና ዜማዎች በቋንቋዎቹ ስለተቀናበሩ) እሷም ለግእዝ ስሱ በመሆን እንጂ ኦሮሚፋን በተለየ ዐይን በማየት አይደለም የሚል ነው፡፡
(4.7) ይሕ በግእዝ ብቻ የመገልገል የኢኦተቤክ ልማድ መንበረ-መንግሥቱ በአክሱማውያን (ትግራውያን)፣በዛጉዌዎች (አገዎች) እጅ እና በየጁ ኦሮሞ ወረሴህ/ወራ-ሼክ እጅ በነበረበት ጊዜ (ለምሳሌ፡- ከየጁ ኦሮሞ የሚወለዱት ታላቁ ራስ ዓሊ ደብዳቤ ሲጽፉ ‹‹ጦማር ዘእምኀበ-ርእሰ-መኳንንት ዓሊ›› በማለት በግእዝ ነው አርእስታቸውን የሚጀምሩት)፤ኋላም ዙፋኑ በአጼ ዮሐንስ ተመልሶ ወደ ትግራይ ባመራበት ዘመን በኢኦተቤክ የግእዝ የበላይነት የጸና ነበር፡፡
(4.8) የቀደመው የግራኝና ደርቡሽ ሰቆቃ (አጼ ዮሐንስ በመተማ ተሰውተው ደርቡሽ ጎንደርን በወረራ ሲያጠፋ በሃይማኖቱ እውቀት ጫፍ የደረሱ ከ20 በላይ መምሕራንን አርዶ ነበርና) በወቅቱ ሀንጎቨሩ እንዳለ ሆኖ በተለይ ደግሞ የአጼ ሱስንዮስ ዘመን ካቶሊካዊ ፍልስፍና ኋላ ፊቱን ቀይሮ ጸጋ/ሦስት ልደት/-ቅብዐት-ተዋሕዶ/ካራ/ የሚል የውስጥ ክፍፍል በመፍጠር ሃይማኖቱ በውሳጣዊ ሽኩቻ ከመዳከሙም በላይ ከሊቃውንት ማዕከላቱ ትግራይ-ጎንደር-ጎጃም-ወሎ-ሸዋ ወጥቶ ወደሌሎች ብሔረሰቦች በስፋት በስብከተ-ወንጌል እንዳይደርስ ይሄው ሽኩቻ እስከ ዘመነ-መሳፍንት ፍጻሜ ዘልቆ ጎታች የነበረ መሆኑን ማስተዋል አይከፋም፡፡ እንጂ የኦሮሚፋ ስብከት ያልተስፋፋው መሐመድ ሐሰን እና ኦቦ ጆቴ እንደሚሉት ለኦሮሚፋ too profane በመሆን አይመስልም፡፡ጥያቄ ላንሳ፡፡ዶክቶር መሐመድ ወደ ኢኦተቤክ ከማለፉ በፊት እስልምና ለቁቤ እና አፋን ኦሮሞ ያበረከተውን ጸጋ ሊተነትንልን ይችል ይሆን?የአፋን ኦሮሞ ቁራን ነበረ?ቁራን በኦሮሚፋ ይቀራ ነበር?አዛንስ?ለንጽጽር እንዲመች ጥያቄዎቹ ቢብራሩ ሸጋ ነው!ስላደገበት እስልምና-እና-ኦሮሞነት ተዛምዶ ለመተንተን የተሻለ ግንዛቤ አለው ብዬ ነው!የእሱ የተጸውኦ(መጠሪያ) ስም ‹‹መሐመድ ሐሰን›› በኦሮሚፋ አይደል!!ይተርጉምልና!!
(4.9) እግረ-መንገድ እስኪ ከ100 ዓመት በፊት በኦሮሚፋ እና በዐማርኛ ቅልቅል (ፍርንዱስ) ሆኖ የግጥም ምጣኔው ‹ሥላሴ› የምንለው ከ3ኛው መስመር ጀምሮ ቤት እየመታ የሚሄድ ባለ 8 መስመርና ባለ 6 ቤት ቅኔ እንስማ፡፡የቅኔው ባለቤት አለቃ ዘወልዴ ይባላሉ፡፡ምናልባት በፕ/ር ታምራት ‹‹ፊተኛይቱና ኃለኛይቱ ኢትዮጵያ›› የሚል መጽሐፍ በተለየ አጻጻፍ ጽፈዋል የሚባሉትና መጽሐፋቸውን ያላገኘንላቸው ዘወልዴ ይሁኑ አይሁኑ አላወቅኩም፡፡ቅኔው የተደረገው በምኒልክ ጊዜ የነበረውን አስተዳደር በመተቸት ነው፡፡የተወሰደው በ1980 ዓ.ም በደርግ ጊዜ በአ/አ/ዩ አማካይነት ከታተመው ‹የግእዝ ቅኔያት የስነ-ጥበብ ቅርስ ክፍል-2› ከተሰኘ መጽሐፍ ገጽ-389 ነው፡፡የሊቁ ቅኔ እንዲህ ይነበባል..
አርካ-ኬቲ፡ሁንዱማ-ጨብሴ፤
ሌንጫ-ጎፍታኮ፡ኢጆሌ-ሌንጫ፤
አሁንም-የእውነት፡ግሩም፡አንበሳ፡የአንበሳ-ኮርማ፡የቢያ፣
በክንድህ-ሰበርኸው፡የሁሉን፡ሶማያ፣
ዱጉማ፡ጎፍታኮ፡ዱጉማ፡አሲ-መና-ኬቲ ገበያ፣
ሀሬ-ጉደቴ፡ፈርዳን-ፉለያ፣
ማሎ፡ማሎ፡ጎፍታ-ኪያ፣
መና-ፈርዳ፡ፉደቴ፡አህያ፡፡
ትርጉም፡- ‹‹አንበሳ የአንበሳ ልጅ፤ጌታየ ክንድህ ሁሉን ሰበረች፤አሁንም የእውነት አስፈሪ አንበሳ የአገር አንበሳ ኮርማ (አንተ)፤የሁሉን በትር በክንድህ ሰበርኸው፤እውነት ጌታዬ ከዚህ ገበያ ቤትህ እንደ አይጠ መጎጥ ፈረሶች ሲርቁ አህያ ከፍ ከፍ ተደረገች፤ምነው ምነው የእኔ ጌታ የፈረስን ቤት አህያ ወሰደች›› የሚል ነው፡፡
ምስጢሩ፡- ባለቅኔው የምኒልክን በባላባቶች ላይ የተገኘ አሸናፊነት አወድሰው ነገር ግን ‹‹በባህሉ ፈረስ እያለ አህያ ቀሚስ እንደማትለብስ እየታወቀ እስዎ ታላላቆችንና ምሁራኑን ትተው ለታናናሾች እና ላልተማሩት ቦታ (ስልጣን) እየሰጡ ነው›› በማለት የምኒልክን አስተዳደር በኦሮሚፋ የሚተች ነው፡፡በውዳሴ ጀምሮ በትችት መቋጨት ከቅኔ ባሕሪያት አንዱ ነዋ!

ይቀጥላል///////

Thursday, July 9, 2015

የኦሮሞ ኢስላሚስቶች ለአረፋ በዓል ሄደው በሳዑዲ ያደረጉትን ይመልከቱ!

  
    በኦሮሚያ ክልል የተነሱ የአብዱል ወሀብ ጥራዝ ነጠቅ  ተከታይ ወሀቢስቶች በጅማ፤ በኢሉባቦር፤ በአርሲና በባሌ የተለያዩ ቦታዎች በኦፊሴል የተነገረና ያልተነገረ የሽብር እንቅስቃሴ ሲያደርጉ ቆይተዋል። በአማራ ክልል ደግሞ የወሎ አክራሪ ወሀቢስቶች ቤተ ክርስቲያን ከማቃጠል አንስቶ ሰው እስከመግደል መድረሳቸውን በማስረጃ የተረጋገጠ እውነት ነው። በስልጤና ወራቤ የከተሙ አሸባሪ ፋናቲኮች ተመሳሳይ ድርጊት ላይ ተሰማርተው መገኘታቸውም ፀሐይ የሞቀው፤ ሀገር ያወቀው ጉዳይ ነው። እነዚህ ሱሪያቸውን የሚያሳጥሩ፤ ካልሲያቸውን የሚያሳዩ፤ የአፍንጫቸውን ስር ጸጉር ሙልጭ አድርገው በመላጨት ጢማቸውን የሚያሳድጉ፤ ግንባራቸው ላይ የተነቀሱ እስኪመስል ድረስ ከመሬት ሲጋጩ የጠቆረ ሰውነት ከማንነት ጋር የተሸከሙ አክራሪዎች የሌላውን መብት እስካልነኩ ድረስ ተቃውሞ የማይቀርብበት ቢሆንም የድርጊታቸው ዋነኛ ምስክር ግን ለማሸበር ልዩ ምልክታቸው ሆኖ መገኘቱ ነው። ወሀቢስቶች ከሱኒና ከሱና ውጪ ያለው ሁሉ ካፊርና ከሀዲ ነው።          ለዚህም ዓላማ ግብ መንታት መታገል፤ መዋጋትና መግደል ብሎም መሞት ጂሀድ ነው። በዚህ ዓላማ ላይ መሞት በጀና/ ገነት/ ልዩ ዓለም የሚያስገኝ ሲሆን 72 ደናግላን ሴቶች ድንግላቸውን በጂሀድ ለሞተው አሸባሪ ለማስረከብ በጥቋቁር ቀሚስ ተሸፋፍነው እንደሚጠብቋቸው ያምናሉ።
ከዚህ በታች የሚታየው ቪዲዮ በሳዑዲ የአረፋ በዓል ለማክበር የሄዱ አክራሪዎች የወቅቱ የኢትዮጵያ ባንዲራ የሆነውን ዓርማ ከተሰቀለበት አውርደው የኦነግን ባንዲራ ሲሰቅሉ ያሳያል። «ሱባንአላህ» የሚለው የኦሮሞ ኢስላሚስት አክራሪ የአማራ ባንዲራ ወርዶ የኦሮሞ መንግሥት በቅርቡ በኦሮሚያ ይቋቋማል ይላል። በዚህ ዓይነት ኦነግ አሸባሪ አይደለምን?
እንግዲህ እነዚህ የመሳሰሉ አሸባሪዎች ናቸው፤ ኢትዮጵያ ተመልሰው ሕዝብን ከሕዝብ፤ ሃይማኖትን ከሃይማኖት ሲያጋጩ የሚስተዋለው።
ደግመን ደጋግመን የምንለው እውነታ ቢኖር ኢትዮጵያ ውስጥ ምቹ ሁኔታ ጠፍቶ እንጂ ለቁጥር የሚያታክቱ አሸባሪዎች አሉ። «አስቀድሞ ነበር፤ መጥኖ መደቆስ፤
አሁን ምን ያደርጋል፤ድስት ጥዶ ማልቀስ»
እንዳይሆን ሰላምን፤ ፍቅርን፤አንድነት፤ ኅብረትንና በጋራ አብሮ መኖርን በሚፈልጉ የእስልምና እምነት ተከታዮች በኩል አካባቢንና ውስጥን የማጥራት ሥራ ከታችኛው እርከን አንስቶ እንዲደረግ ከዚህ በፊት ስንለው እንደቆየነው ሁሉ አሁንም ደግመን ለማስታወስ እንወዳለን።


Monday, May 25, 2015

የጴንጤዎቹ እንደዶክሌ ቀልደኛው ዳዊት ሞላልኝ የሰው ሕጋዊ ሚስት ቀማ!!

ጌታ ለእኔ የማይፈርደው እስከ መቼ ነው? የእግዚያብሔር ቤተሰቦች የእውነት ቃል በእናንተ ካለ እስቲ ፍረዱ !
ፓስተር ዳዊት ሞላልኝ የተባለ ግለሰብ ህጋዊ የትዳር አጋሬን ባለቤቴን በቁሜ ነጠቀኝ::
አቶ ግርማ ዱሜሶ








ይህንን ጽሁፍ እራሳቸው አዘጋጅተው ከእነ ፎቶግራፋቸው የላኩት ግለሰብ ነዋሪነታቸው በሰሜን አሜርካ በአትላንታ ጆርጂያ ግዛት የሚኖሩት አቶ ግርማ ዱሜሶ የተባሉ ግለሰብ ህጋዊ ባለቤቴን ወ/ሮ ትግስት አበበ ደምሴን ፓስተር ዳዊት ሞላልኝ የተባለ ግለሰብ አስነውሮብኝ ትዳሬን አፍርሶታል:: እኔም እነዚህ ሁለት ግለሰቦች ባደረሱብኝ ከባድ የህይወት ወንጀል በተደጋጋሚ ሁለቱም ግለሰቦች በቤተክርስትያን በኩል እንዲጠየቁልኝ እና ክርስቲያናዊ ይቅር እንድንባባል በተደጋጋሚ አሜርካ ውስጥ ለሚገኙ የኢትዮጵያናውያን ቤተክርስትያኖችን ጠይቄ ከቤተክርስትያኖቹ ምላሽ አጥቼያለሁ ስለሆነም ውድ የእግዚያብሔር ቤተሰቦች የሆናችሁ እውነተኛ ክርስቲያኖች ይህንን እውነተኛ ታሪኬን አንብባችሁ ፍርዳችሁን እንድትሰጡኝ በጌታ ኢየሱስ ስም እማጸናችኋለሁ

ቀን 03/16/2015

ለቄስ ዶ/ር ቶሎሳ ጉዲና

አትላንታ ጆርጂያ (USA )

ጉዳዩ ፡ በኔና በትዳሬ ላይ የደረሰውን በደል ፤ ነውርና ጥቃት ይመለከታል!

በእግዚአብሔር የተወደድክና በጣም የማከብርህ መንፈሳዊ አባቴ ( ፓስተሬ ) ነህና “አንተ “ ብልህ እንደ ድፍረት እንደማትቆጥርብኝ ተስፋ አደርጋለሁ ። ተወልጄ ባደኩበት ማህበረሰብና እንዲሁም በእግዚአብሄር ቃል ውስጥም ቢሆን ሰው ፈጣሪን የሚያህል አምላኩና የሥጋ ወላጅ አባቱን “አንተ “ እንጂ “እርስዎ አምላኬ ሆይ “ ብሎ ስጣራ አልሰማሁም ።

በመሆኑም በሚገባኝ መንገድ ከልቤ በሆነ አክብሮት የጌታ ሰላም ፤ ምህረት ፤ጥበቃና ቸርነት እየተመኘሁልህ ፤ እንዲሁም ረጂም ዕድሜና በረከት ይብዛልህ ለማለት እወዳለሁ።

ፓ/ር ፡

ምንም እንኳን አንተን ማድከምና ማሰልቸት ቢሆንም ከዚህ ቀደም በአካልና በሰልክ ደጋግሜ ያጫወትኩህን (በሰፊው የተነጋገርንብትን ) እና አሁንም ድረስ የተቸገርኩበትን ብርቱ ጉዳዬን ከዚህ እንደምከተለው እንደገና ልገልጽልህ ወደድኩ ። ያም ጉዳይ ቀደም ሲል አንተም የሚታውቀውና በቅርቡም በቢሮህ ተገኝቼ በዝርዝር ገልጬልህ በተነጋገርነው መሰረት ሚስቴ የነበረችው ወ/ሮ ትግስት አበበ ደምሴና ፓ/ር ዳዊት ሞላልኝ አበጋዝ የሚባሉ ግለሰቦች ያደረሱብኝን በደልና ጥቃት የሚመለከት ነው ፡፤

እነዚህ ግለሰቦች እንደ ሌሎቹ ቅዱሳን አማኞች መልካምና ጥሩ ስነ-ምግባር ያላቸው እውነተኛ አገልጋዮች መስለውኝ አመንኳቸውና በቅንነትና በየዋህነት በልበ-ንጽህና ቀረብኳቸው እንጂ ከኋላዬ ዞረው ፈጣሪን በመዳፈር ለብቻቸው የተደበቀ እና ስውር የሆነ የግል ሚስጢርና ግንኙነት ኖሮአቸው ነውርን በትዳሬ ላይ ሊሰሩ ይችላሉ ብዬ ለማሰብ አንዳች ስጋትና ግምት አልነበረኝም ፤ ትዳሬን አፍርሰው ህይዎቴን አደጋ ላይ ይጥሉኛል ፤ ለከፋ ብስጭትና ኪሳራ ይዳርጉኛል ፤ ያዋርዱኛል ብዬ ጨርሶ አላሰብኩም ነበር ።

ይሁን እንጂ የቤተክርስቲያን አገልጋዮች በመሆናቸው እምነት ጥዬባቸው ሳለ በገርነቴና በቀናነቴ በነዚህ በእግዚአብሔር አገልጋይ ተብዬዎች በደል ደረሰብኝ ፤ ተጎዳሁ ፤ ተጠቃሁ ።በዚህ በተፈጸመብኝ በደል የተነሳ እጅግ በጣም አዝኛለሁ ። በዋናነት የበደለኝም ብልጣ-ብልጡ አፈ-ጮሌ ፤ አስመሳይ መንፈሳዊ ሰው መሳይ ዳዊት ሞላልኝ የተባለ የ “FBI “ ቤተክርስቲያን ፓ/ርና መሪ ግለሰብ ነው ።

ይህ ያለንበት ዘመን በተለያየ ስፍራ በሃይማኖታዊና በመንፈሳዊነት ስም የምመላለሱ መንፈሰዊ ዱሪዬዎች እጅግ የበዙበት ወቅት በመሆኑ በእግዚአብሄርና በአገልግሎት ስም እያመኻኙ ባለቤቱ የከደነውን አለፈቃድ የሚከፍቱ ፤ ያስቀመጠውን አንስተው የሚወስዱ ፤ የሰውን ኑሮ የሚያናጉ ንጹሕ ፍቅር ባላቸው ጥንዶች መካከል እየገቡ በሰላምና ደስታ ፋንታ ጭቅጭቅንና ሃዘንን የሚያደርሱ የፍቅርና የቅድስና ጠላት የሆኑ ጉዶች የፈሉበት ጊዜ ነው ቢባል ያጋነንኩ አይመስለኝም ።

ፓ/ር ዳዊት ከዚህ ቀደም ማንንም ገጥሞት በማያውቅ ሁኔታ በሃይማኖት ተጀቡኖ ፤ በአገልጋይነት ሰበብ ተሸፍኖ፤ በእግዚአብሄር ስም እየነገደ ፤ በንቀት ድፍረት ተሞልቶ የሥጋ ፊላጎቱን ማርኪያና መደሰቻ ሲል ትዳሬን አፈራርሶታል ።ይህንንም ያደረጉት በተጋባን ዕለት ካረፍንበት ሆቴል ሙሽሪት( ወ/ሮ ትግስት) ቬሎ ልብሷን ቀይራ እኔን በሆቴል ውስጥ ጎልታኝ ሁለቱ ግን የግል ሥጋዊ ፊላጎታቸውን ለመፈጸም አንዴ ብቻ ሳይሆን ሁለቴ የድፍረት ሙከራ ፈጽመውብኝ አክሽፈዋለሁ ፤በመቀጠልም በቤተዘመድ በታላቅ እህቴ ቤት በተዘጋጀልን የመልስና ቅልቅል ጥሪ ላይም በዕለቱ የተጠሩት የሥጋ ዘመዶቼ እንኳ ሳይታደሙ በሚያስደነግጥ ሁኔታ እኔን (ሙሽራውንም) ሆነ ዘመዶቼን በንቀት ተመልክተውን ከምንም ሳይቆጥሩን አሳዝነውን እና አሳፍረው ግብዣውን አቋርጠው ተያይዘው መሄዳቸው ፤ በሌላ ቀን ደግሞ ወደ አረፍንበት ሆቴል ድረስ በራሱ መኪና ልወስዳት ሲመጣ ፈቃደኛ አለመሆኔን ለመግለጽ ቢሞክርም ጉልቤው ዳዊትና ሚስቴ ራሷ “ አንተን ያወቅንህ ገና ቅርብ ጊዜ ነው ፤ እኛ ግን የቆዬ ጓደኝነትና የጋራ አገልግሎት አለን ፤ ስለዚህ ከተስማማህ እረፍና ቁጭ በል ካልተመቸህ የራስህ ጉዳይ “ ብለው ዓይኔ እያየ ያለፈቃዴ ሚስቴን ነጥቆኝ ሄዷል ።

እንዲሁም ሌላ ጊዜ ደግም አብረን በአውሮፕላን እየተጓዝን ሳለን እኔን ባሏን “ አንተ መጽሐፍ አንብብ ፤ ዳዊት ብቻውን ነውና እሱ ወደ ተቀመጠበት ወንበር ሄጄ ላጫውተው “ በማለት በአውሮፕላን ውስጥም እንኳ ለብቸኝነት ዳርጋኛለች ። በአንድ ወቅት ደግሞ አንድ

ከተማ ውስጥ አብሬን በተመሳሳይ ሆቴል ውስጥ ባደርንበት ጊዜ (ዕለት) “ከዳዊት ጋር የአገልግሎት ጉዳይ የሆነ የሚናወራው ነገር አለን “ በማለት lab top computer ይዛ ያረፍኩበትን ሆቴል መኝታ ክፍል በር ዘግታብኝ ከሄደች በኋላ የት እንዳደረች ሳላውቅ በ2ኛው ቀን ምግብ መመገቢያው ውስጥ ከግለሰቡ (ዳዊት ) ጋር ቁርስ ስበሉ ለዚያውም ከሩቅ እስካ አየኋቸው ሰዓት ድረስ የትና ምን ሲሰሩ እንዳደሩ እግዚአብሔርና እነሱ ብቻ ናቸው የሚያውቁት ።

በሌላውም የምሳና የእራት ፤ እንዲሁም የቁርስና ቡና ሰዓታት እሷ ሁሌ ከሰውዬው (ዳዊት ) ጋር በመሆን ለብቻቸው ተጣብቀው ስላሉ (ስለምቀመጡ ) ከሙሽራዋ ሚስቴ ጋር ማዕድ ለመቆረስ እንኳ አልታደልኩም ነበር ።የስልክ አጠቃቀሟም ቢሆን ባለሁለት ቀፎ ስለሆነ ከዳዊት ጋር በስልክ ስታወራ ከኔ ርቃ ወይም መኝታ ቤት ገብታ ዘግታ በመቆለፍ ስለሆነ አብሬያት በቆየሁባቸው ጥቂት ወራት የብቸኝነትን ህይዎት ነበር የተጋፈጥኩት ።

አትላንታ ከተማ ተመልሰን በገዛ ቤታችን በእንግድነት ሰውዬውን ( ዳዊትን ) ባስጠጋነው ወቅትም ቢሆን እኔን ሳሎን ( ምግብ ቤት ውስጥ) ትተውኝ “ ስለ አገልግሎት የምንመካከረው ጉዳይ አለን” ወዘተ .. በማለት በራሴ መኝታ ቤት ወይም እንዲተኛበት በሰጠነው መኝታ ክፍል ውስጥ ቢያንስ ለ2 እና ከዚያ በላይ ሰዓታት ያህል በር በመቆለፍ ያደረጉትን አገልግሎት ፈጣሪ ብቻ ይመልከተው ከማለት ሌላ ለማውራት የማይቻለኝ የሚቀፍና ህሊናን የሚያደማ ነገር ነው ።

ይህ ብቻም ሳይሆን ባጋጣሚ እኔ አስቀድሜ ወደ መኝታ ቤቴ ውስጥ ከገባሁ ደግሞ ሌላ ሰበብ ይፈጥሩና “ ከዳዊት ጋር የሚንሰራው አጣዳፊ ጉዳይ አለኝ “ በማለት ኮምፒዩተሯን ይዛ እስከ እኩለ-ሌልት አንዳንዴም እስኪነጋ በሌላው ክፍል ወይም በሳሎናችን ውስጥ አብረው ያድሩ እንደነበር እነሱ ራሳቸው (ዳዊትና ትግስት ) ባሉበት ያንተ ረዳት ፓስተሮችም በተገኙበት ቢሮህ ውስጥ ለበርካታ ሳዓታት ( 7 ሰዓት ) ሙሉ በግልጽ ስንነጋገር አለመካዳቸው የሚታወስ ነው ።

ይህ ድንበርና ገደብ የለሽ መንፈሳዊ ሽፋንና ሃይማኖታዊ ሰበብ ከባል ስልጣንና ፈቃድ ውጪ የተሰወረ ሚስጢራዊ አገልግሎት ሊደረግ ሲታሰብ ምን ሊሆን እንደሚችል ፍርዱን ለፈጣሪና አመዛዛኝ ህሊና ላለው ሰው ሁሉ ትቻለሁ ።

ሌላው ደግሞ በአጋጣሚ እንኳ እግሯን አንድ ነገር ስያደናቅፋት ፤ ዕቃ ስወድቅባት እና ድንገት የሆነ ድንጋጤ ስሠማት በቁልምጫ “ዴቭ ድረስልኝ “ ስትል መስማት፤ እንዲሁም ከወላጆቿ ፤ከሥጋ ዘመዶቿና አብሮ አደግ ጓደኞቿ እንዲሁም ከኔና እሷ ፎቶግራፎች ይልቅ የዳዊትን ፎቶዎዎች በመኝታዬ ራስጌና ግርጌ ፤በሳሎን ቤትና የማድ ቤት ( ኩሽና ) ማቀዝቀዣ ላይ ዘወትር ማየት አዕምሮን የሚያደማና ህሊናን የሚያቆሽሽ ትዕይንት ነበር ። እስቲ አትታዝቡኝና በሷ ልብና አምሮ ውስጥ ይህ ዳዊት ምኗ ይሆን ? እኔስ ምኗ ነበርኩ ?

በአጋጣሚ ይህንን ደስ የማይል ታሪክና ዜና ለሚሰሙትም ሆነ እሮሮዬን ለሚያነቡት ሁሉ ለማለት የሚፈልገው ነገር ቢኖር 1ኛ እንዲህ ያለው እልህን ጭሮ ለከፋ ወንጀል የሚገፋፋው አደናጋሪና አጠያያቂ ክፉ ፈተና በገዛ ቤቴ ስለገጠመኝ እንኳን መሸከምና መታገስ ቀርቶ ለመስማትም ሆነ ለማውራት የማይቻለው የስቃይ ጦርነት እየተፈራረቀብኝ በእግዚአብሔር ጸጋ እስካሁን ድረስ በህይዎት መኖሬ እኔን እራሴ ስገርመኝና ስደንቀኝ የሚኖር የጌታ ጥበቃና ውለታ ነው ። እግዚአብሔር አምላክ የማይቻለውን አስችሎ ከክፉ ሁሉ ጠብቆ ነፍሴን ስላኖራት ክብር ምስጋና ይህንለት እላለሁ ፤ 2ኛ የተወደደች ፤ እግዚአብሔርን የሚታውቅ ፤ የምትፈራ ፤ በቃሉም የምትመራ ፤ ለፈጣሪ ፤ ለባሏ ፤ለህሊናዋ ፤ለኑሮዋ ታማኝ የሆነች መልካም ሴት ( ሚስት ) አግኝቶ አዕምሮው ካልተቃወሰ ( የጤና ችግር ከላጋጠመው ) በቀር ማን በዋዛ ሚስቱን ይጥላል ? ( ይተዋል ) ? ያልታደልኩትን እኔን ካልሆነ በቀር እንዲህ ዓይነቱ ውንብድና ፤ ሃፍረት የሌለው ጥቃት በማን ላይስ ደርሶ ያውቃል ?

ይህ ከመሆኑ በፊት ምንም እንኳን በውቅቱ የገባሁበት አጣብቂኝ ለማውራትም እንኳ የሚቀፍ ፤ ውስብስብ ፤ የከረፋ ቆሻሻና ጸያፍ ከመሆኑ የተነሳ ልታገሱት የማይቻል ቢህንም ፤ ለብዙ ዘመን ተጠምቼ ፤ ተመኝቼና በትዕግስት ጠብቄ ያገኘሁት ፤ ብዙ ዋጋ የከፈልኩበት ትዳሬ ስለሆነ ሙሉ ለሙሉ ከመበላሸቱ በፊት እስቲ ይሁን ብዬ ፤ ይቅር ለእግዚአብሔር በማለት ሁሉን ረስቼ ፤የማይቻለውን ችዬ ፤የማይረሳውን ረስቼ ፤ ነገን ብቻ ተስፋ በማድረግ እንደገና ጠጋግኜ ለማዳን የሞከርኩት ትዳሬ አፈር ድሜ በልቷል ።

እንዲህም እንኳን ሆኖ ወዲያውኑም ውዬ ሳላድር ባንድም ሆነ በሌላ ፤ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በኔ ሰበብ የእግዚአብሔር ቤት መጠቋቋሚያና መሳለቂያ ከሚሆን ፤ሌሎች ቅዱሳንና እውነተኛ ታማኝ የሆኑ አገልጋዮችና መሪዎች ስም በመጥፎ ምሳሌ አብሮ ከሚነሳ ( ከሚጠፋ) ፤አገልግሎታቸው ከሚተች ፤ራዕያቸው ፤ ዓላማቸውና ትጋታቸው ዋጋ እንዳያጣ ፤ሳይጣን ከሚደሰት ፤ ሁላችንም የዓለም አጀንዳ ከሚንሆን፤ እግዚአብሔርንና መንፈሱን ከማሳዘን ፤ በተለይም በእምነታቸው ያልበረቱ አዳዲስ አማኞች ግራ እንዳይጋቡ እኔው ደግሜ ደጋግሜ ልጎዳና የሚቻል ከሆነ እስቲ እንደገና ትዳሩን ወደ ነበረበት ልመልሰው በማለት ያሰብኩት ቀናነት ዋጋና ትኩረት ተነፈገው።

ይህ ሁሉ ሆኖ ሰውየው ( ፓ/ር ዳዊት ) ይህንን ለፈጸመበት ጥፋትና አስነዋሪ ተግባር እስካሁን አልተገሰጸም ፤ አልተወቀሰም ፤ አልተከሰሰም ይቅርታም አልጠየቀም ። ነገር ግን የከበረውን ትዳሬን አፍርሶ እሱ ግን ዛሬም እያሾፈ በሰላም ይኖራል ፤ እንዳውም ይባስ ብሎ ቤተክርስቲያንን ይመራል ፤ የእግዚአብሄርን ቃልና ፈቃድ አስተምራለሁ ፤ የክርስቶስን ዓላማ እያራመድኩ፤ እያስፈጸምኩ ነኝ ይላል ።ግብረ አበሩ የሆነችውም ወ/ሮ ትግስት የራሷን ትዳር ንዳ ዛሬም አብረው በመሆን ሥፍራና ጊዜ እየቀያየሩ በየአብያተክርስቲያናቱ ዘንድ የተለመደውን ተራ ግርግር እየፈጠሩ መንፈሳዊ አገልጋይ ለመባል እየጣሩ ናቸው ። በኔ ላይ በለመዱት ዓይነት አኳኋን በተመሳሳይ ሁኔታ የኔ ዓይነቶቹን ሌሎች የእግዚአብሔር ህዝብ መተራመስ የለበትምና ድርጊቱ ተገላልጦ የማያዳግም ትምህርት ተሰጥቶ ህዝበ-እግዚዝብሔር ከመታለልና ተመሳሳይ ሰለባ ከመሆን መዳን አለበት ።

እነዚህ ፌዘኛ ግለሰቦች ፤ እጥቤ አሿፊ ጩሉሌዎች ሃፍረትና ይሉኝታ የሌላቸው ደንታ-ቢስ ባይሆኑ ነው እንጂ እንኳን በቤተ-እግዚአብሔር ውስጥ ካህን የሆነ ሰው ቀርቶ በዓለም ያሉቱ ካሃዲዎች ዘንድም እንኳ እንዲህ ዓይነቱን ወንጀል ስፈጽሙ ተሰምቶና ተደርጎ አይታወቅም ። እኔ ተራ እቃ ( ንብረት ) ብቻ አይደለም የጠፋብኝ ፤ ገንዘብና ጊዜ ብቻ አልነበረም የባከነብኝ ።ነገር ግን ትዳሬ እኮ ነው የፈረሰው ፤ መተኪያ የሌለውና የዚህ ምድር አስፈላጊ እና እግዚአብሔር ባርኮ ከፈቀደልን እድሎችና መብቶች አንዱ ነው ትዳር::

በሌላ አባባል ትዳር ከእግዚአብሔር ቃልና መመሪያ ውጪ ሌላ ፎርሙላ የለውም ፤ “ ሰው እናት አባቱን ይተዋል ከሚስት (ከባል ) ጋር አንድ ይሆናል፤(ይጣበቃል) “ እንደሚል አንድ ሥጋ ፤አንድ አካል ፤አንድ መንፈስ በመሆን አንድ ዓላማ ይዘው ጥንዶች በፍቅር የሚጣመሩበት ነው ። በዚህ ዓላማ የተጣመሩ ጥንዶች አንዳቸው ከሌላኛው የተለየ ፊላጎት እና የተደበቀ ልዩ ሚስጢርና ፊላጎት ሊኖራቸው አይገባም ፤

ነገር ግን ያልታደለው የኛ ትዳር ግን ገና ስፈጠር ከአጀማመሩ በጨቅላነቱ በአጭር የቀጩት ቢሆንም ትዳሬ ለኔ ህይወትና የከበረ የአምላኬ ስጦታ ነበር ። ትዳር አንዴ ብቻ ነው ፤ ማፍቀርም የምቻለው አንዲትን ሴት ፤ ለዚያውም ከተቻለ አንዴ ጊዜ ብቻ ። ዳስታም ቢሆን ሁሌ የለም፤ በየዓመቱ ሠርግ ለማድረግም የማይታሰብ ነው ። የሆነው ሆኖ ለአንዲት ደቂቃ ( ዕለትም ) እንኳ ቢሆን ያፈቀርኳትን ሴትና የከበረውን ትዳሬን በቀላሉ በፓ/ር ዳዊት ሞላልኝ ምክንያት አጥቻለሁ ።

ስለዚህ የከበረና የናፈቅኩት ፤ የተመኘሁት ጅምር ደስታዬ በእንጭጩ ከመቅጽበት በመቀጨቱ ወደ ሃዘንና ውርደት ተቀይሮ አንገት አስደፍቶኛል ፤እልሀኛ ፤ ቂመኛና በምሬት የተሞላሁ ተናዳጅ አድርጎኝ ሄዷል ።ነገ ደግሞ ምን እንደሚሆንና ምን እንደሚገጥመኝ እርግጠኛ አይደለሁም ።

ይህ ግለሰብ (ዳዊት) ግን ኑሮዬን አፍርሶ ፤ ህይዎቴን አበላሽቶ እንዲህ እንደ ቀልድ እያሾፈ ሊኖር ነው ? ካደረሰብኝ ብርቱ ፈተና የተነሳ በህይወት ለመኖር የማያስችል ፤ ለወንጀል የሚገፋፋ ፤ ለከፋ በሽታና ጥልቅ ሃዘን የምዳርግ ነው የገጠመኝ ። አረ ለመሆኑ በትዳርና በርስት ቀልድ አለ ? በዓይንና በሚስትስ መጫወት ይፈቀዳል ? እንኳን ግፍና በደል በግልጽ በቤቴ ተፈጽሞብኝ ቀርቶ ድርጊቱ ደግሞ ከጥርጣሬ ያለፈ የአደባባይ ጥቃት መሆኑ ይቅርና እንዲሁ በጥርጣሬም እንኳን ቢሆን በሚስቴ የልቅነት ድርጊት የተነሳ የመቅናትም ሆኔ የተጣመመውን የማቅናት መብቱ ለኔ የሚገባኝ ህጋዊ ባል (አባወራ ) አይደለሁምን ?

እስቲ ፍረዱኝ አንድ መንፈሳዊ አገልጋይ በአገልግሎት አሳቦ የራሱን ሚስት እቤቱ አስቀምጦ “ዘመዴ( ካዝኔ) ናት “ እያለ አንዲትን ሌላ ሴት እንደ ኮሮጆ ሸክፏት ፤ እንደ ሻንጣ እየጎተተ ከሀገር ሀገር ፤ ከከተማ ወደ ከተማ በየሆቴሉ ሁሉ አስከትሎ ስጓዝ ትንሽ እንኳን ይሉኝታ አይዘውም ? ያቺስ ሴት ብትሆን የ”ሶሎ ዘማሪ ፤ የሙዚቃ መሳሪያ ተጫዋች ፤ ወይም በመድረክ ላይ የቋንቋ አስተርጓሚ (ሰባኪ ) ሳትሆን የራሷን መደበኛ ኑሮ ትታ እንደ ጭን ገረድ በየሀገሩና መንደሩ የማንንም ወጠምሻ ጎሮምሳ ተከትላው እየዞረች አብራው በየሆቴሉ አብራው ስታድር ሁለቱም ህሊና የላቸውም ዎይ ?

ሁለቱም በገዛ ህሊናቸው ባይኮረኮሩ ፤በመንፈስ ቅዱስ ለምን አልተወቀሱም ? አዕምሮ ቢደነዝዝ ፤ ህሊናቸው የማይወቅሳቸው ፤ የአውዋቂን ምክርና ተግሳጽ የማይሰሙ ፤የህዝብን ትዝብትና ግልምጫን ከምንም የማይቆጥሩ ቢሆኑም ከነአካቴው ሁሉም ይቅርብኝ እንጂ እኔ ግን ትዳሬን በማንም ማስነካት ፤ ሚስቴንም ከማንም ጋር መጋራት ስላልፈለኩ ሳልወድ በግድ ከመካከላቸው ወጣሁ ።በዚህም በዘመኔ ሁሉ የማልረሳ የህይዎት ጠባሳ እና ስብራት ትቶልኛል ፤ አንዳንዴ ቁጭ ብዬ እያሰላሰልኩ ሳስብ ባልጠፋ ሰው ከነዚህ ቅንነት ከጎደላቸው ሰዎች ጋር እኔ ስገጣጠም እግዚአብሔር ለምን ዝም አለኝ ? ይህ ሁሉ ጉዳት ፤ መቁሰል ፤ መድማት ፤ መፈራገጥ ፤መላላጥ ብሎም ለብርቱ ሃዘን መጋለጥ ለማን ይጠቅም ይሆን ? ማንስ ይከብርበት ይሆን ? ማን ከስሮ ቀርቶ ማንስ ያተርፍ ይሆን ? እንዳው ባጭሩ ይህ ዳዊት የሚባል ሰውዬ እንዲህ አቃጥሎኝ አዋርዶኝ እስከመጨረሻው የሚሳካለት መስሎት ይሆን ? ደስታዬን እንዲህ በአጭር

አጨልሞ እሱ ግን እንደ ፈነጨ ሊኖር ? ለማንኛውም የመጨረሻውን ውጤትና ድምዳሜ በያንዳንዷ ሰኮንድና ደቂቃ ከአምላኬ በትዕግስት እጠብቃለሁ ።

ዶ/ር ፡

ፓ/ር ዳዊት የበደለኝ በብዙ አቅጣጫ ነው ፤ለምሳሌ አስቀድመን በጋራ በተስማማነው መግባባት መሰረት በራሱ ቤተክርስቲያን (FBI ) ባለሙያዎች ተቀርጸው የተሰሩትን የሠርጌን ቪዲዮና ከ5000 በላይ የሆኑ ፎቶግራፎችን ኮፒም ሆነ ኦሪጂናል ቅጂዎችን እስከ ዛሬ ድረስ እንዳለገኝ ከልክሎ በማስቀረቱ እንኳን ለዘመድ አዝማድ ፤ ጎደኞቼና ጎረቤቶቼ ፤ የስራ ባልደረቦቼ ፤ ለአብሮ አደጎቼ ይቅርና እኔ ራሴ የጉዳዩ ባለቤት የሆንኩት የሠርጌን ማስታወሻ የማየትና በታሪክነቱ ለማስቀመጥ ዳዊት ከልክሎኛል ። የጋብቻ ወረቀቴንም (Marriage Certificate ) እስካሁን ድረስ በጉልበቱ አስቀርቶታል ።

እኔ ብቻ ሳልሆን መልካም ትዳር እንዲገጥመኝ ተመኝተውልኝ ለጋብቻችን መሳካት የጸለዩ ፤ የለፉ ወገኖች ፤ የረዱን እና በብዙ የደከሙልን ፤ እሩቅና የተሻለ ደረጃ ላይ እንዲንደርስ ከልባቸው ያማጡ ጓደኞችና የስጋ ዘመዶቼ ሁሉ ጭምር በደረሰብኝ ሁኔታ አፍረዋል ፤ አዝነዋል ፤ተበሳጭተዋልም ።

በቆየው የሀገራችን አባባል “ከምርት እንክርዳድ አይጠፋም” እንዲሉ ጥቂት ግለሰቦች (የነዳዊት ግብረአበሮች ) ካላቸው ተመሳሳይ ሥነምግባር እና ባህሪ፤ የግል ጓደኝነት ፤ ውለታና ቀረቤታ የተነሳ ግድፈትና ነውራቸውን ሊያስተባብሉ ፤ እርኩሰትንና ቅጥፈትን አድበስብሰው ነጻ ናቸው ለማለት ደፋ ቀና ሲሉ ፤ የጥፋተኛውን ወንጀል ሸፋፍነው ነውረኛውን በጉያቸው ወሽቀው በመደበቅ ፤ሃቅን በሃሰት በመጨፍለቅ ፤ እኔን በማግለል ለነገራችን ቅርበት የሌላቸውን ንጹሃንን በማታለል ፤ እውነትን በማፈን ፍትህን ለማዛባት ትርምስ ፈጥረው ቅዱሳንን ግራ ለማጋባት ሞክረው ነበር ።

ነገር ግን እኔን የገረመኝና ያናደደኝ “ በሰው ቁስል እንጨት ስደድበት “ ዓይነት አባባል ካልሆነ በቀር የገጠመኝ መከራና ፈተና ከመርግ ይልቅ እጅግ የሚከብደው ውርደትና ሃዘን ፤ ጥቃት ሁሉ እነሱን ገጥሞ ቢሆን ኖሮ ( ራሳቸው በኔ ቦታ ቢሆኑ ኖሮ ) ያለማጋነን ነፍሳቸውን በዛፍ ላይ የሚያንጠለጥሉ ፤ ምናልባትም አዕምሮያቸውን ስተው ፤ ጨርቃቸውን ጥለው የሚያብዱ ወይም ደግሞ በንብረትና በሰው ህይዎት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊያደርሱ እንደሚችሉ አልጠራጠርም ። ፓ/ር ዳዊት ራሱ እኔን የገጠመኝ ዕጣ-ፋንታ ገጥሞት ቢሆን ኖሮ ምን ይውጠው ነበር ? ሁሉም ቢጤዎቹ ካንድ ጉድጓድ የተቀዱ ፤ አንድን ጽዋ በጋራ የጨለጡ አሳፋሪዎች እና selfish ስለሆኑ ታዘብኳቸው ።

መቼም ቢሆን እንደ ሰው ያልሆነ እግዚአብሔር ጻዲቅና መልካም አምላክ ነውና ምህረት ፤ ቸርነት ፤ ጥበቃው ፤ ፍቅሩ ፤ ርህራሄው ያማያልቅበት ፤ ወረት የሌለው በመሆኑ ራራልኝና አጽናንቶ የማይቻለውን እንዲችል ረዳኝና ከክፉው ሁሉ ጠብቆ እስካሁን በህይዎት አኖረኝ እንጂ የተጋራጠብኝ ፈተና ማንም ብርቱ ነኝ ባይ ልታገሰውና ልቋቋመው የማይቻል ከባድ አደጋ ነበር ። የራራልኝ እግዚአብሄር ይመስገን ፤ ነገንም በርሱ ፈቃድ እኖራለሁ ፤ አሜን ።

ለመሆኑ በማንአለብኝነት ይህንን ሁሉ ጥቃት የሚፈጽም ይህ ጉልቤ ጀብደኛ (ዳዊት ) ማን ነው ? “ከወፈሩ አይፈሩ” ነው ነገሩ ? ወይስ ምንን ተማምኖ ? ይህንን ሁሉ በደልና ግፍ ሰው አይቶ ባይፈርድልኝ እግዚአብሔርስ ይወደዋል ዎይ ? ይህ ግድየለሽ ሰላሜን አደፍርሶ ፤እና ህይዎቴን አበላሽቶ ፤ ኑሮዬን አናግቶ እሱ ግን ልፈነጭ ? አይደረግማ !!

የፈጸመውን ድርጊት ተናግሮ ፤ ጥፋቱ ተዘርዝሮ ስህተቱ ተብራርቶ ነውርና ድፍረቱ ተገልጦ ለአደባባይ መቅረብ አለበት ። ምናልባት በመንፈሳዊ አገልግሎት ሽፋንና ሰበብ ያካባተው ሃብት ፤ ያተረፈው ዝናና ክብር አለኝ ብሎ ስለምያስወራ ፤ እንዲሁም የጥፋቱ ተባባሪ ቢጤዎች ፤ ጓደኛና ምኑንም በውል ያልተረዱ ቅንና የዋሆች ያለእውቀት ደጋፊዎች ልኖሩ ስለምችሉ ከሰው ዘንድ እውነተኛ ፍርድ ላላገኝ እችላለሁ ፤ ቢሆንም ከቲፎዞ (ደጋፊ) ብዛት የተነሳ የፍትህ ዳኛና ሃቀኛ ምስክር ስለማይገኝ ፤ ትዳሬ ፈርሶ ፤ህይዎቴ ተበላሽቶ ፤ ራዕዬ ተጨናግፎ ፤ ተስፋዬ ጨልሞ ከአቅሜ በላይ የሆነ አበሳና ውርደት ተሸክሜ ለመኖር ለኔ እጅግ ከባድ ነው ።

ፓ/ር፡

ከዚህ ቀደም ውድ ጊዜህን ሰውተህ ከረዳቶችህ ጋር በመካከላችን ተገኝተህ ለበርካታ ሰዓታት እኛን ( ዳዊት ፤ ትግስትንና እኔን ) ስታወያየን አንተ ራስህ ሰምተህ ፤ አይተህ ፤ግንዛቤ እንዳገኘሀው (እንዳረጋገጥከው ) ፓ/ር ዳዊት እኔና ሚስቴን ባጋባበት ዕለት ወዲያውኑ ከመቅጽበት ከሚስቴ ጋር እንዲንለያይ ዋና ምክንያት ሆኗል፤ ለዚያውም አንዴ ብቻ ሳይሆን ሁለቴ ሦስቴም እንጂ ።

ይህ ድርጊት በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በአበሻ ታሪክ በኔ ብቻ ካልሆነ በቀር የት ሀገር ? መቼ ? በነማን ላይ ደርሶ ያውቃል ? እነዴትስ በጫጉላ ሽርሽር ወቅት ( honey moon time ) ሙሽሪት ሙሽራውን ትታ ፓስተሯን ለመዝናናት በሚል ሰበብና ድፍረት የቃል ኪዳን ሙሽራ ባሏን በሆቴል ውስጥ እንዲሁም በሌላ ጊዜ ደግም በባዶ መኖሪያ ቤት ውስጥ ጥላ ፤ጨርቋን ጥላ እና አዕምሮዋን ስታ ለ7 ቀንና ሌሊት ያህል የምትጠፋው ? በገዛ ቤታችን ውስጥስ ቢሆን ባልን ሳሎን ውስጥ ትቶ ከፓ/ር ጋር መኝታ ቤት ገብቶ በር በመቆለፍ ለሰዓታት ያህል አገልግሎት ላይ ነን ማለትና…ወዘተ ጸያፍና ድፍረት የተሞላባቸው አሳፋሪ ድርጊቶችን መፈጸም የጤና ነው ? ወይስ የእብደት ?

እንዲህ ዓይነቱ ነውርና ልቅ የሆነው ጥፋት ከልክ ያለፈ ፤ መረን የለቀቀ ፤ሚዛኑን የሳተ ፤ ከድንበርም የዘለለ ስለሆነ ልሸከመው የማልችለው በቤቴ ፤ በትዳሬ እየተፈጸመ ነውና የከፋ ነገር ከመምጣቱ በፊት ይታሰብበት በማለት በግልጽ ውይይትና ምክክር አድርገን እናስወግድ ፤ መፍትሄ በመፈለግ እርማት እንውሰድበት የሚል ገንቢ እና ቀና ሃሳብ እንደ አገልጋይ ክርስቲያንና አማኝ በአክብሮት ያቀረብኩላቸው አቤቱታ ና ጥያቄ “ ጌታ ይገስጽህ ! ይህ ሰው (ፓ/ር ዳዊት ) በእግዚአብሔር የተቀባ ፤ የተለቀለቀ መንፈሳዊ ሰው ነው ፤ ስለዚህ ጌታ በቀባው ላይ እጅህን አታንሳ ፤ “ ተብዬ ተኮነንኩ ። ራሱ ዳዊትም ቢሆን “ ያቀረብከው ጥያቄ ለኔ የሚመጥን አይደለም “ በማለት ናቀኝ እንጂ ጆሮውን እንኳ ለጥቂት ለደቂቃ ያህል ልሰጠኝ አልፈለገም ፡፡ በዚህም ተግባሩ የኔን መብት ለራሱ አደረገ ፤ እኔን ግን ለውርደት ለጭንቀት ፤ ለሃዘንና ለኪሳራ ዳረገ። አሁን በዚህች ደቂቃና ሰከንድ ይህንን ደብዳቤ በማዘጋጅበት ሳምንት (ቀናት ) በሀገር ቤት ኢትዪኦጵያ ውስጥ ከዚህቺው ሴት ጋር አብረው ናቸው ። ጨርሰው ልላቀቁ ስላልቻሉ በረቀቀ ሚስጢር ያለሀፍረት አሁንም አብረው እንደተጣበቁ ናቸው ።

ፓ/ር ፡

ምናልባት “ድፍረት ፤ ንቀት ፤ ትዕቢት ወዘተ…የተባሉትን ዓረፍተነገሮች (ቃላት) ለምን ተጠቀምክ ? ለምንስ ደጋገምክ ? ትለኝ ይሆን ?በጣም የሚያናድደው ፤የሚያስገርመውና አሳፋሪው ነገር ይህ ግለሰብ ራሱን ነቢይ እያስባለ መገለጥ ቢጤ እያቀነባበረ የእግዚአብሔርን ቃል እየጠቃቀሰ “ የዓዞ እንቧ “ እንደተባለው የሀገራችን አባባል “ኢየሱስ ያድናል “ ወዘተ….በሚል ቋንቋ የዋሁን ህዝበ-እግዚአብሔር ፊት በእግዚአብሔር ፑልፒት ላይ እየተንጎራደደ መፈክር እያሰማ የትዳርን ክቡርነት ፤ የባልና ሚስትን ህጋዊ ግንኙነት (አብሮነት) ከፈጣሪ የሆነና የተቀደሰ ቃል ኪዳን መሆኑ እንደት ተሰወረበት ? የራሱን ሚስት እቤቱ አስቀምጦ በአፍላ ፍቅራችንና ጅምር ትዳራችን ወስጥ እንደ እርጎ ዝንብ ጥልቅ ብሎ ለምን ገባብን ?

ለነገሩማ ቀድሞውንም ቢሆን ሴራቸው ስላልገባኝ የእግዚአብሔር አገልጋዮች ናቸው በሚል አምኜ ቀረብኳቸው እንጂ እነሱ ግን ያኔም ቢሆን ማስመሰል በተሞላበት የህሰት ትንቢት አደንቁረውኝ ፤በመገለጥ አዋክበውና አጣድፈውኝ ለስውር ዓላማቸውና የግል ጥቅማቸው ማሟያ አቅደው ለይስሙላ ከአጠገባቸው ሊያስቀምጡኝ ፈለጉ እንጂ ያኔ ያላወቅኩት ቆይቼም ቢሆን በኋላ እንዳረጋገጥኩት ለ5 ዓመታት ያህል ዘልቆ የቆየ ግነኝነትና አሳፋሪ ቃል-ኪዳን ነበራቸው ።

በሀገራችን አባባል “ የአይጥ ምስክር ዲንቢጥ ናት “ እንደተባለው ካልሆነ በቀር እነዚያ ቢጤዎቹስ ቢህኑ “ እሱ ዳዊት የፈጸመብህ ድርጊት አግባብ ባይሆንም ጸጥ ፤ ለጥ ብለህ ተቀበልና ዝም በል ። አለበለዚያ ትቀሰፋለህ ፤ ወደ ሲኦል ትገባለህ፤ ለሳይጣን አሳልፎ ይሰጥሃል ፤ ትረገማለህ “ ወዘተ.. እያሉ አስፈራርተው ሲያሸማቅቁ ፤ በሌላ በኩል ደግሞ “ የሚናከብረውና በጌታ የተቀባ ፤የተለቀለቀ ፤በመገለጥና ጥበብ ብሎም የፈውስ ጸጋ ስጦታ አገልግሎቱ እጅግ የጠለቀ ፤ የመጠቀ ነውና የተደረገብህን ድርጊት ሁሉ አሜን ብለህ አርፈህ ኑር” በሚል ማባበል እኔን አታሎ ለማዘናጋት ለሃጥያት ሲተባበሩ ፤በሃሰት ሲመሰክሩ ፤ አንዳች ፈጣሪን ባይፈሩ ፤ለማንም ባይራሩ ፤ ለሃቅ ባይቆረቆሩ ፤ በእግዚአብሔርም ሳይጠሩ ለክብራቸው ፤ ለዝናቸው ፤ ለጥቅማቸውና ለእንጀራቸው ያንን ያህል በድርቅና ከተከራከሩ ትዳሬ ደግሞ ለኔ ከእንጀራና ሆድ የሚበልጥ ፤ ከዝና ፤ ከክብርና ጊዜያዊ ጥቅም ያለፈ ህይዎትና ኑሮዬ መሆኑን ለማወቅ እንዴት ተቸገሩ ?

ስለዚ ይህ መቼም “ በሰው ቁስል እንጨት ስደድበት “ እንዲሉ ንቀት ፤ ትዕቢት፤ ድፍረትና “ ነጌ በኔ” አለማለት ካልሆነ በቀር ሌላ አንዳችም ምክንያት ሊኖር አይችልም እንዳውም በኔ ቦታ ሆኖ ካዩት ከድፍረት ያለፈ ጭካኔ ነው እላለሁ ። እኔ ደግሞ ተበድዬ ፤ ተጎድቼ ፤ ተጠቅቼ ፤ ተደፍሬና ተንቄ ሽንፈትን አሜን ብዬ በውርደትና በሃዘን የተሞላ ህይዎት ለመኖር ስለማልፈልግ አንድ ስፍራ ላይ ባንድ ወቅት

ባንዴ መቋጨትና መቆረጥ አለበት ። ያንን ለማምጣት ደግሞ እስከ ህይዎቴ ፍጻሜ ድረስ ዋጋ ለመክፈል ዝግጁ ነኝ ፤ የእውነት አምላክ ፤የቅኖች ወዳጅ ፤ የምስኪኖች አለኝታ የሆነው ፈጣሪዬ ደግሞ ለአረመኔዎችና ለነውረኞች አሳልፎ ስለማይሰጠኝ ፤ ጥቃቴንም ስለማይወድ በሱ እየታመንኩ ላደርገው የወሰንኩትን በአርሱ ታምኜ እፈጽማለሁ ።

አዎን ከዚህ በላይ ያልኩት ሁሉ በኔ ላይ የተፈጸመ እውነት የሆነ ዓይን ያወጣ ጥርሱን ያገጠጠ ብልግናና በቃላት የማይገለጽ ከባድ በደልና ግፍ ነበር ። ዛሬ ዛሬ በየቦታው አፈ-ጮማ አተራማሽ መተተኛና ፈጣጣ ጋጠ-ወጥ ጮሌ ሁሉ የእግዚአብሔርን ቤት እያጥለቀለቀ የስንቱ ምስኪኖች ትዳር ደቀቀ ? አረ የፍትህ ያለህ ! የጽድቅ ያለህ ! የቅድስና ያለህ ! አለቅን ፤ ደቀቅን !! እባካችሁ ድረሱልን !!!

ለመሆኑ ትዳርን ማፍረስ ቤተክርስቲያንን ማፍረስ አይደለምን ? ለዚያውም የቤተእምነት መሪና አገልጋይ ሆኖ የንጹሃንን ትዳር እያረከሱ ፤ ቤተሰብን እያፈረሱ ቤተክርስቲያንን እያስወቀሱ “የተቀባ ፤የበቃ “ ወዘተ … አገልጋይ መሆን ይቻላል ? ትንቢት እየተናገሩ መገለጥ እየቀበጣጠሩ የትዳርን ክቡርነት እንዴት ዘነጉ ? ሚስት ለባል ፤ ባልም ለሚስት ብቻ መሆናቸውን ለማረጋገጥ ለነሱ ብቻ ሲባል ሌላ ነቢይ መቅጠር ( ልዩ መላዕክት ከሰማይ ማስመጣት ) አለብን ዎይ ? “እግዚአብሔር እንዲህና እንድያ ብሎሃል” እያለ ሌት ተቀን እየሰበከ እራሱ ግን ለምን አልኖረበትም ? ራሱ ልፈጽመው ያልቻለውን በጉልበት ልያሽክመን ለምን ይጥራል ?

ደግሞስ የኔ አንዲቷ ነጠላ ህይዎት (ነፍስ) ቤተክርስቲያን አይደለችምን ? የእግዚአብሔር መንፈስ ማደሪያ ፤ የክብሩም መገለጫ ቤተክርስቲያን አይደለሁም ዎይ ? ይህ ዓይኑን በጨው የታጠበ ደፋር ግለሰብ ህይዎቴንና ዕድሌን አበላሽቶ ደስታዬን ወደ ሃዘን ለውጦ ቤተክርስቲያንን ሊመራ ?ህዝብን ሊያገለግል ? “ It is not fair “ (ፍትሃዊና አግባብ አይደለም ) ፤ እሷስ ወ/ሮ ትግስት ብትሆን ልማደኛ ባትሆን ኖሮ ከበፊተኛው ስህተቷ ለምን አልታረመችም ? ከኔ በፊት ጀምሮ ነጋ ጠባ የትዳር ቀበኛና ጸር “Allergy “ (የፓስተሮች ቀማሽ ) ይመስል በበፊቱ ነውርና ስህተቷ ትምህርትም ሆነ ምክር ችግርና ግሳጼው ሁሉ መታረም ስገባት እንዴት እንደገና ለአግልግሎት በቃች ? ከኔ በፊት የነበራትን ትዳሯንም እንዲሁ በተመሳሳይ ተግባር ከሌላኛው ፓስተሯ ጋር በዝሙት ተጠርጥራ ትዳሯ እንደፈረሰ ከኔ በቀር ሁሉም የአከባቢያችን መንፈሳዊ መሪዎች የሚታውቁት የቅርብ ጊዜ ታሪክ ነው ። የራሷን ጽንስ (የኑሮ ጅምር ) አጨናግፋ (አኮላሽታ ) ፤ በተለያየ ጊዜና ወቅት ካገባቻቻው ባሎቿ መካከል አንዱንም እንኳ በአግባቡ ይዛ የራሷ ለማድረግ አቅቷት ሁሉንም በየተራ በየቦታው በአደባባይ እያፈረጠች ፤ እንደገና አዘናግታ ከሌሎች ተረኞች ጋር የምትከንፍ ያልሰከነች ሴት አሁን ከሰሞኑ ደግሞ ስፍራና ቤተክርስቲያን ቀይራና ለዋውጣ አዳዲሶቹን መሪዎች ጥብቅ ብላ የቤተእምነቱን ቁልፍ እንዴት ተረከበቻቸው ?

ለማስመሰልና ለጉራ፤ ብሎም ለዝና ብሎም ለድብቅ ዓላማ ካልሆነ በስተቀር የራሱን ቤት ያቃተው ሰው የእግዚአብሔርን ቤት ለመጠበቅና ለማገልገል እንዴት ተገባው ? ለማጭበርበር ካልሆነ በቀር የራሱን ጽንስና ራዕይ ገሎ የሰው ቤት ሄዶ የሌላውን ልጅ ተንከባክቦ ለማስተማር ቀርቶ ጉንጭ እንኳን ለመሳም ሃላፊነት የሚጣልበት ስበእና አለው ለማለት አያስችልም ።እንዲህ ዓይነቱ ሰው ካለ ራዕይ ለመጠበቅ ከቶ አይቻለውም ፤ ምክንያቱም እውነተኛ አገልግሎትና ታማኝነት ከራስ ቤትና ትዳር መጀመር ስለምገባው ። እውነተኛዋ የክርስቶስ ቤተክርስቲያን ካለች እንዲህ ዓይነቱን ዓይን ያዋጣ ድፍረትና ተራ ቁማር መዋጋት ተጋቢ ይመስለኛል ።

ምክንያቱም በኔ በኩል የችግሩ ሰለባ ከመሆኔም በላይ እንደ ባለ አዕምሮ ሳሰላስል እነዚህ እና ቢጤዎቻቸው ባለቤቱ የከደነውን ያለፈቃድ የሚከፍቱ ፤ አንዱ የገነባውን የሚንዱ ፤በፈጣሪ ስም ፤ በሃይማኖት ሰበብ ተገቢ ያልሆነን ተግባርን የሚሰሩ ፤ለማንም የማይራሩ ከስህተታቸው የማይማሩ ፤ የራሳቸውን ትተው የሰውን ሚስት ( ባል ) ለመቅመስ ሌት ተቀን የሚዞሩ ፤ ለከበረው ትዳርና ጤነኛ ፍቅር እንቅፋት ብቻ ሳይሆኑ ለሰሩት ጥፋትና ስህተት በንቀት ጆሮ ዳባ ብለው (ችላ ባይ ከመሆናቸው የተነሳ )ጉዳቴ ዕለት በዕለት ይበልጥ እየተሰማኝ ስለሆነ የሚወስነው ውሳኔ እየክፋ እንደመጣ ተገንዝቤያለሁ ።

በመሆኑም ስማቸው ከዚህ በላይ በተደጋጋሚ የጠቀስኳችው ግለሰቦች (ፓ/ር ዳዊትና ግብረ አበሩ ወ/ሮ ትግስት ) እንዲሁም ቢጤዎቻቸው በሰው ላይ በደልና ነውር እያደረሱ ፤የንጹሃንን ትዳር እያፈረሱ በእግዚአብሔር ቤትና በቅዱሳን መካከል መሽገው ፤ሃጥያታቸውን ሸሽገው ሚስኪኖችን አንገት እያስደፉ ፤ የሰላማዊ ኑሮን ጣዕምና ትርጉም እያጠፉ መላውን ቅድዱሳን በሃሜትና በአሉባልታ እያተራመሱ ቤተ-እምነቶችን መነጋገሪያ ፤ መሳለቂያ እያደረጉ መቀጠል ተገቢ አይደለምና ጉዳዩን ለህዝብ ሚዲያ እና ለመላው አብያተ-ክርስቲያናት ለማቅረብ ወደድኩ ።

አዎን ፤ በቃ ፤ የእግዚአብሔር ቤት ይህንን ከመሳሰለ የነውር ተግባር ከነዚህ ዓይነቶቹ አስመሳይ ነውረኞች ልጠራ ይገባል ፤እኔም ከእንግዲህ ጥፋተኛው ቅጣቱን እስኪቀበል ፤ ነውረኛው በነውሩ እስኪጸጸት ፤ እግዚአብሔርን ፤ ህዝቡንና ተበዳዩን ይቅርታ እስኪጠይቅ ፤ ቁስሌ እስኪጠገን ፤ህመሜ እስኪፈወስ ፤ ምናልባት ተመሳስለው እና ተደብቀው በየቦታው የተሸሸጉ ነውረኞች ካሉ ያጨለሙት

ተስፋዬ እስኪታደስ ፤ ሃላፊነት የጎደላቸው መንፈሳዊ ጀብደኞች ያኮላሹት ራዕዬ እስኪመለስ ፤ የጌታ ፈቃዱ ሆኖ በህይዎት እስካለሁ ይህንን ስድ አልለቀውም ።

ሌላው ቢቀር እንኳ የዚህን ጨዋ መሳዪ ተግባር ሰው ሁሉ ይስማውና ባላጌዎች ይፈሩበት ፤ ጥፋተኞች ይታረሙበት ፤ ትውልድ ይማርበት ፤ያፈለገው ንሰሃ ይግባበት ፤ዱሪዬዎች አደብ ይግዙበት ፤ ዝንጉዎች ይጠንቀቁበት ፤የተጎዳው አእምሮና መንፈሴ ይታደስበት ፤ እግዚአብሔር ይክበርበት ።

እንዲሁም ተመሳሳይ በደልና ግፍ በሰውር በቅዱሳን የግል ኑሮና ቤተሰብ ህይዎት ላይ እየተፈራረቀባቸው በአጓጉል ኋላ ቀርና በሃይማኖት ስም ማስፈራሪያነት ከደረሰባቸው በደልና ጥቃት ጋር ተሸማቀው “ታሪኬ ከበደለኝ ሰው ጋር አብሮ ከሚጋለጥ ጥቃቱን ተሸክሜ ፤የጎዱኝን ነውረኞች አበሳ ደብቄ ልኑር “ የሚሉት ሳይቀሩ ሌባውን ሌባ ፤ነውረኛውን ነውረኛ ፤ዋሾ አስመሳዩን ቀጣፊ ፤ወዘተ…እያሉ በድፍረት ተናግረው ለማጋለጥ ጉልበት ያግኙበት።

በሌላ በኩል ሰውዬው ( ፓ/ር ዳዊት ) ብልጣ-ብልጥ ፤ አስመሳይ ጮሌ ፤ ምላሱ ቅቤ ፤ልቡ ጩቤ ስለሆነ ፤የገነነ ዝና ፤ እውቅና ፤ ገንዘብና ብዙ ቢጤዎች ስላሉት ብቻ እኔው ተጠቅቼ ፤ፍትህ አጥቼ ፤ በቀሪ ዘመኔ ሁሉ ተቀጥቼ አልኖርምና ሃቀኛ ዳኛ ፤አመዛዛኝ ህሊና ፤ ከአድልዎ የጸዱ ፍትህን የሚያስከብሩ ፤ ለእግዚብሔርና ቤቱ የሚቆረቆሩ ፤ ህዝበ-እግዛብሔርን የሚያፈቅሩ፤ በጽድቅ የሚኖሩ ፤ለሚስኪኖች የሚከራከሩ ፤ነውረኛ ጥፋት ፈጻሚዎችን በድፍረት በመገሰጽ የሚመክሩ የሚያስተምሩ በፍቅር የሚገሩ ፤ ነውርንና እርኩሰትን የሚጸየፉ እውነተኛ የእግዚአብሔር አገልጋይ ዳኞች አሁንም በአምላኬ ቤት ልኖሩ እንደሚችሉ እርግጠኛ በመሆን ይህንን ጉዳቴን ፤ አበሳዬንና ገበናዬን ዘርዝሬ አቅርቤያለሁ ።

ፓ/ር፡

ይህንንም ሳደርግ አንተ ብቻ ሳትሆን ሌሎች የእግዚአብሔር ሰዎች ፤ የጌታ አገልጋዮች ፤መንፈሳዊ መሪዎችና መላው ቅድሳን ሁሉ “ እኛ በቦታው አልነበርንም ፤ አልሰማንም ፤ አላየንምና አንዳች ነገር ከቶ አያገባንም” ወዘተ… እንዳይሉ ይህንን ደብዳቤና የከዚህ ቀደሞቹን ዝርዝር ጉዳዮች የያዙ ኮፒዎችን ሁሉም በያሉበት አድራሻ በተከታታይ የሚልክላቸው (የማሰራጭ ) መህኑን አልሸሽግም ።

ለዚህም ዋና ምክንያቴ ኪሳራዬ ባይካስም ፤ጉዳቴ ስብራቴ ባይጠገንም ፤ ቁጭት እልሄ በርዶ ቁስሌ ባይፈወስም ትዳሬን እንደሆነ እስከመጨረሻው ያጣሁ፤ የፈራረሰ እና ያከተመለት ፤ የሞተ ነገር ቢሆንም እኔ ተጎድቼ ፤ተዋርጄ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ሌላው ትውልድ ዘላቂ መፍትሄና ያማያዳግም ትምህርት ያገኝበታል ብዬ በመገመት ነው ፤ አዎን ከተቻለ የኔ ትዳር ተኮላሽቶ ታሪኬም ተበላሽቶ ከእንግዲህ ግን የምስኪን ወገኖቼን ትዳርና ኑሮ ከሚያኮላሹና ከሚያበላሹ አገልጋይ ተብዬ መንፈሳዊ ዱሪየዎች ለመታደግ ነው።

ፓ/ር ፡ እጅግ በጣም የማከብርህ ትልቅ የእግዚአብሔር አገልጋይና መሪ ነህ ። ፓስተሬ እንደ መሆንህ መጠን በአከባቢዬ አንድ የእግዚአብሔር ሰው የሚለው እና የጉዳዬን ዝርዝር ታሪክ በቅርበት የሚያውቅ ካንተ የበለጠ ከእግዚአብሔር በቀር ሌላ ማንም የለም ።

ከመነሻው እስከሁን ያለውን ታሪኬን ከሞላ-ጎደል ታውቀዋለህ ፤ በተለይም ጉዳቴን ፤ ስብራቴን ፤ሃዜኔና እንባዬን ፤ እንዲሁም ጥልቅ ቁጭቴን መገመት ከቶ አያቅትህም ብዬ አስባለሁ ። ስለሆነም ከዚህ ቀደም ከአንዴም ሁለቴ በኛ ጉዳይ እንባህን ስታፈስ ደጋግሜ አይቸሃለሁ ።በሌሎች ቅዱሳን ዘንድም ቢሆን የነዚህ ነውረኞች ነውርና ቀልድ ከማንም የተሰወረ አይደለም ፤ ያለንበት ወቅት ከምንጊዜውም በለይ በእርኩሰትና በክፋት የተሞላ ሆኗል ፤ ክህደት በመብዛቱ ቅጥፈት ነግሶ ዘመኑ እጅግ ከባድ ሆኖብናል ።

ስለዚህ እውነት ታፍኖ ሃቅ በመታነቁ ምክንያት ፍትህን አስከብሮ ለጽድቅ የሚፈርድ ዳኛ ይቅርና የቅርብ የሆነ ታማኝ ጓደኛ የታጣበት አስደንጋጭ ወቅት ላይ ደርሰናል። እኔ ያለእግዚአብሔር በቀር ሃብት ፤ ዘመድ፤ ወገንና ደጋፊ የለኝም ።

በዚህ ቁርጥና ፈታኝ ወሳኝ ወቅት አንተ ግን እንደ አባት ፤ የእምነት ሰው ፤ የቤተከርስቲያን መሪና የህዝብ አገልጋይ የመፍትሄ ምክርህ ፤ እገዛህ ፤ አስተያየትና ውሳኔህ ምንድን ነው ?

በተጨማሪም የተፈጸመብኝ በደል ፤ ግፍና ጥቃት ዘርዝሬ ከላይ በጠቀስኩት መሰረት ለሚዲያዎችም ጭምር ለማሰራጨት የወሰንኩ መሆኔን በክብሮት እየገለጽኩ ከፈጣሪዬና ካአንዲት ነፍሴ በቀር አንዳች ለሌለኝ ለኔ ለብቸኛውና ምስኪኑ ሰው አሁንም እንዲትጸልይልኝ ጭምር በጌታ አደራ እላለሁ ።

በጌታ እወደሃለህ

እጅግም አከብርሃለሁ

እግዚአብሔርና ቃሉ ብቻ እውነትና ትክክል ናቸው !

ከእንግዲህ በዘመኔ ሁሉ ማንንም አላምንም !!

እውነት ብትቀጥን እንጂ ጨርሳ ተበጥሳ አታውቅም !!!

ግርማ ዱሜሶ

Email; gelgela09@yahoo.com

ግልባጭ ፡

ለኢትዮጵያ ወንጌላዊያን አብያተ ክርስቲያናት በሙሉየእግዚአብሔር ቅዱሳን ሁሉ በያሉበትአበሻ ነክ ለሆኑ የኢትዮጵያዊያን ሚዲያዎችና ድህረ-ገጾች በሙሉ ።

Sunday, April 26, 2015

ኢትዮጵያ ውስጥ የተዳፈነ አክራሪነት አለ!

ወደድንም ጠላንም ኢትዮጵያ ውስጥ በእምነት ተከባብሮ የመኖር የቆየውን ልምድ በተቃራኒው የሚፈታና የሚመለከት የፍጅት፤ የእልቂት፤ የሁከትና ኢስላማዊ መንግሥት የማቋቋም የተዳፈነ አክራሪ ኃይል አለ። ይህንን ጉዳይ ጠበቅ አድርገን መናገራችን እርስ በእርስ አለመተማመንን እንዲኖር ሳይሆን በመሬት ያለውን እውነታ ደብቀን «የኢስላሚክ ስቴት ሽብርተኛ ቡድን እኛን አይወክለንም» የሚለው ወቅታዊ መፈክር የችግሩን አደገኛነት ስለማይለገልጽ ላይ ላዩን ማውራቱ ለአብሪነት በቂ መልስ መሆን ስለማይችል ብቻ ነው። በተለይ መንግሥት ከቀበሌ አንስቶ በሀገር አቀፍ ደረጃ ሕዝቡን እያወያየ ያለውን የአክራሪ ኃይል በተለይም ወጣቱን በማሳተፍ ስር ነቀል መፍትሄ ካልሰጠበት ውሎ አድሮ አደጋውን መቀልበስ ከማይቻልበት መድረሱ አይቀርም። ይህንን ሐቅ ከሚያረጋግጡልን ማስረጃዎች አንዱ «ጀማል ሀሰን አሊ ይመር» የተባለ ከሙስሊም ቤተሰብ የተገኘ ኦርቶዶክሳዊ፤ በሙስሊም ቤተሰቦቹና ጓደኞቹ መካከል ያለውን ችግር ከተወለደበት መንደር ባሻገር እየተከሰተ ያለውን የአክራሪነት አደጋ በዓይን ምስክርነት እንዲህ ያወጋናል።

ሦስት መልዕክቶች አሉኝ!
መልዕክቶቹም ክርስቲያኑንና ሙስሊሙን ኅብረተሰብ እና መንግሥትን ይመለከታሉ፡፡

መልዕክት አንድ-ለሙስሊም ወገኖቻችን፡-በፎቶው ላይ በቀኝ በኩል ያለው የሥጋ ወንድሜ "አህመድ ሀሰን" ሲሆን በግራ በኩል ያለሁት ደግሞ እኔ ጀማል ሀሰን ነኝ፡፡ ነገር ግን ስመ ጥምቀቴ ገብረ ሥላሴ ነው፡፡ ሁለቱ ሴቶች ደግሞ ወላጅ እናቴና አኅቴ ሲሆኑ ከእኔ ጋር በልጅነት የተነሳው ነው፡፡ ሙስሊም የሆነው የሥጋ ወንድሜ አህመድ ከደቡብ ወሎ ወደ አዲስ አበባ እኔን ክርስቲያን ወንድሙን ሊጠይቀኝ መጥቶ 3 ሳምንት እኔ ጋር ከርሞ ከሄደ ዛሬ ገና 8ኛ ቀኑ ነው፡፡
ጁምዓ ጁምዓ አህመድን አንዋር መስጊጂድ አድርሼው እኔ ራጉኤል ቤተ ክርስቲያን እገባ ነበር፡፡ የሙስሊም ሥጋ ቤት ሄደን ገዝተን እቤት ሄደን እኔው ራሴ ሠርቼ አህመድ ሲመገብ ነው የቆየው፡፡ እኔ ደግሞ አባቴን ሀሰን ዓሊንና ሌላውንም ሙስሊም ቤተሰቤን ልጠይቅ ወሎ ስሄድ ለብቻዬ በግ ያርዱልኛል፡፡ በአጠቃላይ ከእኔም ቤተሰብ አልፎ ወሎ ስሄድ የማየው የክርስቲያኑና የሙስሊሙ ፍቅርና ተቻችሎ መኖር እንዴት ያስቀናል መሰላችሁ!!! ቤተ ክርስቲያን ሲሠራ ሙስሊሞቹ በገንዘብም በጉልበትም ሲረዱ በዓይኔ ተመልክቻለሁ፡፡ መስጂድም ሲሠራ ሕዝበ ክርስቲያኑ አብሮ ከሙስሊሞች ጋር ሠርቷል፡፡
ነገር ግን ይህ እጅግ ያስቀና የነበረው የክርስቲያኑና የሙስሊሙ ፍቅርና መተሳሰብ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየደበዘዘና መጥፎ ጥላ እያጠላበት መጥቷል፡፡

ባለፈው መስከረም ወር ላይ ግሸን ማርያም ደርሼ በዚያው ቤተሰቦቼን ጠይቄ እስከ ቦረና አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫና አባ ጽጌ ድንግል ገዳማት ድረስ በእግሬ ለ7 ሰዓት ተጉዤ ሄጄ ነበር፡፡ አጎቴ ሼህ እንድሪስ ምን አሉኝ መሰላችሁ? "እናንተ ከከተማ የምትመጡ ልጆቻችንኮ ልታስቀምጡን አልቻላችሁም" አሉኝ፡፡ ሼኹን ለምን እንዲህ እንዳሉ ስጠይቃቸው ወደ ዐረብ ሀገራት ሄደው የተመለሱ የሙስሊም ወንዶች ልጆቻቸው ጉዳይ በጣም እንዳሳሰባቸው ነገሩኝ፡፡ ምክንያቱም ሁሉም ከዐረብ ሀገራት የተመለሱት ልጆቻቸው በዚያ በሰፈራቸው ክርስቲያኖች መኖር የለባቸውም የሚል ጽኑ አቋም አላቸው፡፡ ዕድሜ ጠገብ ቃልቻዎችንና ሼኾችን "እናንተ ሙስሊም አይደላችሁም" ይሏቸዋል፡፡ የዋሐቢዝምን ጽንፈኛ አቋም ካላራመዱ ማለትም ከክርስቲያኖች ጋር ቡና ከጠጡና በችግርና በደስታ ከተረዳዱ ሙስሊም እንዳልሆኑ ይነግሯቸዋል፡፡ ወጣቶችን እየሰበሰቡ ጥላቻን ይሰብኳቸዋል፡፡ ሲመክሩ ውለው የሚያድሩት እስልምናን በኃይል ስለማስፋፋትና ክርስቲያኖችን ስለማጥፋት ነው፡፡ ዕድሜ ጠገብ ቃልቻዎቹና ሼኾቹ ደግሞ በዚህ ፈጽሞ አይስማሙም፡፡ "እንደቀድሞው ተዋደንና ተቻችለን እንኖራለን" የሚል ጽኑ አቋም አላቸው፡፡ አጠቃላይ የወጣቶቹ ሙስሊሞች ሁኔታቸው ሼህ እንድሪስንም ሆነ ሌሎቹን ታላላቅ ሽማግሌዎች በጣም አሳስቧቸዋል፡፡ እነሱ ካለፉ በኃላ ተረካቢውና መጪው ትውልድ ያስፈራቸዋል፡፡

ሼኹ እውነታቸውን ነው፡፡ እኔም በዘዴ ቀርቤ የዋሐቢዝምን ጽንፈኛ አቋም የሚያራምዱ ሙስሊም ወጣቶችን ሳናግራቸው የሰጡኝ መልስ እውነትም አስፈሪ ነው፡፡ "ክርስቲያኖችን እናጠፋለን ኢትዮጵያንም እንገዛለን" የሚል ጽኑ አቋም አላቸዉ፡፡ እኔ በዚያው ቦረና ወግዲ አባ ጽጌ ድንግል ገዳም ስሄድ ያየሁትን ልንገራችሁ፡፡ መነኮሳቱ ከገዳሙ ወጥተው ገበያ እንኳን መሄድ አይችሉም፡፡ ሲሄዱ ጠብቀው መንገድ ላይ በድንጋይ ይመቷቸዋል፡፡ ሴቶቹ መነኮሳት ብቻቸውን ወደ ወንዝ ወርደው ውኃ መቅዳት አይችሉም ምክንያቱም የመደፈር አደጋ ላይ ይወድቃሉ፡፡

ውድ ሙስሊም ወገኖቻችን፡- ሰሞኑን የISIS ጽንፈኛ ኢስላማዊ አሸባሪ በክርስቲያኖች ላይ የፈጸመውን እጅግ ዘግናኝ ድርጊት ከልብ አውግዛችሁ ቂርቆስ ሰፈር የታረዱት ሰማዕታት ቤተሰቦች ዘንድ መጥታችሁ አብራችሁን ስታለቅሱ አይቻለሁ፡፡ ምስጋናዬንና አድናቆቴን ሳልገልጽ አላልፍም፡፡ ግን በተቃራኒው ዋሐቢዝምን የሚያራምዱ ልጆቻችሁ በዘመናዊው መገናኛዎች አማካኝነት "እሰይ ታረዱ" ሲሉ እያየናቸውና እየሰማናቸው ነው፡፡ በየፌስቡኩ አስተያየታቸው ላይ አንድ ሙስሊም እንኳን "አላህ ነፍሳቸውን ይማር" ብሎ ምኞቱን የገለጸ የለም፡፡ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ባገኘነው መረጃ መሠረት "ሀዘናችንን በጋራ እንግለጽ ድርጊቱንም በጋራ እናውግዝ" ተብሎ ለሁለቱም እምነቶች በየዩኒቨርሲዎቹ ግቢ ውስጥ በተዘጋጀው መርሀግብር ላይ ሙስሊም ተማሪዎች አልተገኙም፡፡ ይህ ምን ማለት እንደሆነ መገመት ይቻላል፡፡ እኔ ግን የድርጊቱ ደጋፊዎች መሆናቸውን ነው የምረዳው፡፡ በየዩኒቨርሲዎቹ ግቢ ውስጥ ሙስሊሙና ክርስቲያኑ ተማሪ በጠላትነት ነው የሚተያየው፡፡ ይህንንም ከዩኒቨርሲዎች የወጣን ሁላችን በተግባር አይተነዋል፡፡ በአንድ ትልቅ የመንግሥት መ/ቤት ውስጥ አብሮኝ የሚሠራ ሙስሊም ጓደኛዬም ከዚህ በፊት እነ አልቃይዳ እውነኛዎቹ ሙስሊሞች እነርሱ መሆናቸውን ሽንጡን ገትሮ ሲከራከረኝ ነበር፡፡

ወደ መፍትሄው እንምጣ........
ውድ ሙስሊም ወገኖቻችን! እንደቀድሞው እንዳማረብን እንዴት ተከባብረንና ተዋደን እንኑር??? መፍትሄው ቀላል ነው፡፡ ይሄኛው መልዕክት መንግሥትም ይመለከታልና ባለሥልናት ሁላችሁ ስሙ፡፡ መንግሥት እንኳን ለህልውናህ ስትል ሳትወድም ቢሆን በግድ ትሰማለህ ንጹሐን ሙስሊም ወገኖቻችን ግን የድሮውን መዋደድና መተሳሳብ ብሎም መቻቻል እንዳለ ይዘን መቀጠል ከተፈለገ ለጉዳዩ አጽንኦት በመስጠት ችግሩን በግልጽ መነጋገር አለብን፡፡
የችግሩ የመጀመሪያው መፍትሔ ችግሩ መኖሩን አምነን እንቀበል! የአጎቴ የሼህ እንድሪስ ሀሳብ በጣም ትክክል ነው፡፡ ዋሐቢዝምን የሚያራምዱ "አዳዲስ ዘመነኛ ሙስሊሞች" የነገዎቹ አልቃይዳዎችና ISISዎች ናቸው፡፡ እኔ በዚህ 101% እርግጠኛ ነኝ! በየመስጂዱ ውስጥ ለወጣቶቹ ሙስሊሞች ምን ዓይነት ሥልጠናና ትምህርት እንደሚሰጥ እኔው ራሴ እምነቱ ውስጥ በነበርኩበት ወቅት ያየሁትንና የተማርኩትን ነው እየመሰከርኩ ያለሁት፡፡ መንግሥት ሆይ! ንጹሐን ሙስሊም ወገኖቻችን ሆይ! ችግሩን በየሚዲያው በቀን ሺህ ጊዜ "ISIS እስልምናን አይወክልም" በሚል ፉከራና ሽለላ ችግሩን መቅረፍ እንደማይቻል እመኑ፡፡ ጥቂት የማይባሉ የነገዎቹ አልቃይዳዎችና ISISዎች በሀገራችን ሞልተዋል፡፡
በኢትዮጵያ ውስጥ የሩቁን ትተን በቅርቡ በጂማ፣ በስልጤ፣ በኢሉባቡርና በሌሎቹም ክልሎች ጽንፈኛና አክራሪ ሙስሊሞች ቤተ ክርስትያን ውስጥ እየገቡ በጸሎት ላይ የነበሩትን ክርስቲያኖች በገጀራ ሲቆራርጧቸው ያኔ isis አይታወቅም ነበርኮ! "isis የትኛውንም ሃይማኖት አይወክልም" የሚል ባዶ ፉከራ እያሰማችሁ የምታጃጅሉን ለምንድነው? ክርስቲያኖችን በገጀራ እየቆራረጠ ቤ/ክንን ሲያቃጥል ደነበረው ያ ሁሉ ኢትዮጵያዊ ሙስሊም ከነ ገጀራው ማንን ነበር የሚወክለው? የዛኔ የትኛው ሙስሊም ነው በአደባባይ ወጥቶ እኛን አይወክልም ያለው? የisis ዘግናኝ ድርጊት እኛ ሀገር ከተጀመረ ቀየኮ!
isis ዛሬ የፈጸመው አረመኒያዊና እጅግ ዘግናኝ ተግባር በዓይነቱም ሆነ በይዘቱም ከዚ በፊት በሀገራችን ከተፈጸመው ጋር ምንም ልዩነት የለውም። "እውነኛዎቹ ሙስሊሞች እነ አልቃይዳ ናቸው" ያለኝ ያ የመንግሥት መ/ቤት ጓደኛዬ ሁኔታዎች ቢመቻቹለትና አጋጣሚውን ቢያገኝ እኔንም አጋድሞ እንደሚያርደኝ እርግጠኛ ነኝ፡፡ በየገጠሩ ያሉ ጽንፈኛ አክራሪዎች ሁኔታዎች በተመቻቹላቸው ጊዜ ምን እንዳደረጉ አይተናል፡፡
ኢትዮጵያው ውስጥ የሚገኙ ሙስሊም መምህራን በተለያየ ጊዜ የአመጽ ቅስቀሳ ሲያደርጉ የተቀረጸውን ቪዲዮ ማየት እንችላለን፡- "በዚህ ማንም ክርስቲያን አንገቱን ቀና አድርጎ አይሄድም፡ በሜንጫ ነው አንገታቸውን የምንላቸው" "ኪዳነ ምሕረት ቤ/ክንን እናቃጥላታለን..." ሲሉ የነበሩ አመጸኛ አክራሪዎች አጋጣሚውን ቢያገኙና ሁኔታዎች ቢመቻቹላቸው የተናገሩትን ተግባራዊ ማድረጋቸው አይቀርም፡፡ ደግሞም ተግባራዊ አድርገውት አሳይተውናል፡፡

እውነታውን አንሸፋፍን! የመጀመሪያው መፍትሔ ይሄ ነው፡፡ ጉዳዩ የማይመለከታችሁ ንጹሐን ሙስሊም ወገኖቻችንና መንግሥት ችግሩን አምናችሁ ተቀበሉና ወደ መፍትሔው በጋራ እንምጣ፡፡ ዝም ብሎ በአፍዓ ብቻ አክራሪነትን እንቃወም ማለት ብቻ ሳይሆን በሀገራችን ያሉ አክራሪዎቻችንን በተግባርም እንቃወማቸው፡፡ የጽንፈኛዎቹን እንቅስቃሴዎቻቸውን ተከታትሎ ለሕዝብ ይፋ ማድረግና ግለሰቦቹንም ለይቶ መረጃ አጠናክሮ ለሕግ ማቅረብ ቀጣዩ ተግባር ይሁን፡፡ ንጹሐን ሙስሊም ወገኖቻችን ይህን ማድረግ ስትችሉ ነው isis እንደማይወክላችሁ የምናውቀው፡፡ "isis እስልምናን አይወክልም" ስትሉን ሳይሆን "እኛ የ isis ን ድርጊት እንጸየፋለን" ስትሉን ነው የምናምናችሁ፡፡ እናንተ የጽፈኛ አሸባሪዎችን ድርጊት በጽኑ የምትቃወሙ መሆናችሁን በተግባር አሳዩን እንጂ ጽፈኛ አሸባሪዎቹን እስልምናን አይወክልም አትበሉን፡፡ ጽንፈኛ ኢስላማዊ አሸባሪዎቹ "ክርስቶስን ክዳችሁ አላህን ብቻ አምልኩ..." እያሉ ነው ሰማዕታት ወንድሞቻችን ያረዱብን፡፡ ሰያፊዎቹ ቢያንስ እነሱ ለራሳቸው ሙስሊሞች ናቸው እናንተ በግድ "ሙስሊም አይደላችሁም እስልምናንም አትወክሉም" ልትሏቸው አትችሉም፡፡ እነሱ ሃይማኖት ለአላህ ብቻ እስከሚሆን ድረስ ነው እየገደሉና እያረዱ ያሉት፡፡

ስለዚህ ንጹሐን ሙስሊም ወገኖቻችን ፖለቲካኛውን አስተሳሰብና አነጋገር ተውትና በጎረቤትኛና በዘመድኛ አስተሳሰብ እንተሳሰብ፡፡ በፍቅርና በመውደድኛ ቋንቋ እንነጋገር፡፡ "isis እስልምናን አይወክልም" ስትሉን ሳይሆን "እኛ የ isis ን ድርጊት እንጸየፋለን" ስትሉን ነው የምናምናችሁ፡፡ እናንተ የጽፈኛ አሸባሪዎችን ድርጊት በጽኑ የምትቃወሙ መሆናችሁን በተግባር አሳዩን እንጂ ጽንፈኛ አሸባሪዎቹን እስልምናን አይወክልም አትበሉን፡፡ የድርጊቱ ፈጻሚዎች ተጸየፏቸውና ተቃውሞአችሁን አብራችሁን ሆናችሁ በተግባር አሳዩን፡፡ አቤት ያኔ ፍቅራችን ሲደረጅ........

መልዕክት ሁለት-ለክርስቲያን እኅት ወንድሞቼ፡- ከዚህ ከሊቢያው ሰማዕታት ወንድሞቻችን ምን ተማርን??? የትኛውም ሐዋርያ በክብር ዐረፈ የሚል ገድል የለውም፡፡ ሁሉም ሐዋርያት "ተዘቅዝቆ ተሰቀለ፡ አንገቱን በሰይፍ ተቆረጠ፡ በእሳት ተቃጠለ፡ ቆዳው ተገፈፈ..." የሚል ገድል ነው ያላቸው፡፡ ሰማዕታት ሁሉ በሐዋርያት መንገድ ተጉዘው ሰማዕትነታቸውን ፈጸሙ፡፡ በስንክሳሩ መጽሐፍ ላይ ስናነበው የኖርነውን የሐዋርያትንና የሰማዕታትን ታሪክ ወንድሞቻችን ዛሬ በዚህ በ21ኛው ክፍለ ዘመንም በተግባር አሳዩን፡፡ ወንጌልን በተግባር ሰበኩልን፡፡ ክርስቶስን ክደው የአንገታቸውን ክር በጥሰው ቢሆን ኖሮ ማንም አይነካቸውም ነበር፡፡ ሦስት ቀን ሙሉ በረኀብ አሠቃይተዋቸው እስከ መጨረሻው ድረስ በጽናት ቆይተው አንገታቸውን በጸጋ ለሰይፍ ሲሰጡ ስናይ ከጥልቅ ሀዘን ባለፈ ምን ተሰማን በእውነት!?
እኛስ በቃል ሰይፍ ብቻ ታርደን የክብር ባለቤት መድኀኔዓለም ክርስቶስን የካድን ስንቶቻችን እንሆን?
አንድ ዐይን ያለው ሰው በአፈር አይጫወትም፡፡ ሐዋርያው "ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለተሰጠች አንዲት ሃይማኖት እንድትጋደሉ እየመከርኋችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ" ያለው ለዚህ ነው፡፡ ይሁ 1፡3፡፡ ሞት እንደሆነ ሰው በዝሙት ይሞታል፡ በመኪና አደጋ ይሞታል፡ በትንታ ወይም የሚበላው እህል አንቆትም ይሞታል፡፡ ምን!... በኃጢአት ላይ ኃጢአት ለመጨመርና እህል ለማመላለስ ተኖረ አልተኖረ!....፡፡ ክርስቶን እንዲህ ሞቱን በሚመስል ሞት አክብሮ ሰማዕት ሆኖ መሞት ምንኛ መታደል ነው!!! ሰማዕታት ወንድሞቻችን ዛሬ ክርስቶስን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ተባብረውት በእቅፉ ውስጥ ናቸው፡፡ ክርስቶስን በሞታቸው ያከበሩት የሰማዕታቶቻችን በረከታቸው ይደርብን በእውነት!!! አባቶችን በገዳም ሰማዕታትን በደም ያጸና አምላክ እኛንም በሃይማኖት በምግባር ያጽናን!

ታስታውሳላችሁ አይደል አሁን በወጣቱ ዘንድ ያለውን የክርስትናውን መነቃቃት የተፈጠረው በበሻሻ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በተሰየፋ ክርስቲያኖች አማካኝነት ነው፡፡ ዛሬም እነዚህ 30 የሊቢያ ሰማዕታት ወንድሞቻችን የለኮሱት የእምነት ችቦ በእያንዳንዳችን ልብ ውስጥ እየተቀጣጠለ ክርስትናችንን በዓለም ዙሪያ አጠንክሮ እንደሚያስፋፋው ሳይታለም የተፈታ ነው!!! ነገር ግን አካሄዳችን ሁሉ በፍጹም ፍቅርና በትዕግስት ይሁን፡፡ ለሙስሊም ወገኖቻችን ፍቅር እንስጥ፡፡ እንደቀድሞው ተዋደንና ተቻችለን እኑር፡፡ በፍቅር የሚሞትለት አንጂ በጥላቻ የሚገደልለት አምላክ እንደሌለን ፍቅር ሰጥተን እናሳያቸው፡፡ በቀል የእኔ ነው ያለ አምላካችን ለእኛ ግን "ጠላቶቻችሁን ውደዱ" የሚል መመሪያ ነው የሰጠን!!!

መልዕክት ሦስት-ለቤተ ክህነትና ለቤተ መንግሥት፡- እግዚአብሔር አምላክ ከሁለቱም ወገን በአንድ ጊዜ ቀንድ ቀንዱን ነቅሎ ሲወስድ አይታችሁ ያልተማራችሁ አሁን ሰው ነግሯችሁ ልትሰሙ ስለማትችሉ ምንም አልልም! ዝምምምም.....

ohhh ሙስሊሞች አንድ የረሳኃት መልዕክት ትዝ አለችኝ! ጀማል የሚባል ልጅ አብሮ ተሰይፏል እያላችሁ ነው መረጃ ግን አልተገኘም፡፡ እስቲ ቤተሰቦቹን ጠቁሙንና አብረን ሄደን እናስተዛዝን??? እስካሁን ጀማል የሚባል የተሰየፈ ከሌለ ግን ምናልባት ወደፊት እኔ ተሰይፌ ያኔ "ካፊሩ ጀማል ተሰየፈ" የምትሉበት ጊዜ ከመጣ እሰየው ነው!

Saturday, April 25, 2015

የኢስላሚክ ስቴት ሽብርተኛ ቡድን የሚያርደው የእስልምና መርህ ያልተቀበሉትን ወይም በትክክል የማይፈፅሙትን ሁሉ ነው!

በኢትዮጵያ ውስጥ እስላሙ ከክርስቲያኑ ጋር ተስማምቶ ለዘመናት ኖሯል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን በኢትዮጵያችን ያልታየ ኢስላማዊ ጠባዮች "የኒቃብ:ጂልባብና ሂጃብ ነው ውበቴ" መፈክር መሰማት የጀመረው ኢትዮጵያዊው ሙስሊም ከሃይማኖታዊ ህጉ ጋር በጣም ቅርርብ በመጀመሩና በተግባር ወደማሳየት በመሸጋገሩ እንጂ ቀድሞውኑ በትእዛዝ ስላልተሰጠው አልነበረም። እንደዚሁ ሁሉ ኢትዮጵያዊ ባህልና ወግ ወደፅንፍ እንዳይሄድ ስላቆየውና ሃይማኖታዊ እውቀቱ ወደአዲሱ የማክረር ድርጊት ስላልመራው እንጂ ስላልተፃፈለት አይደለም። በአሁኑ ሰአት በተለይ ወጣቱ ሙስሊም ከቁርአን እና ከመሀመድ ሱና መጻሕፍት ማለትም ( ሳሂህ አልቡካሪ 93 ምእራፍ ያለው: ሳሂህ ሙስሊም 43 ምእራፍ ያለው: ሱናን አቡዳውድ 41 ምእራፍ ያለው: ማሊክስ ሙዋትዋ 61 ምእራፍ ያለያላቸውና ከ6 ሺህ በላይ አንቀፆችን አንብበው ወደተግባር ሲገቡ የሚመጣው ውጤት አይ፣ ኤስ IS መምሰል ነው። እውነቱ እሱ ነው። ከእስልምና ወደክርስትና የተመለሰው " ሳም ሻሙን" ለአይ፣ ኤስ መነሻና አራጅነት ምክንያቶችን በእንግሊዝኛ በመረጃ አስደግፎ እንዲህ አብራርቶታል። "ከባለቤቱ ያወቀ ቡዳ ነው እንዲሉ"
 Sam Shamoun

The Quran commands Muslims to fight all unbelievers:

Fight those who believe not in God nor the Last Day, nor hold that forbidden which hath been forbidden by God and His Apostle, nor acknowledge the religion of Truth, (even if they are) of the People of the Book, until they pay the Jizya with willing submission, and feel themselves subdued. S. 9:29

The above emphatically exhorts Muslims to conquer the following groups of people until they pay a sum of money (Jizya) as a sign of their subjection and humiliation:

Atheists/Agnostics (those who believe not in God nor the Last Day).
Jews and Christians (people of the Book).
Everyone else, whether Hindus/ Magians, Buddhists etc., since these groups do not prohibit what Muhammad forbade nor believe in Islam, the so-called "religion of Truth".
Please note that the passage does not limit the taking of Jizya from the Jews and Christians; it clearly says that the Jizya is to be extracted from all of the subjugated groups that are listed, i.e. those who do not believe in Allah and the last day, or forbid what Muhammad forbade etc.

To say, as some try do, that this verse is referring only to the Jews and Christians makes absolutely no sense when we note that these groups believe in Allah and the last day, just as the Quran testifies:

And dispute ye not with the People of the Book, except with means better (than mere disputation), unless it be with those of them who inflict wrong (and injury): but say, "We believe in the revelation which has come down to us and in that which came down to you; Our God and your God is one; and it is to Him we bow (in Islam)." S. 29:46

Those who believe (in the Qur'an), those who follow the Jewish (scriptures), and the Sabians and the Christians, - any who believe in God and the Last Day, and work righteousness, - on them shall be no fear, nor shall they grieve. S. 5:69, cf. 2:62

This last reference presupposes that Jews and Christians are among those who believe in Allah and the last day. How, then, can the Jews and Christians be listed with those who do not believe in the existence of God and the final judgment? Doesn’t this make it rather obvious that the Quran has some other group in view besides the Jews and Christians from whom Jizya can be extracted?

This, perhaps, explains why Muslim leaders such as Umar ibn al-Khattab took Jizya from the Persians even though they were labeled pagans, specifically al-mushrikeen or those who ascribe partners with Allah:

Narrated Jubair bin Haiya:

'Umar sent the Muslims to the great countries to fight the pagans. When Al-Hurmuzan embraced Islam, 'Umar said to him, "I would like to consult you regarding these countries which I intend to invade." Al-Hurmuzan said, "Yes, the example of these countries and their inhabitants who are the enemies of the Muslims, is like a bird with a head, two wings and two legs; If one of its wings got broken, it would get up over its two legs, with one wing and the head; and if the other wing got broken, it would get up with two legs and a head, but if its head got destroyed, then the two legs, two wings and the head would become useless. The head stands for Khosrau, and one wing stands for Caesar and the other wing stands for Faris. So, order the Muslims to go towards Khosrau." So, 'Umar sent us (to Khosrau) appointing An-Nu’man bin Muqrin as our commander. When we reached the land of the enemy, the representative of Khosrau came out with forty-thousand warriors, and an interpreter got up saying, "Let one of you talk to me!" Al-Mughira replied, "Ask whatever you wish." The other asked, "Who are you?" Al-Mughira replied, "We are some people from the Arabs; we led a hard, miserable, disastrous life: we used to suck the hides and the date stones from hunger; we used to wear clothes made up of fur of camels and hair of goats, and to worship trees and stones. While we were in this state, the Lord of the Heavens and the Earths, Elevated is His Remembrance and Majestic is His Highness, sent to us from among ourselves a Prophet whose father and mother are known to us. Our Prophet, the Messenger of our Lord, has ordered us to fight you till you worship Allah Alone or give Jizya (i.e. tribute); and our Prophet has informed us that our Lord says:-- "Whoever amongst us is killed (i.e. martyred), shall go to Paradise to lead such a luxurious life as he has never seen, and whoever amongst us remain alive, shall become your master." (Al-Mughira, then blamed An-Nu’man for delaying the attack and) An-Nu'man said to Al-Mughira, "If you had participated in a similar battle, in the company of Allah's Apostle he would not have blamed you for waiting, nor would he have disgraced you. But I accompanied Allah’s Apostle in many battles and it was his custom that if he did not fight early by daytime, he would wait till the wind had started blowing and the time for the prayer was due (i.e. after midday)." (Sahih al-Bukhari, Volume 4, Book 53, Number 386)

Now lest a Muslim say that the Persians were also classified as being from the people of the book note the following text:

And this is a Book which We have revealed as a blessing: so follow it and be righteous, that ye may receive mercy: Lest ye should say: "The Book was sent down to two Peoples before us, and for our part, we remained unacquainted with all that they learned by assiduous study:" S. 6:155-156

The two peoples mentioned here are the Jews and Christians:

(Lest ye should say) so that you will not say, O people of Mecca, on the Day of Judgement: (The Scripture was revealed only to two sects) the people of two religions (before us) i.e. the Jews and Christians, (and we in sooth were unaware) ignorant (of what they read) their reading of the Torah and the Gospel; (Tanwîr al-Miqbâs min Tafsîr Ibn ‘Abbâs; source)

We have revealed it, lest you should say, 'The Scripture was revealed only upon two parties - the Jews and the Christians - before us and we (in has been softened, its noun omitted, in other words [read as] inna) indeed have been unacquainted with their study', their reading [of the scripture], not knowing any of it, since it is not in our own language. (Tafsir al-Jalalayn; source)

Clearly, the Quran doesn’t include anyone other than the Jews and Christians as the people of the book since they were the only ones who were given the book from Allah. Therefore, if the Quran were limiting the taking of Jizya to the people of the book then Muhammad violated the orders of his own scripture by permitting the Persians to pay it since they are not part of this group.

In fact, Muhammad himself is reported to have permitted his followers to take Jizya from the pagans/polytheists:

Chapter 2: APPOINTMENT OF THE LEADERS OF EXPEDITIONS BY THE IMAM AND HIS ADVICE TO THEM ON ETIQUETTES OF WAR AND RELATED MATTERS

It has been reported from Sulaiman b. Buraid through his father that when the Messenger of Allah (may peace be upon him) appointed anyone as leader of an army or detachment he would especially exhort him to fear Allah and to be good to the Muslims who were with him. He would say: Fight in the name of Allah and in the way of Allah. Fight against those who disbelieve in Allah. Make a holy war, do not embezzle the spoils; do not break your pledge; and do not mutilate (the dead) bodies; do not kill the children. When you meet your enemies who are polytheists, invite them to three courses of action. If they respond to any one of these, you also accept it and withhold yourself from doing them any harm. Invite them to (accept) Islam; if they respond to you, accept it from them and desist from fighting against them. Then invite them to migrate from their lands to the land of Muhajirs and inform them that, if they do so, they shall have all the privileges and obligations of the Muhajirs. If they refuse to migrate, tell them that they will have the status of Bedouin Muslims and will be subjected to the Commands of Allah like other Muslims, but they will not get any share from the spoils of war or Fai' except when they actually fight with the Muslims (against the disbelievers). If they refuse to accept Islam, demand from them the Jizya. If they agree to pay, accept it from them and hold off your hands. If they refuse to pay the tax, seek Allah’s help and fight them. When you lay siege to a fort and the besieged appeal to you for protection in the name of Allah and His Prophet, do not accord to them the guarantee of Allah and His Prophet, but accord to them your own guarantee and the guarantee of your companions for it is a lesser sin that the security given by you or your companions be disregarded than that the security granted in the name of Allah and His Prophet be violated. When you besiege a fort and the besieged want you to let them out in accordance with Allah’s Command, do not let them come out in accordance with His Command, but do so at your (own) command, for you do not know whether or not you will be able to carry out Allah’s behest with regard to them. (Sahih Muslim, Book 019, Number 4294)

All of this presupposes that Islam permits the existence of other religions and worldviews under its umbrella, provided that those who embrace such beliefs are willing to pay Jizya.

This may account for why the following Muslim scholar believed that Q. 9:29 refers to all disbelieving groups, not just to Jews and Christians:

Verse 28 appearing earlier referred to Jihad against the Mushriks of Makkah. The present verses talk about Jihad against the People of the Book. In a sense, this is a prelude to the battle of Tabuk that was fought against the People of the Book. In Tafsir al-Durr al-Manthur, it has been reported from the Quran commentator, Mujahid that these verses have been revealed about the battle of Tabuk. Then, there is the reference to ‘those who were given the Book’. In Islamic religious terminology, they are referred to as ‘ahl al-Kitab’ or People of the Book. In its literal sense, it covers every disbelieving group of people who believe in a Scripture but, in the terminology of the Holy Quran, this term is used for Jews and Christians only - because, only these two groups from the People of the Book were well-known in and around Arabia. Therefore, addressing the Mushriks of Arabia, the Holy Quran has said…

lest you should say, "The Book was sent down only upon two groups before us, were ignorant of what they studied." – 6:156

As for the injunction of Jihad against the People of the Book given in verse 29, it is really not particular to the People of the Book. The fact is that this very injunction applies to all disbelieving groups - because, the reasons for the injunction to fight mentioned next are common to all disbelievers. If so, the injunction has to be common too. But, the People of the Book were mentioned here particularly to serve a purpose…

Regarding the instruction given in this verse that once these people have agreed to pay jizyah, fighting should be stopped, a little explanation may be useful. According to the majority of Muslim jurists, it includes all disbelievers – whether from the People of the Book or from those other than them. However, the Mushriks of Arabia stand excluded from it for jizyah was not accepted from them. (Mufti Shafi Usmani, Maariful Quran, Volume 4, pp. 360-361, 365; source; bold and underline emphasis ours)

But this contradicts other passages of the Quran, as well as specific Islamic narratives, which demand that those who claim that Allah has a son or that he has co-equal partners must convert to Islam or die:

And an announcement from God and His Apostle, to the people (assembled) on the day of the Great Pilgrimage,- that God and His Apostle dissolve (treaty) obligations with the Pagans (al-mushrikeen- literally, those who associate partners with God). If then, ye repent, it were best for you; but if ye turn away, know ye that ye cannot frustrate God. And proclaim a grievous penalty to those who reject Faith. (But the treaties are) not dissolved with those Pagans (al-mushrikeen) with whom ye have entered into alliance and who have not subsequently failed you in aught, nor aided any one against you. So fulfil your engagements with them to the end of their term: for God loveth the righteous. But when the forbidden months are past, then fight and slay the Pagans (al-mushrikeen) wherever ye find them, an seize them, beleaguer them, and lie in wait for them in every stratagem (of war); but if they repent, and establish regular prayers and practise regular charity, then open the way for them: for God is Oft-forgiving, Most Merciful. If one amongst the Pagans (al-mushrikeen) ask thee for asylum, grant it to him, so that he may hear the word of God; and then escort him to where he can be secure. That is because they are men without knowledge… O ye who believe! Truly the Pagans (al-mushrikoon) are unclean; so let them not, after this year of theirs, approach the Sacred Mosque. And if ye fear poverty, soon will God enrich you, if He wills, out of His bounty, for God is All-knowing, All-wise… The Jews call 'Uzair a son of God, and the Christians call Christ the son of God. That is a saying from their mouth; (in this) they but imitate what the unbelievers of old used to say. God's curse be on them: how they are deluded away from the Truth! They take their priests and their anchorites to be their lords in derogation of God, and (they take as their Lord) Christ the son of Mary; yet they were commanded to worship but One God: there is no god but He. Praise and glory to Him: (Far is He) from having the partners they associate (yushrikoon) (with Him). Fain would they extinguish God's light with their mouths, but God will not allow but that His light should be perfected, even though the Unbelievers may detest (it). It is He Who hath sent His Apostle with guidance and the Religion of Truth, to proclaim it over all religion, even though the Pagans may detest (it). S. 9:3-6, 28, 30-33

The foregoing plainly states that:

Muslims must fight and slay al-mushrikeen wherever they find them unless they repent and convert to Islam.
Al-mushrikeen are unclean and therefore cannot approach the sacred mosque, that is the Kaba in Mecca.
Jews and Christians are al-mushrikeen because they ascribe partners with God, i.e. Jews believe that Ezra is God’s son and that their rabbis are lords besides God, whereas the Christians profess that Jesus is the Son of God and that he and the Christian monks are lords in place of God.
What this basically implies is that Muslims must fight and slay the Jews and Christians until they repent and become Muslims. The hadith literature provides substantiation for our exegesis since it quotes Muhammad as saying that he was ordered to fight the people, not just the Meccans, until they become Muslims:

Narrated Ibn ‘Umar:

Allah's Apostle said: "I have been ordered (by Allah) to fight against the people until they testify that none has the right to be worshipped but Allah and that Muhammad is Allah's Apostle, and offer the prayers perfectly and give the obligatory charity, so if they perform a that, then they save their lives an property from me except for Islamic laws and then their reckoning (accounts) will be done by Allah." (Sahih al-Bukhari, Volume 1, Book 2, Number 24)

Narrated Anas bin Malik:

Allah's Apostle said, "I have been ordered to fight the people till they say: ‘None has the right to be worshipped but Allah.’ And if they say so, pray like our prayers, face our Qibla and slaughter as we slaughter, then their blood and property will be sacred to us and we will not interfere with them except legally and their reckoning will be with Allah." Narrated Maimun ibn Siyah that he asked Anas bin Malik, "O Abu Hamza! What makes the life and property of a person sacred?" He replied, "Whoever says, ‘None has the right to be worshipped but Allah’, faces our Qibla during the prayers, prays like us and eats our slaughtered animal, then he is a Muslim, and has got the same rights and obligations as other Muslims have." (Sahih al-Bukhari, Volume 1, Book 8, Number 387)

Chapter 9: COMMAND FOR FIGHTING AGAINST THE PEOPLE SO LONG AS THEY DO NOT PROFESS THAT THERE IS NO GOD BUT ALLAH AND MUHAMMAD IS HIS MESSENGER

It is narrated on the authority of Abu Huraira that when the Messenger of Allah (may peace be upon him) breathed his last and Abu Bakr was appointed as his successor (Caliph), those amongst the Arabs who wanted to become apostates became apostates. 'Umar b. Khattab said to Abu Bakr: Why would you fight against the people, when the Messenger of Allah declared: I have been directed to fight against people so long as they do not say: There is no god but Allah, and he who professed it was granted full protection of his property and life on my behalf except for a right? His (other) affairs rest with Allah. Upon this Abu Bakr said: By Allah, I would definitely fight against him who severed prayer from Zakat, for it is the obligation upon the rich. By Allah, I would fight against them even to secure the cord (used for hobbling the feet of a camel) which they used to give to the Messenger of Allah (as zakat) but now they have withheld it. Umar b. Khattab remarked: By Allah, I found nothing but the fact that Allah had opened the heart of Abu Bakr for (perceiving the justification of) fighting (against those who refused to pay Zakat) and I fully recognized that the (stand of Abu Bakr) was right. (Sahih Muslim, Book 001, Number 0029)

It is reported on the authority of Abu Huraira that the Messenger of Allah said: I have been commanded to fight against people so long as they do not declare that there is no god but Allah, and he who professed it was guaranteed the protection of his property and life on my behalf except for the right affairs rest with Allah. (Sahih Muslim, Book 001, Number 0030)

It is narrated on the authority of Jabir that the Messenger of Allah said: I have been commanded that I should fight against people till they declare that there is no god but Allah, and when they profess it that there is no god but Allah, their blood and riches are guaranteed protection on my behalf except where it is justified by law, and their affairs rest with Allah, and then he (the Holy Prophet) recited (this verse of the Holy Qur'an): "Thou art not over them a warden" (lxxxviii, 22). (Sahih Muslim, Book 001, Number 0032)

It has been narrated on the authority of Abdullah b. 'Umar that the Messenger of Allah said: I have been commanded to fight against people till they testify that there is no god but Allah, that Muhammad is the messenger of Allah, and they establish prayer, and pay Zakat and if they do it, their blood and property are guaranteed protection on my behalf except when justified by law, and their affairs rest with Allah. (Sahih Muslim, Book 001, Number 0033)

And:

And he (peace and blessings of Allaah be upon him) said: "I have been sent just before the Hour with the sword, so that Allaah will be worshipped ALONE with no partner or associate." Narrated by Ahmad, 4869; classed as saheeh by al-Albaani in Saheeh al-Jaami', 2831. (Question No. 34647: The reason why jihaad is prescribed; source; capital and underline emphasis ours)

Thus, even Jews and Christians, not just the Arab pagans, had to convert to Islam otherwise Muslims would have to kill them as well if they didn’t.

This further implies that Jews and Christians could not approach Mecca since, being al-mushrikeen, they are unclean. We again find the hadiths substantiating this very point:

Narrated Ibn 'Umar:
Umar expelled the Jews and the Christians from Hijaz. When Allah's Apostle had conquered Khaibar, he wanted to expel the Jews from it as its land became the property of Allah, His Apostle, and the Muslims. Allah's Apostle intended to expel the Jews but they requested him to let them stay there on the condition that they would do the labor and get half of the fruits. Allah’s Apostle told them, "We will let you stay on thus condition, as long as we wish." So, they (i.e. Jews) kept on living there until 'Umar forced them to go towards Taima' and Ariha'. (Sahih al-Bukhari, Volume 3, Book 39, Number 531)

It has been narrated by 'Umar b. al-Khattab that he heard the Messenger of Allah (may peace be upon him) say: I will expel the Jews and Christians from the Arabian Peninsula and will not leave any but Muslim. (Sahih Muslim, Book 019, Number 4366)

To summarize the contradictions:

Q. 9:29 along with certain Islamic narrations teach that Muslims are to fight all the unbelievers until they pay the Jizya and feel subdued. This presupposes that Islam allows even pagans to live under Muslim rule without having to convert to the Islamic faith.
Q. 9:1-6, 28, 30-33 all say that Muslims are to kill those who associate other beings with God, including Jews and Christians, until they repent and become Muslims. The hadith literature provides attestation that this is precisely what Muhammad commanded, specifically, that he (and subsequently his followers) was to fight all the people until they became Muslims. This naturally assumes that Jews and Christians, not just the pagans, must convert to the Islamic faith or die.
There is a way in which Muslims can reconcile Q. 9:29 with what immediately precedes and follows. One can understand from Sura 9 that all those who convert to Islam, whether pagans, Jews, Christians etc., are to pay Jizya as a sign that they have been subdued and brought into the fold of Islam.

Although this may solve the contradiction within the Quran it doesn’t help resolve the problems raised by the hadith literature. The Islamic narratives quote Muhammad as expressly stating that the people must be fought until they testify that Allah is god and that he is his messenger which not only contradicts the Quran but also conflicts with the other reports that we quoted where Muslims allowed pagans such as the Persians to remain in their religion provided that they paid Jizya.

Hence, no matter how a Muslim tries to reconcile all of this some of the contradictions will still remain.

All Quranic citations were taken from the Abdullah Yusuf Ali version.