Tuesday, March 13, 2012

ፕሬዚዳንት ግርማ አረፉ? ወይስ ዳኑ?



አዲስ አበባ ሲቲ ኦንላይን እንደዘገበው ፕሬዚዳንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ በተወለዱ በ88 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን ዘግቧል።(አዲስ ነገር ኦንላይን ዘገባውን ከደረገጹ ከሰዓታት በኋላ ሰርዞታል)
በተለያዩ ድረ ገጾች ማለትም ኢሳት ቲቪ፣ድሬ ትዩብ፣ ኢትዮ ትዩብ፣ ደ ብርሃን፣ዘሐበሻ ብሎግና የቦ የመሳሰሉት ድረ ገጾች ፣ከአዲስ አበባ ኮሪያ ሆስፒታል ወደሳውዲ አረቢያ መጓዛቸውና እዚያው እንዳረፉ ያወጡት ዘገባ እስካሁን እንዳለ ነው።
ይሁን እንጂ የመንግሥት የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቃለ አቀባይ ለቪኦኤ አሁን ማምሻውን በሰጠው መረጃ ፕሬዚዳንቱ በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኙ የገለጸ ሲሆን በመንግስታዊው ቴሌቪዥኑ ደግሞ በቅርቡ እንደሚመለሱ ተነግሯል።