Tuesday, March 6, 2012

ሰበር ዜና! «ዘመድኩን በቀለ የ5 ወራት እስር ተፈረደበት»

ለቀበጠች አማት ሲሦ በትር አላት


ሕገ ቤተክርስቲያንንና ሕገመንግሥትን በጫማው ረግጦ፣ ከሕግ በላይ ሆኖ በሕዝብና በቤተክርስቲያን ተወዳጅ የሆኑ ሰባክያነ ወንጌልና ዘማሪያንን አፉ እንዳመጣለት ተሃድሶና መናፍቅ እያለ ሲሳደብና ሲወራጭ የነበረው ዘመድኩን የ5 ወራት የእሥር ዋራንት ተቆረጠለት፡፡

ዛሬ የካቲት 27 ቀን 2004 ዓ.ም በአራዳ ምድብ ችሎት የዋለው ፍርድ ቤት ግራ ቀኙን ካየ በኋላ ዘመድኩን ሕግን በመጣስ በተለይም በመጋቤ ሀዲስ በጋሻው ደሳለኝ ላይ ባደረሰው የሞራልና የስም ማጥፋት፣ እንዲሁም የዛቻ ወንጀል ፍርዱ ሊወሰንበት መቻሉ ታውቋል፡፡ ዐቃቤ ሕግ ፍርዱ አንሷል ቢልም፣ የዘመድኩን ጠበቃ የልጆች አባት፣ የብዙ ቤተሰብ አስተዳዳሪና ወላጅ እናቱ በቅርብ የሞቱበት መሆኑን አስረድቶ የፍርድ ማቅለያ ሃሣብ በማቅረቡ ሊቃለልለት እንደቻለ እማኞቻችን ገልጸዋል፡፡

ይሁ እንጂ 5 ወሩም ቢሆን እንደማይፈረድበት የገመተው ዘመድኩን፣ እጅግ መደንገጡንና ያዙኝ ልቀቁኝ ሲሉ የነበሩ ተባባሪ የውንብድና ጓደኞቹ ሲያለቅሱ እንደነበር ተስተውሏል፡፡ የዝግጅት ክፍላችን ዘመድኩንን እግዚአብሔር ያውጣህ እያለ፣ የ5 ወራት የእሥር ቤት ቆይታህ የትምህርት፣ የንስሐ እና የመስተካከል ቆይታ ያድርግልህ በማለት ለማኅበረ ቅዱሳን ጓደኞቹ "የአህያ ባል ከጅብ አያስጥልም" በሚል ተረት ይሰናበታቸዋል፡፡
እግዚአብሔር ለሁላችንም ማስተዋልን ያድለን!!!
አሜን!!!
ምንጭ ፣http://dejeselaam-dejeselaam.blogspot.com/2012/03/blog-post_06.html