Thursday, October 29, 2015

መምህር ግርማ ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄም ወድቅ ተደርጓል።

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 18፣ 2008 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ትናንት በቁጥጥር ስር የዋሉት መምህር ግርማ ወንድሙ ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበዋል።

መምህር ግርማ ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄም ወድቅ ተደርጓል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የፖሊስ መርማሪ ቡድን ዛሬ ግለሰቡን በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ የወንጀል ችሎት አቅርቧቸዋል።

ፖሊስ ግለሰቡ በተጠረጠሩበት የማታለል ወንጀል ቀሪ የምርመራ ስራ ስላሉብኝ ተጨማሪ 14 ቀን ይፈቀድልኝ ብሏል።

ተጠርጣሪው በራሳቸውና በጠበቃቸው በኩል ፖሊስ የጠየቀውን ተጨማሪ ጊዜ  በመቃወም የዋስትና መብታቸው እንዲከበር ጠይቀዋል።

የፖሊስ የምርመራ ቡድን በበኩሉ እሳቸው ቢለቀቁ ሌሎች ተፈላጊዎችን እና የተለያዩ ሰነዶችን ስለሚያሸሹብን ጥያቄያቸው ውድቅ ይሁን ብሏል።

ፍርድ ቤቱ የሁለቱንም ወገን ክርክር መርምሮ ፖሊስ አብዛኛውን የምርመራ ስራ ያካሄደ በመሆኑ ለቀሪ የምርመራ ስራዎቹ ይረዳል በማለት ከጠየቀው የ14 ቀን ጊዜ ውስጥ 7 ቀን ብቻ ፈቅዷል።

ውጤቱን ለመጠባበቅም ለጥቅምት 25 2008 ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል።

የወንጀሉ ዝርዝር

ፖሊስ መምህር ግርማ  በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ምክንያት የሆነው ወንጀል የተፈፀመው መስከረም 2006 ዓ.ም ነው ብሏል።

በየካ ክፍለ ከተማ በተለምዶ ወሰን ግሮሰሪ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ የሚኖሩት አቶ በላይነህ ከበደ በመምህር ግርማ የማታለል ወንጀል የተፈጸመባቸው ግለሰብ ናቸው።

እንደ ፖሊስ የምርመራ መዝገብ እኚህ ግለሰብ ከትዳር አጋራቸው ጋር 400 ካሬ ሜትር ላይ ባረፈ መኖሪያ ቤታቸው ይኖሩ ነበር።

እንደ ምርመራ መዝገቡ መምህር ግርማ የግል ተበዳይን እምነት በመጠቀም የምትኖርበትን መኖሪያ ቤት እስከ ጥር 30 2006 ሽጠህ ካልወጣህ አስከሬንህ ይወጣል ይሏቸዋል።

የፖሊስ የምርመራ መዝገብ እንደሚለው ልጅ ያልወለዱት ባልና ሚስት ከመሞት መሰንበት በማለት ይህንን ቤት በጣም በዝቅተኛ ዋጋ በ800 ሺህ ብር ይሸጡታል።

ቤቱ በዚህ ዋጋ እንዲሸጥ መምህር ግርማ በራሳቸው ሰዎች አማካኝነት ብዙ ያልተገባ ስራ ሰርተዋል ነው የሚለው የምርመራ መዝገቡ።

ከዚያም መምህር ግርማ በዚህ ብቻ ሳይመለሱ የግል ተበዳዩን ቦሌ አካባቢ በራዕይ ያየሁት ቦታ አለ እዚያ ነው ገዝተህ የምትኖረው ይሏቸውና ሌላ የማታለያ ዘዴ ቀየሱ ይላል ምርመራው።

ቤቱ የተሸጠበትን 800 ሺህ ብር አምጣና እንዲበረክትልህ ልፀልይበት ብለው በመውሰድ በዚያው ውለው አደሩ፤ የግል ተበዳዩም በእርሳቸው ላይ ያላቸው እምነት ባለመጥፋቱ በትዕግስት ስልክ ቢደውሉላቸውም ስልካቸው ዝግ ሆነባቸው፤ ይባስ ብሎ ከሀገር ወጡ ተባለ የሚለውም ተጠቅሷል።

የግል ተበዳይ ሁኔታው ማታለል መሆኑን ስለተረዱ 2007 መጋቢት ወር ገደማ ለፖሊስ ያመለከቱ ሲሆን፥ እርሳቸው ከሄዱበት እስኪመለሱ ፖሊስ የግል ተበዳዩን እና የምስክሮችን ቃል ተቀብሎ ቆይቶ ተጠርጣሪው መምህር ግርማ ወንድሙን ትናንት በቁጥጥር ስር አውሏቸው ነው ዛሬ ፍርድ ቤት ያቀረባቸው።

ተጠርጣሪው እኔ የተባለውን ሰው ቀይ ይሁን ጥቁር አይቼው አላውቅም፤ ሆን ተብሎ ከጀርባ የተጠነሰሰብኝ ሴራ አለ በማለት ለችሎቱ አስረድተዋል።

ጠበቃቸውም የተጠረጠሩበት ወንጀል ዋስትና የሚከለክል አይደለም፤ ፖሊስም የሚጠበቁ ምርመራዎቹን አጠናቋል፤ ደንበኛዬ የዋስትና መብታቸው ይከበርልኝ በማለት ጠይውቋል።

ይሁን እንጂ ፍርድ ቤቱ የዋስትና ጥያቄያቸውን ውድቅ አድርጓል።





በጥላሁን ካሳ


Wednesday, October 28, 2015

ሰበር ዜና፣ ፖሊስ አጥማቂ ነኝ ባዩ ግርማ ወንድሙን በቁጥጥር ስር አዋለ።


አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 17 ፣ 2008 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ፖሊስ መምህር ግርማ ወንድሙን በቁጥጥር ስር አዋለ።

የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ምንጮች መምህር ግርማ ዛሬ በፖሊስ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን ተናግረዋል።

መምህር ግርማ በተለያዩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አብያተ ክርስቲያናት በማስተማርና በማጥመቅ ሲያገለግሉ የነበሩ ናቸው።

ይሁን እንጂ መምህሩ በማጥመቅ እና በማስተማር በሃገር ውስጥም ይሁን በውጭ ሃገራት ቤተክርስቲያኒቱን ወክለው እንዳያገለግሉ እውቅና መነፈጋቸውን ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ያነገጋረው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ጠቅላይ ቤተክህነት አረጋግጧል።

የፋና ምንጮች መምህር ግርማ ከአገልግሎታቸው ጋር በተያያዘ በወንጀል ሳይጠረጠሩ እንዳልቀረ ነው የተናገሩት።

ጣቢያችን ሌሎች ተያያዥ መረጃዎችን እየተከታተለ ያቀርባል።


በጥላሁን ካሳ እና 

Tuesday, October 27, 2015

ስለአንዳንድ በኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክ ላይ…ከአንዳንድ የኦሮሞ ጸሐፍት የተሰነዘሩ…ያስቀየሙኝ ክታቦች!!

ከአማን ነጸረ (ክፍል 3)
(6.6) እስኪ እነዚህ ምዕራባውያን ሚሽነሪዎች ስለ ኦሮሞ ሕዝብ ባሕል የነበራቸው አመለካከት ከኢኦተቤክ ሊሻል ይቅርና ምን ያህል የዘቀጠ እንደነበረ በራሳቸው መነጽር እንፈትሽ፡፡ Eric Gilchist የተባለ አሜሪካዊ በነመኩሪያ ቡልቻ ‹‹የአቢሲኒያ ትርክት›› ተጽእኖ ስር ሆኖ እንኳ በሠራው የ2ኛ ዲግሪ (ማስትሬት) ማሙያ ጥናት <<....as a result of their fundamental beliefs, SIM [Sudan Interior Missonary] missionaries viewed all non-Chiristean religious practices as evil and they demanded that their converts compeletly change their life style, with no compromise to accommodate local customs....>> በማለት ሚሲዮናውያኑ ለነባሩ የኦሮሞ ባሕል የነበራቸውን የተዛባ አመለካከት ካሳየን በኋላ Dough Priest የተባለውን በወለጋ ከ10 ዓመታት በላይ የሚሲዮናውያን መሪ የነበርን ትምክተኛ ሰው ጽሑፍ በመጥቀስ <<...the lives of the Galla people in general were one round after another of drunkness,adultery,thievery,lying,fighting,cheating,and worshiping false gods....today,many of the lives in our area have changed greatly....>> እያሉ (ሚሽኖቹ) ራሳቸውን ወለጋን የታደገ መሲኅ አድርገው ይመጻደቁ እንደነበር ጽፏል--ይቅርና ባሕሉን እንደ ባሕል ሊቀበሉ ( Eric Gilchist፡p.74)፡፡አናሲሞስ ነሲብም ቢሆን ሁሉንም የኦሮሞ አኗኗርና ባሕል ‹‹ቅዱስ›› ብሎ የተቀበለ አይመስልም፡፡በአንድ ደብዳቤው ላይ በስብከታቸው ስላመጡት ለውጥ ሲገልጽ ‹‹...በጋብቻ ላይ የሚፈጸም ጋብቻን እና በአካባቢው የሚታዩ ጎጂ ልማዶችን አጥብቀን ተፋልመናል፤እናም በዚህ በኩል ተሳክቶልናል፡፡ከዚህ ሌላ በኅብረተሰቡ መካከል ይዘወተር የነበረው የጥንቆላ፣የድግምት፣ለክፉ መናፍስት መሥዋዕት የማቅረብ ልማድ፣ሐሰተኛ ምስክርነት፣ውሸትና ሌላም ጎጂ ልምዶች ከዓመት ወደ ዓመት እየቀነሱ መጥተዋል›› ብሎ ነበር (ደማቆቹ፡ገ.35)፡፡እዚህ ላይ አንድ ሀቅ ላስታውስ፡፡በሰሜን ኢትዮጵያም ቢሆን አናሲሞስ ያነሳቸው ከክርስትና ጋር የሚቃረኑ ባሕላዊ ጎጂ ልማዶችና አምልኮዎች ነበሩ፡፡ዛሬም ርዝራዣቸው አለ፡፡ችግሩ በኦሮሚያ ብቻ የነበረ/ያለ አይደለም፡፡ስለሆነም ማንም በማንም ላይ ሊመጻደቅ አይችልም፡፡
(6.7) እስልምና የኦሮሞን ባሕል በምልዓት ይቀበላል የሚል ካለም እስኪ እንፈትሽ!! ‹‹Islamic Front for Liberation of Oromia›› የሚል ሃይማኖት ጠቀስ የኦሪሚያ ነጻ አውጪ ሽምቅ ተዋጊ በሼክ አብዱል ከሪም (ሼክ ጃራ አባ ገዳ) መፈጠሩን፣በባሌ አካባቤ ‹‹የሶማሌ አቦ...›› የሚባል አፍቃሬ-ሶማሊያ የኦሮሞ ሙስሊሞች የፖለቲካ ቡድን በታሪክ መታየቱን፣ይኸው ቡድን በ1969 ዓ.ም ከዚያድ ባሬዋ ሶማሊያ በእስልምና ስም ተቃቅፎ ኢትዮጵያን ያውም ሐረርጌን መውጋቱን፣ከሽግግር መንግስቱ ምስረታ ጀምሮ በተደጋጋሚ በምድረ-ኦሮሚያ እየተንቀሳቀሱ በወሐቢያና በሃዋርጃ ስም ብሔር ሳይለዩ ኦርቶዶክሳውያንና ለዘብተኛ ሙስሊሞችን እንዲሁም ፕሮቴስታንቶችን በተለይ ደግሞ የመካነ-ኢየሱስ ሉተራውያንን ያጠቁ የሙስሊም አክራሪዎችን ድርጊት እንደቀላል የእኩልነት ጥያቄ ብቻ እንድናየው እነ አባስ ሀጂ ስለመከሩን እንዳላየ እንለፈው፡፡ነገር ግን ከአክስት ልጅ ጀምሮ መጋባትን የሚፈቅደው የእስልምና ስብከት እንኳንስ ከአክስት ልጅ ጋር ከጎሳ አባል ጋርም ጋብቻን ከሚከለክለው የኦሮሞ ብሉይ ልማዳዊ ሕግ ያለው ተቃርኖ፣ኦሮሙማን በምድረ-ኦሮሚያ ለመገንባት ከሚታገለው የኦሮሞ ብሔርተኝነት ጋር ‹ድንበር-ለምኔ› የሚለው ዘመናዊው እስልምና ያለው አለመጣጣም፣እንዲሁም ወደ ድሬ ሼክ ሁሴን መሄድን ወደ አባ ሙዳ እንደሚደረግ ምትክ መንፈሳዊ ጉዞ (ጂላ) የማይመለከተው የዘመኑ እስልምና (ወሀቢዝም) በነአባስ ሐጂ (Abas Haji:p.110-113) ቀደም ሲል ለስላሳ ትችት ሲደርስበት የነበረ ቢሆንም አሁን አሁን ግን እስልምና በኦሮሚያ ኤሊቶች ዙሪያ ኃይል እየተሰማው ስለመጣ ነው መሰለኝ ትንፍሽ የሚል የለም፡፡በነገራችን ላይ የልሂቁን ኦሮሞ ድምጽ የሚቃኙት በዋናነት ሙስሊም የመደብ ጀርባ ያላቸው ኦሮሞ ልሂቃን ሲሆኑ በተከታይነት የምዕራብ ኦሮሚያ ፕሮቴስታንቶች ያጅቧቸዋል፡፡ለሃይማኖት ልዩነት ልበ-ሰፊ ከነበረው ሜጫ እና ቱለማ መፍረስ በኋላ ባሉ ኦሮሞ-ተኮር አደረጃጀቶች ኦርቶዶክሳውያን ኦሮሞዎች በኅቡዕና በገሀድ ክፉኛ እንዲሸማቀቁና ከኦሮሞነት እንደወረዱ እንዲሰማቸው ሰፊ አግላይ ፕሮፖጋንዳ ተሰርቷል፤እየተሰራ ነው፡፡
(6.8) ካቶሊክስ ለምን ይቅርባት?!ትፈተሸ::የካቶሊክ ሚሽነሪዎች ገና ወደ ክርስትና ያልገባችውን ምድረ-ኦረሚያ (ፊንፊኔ) እንዴት ይመለከቷት እንደነበር አባ አንጦንዮስ ሲጽፍ ‹‹...የፊንፊኔና የአካባቢው ሕዝብ በጨለማ ውስጥ በሞት ጥላ ስር ይኖር ስለነበር የወንጌል ስርጭት በእርግጥ አስፈላጊ እንደነበር አባ ቶረን ሻኽኝ አስረድተው በአካባቢው የወንጌል ትምህርት ለማድረስ ቢያንስ አራት ወይም አምስት ተጨማሪ ሚሲዮናውያን እንደሚያስፈልጉዋቸው ኣሳስበው ነበር››ይሉናል (አባ አንጦንዮስ፡ገ.126) የአባ ቶረን ሻኽኝን የጥቅምት 14 ቀን 1868 ዓ.ም ደብዳቤ ጠቅሰው፡፡የባሪያ ንግድ፣ሴት ልጆችን ያለፈቃዳቸው መዳር፣በጋብቻ ላይ ጋብቻ የመሳሰሉ በኦሮሞና ሲዳማ ግዛቶች የሰፈኑ ልማዶች ለካቶሊካውያን ሚሽነሪዎች ፈተና ሆነው እንደነበርም አባ አንጦንዮስ በዚሁ መጽሐፍ ከገጽ 120 ጀምሮ ለስለስ ባለ የሚሲዮናውያን ቋንቋ በጊዜው የነበረውን ጎጂ ባሕል ተችተው ተርከውታል፡፡
(6.9) ከላይ የቀረቡት በኦሮሞ ባሕልና እምነት ላይ ያሉ አመለካከቶች ከራስ አስተሳሰብ/ሃይማኖት ውጭ ያለውን ባሕላዊ/ሃይማኖታዊ አመለካከት በራሱ በባሕሉ ዐይን ሳይሆን ‹‹በግል›› መለኪያ መለካት የሚያመጣውን የተዛነፈ ችግር ያንጸባርቃሉ፤ችግሩ ይብዛም ይነስም በሁሉም ወገን አለ--በሁሉም--የኢኦተቤክ ምዕመናንና የዋቄፈና አማንያንን ጨምሮ፡፡የዚህ አመለካከት አንጸባራቂ ከሆኑ ግለሰቦች አንዱ የሆነው Krapf የጻፈውን የኛው መሐመድ ሐሰን እንዳለ ገልብጦ በኦሮሞ ጥናት መጽሔት ቁጥር-7 ላይ በገጽ-118 ያሰፈረውን እንይ! <<...the Amhara Clergy were not sensitive to Oromo food habits in which milk, butter and meat were central>> ሲል አስቀምጦታል፡፡በKrapf ፕሮቴስታንታዊ እይታና በመሐመድ የከረረ ብሔርተኛ ምልከታ መሰረት የኢኦተቤክ የዐማራ ብቻ ናት፤የኢኦተቤክ ዶግማና ቆኖና አፈጻጸሙም ከብሔር-ብሔር እየተለያየ መተግበር አለበት!በነመሐመድ እምነት ለምሳሌ፡- የደብረብርሃን ዐማራ ኦሮቶዶክሳውያን በፍልሰታ ከሥጋና ቅቤ ሲታቀቡ የእነሱ ጎረቤት የሆኑት የልቼ እና የሸኖ ኦሮሞዎች ግን በፍልሰታ ስጋና ቅቤ የተከለከሉት በሃይማኖቱ ዶግማና ቀኖና ሳይሆን በዐማራ ቸልተኝነት ነው!!የደጀን (ጎጃም) አባይ ዳር ያሉ የቅ/ሩፋኤል ቤ/ክ አካባቢ ዐማራ ጸዋሚዎች በጾም ከስጋ ታቅበው፤በሌላ በኩል በሰ/ሸዋ ገርበ-ጉራቻ የፍልቅልቅ እና አካባቢዋ የቅ/ሩፋኤል የአባይ ዳር (የደራ?) ኦሮሞ ኦርቶዶክሳውያን ጾማቸውን ከስጋና ወተት ጋር ማከናወን ነበረባቸው!!ይሄ ያልሆነው የኢኦተቤክ ኋላቀር ስለሆነች ነው--በመሐመድና በKrapf አረዳድ!!እሺ!የኢኦተቤክ የጾም ስርዓትስ በነመሐመድ ጥልቅ የነገረ-ኦርቶዶክስ ጥናት የዐማራ ቀሳውስት ፈጠራ ነው ተብሏል!ሰው እንዴት ከግብጽ እስከ ሕንድ፣ከሶርያ እስከ አርመንያ፣ከአቴንስ እስከ ሞስኮ፣ከአስመራ እስከ አልባኒያ ያሉ ኦርቶዶክሳውያን ሁሉ በጾማቸው ወራት ጥሉላት ምግቦችን (የእንስሳት ተዋጽኦዎችን) እንደማይመገቡ ጎግልን ጎልጉሎ መረዳት ያዳግተዋል??መሐመድ ሐሰንን የሚያክል የታሪክ ባለሙያ ለጾም ያን ያህል የተደነገገ ዝርዝር ቀኖና ከሌለው የክርስትና ዘውግ (ፕሮቴስታንት) ሃይማኖታዊ ግንዱ የሚመዘዘውን (ፓስተር?) Krapf ምንጩ አድርጎ እንዴት ስለ ኢኦተቤክ የጾም ቀኖና ብይን ይሰጣል? ከሰጠስ ለምን የረመዳን አጽዋማት በኦሮሚያ ያላቸውን አቀባበል ጨምሮ መርምሮ በንጽጽር አይተነትንልንም?‹‹ሌሊት እየተመገቡ ቀን-ቀን መጾምን የሚደነግገው ረመዳን ከኦሮሞ ባሕል ጋር ያለው ተዛምዶ እንዴት ይታያል?በሙስሊምና በኦሮሞ ኦርቶዶክሳውያን መካከል ያለው የሃይማኖት ሕገጋት አቀባበል ከኦሮሞ ባሕል ጋር ያለው አንጻራዊ ውሕደትስ?›› ብለን ብንጠይቅስ?
7-- ክስ-ሰባት፡- የኢኦተቤክ እንደመሬት ከበርቴ (ባለ‹‹ሲሶ›› ግዛት)!!
በሁሉም የሀገራችን ጸሐፍያን የኢኦተቤክ ባለሲሶ ይዞታ የነበረች መሆኗ በስፋት ተጽፏል--በራሷ መጻሕፍት ሳይቀር፡፡እነ መኩሪያ ቡልቻም ይህንኑ ደጋግመው ጽፈውታል፡፡አባስ ሐጂም የቡልቻን ጽሑፍ ጠቅሶ <<...the clergy were given land that was confiscated from the Oromo peasants and become landlords, they owned Oromo peasants as Gabbars (serfs) and thrived upto their labour...>> በማለት ብሶቱን ያቀርባል (Mekuria cited in Abas Haji:p.104)፡፡ጥሩ፡፡እዚህ ላይ አንድ እውነት አለ::በኦሮሞም ሆነ በተቀሩት ብሔር-ብሔረሰቦች (ዐማሮችንና ትግራውያንን ጨምሮ) ‹የሰሞን መሬት› የሚባል የቤ/ክ ይዞታ አይነት ነበር፡፡ነገር ግን የዚህ መሬት ይዞታ ለስሙ የኢኦተቤክ ይባል እንጂ ባለቤቶቹ ተመልሰው መኳንንቱና መሳፍንቱ ነበሩ፤ያዙበታል፤ምርቱን ይቆጣጠራሉ፤እንዲሁም ሲሞቱ ለልጆቻቸው ያወርሱታል--መሳፍንቱ፡፡የካሕናቱ እጣ-ፈንታ በመሳፍንቱ ስር ቅጥረኛ ሆኖ በድርጎ (የእለት ምግብ) ብቻ ማገልገል ነው፡፡በሌላ አነጋገር ካሕናቱ የበላይነታቸው በመንፈሳዊ ጉዳዮች እንጂ በቤ/ክ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች የማዘዝ መብት አልነበራቸውም፡፡ስለሆነም መሳፍንቱ በካሕናት ስም በተቆጣጠሩት ይዞታ መልሰው ካሕናቱን በእለት ምግብ ብቻ እየደለሉ በማስገልገል የተረፈውን ምርት ለግላቸው ይጠቀሙበታል፡፡ይሕ የባላባትና የደሃ ካሕናት ሥርዓታዊ የብዝበዛ ግንኙነት በተለምዶ ‹‹የቶፋ ሥርዓት›› ይባላል፡፡እንዲሕ ስር ሰድዶ የኖረው ሥርዓት ብዙም አይተረክም፡፡በቤተክሕነት ወገኖች የቀደሙ ነገሥታትንና ባላባቶችን አንዳንድ የማይካዱ ውለታዎች እንደማሳነስ ስለሚቆጠር ይመስለኛል የማይተረከው፡፡በዓለማዊ ጸሐፍት ደግሞ አንድም አሰራሩን በቅርብ ካለማወቅና ከቸልተኝነት፣ሁለትም ባለፉት 40 እና 50 ዓመታት ተራማጆቻችን (ተራ-ማጆች!) የኢኦተቤክ’ንን በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ በጅምላ ፈርጆ ማሳቀል ቀላል ስራ ስለሆነላቸው ይመስለኛል፡፡እንጂማ የኛ ወላጆች (ወላጅ አባቴ ካሕን ነበር!) በልመና እንጀራ ተማሩ፤ከእጅ ወደ አፍ እንኳ ሊባል በማይችል የሰቆቃ ኑሮ እድሜያቸውን ገፉ፤የረባ ጥሪት ለልጆቻቸው ሳያኖሩ ድኅነትን አውርሰውን ያለእድሜያቸው ተንከራተው አለፉ፡፡ሞቱ፡፡‹‹ሕያዋን ለነገሥታት፤ሙታን ለካሕናት ይገብራሉ›› በሚለው ብሂል በሙታን ተዝካርና የሙት አልባሳት ሲደጎሙ ኖረው ሞቱ፡፡በዋናነት 5ቱ ቀዳስያንና በዙፋኑ ዙሪያ ያሉ ‹‹ካሕናተ-ደብተራ›› ብቻ ነበሩ የንጉሡና የምዕመኑ እርጥባን ተቋዳሾች፡፡የተቀረው ለማኝ ነው፡፡በካሕናቷ ‹ምንዳቤ ወረኀብ› የኢኦተቤክ ‹የልመና ሃይማኖት› ተብላ ትጠራ ነበር፤አሁንም ይሕ ስያሜ በከፊል አለ፡፡ይሄ ይታወቃል፡፡ታሪክ ሲጻፍ ግን ‹‹ባለሲሶ ግዛት›› ይባልልናል!!ግና እንዲያ እንዳልሆነ ይታወቅ ነበር፡፡ስለመታወቁ ማስረጃ እንቁጠር...