Sunday, January 29, 2012

«ገና በመንገድ ሳለህ ከባላጋራህ እንድትታረቅ ትጋ»ሉቃ 12፣58

ከዚህ ቀደም ስለእርቅ ጉዳይ በተነሳ ሃሳብ ዘመድኩንን ኃያልና የማይንበረከክ ክንድ ባለቤት እንደሆነ አጋኖ ደጀሰላም ብሎግ ዘግቦ ነበር። ዘመድኩንም ሲኦል ብወርድ እንኳን ከበጋሻው ጋር እርቅ አይሞከርም በማለቱም ተገርመን አስተያየት ጽፈን በደጀሰላም ላይ አስነብበናል። ሰጥተን የነበረውም አስተያየት ከላይ የሰጠነውን ርእስ መሰረት ያደረገ ነው። በወቅቱ የሰጠነውን አስተያየት እንዳለ አቅርበነዋል፣
«Anonymous said... ከሳሽንም ተከሳሽንም በደንብ አውቃቸዋለሁ። ወደ ዝርዝር ብንገባ ከአምላክ የሚያጣላ ይሆናልና ተከድኖ ይብሰል። የሆኖ ሆኖ ፍርድ ቤት ስለምስጢረ ሥላሴ ሳይሆን ስለስመ ማጥፋት ወንጀል የቀረበ ክስን እያየ እንደሆነ ከክሱ ጭብጥ ስንረዳ ከሳሽና ተከሳሽ ክርክሩን በእርቅ ቢጨርሱት 1/ የእግዚአብሔር ልጆች ይባላሉ ። 2/ሃይማኖተኞች ሃይማኖት በሌላቸው(ዓለማውያን) ፍርድ ቤቶች የሚያደርጉት ክርክር ሃይማኖቱን ያስነቅፋልና ይህንን ለማስቀረት 3/የበደሉንን ይቅር ማለት ስለሚገባን ዘመድኩን ዕርቅ አልቀበልም ማለቱ እውነተኛ ኦርቶዶክሳዊ መሆኑን ሳይሆን የሚያመለክተው አለማወቁን፤ ግብዝነቱንና የታይታ ክርስቲያን መሆኑን እንጂ የክርስቶስ ልጅ መሆኑን አይደለም። ክርስቶስ ፍርድ ቤት ይለያችሁ ሳይሆን ያለው ከባላጋራህ ጋር አስቀድመህ ታረቅ ነው ያለው። እኔ ከአንድ እስላም ጋር ብጣላና ብታረቅ በሰውነቱ እንጂ የሱን ሃይማኖት ለመቀበል ስላልሆነ ዘመድኩን እሱ ከበጋሻው ጋር ታረቀ ማለት እሱ እንደሚለው ተሃድሶ ሆነ ማለት አይደለም። የሚያሳብቅ ውሸት መሆኑ ደግሞ ሲዖልም ቢሆን እወርዳለሁ በማለት አንድ ክርስቲያን በህይወት ዘመኑ ዕድል ፈንታውና የፍርድ ዕጣው በፍጹም ሊሆን ቀርቶ ሊመኝ የማይገባውን መናገሩ አሳዛኙ አባባል ነው። እውነተኛ ክርስቲያን ነኝ ለማለት ማረጋገጫና ሌላውን የማሰመኛ ቃል አድርገን ሲዖልም ቢሆን እወርዳለሁ ማለት ከየት የተገኘ ትምህርት ነው። እኛ እድል ፈንታችንና መንፈሳዊ ፍላጎታችን መቼም ቢሆን ከክርስቶስ ጋር መኖር ነው እንጂ ሲዖልም ቢሆን ወርደን የምናረጋግጠው እውነተኛነታችን ስለሌለ ይህንን ቃል ከመጠቀም(ሎቱ ስብሐት)እንላለን። ሳጠቃልል ዘመድኩን የምትረታ መሆንህን ብታውቅ እንኳን ከፍርድ ቤት ክርክርና ጭቅጭቅ በኋላ ከምታገኘው የረቺነት ኃላፊ ጠፊ ዝና ይልቅ ለክርስቶስ ብለህ ሁሉን ትተህ የምታደርቀው እርቅ ብዙ ኃጢአትህን ይሸፍናል፤ ሰማያዊ ክብርንም ያስገኝልሃልና ከልብህ መክረህ ታረቁ የሚሉ ሽማግሌዎች ካሉ ወደመጡበት አትመልስ ወንድማዊ ምክሬ ነው። September 10, 2011 12:37 PM የሚል አስተያየት ሰጥተን የሰማን የለም።
የያኔውን የደጀሰላም ብሎግ «ወደፊት በሉለት ይለይለት» ሙሉ ጽሁፍን ለማንበብ ከፈሉጉ (እዚህ ላይ ይጫኑ)
  አሁን ደግሞ «ደጀሰላአም» የተሰኘ ብሎግ በወቅቱ ብለነው የነበረውን አስተያየት የሚያጠናክርና የክሱ ሂደት የፈራነው ግምት የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ መድረሱን ከታች አስነብቦናል። መልካም ንባብ!

Friday, January 27, 2012

ሕሙም እንዳይረዳ የተቃውሞ ዘመቻ!


የአቶ እንዳለ ገብሬን ሕይወት ለመታደግ የገቢ ማሰባሰቢያ መንፈሳዊ ጉባዔ ሊካሄድ ነው
"ማኅበረ ቅዱሳን" ጉባዔው እንዲካሄድ በመፍቀዳቸው ብፁዕ አቡነ ፊሊጶስን ስም አጠራራቸው እስኪረሳ እንዲያልፉ እርግማን አወረደባቸው
ባደረበት የልብ ሕመም ምክንያት ውጭ ሀገር ሄዶ ካልታከመ በስተቀር የመዳን ተስፋው የመነመነው የአቶ እንዳለ ገብሬን ሕይወት ለመታደግ ከ450 ሺህ በላይ ወጪ የተጠየቀ ሲሆን፣ ቤተክርስቲያንን በማገልገል ላይ ያሉት መምህራንና ዘማርያን፣ በጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት አዳራሽ ጥር 20 ቀን 2004 ዓ.ም ከቀኑ ሰባት ሰዓት የሚጀምርና ገቢው ለዚሁ ወንድም መታከሚያ የሚውል መንፈሳዊ ጉባዔ አዘጋጅተዋል፡፡
ይህንን የተቀደሰና ሁሉም ወገን ሊረባረብበት የሚገባ ዕርዳታ በወንጌሉ ቃል መታጀቡና መመራቱ በዘልማድ ማኅበረ ሰይጣን የሚባለውና ራሱን "ማኅበረ ቅዱሳን" እያለ የሚጠራው ፈሪሳዊ ማኅበርን በማስኮረፉ ጉባዔውን ለማደናቀፍ በመውተርተር ላይ ይገኛል፡፡ ካለ እኔ በስተቀር ቤተክርስቲያን ልጅ የላትም የሚለው ይኸው ማኅበር፣ ልዩ ልዩ አቃቂሮችን በማውጣት ራሱ ፈራጅ፣ ራሱ ፈጻሚ በመሆን በምዕመናንና በቤተክርስቲያን መካከል እንደ ግድግዳ ቆሞ ማወክ ከጀመረ ዓመታት ያስቆጠረ ሲሆን፣ ይህንኑ ጉባዔ ያዘጋጁት ለእርሱ ዓላማ አንገዛም ያሉ ሰባክያነ ወንጌልና መዘምራን በመሆናቸው፣ እንደተለመደው የተሃድሶ ታፔላውን ከፍ አድርጎ በማንሳት ያዙኝ ልቀቁኝ እያለ ነው፡፡(ዘመቻውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ)
ዘወትር ስድብና ዕርግማን ከአፉ የማይጠፋው "ማኅበረ ቅዱሳን" የወንድማችንን ሕይወት ለመታደግ ማንኛውም ሰብዓዊ ፍጡር ዕርዳታ እንዲያደርግለት በመማጸን ፈንታ በሲኖዶስ ያልታገዱትና ያልተከለከሉት ሰባክያንና ዘማርያን እንደታገዱና እንደተወገዙ አስመስሎ በማውራት ጠቅላይ ቤተክህነት አዳራሽ ለምን ተፈቀደላቸው ብሎ በመጮህ ላይ ነው፡፡ ይባስ ብሎም፣ "አንድ አድርገን" በተባለው ብሎጉ፣ ". . . ፈቃጆች ነገ ስም አጠራራቸው እስኪረሳ ድረስ ያልፋሉ. . ." በማለት ሆን ብሎ በስም ባይጠራቸውም ጉባዔው እንዲካሄድ የፈቀዱትን እነአቡነ ፊሊጶስን ወርፏል፡፡

Thursday, January 26, 2012

መግደልና ማቃጠል!!





በሀላባ ቁሊቶ አክራሪ ሙስሊሞች ለጥምቀት በዓል በወጡ ክርስቲያን ምዕመናን ላይ ጉዳት አደረሱ

የሀላባ እና አካባቢው ምዕመናን ከፍተኛ ክርስቲያናዊ ገድል በመጋደል ሃይማኖታቸውን መከላከላቸው ተሰማ

ጉባ በተባለች አነስተኛ መንደር ለገበያ በወጡ ክርስቲያኖች ላይ የማኅተም መበጠስና የገንዘብ ዝርፊያ ተካሂዷል

መንግሥት ተገቢውን እርምጃ ካልወሰደ መጪው ጊዜ እጅግ አስቸጋሪ እንደሚሆን ተገምቷል


በደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ከሻሸመኔ በስተምዕራብ በግምት 75 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በምትገኘው በሀላባ ቁሊቶ ከተማ ጥር 12 ቀን 2004 ዓ.ም ለጥምቀት በዓል በወጡ ክርስቲያኖች ላይ ጥቃት መድረሱን ከዚያው አካባቢ የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡

ሆን ተብሎ እና ታቅዶ በተሰነዘረው በዚህ ጥቃት በርካታ ክርስቲያን ወንዶችና ሴቶች፣ ሕፃናትና ዐዋቂዎች ከፍተኛ የመፈንከትና የመቁሰል አደጋ ደርሶባቸዋል፡፡ ጉዳቱ የደረሰው ምዕመናን የቅዱስ ሚካኤልና የመድኃኔዓለም ታቦታትን ወደ ቤተመቅደስ ለመመለስ አጅበው በሚጓዙበት ወቅት መሆኑን ምንጮቻችን አረጋግጠዋል፡፡ በዕለቱ በክርስቲያኖች በኩል ከወትሮው የተለየ ግጭትን የሚያነሳሳ ምንም ነገር አለመፈጸሙንና ታቦታቱ ተጉዘው በከተማዋ አደባባይ ለዕረፍት በቆሙበት ወቅት፣ አድፍጠውና ተዘጋጅተው ምቹ ሰዓትና ቦታ ይጠብቁ በነበሩ ሙስሊሞች በኩል የድንጋይ እሩምታ መጀመሩን እማኞቻችን አስረድተዋል፡፡