Wednesday, January 2, 2013

አቡነ አብርሃም ቃለ ዐዋዲን ጥሰው ሕገ ወጥ ሥራ እንዲሠራ ትዕዛዝ አስተላለፉ!

 በአዲስ አበቤው ካህን ዘንድ «የጉድ ሙዳይ» የሚል ስመ ተጸውዖ አላቸው። በየሄዱበት የራሳቸውንና የማቅን ስርወ መንግሥት ማደራጀት ተቀዳሚ ተግባራቸው ነው። ከአሜሪካ ተነስተው ሐረር ከወረዱ አንስቶ እንደ በቆሎ የሚጠብሱት የሐረር ምእመናንና ካህናት ፍዳውን እያየ ነው። ከብዙ ወሰን አልባና ጠያቂ የለሽ እርምጃዎቻቸው መካከል በ /www.deselaam-dejeselaam.blogspot.com/ ያገኘነውን  መረጃ፤ አካፍለናችሗል።። መልካም ንባብ!

በሐረር መድኃኔዓለም ደብር አስተዳዳሪ ላይ ሥልጣነ ክህነት እስከመያዝ የሚያደርስ እርምጃ እንደሚወስዱ አስጠነቀቁ
የዘረኝነት መንፈስ የተጠናወታቸው አቡነ አብርሃም ከጉርሱም ያመጡትን ጎጃሜ የቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ መልአከ ምሕረት ነፃነትን የሐረር መድኃኔዓለም ስብከተ ወንጌል ኃላፊ ሆኖ እንዲመደብ አስገዳጅ ትዕዛዘ አስተላለፉ፡፡ ሊቀጳጳሱ ይህንን ትዕዛዝ ከማስተላለፋቸው በፊት በዓመታዊው የቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓል ላይ ለመገኘት ወደ ቁልቢ የሄዱ ሲሆን ወደ ሐረር እስከሚመለሱ አላደርስ ብሏቸው ካሉበት ሆነው የመድኃኔ ዓለም አስተዳዳሪውንና የሰበካ ጉባዔው ምክትል ሰብሳቢውን ጠርተው ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል፡፡
ለማስጠንቀቂያው የተጠቀሰው ዋና ምክንያት የደብሩ ሰበካ ጉባዔ በውስጥ ካሉት ካህናት መካከል በማስታወቂያ አወዳድሮ መመደቡ ሲሆን፣ ደብሩ ይህንን ሽሮ የሥራ መደቡን ለጉርሱሙ የራጉኤል ደብር አለቃ ክፍት አድርጎ ለምን አልተቀበላቸውም የሚል ነው፡፡ የምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤቱ የደብሩን ስብከተ ወንጌል ኃላፊ ቀሲስ ፋሲል አጥናፉን በዕድገት ወደ ራሱ ጽ/ቤት ስብከተ ወንጌል ክፍል ሲወስድ በተፈጠረው ክፍት መደብ ላይ የደብሩ ሰበካ ጉባዔ አወዳድሮ መቅጠሩ በአቡነ አብርሃም ዘንድ እንደ ጥፋትና ድፍረት ተቆጥሯል፡፡
ቃለ ዐዋዲው የደብሩ ሰበካ ጉባዔ ከካህናት መካከል አወዳድሮ በደብሩ ስብከተ ወንጌል ኃላፊነት የሥራ መደብ ላይ የመመደብ ሙሉ ሥልጣን ያለው ሲሆን የተመደቡት ካህንም ሙሉ መስፈርቱን አሟልተው ዕድገቱን እስካገኙ ድረስ አቡነ አብርሃም በሥራ አስኪያጃቸው በኩል ይህንኑ ተቀብለው ማፅደቅ ነበረባቸው፡፡ ይሁን እንጂ፣ እርሳቸው ይህንን በጉልበት ሽረው "የጉርሱሙን አስተዳዳሪ ተቀበሉ"! ብለው ትዕዛዝ ሲያስተላልፉ በየትኛው ማስታወቂያ አወዳድረው እንደቀጠሩ ሲጠየቁ "ዕወቅ እንጂ፣ አትመራመር" በሚል አምባገነናዊ አስተሳሰብ ያሻኝን አደርጋለሁ በሚል ስሜት ቀጭን ትዕዛዝ በማስተላለፍ ላይ መሆናቸው ታውቋል፡፡
የጉርሱሙ የደብር አስተዳዳሪ መልአከ ምሕረት ነፃነት ወደ ሐረር መድኃኔዓለም ደብር ስብከተ ወንጌል ኃላፊነት መደብ ተዛውረው ሲመጡ የሽረት(የዝቅታ) ያህል ነው፡፡ "አቡነ አብርሃም ለሰውዬው ካዘኑላቸው ለምን እዚያው ሀገረ ስብከት ጽ/ቤቱ ውስጥ ቦታ አልፈለጉላቸውም"? ብለው ብዙዎች ይጠይቃሉ፡፡ ነገር ግን አቡነ አብርሃምም ሆኑ አስተደሳዳሪው ያንን መደብ ለመያዝ የቋመጡበት ምክንያት በይፋ ባይታወቅም፣ ቤተክርስቲያንን በጎጃሜዎች ለመሙላት እና እግረ መንገድም አድባራትንና ገዳማትን በ"ማኅበረ ቅዱሳን" አባላት ለማስያዝ  ነው ሲሉ ብዙዎች አስተያየት ይሰጣሉ፡፡

የማኅበረ ቅዱሳን ሁለት ቢላዋ!


በየድረ ገጹ የስድስተኛው ፓትርያርክ ምርጫ መደረግ የለበትም እያለ የሚያላዝነው ማኅበረ ቅዱሳን በከፍተኛ አመራሩ በኩል የፓትርያርክ አስመራጭ ኮሚቴ አባል ነው። በሌላ መልኩ ከአመራሮቹ አንዱ  ለቪኦኤ በሰጠው የግሉ መግለጫ እርቅ ይቅደም በማለቱ ከሥልጣኑ አባረውታል። ማቅ በሁለት ቢላዋ እየበላ ይህንን የዋህ ህዝብ ያታልላል። ከአስመራጩ አንዱ የሆነው የማቅ አመራር ምነው ድምጹ አይሰማ? ይህንን ደብዳቤ ተመልከቱ!!


Tuesday, January 1, 2013

ሁሉም ፓትርያርኮች የመንግሥት ጥገኞች ነበሩ!

ቤተክርስቲያኒቱ  ከምሥረታዋ ጀምሮ  የነገሥታቱ እጅ ተለይቷት አያውቅም። የሲሶ መንግሥትነት ድርሻዋም ከዚሁ ይመነጫል። የረጅሙን ዘመን የእንዴትነቱን ታሪከ ለጊዜው እንተወውና ስለፓትርያርኮቹ እውነታ ግን ጥቂት እንበል።

አጭር ምልከታ፡

1/ እጨጌ ገብረ ጊዮርጊስ /አቡነ ባስልስዮስ/
ትውልድ መንደራቸው ከሸዋ መርሐ ቤቴ የሆኑት ብጹእ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ /መምህር ገ/ጊዮርጊስ/ እየተባሉ በመናገሻ ማርያም፣ በኢየሩሳሌምና በኋላም በእጨጌነት የደብረ ሊባኖስ ሹም ሆነው ሲያገለግሉ ቆይተው በጣሊያን ወረራ ወቅት እስከ ማይጨው ድረስ ንጉሠ ነገሥቱን ተከትለው በመሄድ ውጊያውን አብረው ተካፍለዋል። በኋላም የጣሊያን ኃይል እየገፋ  ሲመጣ ከንጉሡ ጋር አፈግፍገው ንጉሡ ወደ ለንደን ሲሸሹ እጨጌው ደግሞ ወደ ኢየሩሳሌም ኮብልለዋል። ጣሊያንም ሀገሪቱን ከተቆጣጠረ በኋላ በጎቻቸውን በትነው በምንደኝነታቸው የተነሳ ወደ ሀገራቸው በፈረጠጡት በግብጻዊው ሊቀ ጳጳስ አባ ቄርሎስ ምትክ ከመጀመሪያዎቹ ኢትዮጵያውያን ጳጳሳት መካከል መጀመሪያ አባ አብርሃምን፣ እሳቸው ሲሞቱ ደግሞ  አባ ዮሐንስን የኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ አድርጎ ጣሊያን ሲሾም ሹመቱን አሜን ብለው በየተራ ተቀብለው ነበር። እንደነ አቡነ ጴጥሮስ የመሳሰሉት ጳጳሳት ለጣሊያን ወራሪ ኃይል ሕዝቡም፣ መሬቱም እንዳይገዙ ሲገዝቱና እስከ ሰማእትነት ሲደርሱ ሌሎቹ ጳጳሳት ደግሞ የጣሊያንን ሹመት እሰየው ብለው መቀበላቸው አይዘነጋም።
ከአምስቱ ዓመት የሕዝቡ መከራ በኋላ ጣሊያን ሲባረር የንጉሠ ነገሥቱን መመለስ ተከትለው እጨጌ ገ/ጊዮርጊስም ተመልሰው ወደ ሀገራቸው ገብተዋል።  ከዚያም በ1940 በግብጻዊው ፓትርያርክ አባ ዮሳብ እጅ ሊቀ ጳጳስ፡ እንደገናም ሌሎች ቀደምት ጳጳሳት እያሉ አጼ ኃ/ሥላሴ በተገኙበት ሥነ ሥርዓት በፓትርያርክ ቄርሎስ እጅ ካይሮ ላይ በሚገኘው ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ፓትርያርከ ዘኢትዮጵያ ተብለው መሾማቸውን የቤተክርስቲያን ታሪክ ያስረዳል።
ምንም እንኳን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ለ1600 ዓመታት በፈጠራ ሕግ በግብጾች የምንዳ አስተዳደር እጅ መቆየትዋን እንዲያበቃ ንጉሠ ነገሥት ኃ/ሥላሴ ከፍተኛ ሚና ቢጫወቱም የፈለጉትን ሰው ወደ  ቤተ ክርስቲያኒቱ ከፍተኛ  የሥልጣን እርከን ማምጣት መቻላቸውን ማስተባበል የማይቻል እውነት ነው። ኢትዮጵያውያን ጳጳሳትም ለጣሊያን ፋሺዝም ሳይቀር የስልጣን ሹመት ፈቃደኛነታቸውን በማሳየት አፍቃሬ ሲመታቸው እስከየት ድረስ እንደሆነ ማሳየታቸውንም  የሚዘነጋ አይደለም።
የሀገሪቱ ሕዝብ በገባር ሥርዓት ውስጥ በጭሰኝነት መከራ እየተጠበሰና ርስት አልባ ሆኖ  እየተሰቃየ  ሳለ በነገሥታቱ የተሾሙት የቤተ ክርስቲያኒቱ መሪዎች ግልጽ ወገንተኝነታቸው ከነገሥታቱ ጋር  ነበር። ለምሳሌ ያህልም እንደ ደብረ ሊባኖስ ያሉ ትላልቅ ገዳማት  በርስትነት በተቆጣጠሩት ኩዳድ መሬት ላይ የገባሩ ሥርዓት አንዱ አካል በመሆን በክርስቲያን ሕዝባቸው ላይ ጭሰኝነትን መትከላቸው አይዘነጋም። ነገሥታቱ ሲያጠፉ የምትገስጽና የምትመክር ቤተ ክርስቲያን በአመራርዋ እስካሁን አልነበረችም። ይህ እውነት ቢዘገንነንም እውነት ነው። በሐብታምና በደሃ፡ በጨዋ ዘርና በባሪያ፣ በአሳዳሪና በገባር መካከል ያለውን የወንጌል እውነት ማንንም ሳትፈራና ሳታፍር ማስተማር ሳትችል ነጻነቷን ለነገሥታቱ አስረክባ መቆየትዋም አሌ የማንለው ሐቅ ነው። ከነገደ ዛግዌ ወገን ላይ በስመ ኢ- ሰሎሞናዊ ሽፋን ንግሥናን ከመቀማት አንስቶ  አይሁዳዊቷ  ሀገር እስራኤል ነጻነቷን ስታውጅ አናውቅሽም ያሏት፣ ነገር ግን  በስመ ነገደ ይሁዳ  ኢትዮጵያን ለሚገዙ ነገሥታት ታማኝ ሆና ቤተ ክርስቲያኒቷ  መቆየትዋም ለዛሬ የአስተዳደር ድክመትና የሌሎች ወገኖች ደጋፍ  መታጣት አንዱ ምክንያት መሆኑ ይታወቃል። ይህንኑ ተከትሎ የመጡ መሪዎች ሁሉ ለመጠቀሚያነት እጃቸውን ለማስገባት መቻላቸውም  እርግጥ ነው።
2/  ሊቀ ሥልጣናት መልእከቱ/ አቡነ ቴዎፍሎስ

በዚህ የዘመናት ጉዞ አንዱ ክፍል ሆነው በንጉሡ ድጋፍ ፕትርክናውን የጨበጡት አቡነ ባስልዮስም በዚሁ ታሪክ ውስጥ አልፈው በእንደራሴነት ዘልቀው ፓትርያርክ የሆኑት አቡነ ቴዎፍሎስም ከንጉሠ ነገሥቱ ዘንድ ትልቅ ድጋፍ እንደነበራቸው አይካድም። አንዳንድ ጳጳሳት የሳቸውን ፓትርያርክ  መሆን አጥብቀው ከመቃወም አልፈው ደርግ  እርምጃ ሲወስድባቸው እንኳን ድጋፍ እስከመስጠት መድረሳቸው በተደገፈ መረጃ ጭምር የሚነገር እውነት ነው። አቡነ ቴዎፍሎስ በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ ለልማትና ለመንፈሳዊ መነቃቃት መፈጠር ጉልህ ሚና እንዳላቸው ባይካድም ለንጉሡ ሥርዓት ቅርበት እንዳላቸውም  አይዘነጋም።  በአጼ ኃ/ሥላሴ ድርጊት ያቄሙ ጳጳሳት ከአዲሱ ሃይማኖት የለሽ መንግሥት ጋር ወግነው አቡነ ቴዎፍሎስ  እንዲታሰሩ መስማማታቸው ሳያንስ ፓትርያርኩ በእስር  እያሉ ሌላ ፓትርያርክ ለመሾም ራሳቸውን ለማጨት የፈለጉ ነበሩ።  ብልጡ ደርግ ግን አቋም የለሾች መሆናቸውን አይቶ ከወላይታ አንድ ደብር የተገኙትን ባሕታዊ አባ መልዓኩን ለፓትርያርክነት አቅርቦ ጳጳሳት ሳሉ ተራ መነኩሴው በአንድ ጊዜ አቡነ ተ/ሃይማኖት አሰኝቶ ለፓትርያርክነት ለማብቃት ችሏል። ብዙዎቹ ጳጳሳት በሹመቱ ቅሬታ ቢኖራቸውም አይምሬው ደርግ እንደሚሰለቅጣቸው ስላወቁ ባይወዱም ምርጫውን በመንፈ ቅዱስ  እንደተደረገ ቆጥረው ለመቀበል መገደዳቸው ይታወቃል። በምርጫው ላይ የደርግ ጣልቃ ገብነት እንደነበረ  ቢታወቅም  ከአምስቱም የፓትርያርኮች ዘመን በተሻለ  የአቡነ ተ/ሃይማኖትን ፓትርያርክነት ሕዝቡ ከልቡ ተቀብሎት እስከ ዛሬም በታሪካዊነቱ ያወሳዋል። ደርግም ሳያውቀው ከሥልጣን ጥመኞቹ ጳጳሳት እጅ መንጭቆ ለአንድ ባህታዊ አሳልፎ በመስጠት ቤተ ክርስቲያኒቱን ጠቅሟታል። ሌላው ቢቀር አቡነ ተ/ሃይማኖት ጸሎተኛ ባህታዊና መፍቀሬ ነዋይ እንዳልነበሩ  ይመሰከርላቸዋል። ከአለባበስ ጀምሮ እስከ አመጋገባቸው ብርቱ ሰው ነበሩ። ያም ሆነ ይህ በሹመታቸው ላይ የደርግ ፈቃደኝት እንደነበር አይካድም።

3/ አራተኛው ፓትርያርክና ለሁለት ሲኖዶሶች መፈጠር ምክንያት እንደሆኑ የሚነገርላቸው የአባ ገ/ሊባኖስ /አቡነ  መርቆሬዎስ/ ወደ ፓትርያርክነት መምጣትም የደርግ እጅ እንደነበረበት ከጥርጣሬ በላይ በማስረጃ የሚናገሩ የወቅቱን አመራረጥ የተሳተፉት የሚናገሩት ነው። በተለይም የደርግ ማእከላዊ ኮሚቴ አባልና የጎንደር ክ/ሀገር አስተዳዳሪ፣ በኋላም የክ/ሀገሩ የኢሰፓ 1ኛ ጸሐፊ የሆነው የጓድ መልአኩ ወሳኝ ድርሻ እንደነበረበት በሕይወት ያሉ ሰዎች ዘወትር የሚያነሱት ታሪክ ነው። በተለይም አባ መርቆሬዎስ የጎንደር ሊቀ ጳጳስ ሳሉ ዲቁናና ቅስና ለመቀበል ወደ እርሳቸው ዘንድ ይመጡ ለነበሩት በመቶዎች ለሚቆጠሩ ካህናት የሚያቀርቡት ቃለ ቡራኬ “ይህ ሁሉ ወጣት ጠመንጃ ቢሸከም” ይሉ እንደነበር በሥፍራው የነበሩ ካህናትና መነኮሳት እማኞች ዛሬም ያስታውሱታል። ከኢህአዴግ መንግሥት ጥርስ ውስጥም የከተታቸው በአንድ ወቅት ለደርግ መንግሥት የጦርነት ድጋፍ የሚሆን ገንዘብ በቤተ ክርስቲያኒቱ ስም በመስጠታቸውና ይህም በሚዲያ በመነገሩ እንደሆነ  ይገመታል። ከደርግ  ጋር ከምርጫ  እስከ ሃሳብ ድጋፍ ድረስ የተሰናሰሉ እንደነበር ቢያቅረንም በእውነቱነቱ መጋት የግድ ይሆናል።  በአባ መርቆሬዎስ ፓትርያርክነት ዘመን ቤተ ክህነቱ የጥቂት ወገኖቻቸውና ደጋፊዎቻቸው መፈንጫ እንደነበር ጊዜው ቢረዝምም እንዴት እንረሳለን የሚሉ ዛሬም አሉ። የእነ ሊቀማእምራን አበባው ይግዛውን አስተዳደር የሚያስታውሱ  ከደርግ ጋር እስከቆንስላነት የነበራቸው ትስስር በመዘንጋት ተበዳዮች ነበርን ባዮች፣ የእነሱ የግፍ አገዛዝ ይመለስልን ብለን እንዴት በተስፋ እንጠብቃለን? በማለት ጥያቄ ያነሳሉ። ምንም ይሁን ምንም የፓትርያርክ መርቆሬዎስ ቤተ ክህነት ከደርግ ጋር ቁርኝት እንደነበረው መካድ አይቻልም። ይህንን ቁርኝት ተከትሎ በደርግ ተበደልኩ የሚል ወገን የፓትርያርኩን በሥልጣን ላይ መመለስ ባይቀበል አያስገርምም። ያስደንቅ የነበረው ቤተ ክህነቱ በየጊዜው ከሚመጣ  የሀገሪቱ ባለሥልጣ ጋር ሳይለጠፍ ራሱን ችሎ ቢገኝ ነበር።

4/ የአባ ገ/መድኅን/ አባ ጳውሎስ/ ዘመነ ፕትርክና

ይህ ዘመን በብዙ እንከን የተሞላና በፖለቲካ ንፋስ የታመሰ ዘመን ነበር። በአንጻሩም አብያተ ክርስቲያናት በልማት ራሳቸውን ያሳደጉበትና አብዛኛው ካህናት የተሻለ የደመወዝ ተከፋይ መሆን የቻሉበትም ዘመን ነው። ያም ሆኖ ኢህአዴግና አባ ጳውሎስ እስከ ኅልፈታቸው ሳይከዳዱ በመደጋገፍ ጊዜያቸውን የፈጸሙበት ዘመን እንደነበርም  መዘንጋት አይቻልም። አቡነ  መርቆሬዎስን ከማባረር ጀምሮ  አቡነ ጳውሎስን እስከ ማስመረጥና ድጋፉ ሳይቋርጥ እስከመጨረሻው ድረስ ወዳጅነታቸው ሳይረግብ  መቀጠሉን መካድም ግልጹን እውነታ ወደ ውሸትነት አይለውጠውም። አቡነ ቴዎፍሎስ ሲታሰሩ እንደተስማሙት ሁሉ አቡነ መርቆሬዎስ ሲባረሩ በተመሳሳይ መልኩ የሊቃነ ጳጳቱ ብርቱ ድጋፍ ከኢህአዴጉ መራሽ መንግሥት ጋር ነበረ። በአቡነ መርቆሬዎስ ሥልጣንና አስተዳደር ቅሬታ የነበራቸው ጳጳሳትና ሠራተኞች በምትካቸው ሌላ ለመምረጥ ሲቻኮሉም ታይተዋል። ግማሹ እኔ እሾማለሁ በሚል ሂሳብ ሲሆን ገሚሱ ደግሞ  ማንም ይሾም ማንም፣ አባ መርቆሬዎስ ወርደው ብቻ ያሳየኝ ከሚል ጥላቻ የተነሳ ነበር። ስማቸውን መጥቀስ የማንፈልጋቸው ሰዎች አቡነ መርቆሬዎስ ወርደው ለማየት የቱን ያህል ፍላጎት እንደነበራቸው በወቅቱ ከማውረድ ጀምሮ  ለአዲስ ሰው ምርጫ ያደርጉት የነበረው ሩጫ አይረሳንም።
የአባ ጳውሎስ ዘመነ ፕትርክና በአንጻራዊ ሰላምና ልማት  /የመንበረ ፓትርያርክ አዳዲስ ህንጻዎችን ልብ ይሏል/ የታየበት ዘመን ቢሆንም በአስተዳደር  ብልሹነትና  በገንዘብ ምዝበራ ረገድ ከየትኛውም ዘመን በተለየ  እጅግ የከፋ ነበር። በአባ ጳውሎስ ዘመን የጵጵስና ማእርግ የምርጫ ሥነ ምግባር ውጥንቅጡ የወጣበትና ለጵጵስናም የነበረ ክብር የወረደበት ዘመን መሆኑም አይዘነጋም።  መጋቤ ምስጢር ወ/ ሩፋኤል በአንድ ጽሁፉ እንዳለው እንደ ስምዖን ቀሬናዊ ከመንገድ እየተጎተቱ የተጫኑበትና “ብንድራቸው ይሻላል” የተባሉ ሁሉ ሥልጣን ላይ የወጡበት አሳዛኝ ዘመንም እንደነበር ይታወሳል። የእውነት ወንጌል ከመቼውም ጊዜ በላይ ዋጋ ያጣበት፡ ሥጋውያን ማኅበራት ነፍስ የዘሩበት ቢሆንም ብዙዎች የተጋረደውን እውነት ገልጠው ለማየት ይቻሉበትም ዘመን ሆኖ  አልፏል።